የከተማ አስተዳደራችን ተቋማት ጥንካሬ ሰው ላይ የተንጠለጠሉ ሳይሆኑ ቀጣይነት ያላቸው በሲስተም የሚመሩ ጠንካራ ተቋማት የማድረግ ስራ ፍሬው እየታየ ነው።
ዛሬ ጠዋት በደንብ ማስከበር ባለስልጣን የተሰሩ የተቋም ሪፎርም ስራዎችን ጎብኝተናል። ከዚህ በፊት ነዋሪዎች ቅሬታቸውን “ወይ ሀምሳ ወይ አንሳ” የሚል ቅፅል ስም አውጥተውለት እንደነበር አይዘነጋም ።
ይህንን ስም ለመለወጥ እና የነዋሪዎችን እርካታ ለማሳደግ በተከታታይ በተሰራ ሪፎርም በአስተሳሰብ፣ በስነ ምግባር እንዲሁም የዘመነ አሰራር በመተግበር መሰረታዊ ለውጥ አስመዝግቧል ።
ከወረቀት ንክኪ ነፃ፣ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት፣ መረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ ለመስጠት እና ቅሬታዎችንም ለመፍታት የሚያግዙ እንዲሁም የደንብ ጥሰትንም በቀላሉ በመለየት ለማረም የሚስችሉ ናቸው ።
በተጨማሪም የዜጎች ቀጥታ ተሳትፎ መተግበሪያ፣ በ5 ቋንቋ አገልግሎት የሚሰጥ የጥቆማና ቅሬታ ማቅረቢያ ዘመናዊ የጥሪ ማዕከል (calling center)፣ የሁኔታዎች መከታተያ ክፍል (situation room)፣ ዘመናዊ የስልጠና ማዕከል (Smart training center)፣ ዘመናዊ የቢሮ አደረጃጀት (Smart office)፣ የህፃናት ማቆያ፣ የሰራተኛ ካፍቴሪያ፣ የሸማች ሱቅ፣ የሰፖርት ማዕከል (ጂምናዚየም) ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።
በመጨረሻም በትጋት መሰረታዊ ለወጥ ያስመዘገቡትን የተቋሙን አመራሮች እና የኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ቢሯችንን ከልብ አመሰግናለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ዛሬ ጠዋት በደንብ ማስከበር ባለስልጣን የተሰሩ የተቋም ሪፎርም ስራዎችን ጎብኝተናል። ከዚህ በፊት ነዋሪዎች ቅሬታቸውን “ወይ ሀምሳ ወይ አንሳ” የሚል ቅፅል ስም አውጥተውለት እንደነበር አይዘነጋም ።
ይህንን ስም ለመለወጥ እና የነዋሪዎችን እርካታ ለማሳደግ በተከታታይ በተሰራ ሪፎርም በአስተሳሰብ፣ በስነ ምግባር እንዲሁም የዘመነ አሰራር በመተግበር መሰረታዊ ለውጥ አስመዝግቧል ።
ከወረቀት ንክኪ ነፃ፣ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት፣ መረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ ለመስጠት እና ቅሬታዎችንም ለመፍታት የሚያግዙ እንዲሁም የደንብ ጥሰትንም በቀላሉ በመለየት ለማረም የሚስችሉ ናቸው ።
በተጨማሪም የዜጎች ቀጥታ ተሳትፎ መተግበሪያ፣ በ5 ቋንቋ አገልግሎት የሚሰጥ የጥቆማና ቅሬታ ማቅረቢያ ዘመናዊ የጥሪ ማዕከል (calling center)፣ የሁኔታዎች መከታተያ ክፍል (situation room)፣ ዘመናዊ የስልጠና ማዕከል (Smart training center)፣ ዘመናዊ የቢሮ አደረጃጀት (Smart office)፣ የህፃናት ማቆያ፣ የሰራተኛ ካፍቴሪያ፣ የሸማች ሱቅ፣ የሰፖርት ማዕከል (ጂምናዚየም) ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።
በመጨረሻም በትጋት መሰረታዊ ለወጥ ያስመዘገቡትን የተቋሙን አመራሮች እና የኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ቢሯችንን ከልብ አመሰግናለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
❤14👏2
የደንብ መተላለፎች በመከላከል የከተማዋን ገጽታና የገነባው የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን በቢሮ ሪፎርም ስራዎቹ ውጤት ማስመዝገቡ ተገለፀ
21/08/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክብርት አዳነች አበቤ የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ባለፉት ሦስት ዓመታት ያከናወናቸውን የተቀናጁ የሪፎርም ስራዎች ዛሬ ጠዋት በዋናው መስሪያ ቤት በመገኘት የጎበኙ ሲሆን ተቋሙ ከዚህ ቀደም ይነሳበት የነበረውን የአገልግሎት አሰጣጥ በማሻሻል መሰረታዊ ለውጥ ማስመዝገቡን ገልጸዋል።
ከንቲባዋ በጉብኝታቸው ወቅት እንደተናገሩት ነዋሪዎች ቀደም ሲል ለተቋሙ ሰጥተውት የነበረውን አላስፈላጊ ስም ለመቀየር በአስተሳሰብ፣ በሥነ-ምግባር እና በዘመናዊ አሰራር ላይ ተከታታይ ስራዎች ተከናውነዋል።
በዚህም ተቋሙን ከወረቀት ንክኪ ነፃ በማድረግ መረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ ለመስጠት የሚያስችሉ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ማለትም በተለያዩ የስራ ቋንቋዎች አገልግሎት የሚሰጥ የጥሪ ማዕከል፣ የሁኔታዎች መከታተያ ክፍል፣ የስማርት ስልጠና ማዕከል እና ዘመናዊ የቢሮ አደረጃጀቶች ለአገልግሎት ዝግጁ መሆናቸውን ተመልክተዋል።
ለህዝብ ግንኙነት ስራዎች ተብሎ የተገነባው የድምፅና ምስል ስቱዲዮ ደግሞ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራው ለህብረተሰቡ በስፋት እንዲደርስ እያገዘ ይገኛል፡:
ከቴክኖሎጂ ሽግግሩ ጎን ለጎንም ባለሥልጣኑ ለሰው ኃይል በሰጠው ልዩ ትኩረት ለሰራተኞች ምቹ የሥራ አካባቢን ለመፍጠር ያስቻሉ የህፃናት ማቆያ፣ የሰራተኛ ካፌቴሪያ፣ የሸማቾች ሱቅ እና የሰውነት ማጎልመሻ ማዕከልን በማደራጀት ወደ ስራ አስገብቷል።
እነዚህ የተቀናጁ የሪፎርም ስራዎች በውጤት ታጅበው በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎችን መቀነስ መቻሉ ተገልጿል ።
በመጨረሻም ክብርት ከንቲባዋ ለተመዘገበው ስኬት የላቀ አስተዋጽኦ ያበረከቱ የተቋሙን አመራሮችና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮን አመስግነዋል ።
ባለስልጣኑ ያገኘውን የለውጥ ተሞክሮ እስከ ታችኛው የክፍለ ከተማና የወረዳ መዋቅር ድረስ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
ዘገባው፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው
21/08/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክብርት አዳነች አበቤ የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ባለፉት ሦስት ዓመታት ያከናወናቸውን የተቀናጁ የሪፎርም ስራዎች ዛሬ ጠዋት በዋናው መስሪያ ቤት በመገኘት የጎበኙ ሲሆን ተቋሙ ከዚህ ቀደም ይነሳበት የነበረውን የአገልግሎት አሰጣጥ በማሻሻል መሰረታዊ ለውጥ ማስመዝገቡን ገልጸዋል።
ከንቲባዋ በጉብኝታቸው ወቅት እንደተናገሩት ነዋሪዎች ቀደም ሲል ለተቋሙ ሰጥተውት የነበረውን አላስፈላጊ ስም ለመቀየር በአስተሳሰብ፣ በሥነ-ምግባር እና በዘመናዊ አሰራር ላይ ተከታታይ ስራዎች ተከናውነዋል።
በዚህም ተቋሙን ከወረቀት ንክኪ ነፃ በማድረግ መረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ ለመስጠት የሚያስችሉ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ማለትም በተለያዩ የስራ ቋንቋዎች አገልግሎት የሚሰጥ የጥሪ ማዕከል፣ የሁኔታዎች መከታተያ ክፍል፣ የስማርት ስልጠና ማዕከል እና ዘመናዊ የቢሮ አደረጃጀቶች ለአገልግሎት ዝግጁ መሆናቸውን ተመልክተዋል።
ለህዝብ ግንኙነት ስራዎች ተብሎ የተገነባው የድምፅና ምስል ስቱዲዮ ደግሞ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራው ለህብረተሰቡ በስፋት እንዲደርስ እያገዘ ይገኛል፡:
ከቴክኖሎጂ ሽግግሩ ጎን ለጎንም ባለሥልጣኑ ለሰው ኃይል በሰጠው ልዩ ትኩረት ለሰራተኞች ምቹ የሥራ አካባቢን ለመፍጠር ያስቻሉ የህፃናት ማቆያ፣ የሰራተኛ ካፌቴሪያ፣ የሸማቾች ሱቅ እና የሰውነት ማጎልመሻ ማዕከልን በማደራጀት ወደ ስራ አስገብቷል።
እነዚህ የተቀናጁ የሪፎርም ስራዎች በውጤት ታጅበው በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎችን መቀነስ መቻሉ ተገልጿል ።
በመጨረሻም ክብርት ከንቲባዋ ለተመዘገበው ስኬት የላቀ አስተዋጽኦ ያበረከቱ የተቋሙን አመራሮችና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮን አመስግነዋል ።
ባለስልጣኑ ያገኘውን የለውጥ ተሞክሮ እስከ ታችኛው የክፍለ ከተማና የወረዳ መዋቅር ድረስ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
ዘገባው፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው
👍15👏5😁1
በበጀት አመቱ ባለፉት 9 ወራት የደንብ መተላለፎች በ82% እና የወንጀል ምጣኔ በ47% መቀነስ መቻሉ ተገለፀ
22/08/2018ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ እና የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የተቋማቱ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት የ9 ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ።
የመድረኩን መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ ከተማችን የአፍሪካ ትልቋ የቱሪዝም የስህበት ከተማ ሆናለች፤ የከተማዋ ሰላምና ደህንነት አስተማማኝና በመሆኑ በርካታ ሀገር አቀፍ ብቻ ሳይሆን አለም አቀፍ ሁነቶች እየተካሄዱባት ይገኛል፤ ይህንንም ማድረግ የቻልነው ህዝቡን በቀጥታ የሰላም ባለቤት ማድረግ በመቻሉ መሆኑ ገልፀዋል።
በከተማው ከ200ሺ በላይ ለሚሆኑ የሰላም ሰራዊት አባላት በ9 ወራት ውስጥ በድግግሞሽ የአቅም ግንባታ ስራዎች መሰራታቸውን በከተማችን የደንብ መተላለፎች እንዲቀንሱ እና ለከተማዋ የሚመጥን ፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰር ለማፍራት ወታደራዊ እና የንድፈ ሀሳብ ስልጠናዎችን በመስጠት የሰው ኃይሉ ላይ ከፍተኛ ለውጥ መታየቱን ተናግረዋል።
በዕለቱ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንዳሉት በባለፍት 9ወራት የአደባባይ በዓላት በሰላም ተከብረው እንዲጠናቀቁ እና የተለያዮ የደንብ መተላለፎች እንዳይከሰቱ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን ገልፀው።
ይህንንም ለማሳካት ቀደም ብለን ስራዎችን በእቅድ አዘጋጅተን በየሩብ ዓመቱ መገምገም መቻሉን ተናግረው። በዛሬው ዕለትም ምን ሰራን የሚለውን ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመለየት ለቀጣይ የስራ አቅጣጫዎችን ተቀብለን የምንወጣበት መሆኑን ገልፀዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የ2018 በጀት ዓመት በዘጠኝ ወራት በከተማዋ የደንብ መተላለፎችን በመቀነስ እና የሕግ የበላይነትን በማረጋገጥ ረገድ ውጤታማ ሥራዎችን በማከናወኑ በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎች 82% መቀነሱን ሪፖርቱን ያቀረቡት የባስልጣኑ የእቅድ እና በጀት ዳይሬክተር ኮነሬል አድማሱ ተክሌ ተናግረዋል።
በተመሳሳይ የሰላምና ፀጥታ ቢሮ የእቅድና በጀት ዳይሬክተር አቶ ማስረሻ ሀብቴ ሪፖርቱን ሲያቀርቡ እንዳሉት በ9ወራት የወንጀል ምጣኔ ከቀደሙት ጊዜያት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ 47.15 በመቶ መቀነሱን ገልፀዋል።
በመጨረሻም ለመድረክ የቀረቡትን ሀሳብ እና አስተያየቶች ላይ ምላሽ በሁለቱ ተቋማት አመራሮች ምላሽ ተሰቶበት እና የቀጣይ የስራ አቅጣጫ ተቀምጦ መድረኩ ተጠናቋል።
ዘገባው:-የደንብ ማስከበር ኮሙኑኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
22/08/2018ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ እና የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የተቋማቱ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት የ9 ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ።
የመድረኩን መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ ከተማችን የአፍሪካ ትልቋ የቱሪዝም የስህበት ከተማ ሆናለች፤ የከተማዋ ሰላምና ደህንነት አስተማማኝና በመሆኑ በርካታ ሀገር አቀፍ ብቻ ሳይሆን አለም አቀፍ ሁነቶች እየተካሄዱባት ይገኛል፤ ይህንንም ማድረግ የቻልነው ህዝቡን በቀጥታ የሰላም ባለቤት ማድረግ በመቻሉ መሆኑ ገልፀዋል።
በከተማው ከ200ሺ በላይ ለሚሆኑ የሰላም ሰራዊት አባላት በ9 ወራት ውስጥ በድግግሞሽ የአቅም ግንባታ ስራዎች መሰራታቸውን በከተማችን የደንብ መተላለፎች እንዲቀንሱ እና ለከተማዋ የሚመጥን ፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰር ለማፍራት ወታደራዊ እና የንድፈ ሀሳብ ስልጠናዎችን በመስጠት የሰው ኃይሉ ላይ ከፍተኛ ለውጥ መታየቱን ተናግረዋል።
በዕለቱ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንዳሉት በባለፍት 9ወራት የአደባባይ በዓላት በሰላም ተከብረው እንዲጠናቀቁ እና የተለያዮ የደንብ መተላለፎች እንዳይከሰቱ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን ገልፀው።
ይህንንም ለማሳካት ቀደም ብለን ስራዎችን በእቅድ አዘጋጅተን በየሩብ ዓመቱ መገምገም መቻሉን ተናግረው። በዛሬው ዕለትም ምን ሰራን የሚለውን ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመለየት ለቀጣይ የስራ አቅጣጫዎችን ተቀብለን የምንወጣበት መሆኑን ገልፀዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የ2018 በጀት ዓመት በዘጠኝ ወራት በከተማዋ የደንብ መተላለፎችን በመቀነስ እና የሕግ የበላይነትን በማረጋገጥ ረገድ ውጤታማ ሥራዎችን በማከናወኑ በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎች 82% መቀነሱን ሪፖርቱን ያቀረቡት የባስልጣኑ የእቅድ እና በጀት ዳይሬክተር ኮነሬል አድማሱ ተክሌ ተናግረዋል።
በተመሳሳይ የሰላምና ፀጥታ ቢሮ የእቅድና በጀት ዳይሬክተር አቶ ማስረሻ ሀብቴ ሪፖርቱን ሲያቀርቡ እንዳሉት በ9ወራት የወንጀል ምጣኔ ከቀደሙት ጊዜያት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ 47.15 በመቶ መቀነሱን ገልፀዋል።
በመጨረሻም ለመድረክ የቀረቡትን ሀሳብ እና አስተያየቶች ላይ ምላሽ በሁለቱ ተቋማት አመራሮች ምላሽ ተሰቶበት እና የቀጣይ የስራ አቅጣጫ ተቀምጦ መድረኩ ተጠናቋል።
ዘገባው:-የደንብ ማስከበር ኮሙኑኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍5👏3❤1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ከንቲባ አዳነች አቤቤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ያከናወናቸውን የሪፎርም ስራዎች ጉብኝት ላይ ከተናገሩት:-
👍19👏4