በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎች በ82% መቀነሱ ተገለፀ ።
08/08/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የ2018 በጀት ዓመት በዘጠኝ ወራት በከተማዋ የደንብ መተላለፎችን በመቀነስ እና የሕግ የበላይነትን በማረጋገጥ ረገድ ውጤታማ ሥራዎችን በማከናወኑ በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎች 82% መቀነሱን ገለፀ ።
ተቋሙ ሥራውን በቴክኖሎጂ ለማገዝ የኮል ሴንተር (Call Center) እና ስማርት አይሲቲ (Smart ICT) የሥልጠና ክፍሎችን ገንብቶ ወደ ሥራ አስገብቷል ፣ቅሬታዎችን በፍጥነት ለመፍታትና የአገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋ ለማድረግ የሚያስችሉ ዲጂታል አሠራሮች ተዘርግተዋል እንዲሁም ሠራተኞችን የአገልግሎት አሰጣጥ እና ሥነ-ምግባር ለማሻሻል የሚያስችሉ የለውጥ ሥራዎች ማከናወኑ አስታውቋል።
ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ለፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች እና አመራሮች የንድፈ ሐሳብና የተግባር ስልጠናዎችን በመስጠት በአገልግሎት አሰጣጥ፣ በሥነ-ምግባር እና በሰብዓዊ መብት አያያዝ ዙሪያ ለውጥ መምጣቱ ተገልጿል ።
በቀጣይ ባለስልጣኑ የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራውን በማጠናከርና የህብረተሰቡን ተሳታፊነት በመጨመር የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ የነበሩ ጥንካሬዎችን በማስቀጠል እና የታዩ ክፍተቶችን በማረም አዲስ አበባን ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ ማራኪና ሰላማዊ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሠራ አስታውቋል።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
08/08/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የ2018 በጀት ዓመት በዘጠኝ ወራት በከተማዋ የደንብ መተላለፎችን በመቀነስ እና የሕግ የበላይነትን በማረጋገጥ ረገድ ውጤታማ ሥራዎችን በማከናወኑ በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎች 82% መቀነሱን ገለፀ ።
ተቋሙ ሥራውን በቴክኖሎጂ ለማገዝ የኮል ሴንተር (Call Center) እና ስማርት አይሲቲ (Smart ICT) የሥልጠና ክፍሎችን ገንብቶ ወደ ሥራ አስገብቷል ፣ቅሬታዎችን በፍጥነት ለመፍታትና የአገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋ ለማድረግ የሚያስችሉ ዲጂታል አሠራሮች ተዘርግተዋል እንዲሁም ሠራተኞችን የአገልግሎት አሰጣጥ እና ሥነ-ምግባር ለማሻሻል የሚያስችሉ የለውጥ ሥራዎች ማከናወኑ አስታውቋል።
ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ለፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች እና አመራሮች የንድፈ ሐሳብና የተግባር ስልጠናዎችን በመስጠት በአገልግሎት አሰጣጥ፣ በሥነ-ምግባር እና በሰብዓዊ መብት አያያዝ ዙሪያ ለውጥ መምጣቱ ተገልጿል ።
በቀጣይ ባለስልጣኑ የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራውን በማጠናከርና የህብረተሰቡን ተሳታፊነት በመጨመር የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ የነበሩ ጥንካሬዎችን በማስቀጠል እና የታዩ ክፍተቶችን በማረም አዲስ አበባን ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ ማራኪና ሰላማዊ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሠራ አስታውቋል።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
👍12❤5
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የለውጥ ጉዞና የሪፎርም ስኬቶቹ
09/08/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ሪፎርም ከተደረገ በኋላ ባሉት 3 ዓመታት የተቀናጀ የሪፎርም ስራ በማከናወን የከተማውና የተቋም ገፅታ እየገነባ ይገኛል፡፡
ተቋሙ የደንብ መተላለፎችን ከመቆጣጠር ባለፈ የውስጥ አሰራሩን በማዘመን እና ለሰራተኞቹም ሆነ ለተገልጋዮች ምቹ የስራ ሁኔታን በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ ለውጥ አስመዝግቧል፡፡
በተለይም የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን የተገነቡት የኮል ሴንተር እና የስማርት ስልጠና ማዕከላት ተቋሙን አገልግሎቱ በቴክኖሎጂ ለመስጠት ምቹ ሁኔታ አየፈጠሩ ይገኛል።
ባለስልጣኑ ለህዝብ ግንኙነትና ለሚዲያ ስራዎች ተብሎ የተገነባው የድምፅና ምስል ስቱዲዮ ደግሞ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራው ለህብረተሰቡ በስፋት እንዲደርስ እያገዘ ይገኛል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ለሰራተኞች ምቹ የሥራ አካባቢን ለመፍጠር የተገነቡት ዘመናዊ የህጻናት ማቆያ፣ ጥራቱን የጠበቀ ካፌቴሪያ እና ጂምናዚየም ተቋሙ ለሰው ኃይል የሰጠውን ትኩረት የሚያሳዩ ማሳያዎች ናቸው፡፡
እነዚህ የሪፎርም ስራዎች በውጤት ታጅበው በ2018 በጀት ዓመት በዘጠኝ ወራት ውስጥ ብቻ በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎችን በ82% መቀነስ ተችሏል፡፡
ባለስልጣኑ የተጀመረ የለውጥ ጉዞ እስከ ታችኛው መዋቅር ለማውረድ እና የበለጠ ለማጠናከር የክፍለ ከተማና የወረዳ የደንብ ማስከበር አመራሮች በዋናው መሥሪያ ቤት ጉብኝት በማድረግ ለሰራተኞቻቸውና ለተገልጋዩ ህብረተሰብ ምቹ ሁኔታዎች እንዲፈጥሩ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡
09/08/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ሪፎርም ከተደረገ በኋላ ባሉት 3 ዓመታት የተቀናጀ የሪፎርም ስራ በማከናወን የከተማውና የተቋም ገፅታ እየገነባ ይገኛል፡፡
ተቋሙ የደንብ መተላለፎችን ከመቆጣጠር ባለፈ የውስጥ አሰራሩን በማዘመን እና ለሰራተኞቹም ሆነ ለተገልጋዮች ምቹ የስራ ሁኔታን በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ ለውጥ አስመዝግቧል፡፡
በተለይም የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን የተገነቡት የኮል ሴንተር እና የስማርት ስልጠና ማዕከላት ተቋሙን አገልግሎቱ በቴክኖሎጂ ለመስጠት ምቹ ሁኔታ አየፈጠሩ ይገኛል።
ባለስልጣኑ ለህዝብ ግንኙነትና ለሚዲያ ስራዎች ተብሎ የተገነባው የድምፅና ምስል ስቱዲዮ ደግሞ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራው ለህብረተሰቡ በስፋት እንዲደርስ እያገዘ ይገኛል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ለሰራተኞች ምቹ የሥራ አካባቢን ለመፍጠር የተገነቡት ዘመናዊ የህጻናት ማቆያ፣ ጥራቱን የጠበቀ ካፌቴሪያ እና ጂምናዚየም ተቋሙ ለሰው ኃይል የሰጠውን ትኩረት የሚያሳዩ ማሳያዎች ናቸው፡፡
እነዚህ የሪፎርም ስራዎች በውጤት ታጅበው በ2018 በጀት ዓመት በዘጠኝ ወራት ውስጥ ብቻ በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎችን በ82% መቀነስ ተችሏል፡፡
ባለስልጣኑ የተጀመረ የለውጥ ጉዞ እስከ ታችኛው መዋቅር ለማውረድ እና የበለጠ ለማጠናከር የክፍለ ከተማና የወረዳ የደንብ ማስከበር አመራሮች በዋናው መሥሪያ ቤት ጉብኝት በማድረግ ለሰራተኞቻቸውና ለተገልጋዩ ህብረተሰብ ምቹ ሁኔታዎች እንዲፈጥሩ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡
👍12❤7
አገልግሎት አሰጣጥ ቀልጣፋ ለማድረግ ምቹ የስራ አካባቢ መፍጠር መሠረታዊ ስራ መሆኑ ተገለፀ
13/08/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ለሰራተኞች እና ለተገልጋዮች ምቹ የስራ አከባቢ በመፍጠር የተቋሙ የሚሰጠውን ተልዕኮ በስኬት ለመፈጸም ዝግጁ መሆኑ ገለፀ ።
ጽ/ቤቱ ከህብረተሰብ የሚቀርቡ ጥቆማዎች በመቀበል የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመቅረፍ ለዜጎች ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል የትራንስፖርት አማራጭ ማዘጋጀቱንም የክፍለ ከተማው የደንብ ማስከበር። ሀላፊ መቶ አለቃ ቦጋለ አለሙ ገልፀዋል።
ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የደንብ መተላለፎችን በመቆጣጠር የተሰጠውን ተልዕኮ በውጤት በመፈጸምና በኃላፊነት ከመወጣት ባሻገር ያከናወነው የተቋም ግንባታ የሚበረታታና ሌሎች ጽ/ቤቶች የሚያነሳሳ ነው ሲሉ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ካባ መብራቱ ገልጸዋል ።
በመርሐ ግብሩ የወረዳዎችን የመፈጸም አቅም ለማሳደግ በክፍለ ከተማው ስር ለሚገኙ ለወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤቶች ለትራንስፖርት አማራጭ ለመጠቀምና የመፈፀምና የማስፈፀም አቅም ለማሳደግ የኤሌክትሪክ ሞተር ሳይክል ስጦታ ተበርክቶላቸዋል ።
መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
13/08/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ለሰራተኞች እና ለተገልጋዮች ምቹ የስራ አከባቢ በመፍጠር የተቋሙ የሚሰጠውን ተልዕኮ በስኬት ለመፈጸም ዝግጁ መሆኑ ገለፀ ።
ጽ/ቤቱ ከህብረተሰብ የሚቀርቡ ጥቆማዎች በመቀበል የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመቅረፍ ለዜጎች ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል የትራንስፖርት አማራጭ ማዘጋጀቱንም የክፍለ ከተማው የደንብ ማስከበር። ሀላፊ መቶ አለቃ ቦጋለ አለሙ ገልፀዋል።
ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የደንብ መተላለፎችን በመቆጣጠር የተሰጠውን ተልዕኮ በውጤት በመፈጸምና በኃላፊነት ከመወጣት ባሻገር ያከናወነው የተቋም ግንባታ የሚበረታታና ሌሎች ጽ/ቤቶች የሚያነሳሳ ነው ሲሉ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ካባ መብራቱ ገልጸዋል ።
በመርሐ ግብሩ የወረዳዎችን የመፈጸም አቅም ለማሳደግ በክፍለ ከተማው ስር ለሚገኙ ለወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤቶች ለትራንስፖርት አማራጭ ለመጠቀምና የመፈፀምና የማስፈፀም አቅም ለማሳደግ የኤሌክትሪክ ሞተር ሳይክል ስጦታ ተበርክቶላቸዋል ።
መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
👍7❤4