ባለስልጣኑ ከማዕከል ሰራተኞች ጋር በዘጠኝ ወር እቅድ አፈፃፀም በተከናወኑ ስራዎች እና በቀሪ ወራት የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ውይይት አካሄደ።
ሚያዚያ 16/2016 ዓ.ም
* አዲስ አበባ*
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የበጀት ዓመቱን በዘጠኝ ወር እቅድ አፈፃፀም በተከናወኑ ስራዎች እና በቀሪ ወራት የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ከማዕከል ሰራተኞች ጋር የባለስልጣኑ አመራሮች በተገኙበት በባለስልጣኑ መሰብሰቢያ አዳራሽ ውይይት አካሂዷል።
ባለስልጣኑን በሶስተኛ ሩብ ዓመት የደረሰበት እቅድ አፈፃፀም ያቀረቡት የባለስልጣኑ እቅድና በጀት ዳይሮክቶሬት ዳይሬክተር ኮሎኔል አድማሱ ተክሌ እንዳሉት በ9ወራት ውስጥ በተለያየ መንገድ የተሰበሰበ ከ34 ሚሊየን ብር በላይ ወደ ፍይናንስ ገቢ ማድረግ መቻሉን ገልፀዋል።
አክለውም በቦታ 5840 ቦታዎች እንዲሁም በካሬ ከ10 ሚሊዮን ካሬ በላይ መሬት ወደ መሬት ባንክ እንዲገቡ ተደርገው በባለስልጣኑ እየተጠበቁ ይገኛሉ ብለዋል።
በቀረበው ሰነድ ላይ ውይይት የተካሄደ ሲሆን ሰራተኞችም በቀሪው 3 ወራት ውስጥ ከእቅዳችን ለማሳካት እና ክፋተቶቻችንን ለመሙላት በትጋት ልንሰራ ይገባል ሲሉ ሀሳብ ሰጥተዋል።
የመድረኩን ማጠቃለያ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ የፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፍሁን አሉላ በአጠቃላይ በአመራሩ እና ሰራተኛው ጥረት አሁን ላይ በተቋሙ ጥሩ አፈፃፀም መኖሩ ገልፀው ይህንንም አጠናክረን ልንቀጥል ይገባል በማለት ከሰራተኛው ለቀረበላቸው ሀሳብና አስተያየት ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት የውይይት መድረኩን ተጠናቋል።
ዘገባው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ሚያዚያ 16/2016 ዓ.ም
* አዲስ አበባ*
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የበጀት ዓመቱን በዘጠኝ ወር እቅድ አፈፃፀም በተከናወኑ ስራዎች እና በቀሪ ወራት የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ከማዕከል ሰራተኞች ጋር የባለስልጣኑ አመራሮች በተገኙበት በባለስልጣኑ መሰብሰቢያ አዳራሽ ውይይት አካሂዷል።
ባለስልጣኑን በሶስተኛ ሩብ ዓመት የደረሰበት እቅድ አፈፃፀም ያቀረቡት የባለስልጣኑ እቅድና በጀት ዳይሮክቶሬት ዳይሬክተር ኮሎኔል አድማሱ ተክሌ እንዳሉት በ9ወራት ውስጥ በተለያየ መንገድ የተሰበሰበ ከ34 ሚሊየን ብር በላይ ወደ ፍይናንስ ገቢ ማድረግ መቻሉን ገልፀዋል።
አክለውም በቦታ 5840 ቦታዎች እንዲሁም በካሬ ከ10 ሚሊዮን ካሬ በላይ መሬት ወደ መሬት ባንክ እንዲገቡ ተደርገው በባለስልጣኑ እየተጠበቁ ይገኛሉ ብለዋል።
በቀረበው ሰነድ ላይ ውይይት የተካሄደ ሲሆን ሰራተኞችም በቀሪው 3 ወራት ውስጥ ከእቅዳችን ለማሳካት እና ክፋተቶቻችንን ለመሙላት በትጋት ልንሰራ ይገባል ሲሉ ሀሳብ ሰጥተዋል።
የመድረኩን ማጠቃለያ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ የፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፍሁን አሉላ በአጠቃላይ በአመራሩ እና ሰራተኛው ጥረት አሁን ላይ በተቋሙ ጥሩ አፈፃፀም መኖሩ ገልፀው ይህንንም አጠናክረን ልንቀጥል ይገባል በማለት ከሰራተኛው ለቀረበላቸው ሀሳብና አስተያየት ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት የውይይት መድረኩን ተጠናቋል።
ዘገባው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍2
ባለስልጣኑ “በህብረተሰቡ የላቀ ተሳትፎ የደንብ መተላለፎችን እንከላከላለን” በሚል መሪ ቃል የህዝብ ውይይት አካሄደ
18/08/2016ዓ.ም
*አዲስ አበባ*
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከሁሉም ክፍለ ከተማ ከተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር እና የባለስልጣኑ አመራሮች በተገኙበት በ9 ወር ዕቅድ አፈፃፀም ዙሪያ እና በደንብ ቁጥር 150/2015 የአፈፃፀም መመሪያ ላይ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ አከናወነ።
የመድረኩን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ባለስልጣኑ ከተማችን አዲስ አበባ ለነዋሪዎቿ ምቹ እና ፅዱ እንድትሆን ሌት ተቀን እየሰራ የሚገኝ ተቋም ነው ብለዋል።
አክለውም የ 2016 በጀት አመቱን ሲጀመር እቅዱን ለህዝብ በማስተቸት ወደ ስራ እንደገባ ገልፀው። ለባለስልጣኑ የጀርባ አጥንት የሆነውን የህብረተሰባችንን አስተያየት በመቀበል ስራዎችን ስንሰራ የቆየን ሲሆን በዛሬው ዕለትም በ9 ወራት ውስጥ ምን ተሰራ ምንስ ይቀረናል የሚለውን የምናይበት መድረክ ይሆናል ሲሉ ገልፀዋል።
የባለስልጣኑን የሶስተኛ ሩብ ዓመትን የዕቅድ አፈፃፀም በእቅድ እና በጀት ዳይሮክቶሬት ዳይሬክተር ኮነሬል አድማሱ ተክሌ በበጀት ዓመቱ ከህብረተሰብ ጋር ተቀራርበን በመስራታችን ብዙ ለውጦች መምጣታቸውን ገልፀዋል።
ሌላው በደንብ ቁጥር 150/2015 ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጥ ሰነድ ያቀረቡት የቅድመ መከላከል እና ግንዛቤ ማስጨበጥ ዳይሮክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት ወ/ሮ ሰርካለም ጌታሁን ናቸው ።
በቀረቡት ሁለት ሰነዶች ላይ ሀሳብና አስተያየቶች ከህብረተሰቡ የተሰጡ ሲሆን ስራዎችን በጋራ መስራት ለውጤት እንደሚያደርስ እና ይህንን ለማስቀጠልም ተቀራርቦ መስራት እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል።
ከህብረተሰቡ ጋር በጋራ መስራት ከጀመርን በኋላ ለተቋማችን ትልቅ ኃይል ሆናችኋል ይህም ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ሲሉ የተናገሩት የውይይት መድረኩን ሲመሩ የነበሩት የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ አበባ እሸቴ ናቸው ።
ሌላኛው መድረኩን ሲመሩ የነበሩት የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ ፋፉ እንዳሉት በዛሬው ውይይታችን ያየናቸውን ነገሮች ለሁሉም ህብረተሰብ ማድረስ እንደሚገባ እና ለከተማዋ ልማት እንዲሁም ለተቋሙ ራዕይ እና ተልዕኮ እንቅፍት የሚሆኑ ህገወጦችን ከእናንተ ጋር በመሆን እንታገላለን ብለዋል። ለተነሱ ሀሳብ እና አስተያየት ምላሽ የሰጡ ሲሆን የቀጣይ የስራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
ዘገባው:-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
18/08/2016ዓ.ም
*አዲስ አበባ*
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከሁሉም ክፍለ ከተማ ከተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር እና የባለስልጣኑ አመራሮች በተገኙበት በ9 ወር ዕቅድ አፈፃፀም ዙሪያ እና በደንብ ቁጥር 150/2015 የአፈፃፀም መመሪያ ላይ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ አከናወነ።
የመድረኩን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ባለስልጣኑ ከተማችን አዲስ አበባ ለነዋሪዎቿ ምቹ እና ፅዱ እንድትሆን ሌት ተቀን እየሰራ የሚገኝ ተቋም ነው ብለዋል።
አክለውም የ 2016 በጀት አመቱን ሲጀመር እቅዱን ለህዝብ በማስተቸት ወደ ስራ እንደገባ ገልፀው። ለባለስልጣኑ የጀርባ አጥንት የሆነውን የህብረተሰባችንን አስተያየት በመቀበል ስራዎችን ስንሰራ የቆየን ሲሆን በዛሬው ዕለትም በ9 ወራት ውስጥ ምን ተሰራ ምንስ ይቀረናል የሚለውን የምናይበት መድረክ ይሆናል ሲሉ ገልፀዋል።
የባለስልጣኑን የሶስተኛ ሩብ ዓመትን የዕቅድ አፈፃፀም በእቅድ እና በጀት ዳይሮክቶሬት ዳይሬክተር ኮነሬል አድማሱ ተክሌ በበጀት ዓመቱ ከህብረተሰብ ጋር ተቀራርበን በመስራታችን ብዙ ለውጦች መምጣታቸውን ገልፀዋል።
ሌላው በደንብ ቁጥር 150/2015 ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጥ ሰነድ ያቀረቡት የቅድመ መከላከል እና ግንዛቤ ማስጨበጥ ዳይሮክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት ወ/ሮ ሰርካለም ጌታሁን ናቸው ።
በቀረቡት ሁለት ሰነዶች ላይ ሀሳብና አስተያየቶች ከህብረተሰቡ የተሰጡ ሲሆን ስራዎችን በጋራ መስራት ለውጤት እንደሚያደርስ እና ይህንን ለማስቀጠልም ተቀራርቦ መስራት እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል።
ከህብረተሰቡ ጋር በጋራ መስራት ከጀመርን በኋላ ለተቋማችን ትልቅ ኃይል ሆናችኋል ይህም ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ሲሉ የተናገሩት የውይይት መድረኩን ሲመሩ የነበሩት የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ አበባ እሸቴ ናቸው ።
ሌላኛው መድረኩን ሲመሩ የነበሩት የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ ፋፉ እንዳሉት በዛሬው ውይይታችን ያየናቸውን ነገሮች ለሁሉም ህብረተሰብ ማድረስ እንደሚገባ እና ለከተማዋ ልማት እንዲሁም ለተቋሙ ራዕይ እና ተልዕኮ እንቅፍት የሚሆኑ ህገወጦችን ከእናንተ ጋር በመሆን እንታገላለን ብለዋል። ለተነሱ ሀሳብ እና አስተያየት ምላሽ የሰጡ ሲሆን የቀጣይ የስራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
ዘገባው:-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍3
አዋኪ ድርጊት በሚፈፀምባቸው ንግድ ቤቶች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለፀ፡፡
በቦሌ ክፍለ ከተማ በህጋዊ ንግድ ሽፋን ሺሻ እና አደንዛዥ ዕፅ ሲጨስባቸው ከተገኙ ቤቶች 3ሺህ 80 የሺሻ ዕቃ እና 80 ኪሎ ግራም አደንዛዥ ዕፅ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለጸ
በከተማችን በተለያዩ አካባቢዎች በህጋዊ ንግድ ሽፋን የሚፈፀሙ አዋኪ ድርጊቶች እና ሌሎች ህገ ወጥ ተግባራት ለወንጀል መስፋፋት በምክንያትነት ይጠቀሳሉ፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ፣ከደንብ ማስከበር አባላትና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ችግሩን ለማስወገድ እየሰራ ይገኛል፡፡
በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ ንግድ ቤቶች ላይ በተከናወነ የኦፕሬሽን ስራ ሺሻ እና አደንዛዥ ዕፅ ሲጨስባቸው ተገኝተው እርምጃ እንደተወሰደባቸው እና በህገ ወጥ ድርጊቱ ላይ የተሳተፉ በርካታ ግለሰቦች ጉዳያቸው በህግ አግባብ እየታየ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡
ሰሞኑንም በቦሌ ክፍለ ከተማ በሚገኙ ወረዳዎች ፖሊስ እና የደንብ ማስከበር አባላትና ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት በጋራ ባከናወኑት ተግባር በህገ ወጦች ላይ እርምጃ ተወስዷል፡፡
ከክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው በህጋዊ ንግድ ሽፋን ሺሻ እና አደንዛዥ ዕፅ ሲጨስባቸው ከተገኙ ቤቶች 3ሺህ 80 የሺሻ ዕቃ እና 80 ኪሎ ግራም አደንዛዥ ዕፅ በቁጥጥር ስር በማዋል ከባለ ድርሻ አካላት ጋር የማስወገድ ስራ ተሰርቷል፡፡
ድንገተኛ ቁጥጥር የተደረገባቸው እና ለወንጀል መስፋፋት መንስዔ የሆኑ ድርጊቶች ሲፈፀምባቸው የነበሩት
መኖሪያ ቤትን ጨምሮ ፔንሲዮኖች፣ ማሳጅ ቤቶች እና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ይገኙበታል፡፡
(የአዲስ አበባ ፖሊስ)
በቦሌ ክፍለ ከተማ በህጋዊ ንግድ ሽፋን ሺሻ እና አደንዛዥ ዕፅ ሲጨስባቸው ከተገኙ ቤቶች 3ሺህ 80 የሺሻ ዕቃ እና 80 ኪሎ ግራም አደንዛዥ ዕፅ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለጸ
በከተማችን በተለያዩ አካባቢዎች በህጋዊ ንግድ ሽፋን የሚፈፀሙ አዋኪ ድርጊቶች እና ሌሎች ህገ ወጥ ተግባራት ለወንጀል መስፋፋት በምክንያትነት ይጠቀሳሉ፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ፣ከደንብ ማስከበር አባላትና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ችግሩን ለማስወገድ እየሰራ ይገኛል፡፡
በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ ንግድ ቤቶች ላይ በተከናወነ የኦፕሬሽን ስራ ሺሻ እና አደንዛዥ ዕፅ ሲጨስባቸው ተገኝተው እርምጃ እንደተወሰደባቸው እና በህገ ወጥ ድርጊቱ ላይ የተሳተፉ በርካታ ግለሰቦች ጉዳያቸው በህግ አግባብ እየታየ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡
ሰሞኑንም በቦሌ ክፍለ ከተማ በሚገኙ ወረዳዎች ፖሊስ እና የደንብ ማስከበር አባላትና ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት በጋራ ባከናወኑት ተግባር በህገ ወጦች ላይ እርምጃ ተወስዷል፡፡
ከክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው በህጋዊ ንግድ ሽፋን ሺሻ እና አደንዛዥ ዕፅ ሲጨስባቸው ከተገኙ ቤቶች 3ሺህ 80 የሺሻ ዕቃ እና 80 ኪሎ ግራም አደንዛዥ ዕፅ በቁጥጥር ስር በማዋል ከባለ ድርሻ አካላት ጋር የማስወገድ ስራ ተሰርቷል፡፡
ድንገተኛ ቁጥጥር የተደረገባቸው እና ለወንጀል መስፋፋት መንስዔ የሆኑ ድርጊቶች ሲፈፀምባቸው የነበሩት
መኖሪያ ቤትን ጨምሮ ፔንሲዮኖች፣ ማሳጅ ቤቶች እና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ይገኙበታል፡፡
(የአዲስ አበባ ፖሊስ)
👍5