ባለስልጣኑ የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር አከናወነ
22/03/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ሰኞ ማለዳ ከስራ ገበታ በፊት የሚያካሂደው የእውቀት ሽግግር ፕሮግራም ከተቋሙ ውጪ የሆነ እንግዳ በመጋበዝ የተቋም ውጤታማነት በሚል ርዕስ የባለስልጣኑ አመራሮች እና ሰራተኞች በተገኙበት ተካሂዷል፡፡
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ሳምንቱን ንቁ ሆነን ዉጤታማ ስራ ለማከናወንና በየሳምንቱ ከሰራተኞቻችን ጋር እንደቤተሰብ እየተማማርን መልካም ምኞት በመለዋወጥ ያለንን እውቀት በማካፈል ምንማማርበትና ልምድ የምንለዋወጥበት ነው በማለት አሁን ላይ እየተጠናከረ እየመጣ እንደሚገኝ ገልጸዋል ።
አክለውም በተቋማችን ምቹ የስራ አከባቢ በመፍጠር እንዲሁም የአገልግሎት አሰጣጡን የተሻለና ዘመናዊ በማድረግ በህብረተሰቡ ዘንድ ተቀባይነት ያለው ሰራተኞቹም ለስራ ተነሳሽነት ያለቸው መሆን እንደሚገባ ተናግረዋል ።
የዕለቱ የወርቃማ ሰኞ እንግዳ የግል ከፍተኛ ተቋማት ማህበር ዋና ሰራ አስኪያጅ አቶ ተፈራ ገበየሁ ተቋማዊ ዉጤታማነት ለፐብሊክ ሰርቪስ በሚል ርዕስ ለባለስልጣኑ አመራሮች ሰራተኞች የተዘጋጀ ሰነድ አቅርበዋል ።
በሰነዱ ተቋማዊ ውጤታማነት ከሲቪል ሰርቪስ አንጻር ምን እንደሚመስል ፣ ለተቋማዊ ውጤታማነት አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ ጉዳዮች እና የአገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያ መንገዶች በዝርዝር ቀርበዋል ።
ተቋማዊ ውጤታማነት አንድ ተቋም ያስቀመጣቸውን ግቦች በምን ያህል ደረጃ ማሳካቱ ፣ ለሰራተኞች ምቹ አከባቢ ስለመፍጠሩ እና የተገልጋዩችና የህብረተሰቡን ፍላጎት የማርካቱ አጠቃላይ የግምገማ ውጤት ማሳያና መገለጫ መሆኑን አቶ ተፈራ ገልጸዋል ።
አክለውም ተቋማዊ ውጤታማነት በተግባራዊ ጥረት እና በተቀናጀ ስራ የሚረጋገጥ መሆኑን ተናግረዋል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች
22/03/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ሰኞ ማለዳ ከስራ ገበታ በፊት የሚያካሂደው የእውቀት ሽግግር ፕሮግራም ከተቋሙ ውጪ የሆነ እንግዳ በመጋበዝ የተቋም ውጤታማነት በሚል ርዕስ የባለስልጣኑ አመራሮች እና ሰራተኞች በተገኙበት ተካሂዷል፡፡
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ሳምንቱን ንቁ ሆነን ዉጤታማ ስራ ለማከናወንና በየሳምንቱ ከሰራተኞቻችን ጋር እንደቤተሰብ እየተማማርን መልካም ምኞት በመለዋወጥ ያለንን እውቀት በማካፈል ምንማማርበትና ልምድ የምንለዋወጥበት ነው በማለት አሁን ላይ እየተጠናከረ እየመጣ እንደሚገኝ ገልጸዋል ።
አክለውም በተቋማችን ምቹ የስራ አከባቢ በመፍጠር እንዲሁም የአገልግሎት አሰጣጡን የተሻለና ዘመናዊ በማድረግ በህብረተሰቡ ዘንድ ተቀባይነት ያለው ሰራተኞቹም ለስራ ተነሳሽነት ያለቸው መሆን እንደሚገባ ተናግረዋል ።
የዕለቱ የወርቃማ ሰኞ እንግዳ የግል ከፍተኛ ተቋማት ማህበር ዋና ሰራ አስኪያጅ አቶ ተፈራ ገበየሁ ተቋማዊ ዉጤታማነት ለፐብሊክ ሰርቪስ በሚል ርዕስ ለባለስልጣኑ አመራሮች ሰራተኞች የተዘጋጀ ሰነድ አቅርበዋል ።
በሰነዱ ተቋማዊ ውጤታማነት ከሲቪል ሰርቪስ አንጻር ምን እንደሚመስል ፣ ለተቋማዊ ውጤታማነት አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ ጉዳዮች እና የአገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያ መንገዶች በዝርዝር ቀርበዋል ።
ተቋማዊ ውጤታማነት አንድ ተቋም ያስቀመጣቸውን ግቦች በምን ያህል ደረጃ ማሳካቱ ፣ ለሰራተኞች ምቹ አከባቢ ስለመፍጠሩ እና የተገልጋዩችና የህብረተሰቡን ፍላጎት የማርካቱ አጠቃላይ የግምገማ ውጤት ማሳያና መገለጫ መሆኑን አቶ ተፈራ ገልጸዋል ።
አክለውም ተቋማዊ ውጤታማነት በተግባራዊ ጥረት እና በተቀናጀ ስራ የሚረጋገጥ መሆኑን ተናግረዋል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች
👍2
የባለስልጣኑ የ2ኛ ዙር የአካል ብቃትና የንድፈ ሀሳብ ስልጠና ሂደት የመስክ ምልከታ ተደረገ
22/03/2018 ዓ.ም
** አዲስ አበባ **
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩንቨርሲቲ ሰንዳፋ ካምፓስ ለአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኦፊሰሮች እየተሰጠ ያለው የአካል ብቃትና የንድፈሀሳብ ስልጠና የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ፣ በስልጠናው አስተባባሪዎች እና በዩንቨርስቲው አመራሮች የስልጠና ሂደቱን ምልከታና ጎብኝት ተደርጓል።
በመስክ ምልከታው ስልጠናው በተያዘለት ጊዜና ፕሮግራም በጥሩ ዲሲፕሊን እየተሰጠ መሆኑን ተመልክተዋል።
ሰልጣኞቹ የተግባቦት ጥበብ በንድፈ ሀሳብ ስልጠና ሀገር ወዳድነት፣የሰብዓዊ መብት አያያዝ፣የሃይል አጠቃቀም፣ አገልግሎት አሰጣጥ እና የአካል ብቃት ስልጠና በተገቢው መንገድ እተከታተሉ መሆናቸውን ለማረጋገጥ ተችሏል።
ሰልጣኝ ኦፊሰሮች በበኩላቸው እየተሰጣቸው ያለው ስልጠና ለቀጣይ ስራቸው እጅግ ጠቃሚ መሆኑን ገልፀው ስልጠናው በቀጣይ ቀናትም በተዘጋጀው ፕሮግራም መሰረት እንደሚቀጥል ተገልጿል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ፦ https://linktr.ee/aacodeenforcement
22/03/2018 ዓ.ም
** አዲስ አበባ **
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩንቨርሲቲ ሰንዳፋ ካምፓስ ለአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኦፊሰሮች እየተሰጠ ያለው የአካል ብቃትና የንድፈሀሳብ ስልጠና የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ፣ በስልጠናው አስተባባሪዎች እና በዩንቨርስቲው አመራሮች የስልጠና ሂደቱን ምልከታና ጎብኝት ተደርጓል።
በመስክ ምልከታው ስልጠናው በተያዘለት ጊዜና ፕሮግራም በጥሩ ዲሲፕሊን እየተሰጠ መሆኑን ተመልክተዋል።
ሰልጣኞቹ የተግባቦት ጥበብ በንድፈ ሀሳብ ስልጠና ሀገር ወዳድነት፣የሰብዓዊ መብት አያያዝ፣የሃይል አጠቃቀም፣ አገልግሎት አሰጣጥ እና የአካል ብቃት ስልጠና በተገቢው መንገድ እተከታተሉ መሆናቸውን ለማረጋገጥ ተችሏል።
ሰልጣኝ ኦፊሰሮች በበኩላቸው እየተሰጣቸው ያለው ስልጠና ለቀጣይ ስራቸው እጅግ ጠቃሚ መሆኑን ገልፀው ስልጠናው በቀጣይ ቀናትም በተዘጋጀው ፕሮግራም መሰረት እንደሚቀጥል ተገልጿል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ፦ https://linktr.ee/aacodeenforcement
👍3❤1
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በህገወጥ እርድና እንሰሳት ዝውውር የግንዛቤ ማስጨበጫ የህዝብ ውይይት መድረክ አካሄደ
22/03/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በህገ-ወጥ እንሰሳት እርድና ዝውውር ላይ የሀይማኖት አባቶች፣አባ ገዳዎች ፣ሀደ ሲንቄዎች፣ሲቪክ ማህበራት፣ታዋቂ ግለሰቦች፣ የእድር መሪዎች፣የብሎክ አስተባባሪዎች፣ሴቶች፣ወጣቶች፣ ሰላም ሰራዊት፣የልኳንዳ ቤት ባለቤቶች በተገኙበት በህገወጥ እርድና እንሰሳት ዝውውር የግንዛቤ ማስጨበጫ ንቅናቄና የህዝብ ውይይት መድረክ አካሄደ።
መድረኩ በሀይማኖት አባቶች፣በሀገር ሽማግሌዎች እና አባ ገዳዎች ምርቃት የተጀመረ ሲሆን በመድረኩ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ መዓዛ ተክሉ እንደተናገሩት ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት እርምጃ ከመውሰዱ በፊት ለህብረተሰቡ በደንብ መተላለፎች ላይ ሰፊ ግንዛቤ እየፈጠረ መሆኑን ገልፀው በዛሬው ዕለትም በህገወጥ እርድና እንሰሳት ዝውውር ላይ ለህብረተሰቡን ግንዛቤ በመስጠት በጋራ በመስራትእንደሚገባ ገልፀዋል።
አክለውም እራሳችንን ከተለያዩ በሽታዎች እና ጤንነቱ ያልተረጋገጠ ስጋዎችን በየወንዝ ዳርቻዎች ፣በየአካባቢያችሁ ጨለማን ተገን አድርጎ ባልተፈቀደ ቦታ ፣በግለስብ ቤቶች ከሚታረዱ ህገወጥ እርዶች ከመመገብ እንቆጠብ ሲሉ አሳስበዋል።
በእለቱ ህገወጥ እርድ ሲከናወን ከህብረተሰቡ የተደበቀ አይደለም ከዚህ ጋር ተያይዞ ደንብ ተላልፈው ሲገኙ ጥቆማ በመስጠት እና ከተቋሙ ጎን በመቆም ደንብ መተላለፍን መቀነስ እና ማጥፋት እንደሚቻል ገልፀው ደንብ ተላልፎ የሚገኝ ማንኛውም ግለሰብ ይሁን ድርጅት ደንብና መመሪያው ባስቀመጠው መሰረት እርምጃ እንደሚወሰድበት ተገልጿል ፡፡
በመድረኩም የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የስልጠና ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ጌታሁን ኃብተ ማሪያም በህገወጥ እርድና እንሰሳት ዝውውር ሰነዶችን አዘጋጅቶ በማቅረብ ሰፊ የህዝብ ውይይት ተካሂዷል፡፡
በመጨረሻም ህብረተሰቡ ከደንብ ማስከበር ጎን ለመስራት ተነሳሽነት መኖሩን ገልፀው ከመድረኩ የተነሱትን ሀሳብና አስተያየት የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ መዓዛ ተክሉ፣የደንብ መተላለፍ መከላከል እና ስልጠና ስራዎች አስተባባሪ ወ/ሮ ንፁህ ታጠቅ፣የስልጠና ቡድን መሪ አቶ ጌታሁን ኃ/ማሪያም በጋራ ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት ተጠናቋል፡፡
በአዲስአለም ከፈለኝ
22/03/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በህገ-ወጥ እንሰሳት እርድና ዝውውር ላይ የሀይማኖት አባቶች፣አባ ገዳዎች ፣ሀደ ሲንቄዎች፣ሲቪክ ማህበራት፣ታዋቂ ግለሰቦች፣ የእድር መሪዎች፣የብሎክ አስተባባሪዎች፣ሴቶች፣ወጣቶች፣ ሰላም ሰራዊት፣የልኳንዳ ቤት ባለቤቶች በተገኙበት በህገወጥ እርድና እንሰሳት ዝውውር የግንዛቤ ማስጨበጫ ንቅናቄና የህዝብ ውይይት መድረክ አካሄደ።
መድረኩ በሀይማኖት አባቶች፣በሀገር ሽማግሌዎች እና አባ ገዳዎች ምርቃት የተጀመረ ሲሆን በመድረኩ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ መዓዛ ተክሉ እንደተናገሩት ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት እርምጃ ከመውሰዱ በፊት ለህብረተሰቡ በደንብ መተላለፎች ላይ ሰፊ ግንዛቤ እየፈጠረ መሆኑን ገልፀው በዛሬው ዕለትም በህገወጥ እርድና እንሰሳት ዝውውር ላይ ለህብረተሰቡን ግንዛቤ በመስጠት በጋራ በመስራትእንደሚገባ ገልፀዋል።
አክለውም እራሳችንን ከተለያዩ በሽታዎች እና ጤንነቱ ያልተረጋገጠ ስጋዎችን በየወንዝ ዳርቻዎች ፣በየአካባቢያችሁ ጨለማን ተገን አድርጎ ባልተፈቀደ ቦታ ፣በግለስብ ቤቶች ከሚታረዱ ህገወጥ እርዶች ከመመገብ እንቆጠብ ሲሉ አሳስበዋል።
በእለቱ ህገወጥ እርድ ሲከናወን ከህብረተሰቡ የተደበቀ አይደለም ከዚህ ጋር ተያይዞ ደንብ ተላልፈው ሲገኙ ጥቆማ በመስጠት እና ከተቋሙ ጎን በመቆም ደንብ መተላለፍን መቀነስ እና ማጥፋት እንደሚቻል ገልፀው ደንብ ተላልፎ የሚገኝ ማንኛውም ግለሰብ ይሁን ድርጅት ደንብና መመሪያው ባስቀመጠው መሰረት እርምጃ እንደሚወሰድበት ተገልጿል ፡፡
በመድረኩም የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የስልጠና ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ጌታሁን ኃብተ ማሪያም በህገወጥ እርድና እንሰሳት ዝውውር ሰነዶችን አዘጋጅቶ በማቅረብ ሰፊ የህዝብ ውይይት ተካሂዷል፡፡
በመጨረሻም ህብረተሰቡ ከደንብ ማስከበር ጎን ለመስራት ተነሳሽነት መኖሩን ገልፀው ከመድረኩ የተነሱትን ሀሳብና አስተያየት የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ መዓዛ ተክሉ፣የደንብ መተላለፍ መከላከል እና ስልጠና ስራዎች አስተባባሪ ወ/ሮ ንፁህ ታጠቅ፣የስልጠና ቡድን መሪ አቶ ጌታሁን ኃ/ማሪያም በጋራ ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት ተጠናቋል፡፡
በአዲስአለም ከፈለኝ
👍7❤6