የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን Addis Ababa Code Enforcement Authority
1.36K subscribers
2.65K photos
5 videos
1 file
63 links
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
Download Telegram
ባለስልጣኑ "የመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እምርታ"በሚል መሪ ሀሳብ የውይይት መድረክ አካሄደ

20/03/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን "በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እምርታ "በሚል መሪ ሀሳብ በ2018 በጀት ዓመት የሚከናወኑ የአጭር ጊዜ እቅድ የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ከክፍለ ከተማና ከወረዳ አመራሮች ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል ።

በመድረኩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ሀገራችንን እንዲሁም ከተማችን እያሳዩ የሚገኘውን ፈጣን እድገት ለማስቀጠልና ሁለንተናዊ የብልጽግና ጉዞ ለማሳካት በስልጠናው በጨበጥነው ሞራል በከፍተኛ ተነሳሽነትና በላቀ ቁርጠኝነት ወደ ስራ መግባት እንደሚጠበቅ አስገንዝበዋል ።

አክለውም የአገልግሎት አሰጣጥን በማሻሻል የተገልጋይ እርካታን ለማሳደግ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራትን በማስፋት የግንዛቤ ስራዎች በማጠናከርና በማስፋት የቁጥጥርና የእርምጃ አወሳሰድ ተግባራትን መቀነስ እንደሚገባ ገልፀዋል።

በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እምርታ የ2018 በጀት ዓመት የአጭር ጊዜ እቅድ በባለስልጣኑ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ አቅርበዋል ።

በከተማችን የደንብ መተላለፍ በመከላከል በመቆጣጠርና እርምጃ በመውሰድ እንዲሁም የስልጠና ግንዛቤ ስራዎችን በማጠናከር የተቋሙን አገልግሎት አሰጣጥ ዘመናዊና ተደራሽ በማድረግ የሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመፍታት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ እና ባለቤት በማድረግ ህገወጥነት በከተማችን እንዲቀንስ ማስቻል እንደሚገባ በሰነዱ ተገልጿል ።

የሌብነትና ብልሹ አሰራር በመታገል የ 7/24 የስራ ባህልን በማዳበር በበጀት ዓመቱ ህብረተሰቡንና ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ የተገኘውን ውጤት አጠናክሮ ለማስቀጠል የቀጣይ ሰራዎች ላይ በእቅድ መንቀሳቀስ አስፈላጊ መሆኑን የባለሥልጣኑ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ ገልጸዋል ።

በመጨረሻም በቀረበው ሰነድ ዙሪያ ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽና አስተያየት ተሰጥቶበት መድረኩ ተጠናቋል።

በማጠቃለያው አመራሩና ሰራተኛው በስነ-ምግባር የታነፀ ከብልሹ አሰራር የጸዳ የህዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ የሚሰጠውን ተልዕኮ በአግባቡ መፈጸም የሚችል ለሌሎች አካላትና በስሩ ለሚገኙ ሰራተኞች አርአያ በመሆን ሌት ተቀን መትጋት እንደሚገባ ዋና ስራ አስኪያጁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች
🥰2👍1
ባለስልጣኑ የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር አከናወነ

22/03/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ሰኞ ማለዳ ከስራ ገበታ በፊት የሚያካሂደው የእውቀት ሽግግር ፕሮግራም ከተቋሙ ውጪ የሆነ እንግዳ በመጋበዝ የተቋም ውጤታማነት በሚል ርዕስ የባለስልጣኑ አመራሮች እና ሰራተኞች በተገኙበት ተካሂዷል፡፡

በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ሳምንቱን ንቁ ሆነን ዉጤታማ ስራ ለማከናወንና በየሳምንቱ ከሰራተኞቻችን ጋር እንደቤተሰብ እየተማማርን መልካም ምኞት በመለዋወጥ ያለንን እውቀት በማካፈል ምንማማርበትና ልምድ የምንለዋወጥበት ነው በማለት አሁን ላይ እየተጠናከረ እየመጣ እንደሚገኝ ገልጸዋል ።

አክለውም በተቋማችን ምቹ የስራ አከባቢ በመፍጠር እንዲሁም የአገልግሎት አሰጣጡን የተሻለና ዘመናዊ በማድረግ በህብረተሰቡ ዘንድ ተቀባይነት ያለው ሰራተኞቹም ለስራ ተነሳሽነት ያለቸው መሆን እንደሚገባ ተናግረዋል ።

የዕለቱ የወርቃማ ሰኞ እንግዳ የግል ከፍተኛ ተቋማት ማህበር ዋና ሰራ አስኪያጅ አቶ ተፈራ ገበየሁ ተቋማዊ ዉጤታማነት ለፐብሊክ ሰርቪስ በሚል ርዕስ ለባለስልጣኑ አመራሮች ሰራተኞች የተዘጋጀ ሰነድ አቅርበዋል ።

በሰነዱ ተቋማዊ ውጤታማነት ከሲቪል ሰርቪስ አንጻር ምን እንደሚመስል ፣ ለተቋማዊ ውጤታማነት አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ ጉዳዮች እና የአገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያ መንገዶች በዝርዝር ቀርበዋል ።

ተቋማዊ ውጤታማነት አንድ ተቋም ያስቀመጣቸውን ግቦች በምን ያህል ደረጃ ማሳካቱ ፣ ለሰራተኞች ምቹ አከባቢ ስለመፍጠሩ እና የተገልጋዩችና የህብረተሰቡን ፍላጎት የማርካቱ አጠቃላይ የግምገማ ውጤት ማሳያና መገለጫ መሆኑን አቶ ተፈራ ገልጸዋል ።

አክለውም ተቋማዊ ውጤታማነት በተግባራዊ ጥረት እና በተቀናጀ ስራ የሚረጋገጥ መሆኑን ተናግረዋል ።

ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች
👍2
የባለስልጣኑ የ2ኛ ዙር የአካል ብቃትና የንድፈ ሀሳብ ስልጠና ሂደት የመስክ ምልከታ ተደረገ

22/03/2018 ዓ.ም
** አዲስ አበባ **

በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩንቨርሲቲ ሰንዳፋ ካምፓስ ለአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኦፊሰሮች እየተሰጠ ያለው የአካል ብቃትና የንድፈሀሳብ ስልጠና የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ፣ በስልጠናው አስተባባሪዎች እና በዩንቨርስቲው አመራሮች የስልጠና ሂደቱን ምልከታና ጎብኝት ተደርጓል።

በመስክ ምልከታው ስልጠናው በተያዘለት ጊዜና ፕሮግራም በጥሩ ዲሲፕሊን እየተሰጠ መሆኑን ተመልክተዋል።

ሰልጣኞቹ የተግባቦት ጥበብ በንድፈ ሀሳብ ስልጠና ሀገር ወዳድነት፣የሰብዓዊ መብት አያያዝ፣የሃይል አጠቃቀም፣ አገልግሎት አሰጣጥ እና የአካል ብቃት ስልጠና በተገቢው መንገድ እተከታተሉ መሆናቸውን ለማረጋገጥ ተችሏል።

ሰልጣኝ ኦፊሰሮች በበኩላቸው እየተሰጣቸው ያለው ስልጠና ለቀጣይ ስራቸው እጅግ ጠቃሚ መሆኑን ገልፀው ስልጠናው በቀጣይ ቀናትም በተዘጋጀው ፕሮግራም መሰረት እንደሚቀጥል ተገልጿል።

መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ፦ https://linktr.ee/aacodeenforcement
👍31