ባለስልጣኑ በከተማዋ በ83.8% የደንብ መተላለፎች  እንዲቀንስ ማድረግ መቻሉ ተገለፀ
ጥቅምት 4/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2018 በጀት ዓመት የ1ኛ ሩብ አመት እቅድ አፈጻጸም የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ከክፍለ ከተማ እና ከወረዳ አመራሮች ጋር ባለስልጣኑ መሰብሰቢያ አደራሽ የግምገማ መድረክ አካሂዷል ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ባለስልጣኑ በከተማ አስተዳደሩ የተሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ እየተወጣ መሆኑን በመግለፅ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ጊዜ አንፃር የደንብ ጥሰት በ83.8% መቀነሱን ገልፀዋል።
በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎችን ከመከላከልና ከመቆጣጠር ባሻገር በሰው ተኮር ተግባራት ፣ በአቅመ ደካማ በቤት እድሳት፣በደም ልገሳ ፣ በችግኝ ተከላ እና ማዕድ የማጋራት በርካታ ስራዎች በመስራት በሩብ ዓመቱ የበኩሉን እየተወጣ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል ።
በመድረኩ የባለስልጣኑ የ2018 በጀት ዓመት የ1ኛ ሩብ አመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በባለስልጣኑ እቅድና በጀት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በኮለኔል አድማሱ ተክሌ ቀርቧል።
በሪፖርቱ የደንብ ጥሰቶችን ከመከላከልና ከመቆጣጠር እርምጃ ከመውሰድ አንፃር ፣ ከኢንሸቲብ ስራዎች፣ከግንዛቤ ፈጠራ አና ከመልካም አስተዳደር አንፃር የተሰሩ ስራዎች በዝርዝር ተመላክተዋል።
በሩብ አመቱ ከደንብ ተላላፊዎች ቅጣት እና ከተወረሱ ንብረቶች ጨረታ ሽያጭ ከከ60 ሚሊዮን ብር በላይ ለከተማው ገቢ በማድረግ ለከተማው ልማት እንዲውል መቻሉን በሪፖርቱ ተገልጿል ።
በግምገማው የክፍለ ከተማ እና የወረዳ አመራሮች በቀረበው ሪፖርት ዙሪያ መነሻ በማድረግ በቡድን በመከፋፈል ከመልካም አስተዳደር ፣ ከአገልግሎት አሰጣጥ ፣ ከብልሹ አሰራር ፣ የደንብ ጥሰቶችን ከመቀነስ እና ታቅደው የተፈጸሙ ክንውኖች በአፈጻጸም ወቅት ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እና ተግዳሮቶችን ለመፍታት የተወሰዱ መፍትሔዎች ላይ በባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች አወያይነት ሰፊ ውይይት ተደርጎል።
በውይይት ከተሳታፊዎች ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጁ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል
በመጨረሻም የቀጣይ የስራ አቅጣጫዎች የተቀመጡ ሲሆን በተለይ የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ብክለት ለመከላከል በትኩረት እንዲሰራና በካዮቹ ተጠያቂ እዲደረጉ የቀጣይ የስራ አቅጣጫ በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል ።
ዘገበው ፡-የባለሥልጣኑ ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው፡፡
ጥቅምት 4/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2018 በጀት ዓመት የ1ኛ ሩብ አመት እቅድ አፈጻጸም የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ከክፍለ ከተማ እና ከወረዳ አመራሮች ጋር ባለስልጣኑ መሰብሰቢያ አደራሽ የግምገማ መድረክ አካሂዷል ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ባለስልጣኑ በከተማ አስተዳደሩ የተሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ እየተወጣ መሆኑን በመግለፅ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ጊዜ አንፃር የደንብ ጥሰት በ83.8% መቀነሱን ገልፀዋል።
በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎችን ከመከላከልና ከመቆጣጠር ባሻገር በሰው ተኮር ተግባራት ፣ በአቅመ ደካማ በቤት እድሳት፣በደም ልገሳ ፣ በችግኝ ተከላ እና ማዕድ የማጋራት በርካታ ስራዎች በመስራት በሩብ ዓመቱ የበኩሉን እየተወጣ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል ።
በመድረኩ የባለስልጣኑ የ2018 በጀት ዓመት የ1ኛ ሩብ አመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በባለስልጣኑ እቅድና በጀት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በኮለኔል አድማሱ ተክሌ ቀርቧል።
በሪፖርቱ የደንብ ጥሰቶችን ከመከላከልና ከመቆጣጠር እርምጃ ከመውሰድ አንፃር ፣ ከኢንሸቲብ ስራዎች፣ከግንዛቤ ፈጠራ አና ከመልካም አስተዳደር አንፃር የተሰሩ ስራዎች በዝርዝር ተመላክተዋል።
በሩብ አመቱ ከደንብ ተላላፊዎች ቅጣት እና ከተወረሱ ንብረቶች ጨረታ ሽያጭ ከከ60 ሚሊዮን ብር በላይ ለከተማው ገቢ በማድረግ ለከተማው ልማት እንዲውል መቻሉን በሪፖርቱ ተገልጿል ።
በግምገማው የክፍለ ከተማ እና የወረዳ አመራሮች በቀረበው ሪፖርት ዙሪያ መነሻ በማድረግ በቡድን በመከፋፈል ከመልካም አስተዳደር ፣ ከአገልግሎት አሰጣጥ ፣ ከብልሹ አሰራር ፣ የደንብ ጥሰቶችን ከመቀነስ እና ታቅደው የተፈጸሙ ክንውኖች በአፈጻጸም ወቅት ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እና ተግዳሮቶችን ለመፍታት የተወሰዱ መፍትሔዎች ላይ በባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች አወያይነት ሰፊ ውይይት ተደርጎል።
በውይይት ከተሳታፊዎች ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጁ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል
በመጨረሻም የቀጣይ የስራ አቅጣጫዎች የተቀመጡ ሲሆን በተለይ የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ብክለት ለመከላከል በትኩረት እንዲሰራና በካዮቹ ተጠያቂ እዲደረጉ የቀጣይ የስራ አቅጣጫ በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል ።
ዘገበው ፡-የባለሥልጣኑ ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው፡፡
👍4❤1
  ወንዝና አካባቢ የበከሉ ተቋማትና ግለሰቦች 1.800,000 (አንድ ሚሊዮን ስምንት መቶ ሺህ) ብር ተቀጡ
ጥቅምት 04/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአዲስ ከተማ እና በጉለሌ ክፍለ ከተማ 9 ግለሰቦችና ተቋማት ወንዝና የወንዝ ዳርቻ በመበከላቸው በደምብ ቁጥር 180/2017 መሰረት (አንድ ሚሊዮን ስምንት መቶ ሺህ) ብር በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱ አስታወቀ።
ባለስልጣኑ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ
ሁሴኔ አብዳለ 150,000፣ ዳኞ አሞኔ 150,000፣ዝናሽ አሰፋ 100,000፣ኤ,ቲ,ኤ,ኤ ድርጅት 300,000፣ኦሮሚያ ግብርና ህብረት 300,000፣ገዛኸኝ ባዴ 50,000፣ሙላቱ አስረድ 50,000 በአጠቃላይ 1,500,000 (አንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሺህ) ብር የቅጣት እርምጃ ተወስዶባቸዋል።
በተመሳሳይ በጉለሌ ክፍለ ከተማ ሁለት ግለሰቦች የሽንት ቤት ፍሳሽ ወደ ወንዝ በመልቀቅ ወንዝና አካባቢውን በመበከላቸው ጌትዬ ነጋሽ እና እነ እሱባለው ማስረሻ እያንዳንዳቸው 150,000 (አንድ መቶ ሀምሳ ሺህ ብር) በድምሩ 300,000 (ሶትት መቶ ሺ ብር) ተቀጥተዋል።
ባለስልጣኑደ የተለያዩ ቆሻሻ በመልቀቅ ወንዝና አካባቢን የሚበክሉ ግለሰቦችና ተቋማት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ እያሳሰበ ወንዝና የወንዝ ዳርቻ የሚበክሉ ግለሰቦችና ተቋማትን እንደማይታገስ አስታውቋል።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ መረጃ በመስጠት ሀገራዊ ግዴታቸው የሚወጡ ነዋሪዎችን እያመሰገነ መላው የከተማው ነዋሪ ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች ጥቆማ 9995 ነፃ የስልክ መስመር እንዲጠቀሙ መልዕክቱን አስተላልፏል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ጥቅምት 04/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአዲስ ከተማ እና በጉለሌ ክፍለ ከተማ 9 ግለሰቦችና ተቋማት ወንዝና የወንዝ ዳርቻ በመበከላቸው በደምብ ቁጥር 180/2017 መሰረት (አንድ ሚሊዮን ስምንት መቶ ሺህ) ብር በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱ አስታወቀ።
ባለስልጣኑ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ
ሁሴኔ አብዳለ 150,000፣ ዳኞ አሞኔ 150,000፣ዝናሽ አሰፋ 100,000፣ኤ,ቲ,ኤ,ኤ ድርጅት 300,000፣ኦሮሚያ ግብርና ህብረት 300,000፣ገዛኸኝ ባዴ 50,000፣ሙላቱ አስረድ 50,000 በአጠቃላይ 1,500,000 (አንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሺህ) ብር የቅጣት እርምጃ ተወስዶባቸዋል።
በተመሳሳይ በጉለሌ ክፍለ ከተማ ሁለት ግለሰቦች የሽንት ቤት ፍሳሽ ወደ ወንዝ በመልቀቅ ወንዝና አካባቢውን በመበከላቸው ጌትዬ ነጋሽ እና እነ እሱባለው ማስረሻ እያንዳንዳቸው 150,000 (አንድ መቶ ሀምሳ ሺህ ብር) በድምሩ 300,000 (ሶትት መቶ ሺ ብር) ተቀጥተዋል።
ባለስልጣኑደ የተለያዩ ቆሻሻ በመልቀቅ ወንዝና አካባቢን የሚበክሉ ግለሰቦችና ተቋማት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ እያሳሰበ ወንዝና የወንዝ ዳርቻ የሚበክሉ ግለሰቦችና ተቋማትን እንደማይታገስ አስታውቋል።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ መረጃ በመስጠት ሀገራዊ ግዴታቸው የሚወጡ ነዋሪዎችን እያመሰገነ መላው የከተማው ነዋሪ ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች ጥቆማ 9995 ነፃ የስልክ መስመር እንዲጠቀሙ መልዕክቱን አስተላልፏል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍4
  ባለስልጣኑ በጥናት  አዘገጃጀት ዙርያ ስልጠና ሰጠ
ጥቅምት 5/2018
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በጥናት አዘገጃጀት ዙርያ ለማዕከሉ ዳይሬክተሮች ፣ ቡድን መሪዎች እና የክፍለ ከተማ የስልጠና ባለሙያዎች ስልጠና ተሰጥቷል ።
ስልጠናውን ያስጀመሩት የባለሥልጣኑ የጽ/ቤት ኃለፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ የባለስልጣኑ የስልጠናና ጥናት ዳይሬክቶሬት በተለያዩ የደንብ መተላለፎች ዙርያ ጥናቶች መስራቱን ጠቁመው በ9ኙ የደንብ መተላለፎች ዙርያ ምንጮች ለማወቅ እና ችግር ፈች ጥናት ወሳኝ በመሆኑ ሰልጣኞች ስልጠናውን በትኩረት በመከታተል ችግሮችን በመለየት ወደ መፍትሄ መግባት እንደሚችል አስገንዝበዋል።
ስልጠናው ከአዲስ አበባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስ የሰው ሀብት ልማት ቢሮ የሰው ሀብት ልማት ዳይሬክተር በሆኑት አቶ ተፈራ ሙሉነህ ተሰጥቷል።
በስልጠናው ጥናት እንዴት እንደሚዘጋጅ፣ ስለ ጥናት አይነቶች ፣ ሰለ አጠናን ዘዴዎች፣ ጥናት ችግርን ለመፍታትና የችግሩን ዋና ምንጭ ለማወቅ እንደሚረዳ፣ ሰለ ጥናት አዘገጃጀት ቅደም ተከተል ዳራ ፣አለማ፣ወሰን ፣የተዛማጅ ጥናት ቅኝት እና ስለ ጥናት መሰረታዊ ባህሪ በመሳሰሉት ዙርያ ላይ ስልጠና ተሰጥቷል።
በመጨረሻም የባለስልጣኑ የደንብ መተላለፍ መከላከልና ግንዛቤ ማስጨበጫ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰርካለም ጌታሁን ጥናቶች በማዕከል ደረጃ ብቻ ሳይሆን እስከታችኛው መዋቅር ድረስ መጠናትና ስላለባቸው ሰልጣኞች የወሰዱት ስልጠና እስከታች እንዲወርዱ እና ጥናቶች እንዲሰሩ አቅጣጫ በመስጠት ስልጠናው ተጠናቋል ።
ዘገባው ፦ የባለሥልጣኑ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ጥቅምት 5/2018
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በጥናት አዘገጃጀት ዙርያ ለማዕከሉ ዳይሬክተሮች ፣ ቡድን መሪዎች እና የክፍለ ከተማ የስልጠና ባለሙያዎች ስልጠና ተሰጥቷል ።
ስልጠናውን ያስጀመሩት የባለሥልጣኑ የጽ/ቤት ኃለፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ የባለስልጣኑ የስልጠናና ጥናት ዳይሬክቶሬት በተለያዩ የደንብ መተላለፎች ዙርያ ጥናቶች መስራቱን ጠቁመው በ9ኙ የደንብ መተላለፎች ዙርያ ምንጮች ለማወቅ እና ችግር ፈች ጥናት ወሳኝ በመሆኑ ሰልጣኞች ስልጠናውን በትኩረት በመከታተል ችግሮችን በመለየት ወደ መፍትሄ መግባት እንደሚችል አስገንዝበዋል።
ስልጠናው ከአዲስ አበባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስ የሰው ሀብት ልማት ቢሮ የሰው ሀብት ልማት ዳይሬክተር በሆኑት አቶ ተፈራ ሙሉነህ ተሰጥቷል።
በስልጠናው ጥናት እንዴት እንደሚዘጋጅ፣ ስለ ጥናት አይነቶች ፣ ሰለ አጠናን ዘዴዎች፣ ጥናት ችግርን ለመፍታትና የችግሩን ዋና ምንጭ ለማወቅ እንደሚረዳ፣ ሰለ ጥናት አዘገጃጀት ቅደም ተከተል ዳራ ፣አለማ፣ወሰን ፣የተዛማጅ ጥናት ቅኝት እና ስለ ጥናት መሰረታዊ ባህሪ በመሳሰሉት ዙርያ ላይ ስልጠና ተሰጥቷል።
በመጨረሻም የባለስልጣኑ የደንብ መተላለፍ መከላከልና ግንዛቤ ማስጨበጫ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰርካለም ጌታሁን ጥናቶች በማዕከል ደረጃ ብቻ ሳይሆን እስከታችኛው መዋቅር ድረስ መጠናትና ስላለባቸው ሰልጣኞች የወሰዱት ስልጠና እስከታች እንዲወርዱ እና ጥናቶች እንዲሰሩ አቅጣጫ በመስጠት ስልጠናው ተጠናቋል ።
ዘገባው ፦ የባለሥልጣኑ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍5❤1