ባለስልጣኑ የመስከረም ወር መደበኛና ወቅታ ተግባራትን ከክፍለ ከተማ አመራሮች ጋር ገመገመ
መስከረም 28/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የመስከረም ወር በእቅድ አፈፀፀምና ወቅታዊ ስራዎች በተመለከ ከክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች ጋር የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ውይይት አደረገ።
በመድረኩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የመስከረም ወር የአደባባይ በዓላት የነበሩበት ቢሆንም ከዚህ ጎን ለጎን በካስኬዲንግ የወረዱትን ተግባራት በጥራት መስራት መቻሉ ጠቁመዋል።
በውይይቱ የመስከረም ወር እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እያንዳንዱ ክፍለ ከተማ ያቀረበ ሲሆን በወሩ የአደባባይ ሁነቶች ላይ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን ፣ በ9ኙ የደንብ ጥሰቶች የመከላከል ፣የመቆጣጠር እና አስተዳደራዊ እርምጃ የመውሰድ ስራዎች መሰራታቸውን ገልፀዋል።
በመድረኩ በድክመትና በጥንካሬ የታዩ ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰዱ እርምጃዎች በሪፖርቱ በዝርዝር ቀርበዋል።
በወሩ የተሰሩ ስራዎች ጠንካራ እንደነበረ የተገለፀ ሲሆን መሬት ባንክ የገቡ መሬቶች ላይ መረጃ በጥንቃቄ መሰራት እንዳለበት እና አስተዳደራዊ ቅጣቶች የቅጣት ደረሰኝ በትክክል መከፈላቸው መረጋገጥ እንደሚገባ የትኩረት አቅጣጫ በማስቀመጥ መድረኩ ተጠናቋል።
ዘገባው፦ የባለስልጣኑ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
መስከረም 28/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የመስከረም ወር በእቅድ አፈፀፀምና ወቅታዊ ስራዎች በተመለከ ከክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች ጋር የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ውይይት አደረገ።
በመድረኩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የመስከረም ወር የአደባባይ በዓላት የነበሩበት ቢሆንም ከዚህ ጎን ለጎን በካስኬዲንግ የወረዱትን ተግባራት በጥራት መስራት መቻሉ ጠቁመዋል።
በውይይቱ የመስከረም ወር እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እያንዳንዱ ክፍለ ከተማ ያቀረበ ሲሆን በወሩ የአደባባይ ሁነቶች ላይ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን ፣ በ9ኙ የደንብ ጥሰቶች የመከላከል ፣የመቆጣጠር እና አስተዳደራዊ እርምጃ የመውሰድ ስራዎች መሰራታቸውን ገልፀዋል።
በመድረኩ በድክመትና በጥንካሬ የታዩ ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰዱ እርምጃዎች በሪፖርቱ በዝርዝር ቀርበዋል።
በወሩ የተሰሩ ስራዎች ጠንካራ እንደነበረ የተገለፀ ሲሆን መሬት ባንክ የገቡ መሬቶች ላይ መረጃ በጥንቃቄ መሰራት እንዳለበት እና አስተዳደራዊ ቅጣቶች የቅጣት ደረሰኝ በትክክል መከፈላቸው መረጋገጥ እንደሚገባ የትኩረት አቅጣጫ በማስቀመጥ መድረኩ ተጠናቋል።
ዘገባው፦ የባለስልጣኑ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
❤6
በእግረኞች መንገድ በተሽከርካሪ በመሄድ ደንብ የተላለፈው ግለሰብ እና ወንዝን የበከለ ድርጅት መቀጣቱ አስታወቀ
29/01/2018 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በንፋስ ስልክ ላፍቶ በልማት ኮሪደር በተሰራው እግረኞች መንገድ ላይ በመኪና በመሄድ ደንብ ተላልፎ የተሰወረን አሽከርካሪ ከአዲስ አበባ ትራፊክ ፖሊስ ጋር በመተባበር በቁጥጥር ስር በማዋል 5ዐ,000( ሀምሳ ሺህ ) ብር መቅጣቱን አስታወቀ ።
በተያያዘ ዜና የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ፅ/ ቤት በወረዳ 5 ልዪ ቦታ ዘነበ ወርቅ አደባባይ ኤስ አይ ኤም የተባለ ግብረ ሰናይ/NGO/ድርጅት ፍሳሽ ቆሻሻ ወደ አስፖልት እና ወንዝ በመልቀቅ 300,000ብር(ሶስት መቶ ሺ) ብር በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዷል።
ህብረተሰቡ በከተማዋ ውስጥ በመንግስትና በህዝብ ሀብት የተገነቡ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ መሠረተ ልማቶችን ደህንነት በመጠበቅ መገልገልና መጠቀም እንደሚገባ አስታውቋል ፡፡
ባለስልጣኑ ህብረተሰቡ ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች መረጃ በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን ያቀርባል።
መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
29/01/2018 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በንፋስ ስልክ ላፍቶ በልማት ኮሪደር በተሰራው እግረኞች መንገድ ላይ በመኪና በመሄድ ደንብ ተላልፎ የተሰወረን አሽከርካሪ ከአዲስ አበባ ትራፊክ ፖሊስ ጋር በመተባበር በቁጥጥር ስር በማዋል 5ዐ,000( ሀምሳ ሺህ ) ብር መቅጣቱን አስታወቀ ።
በተያያዘ ዜና የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ፅ/ ቤት በወረዳ 5 ልዪ ቦታ ዘነበ ወርቅ አደባባይ ኤስ አይ ኤም የተባለ ግብረ ሰናይ/NGO/ድርጅት ፍሳሽ ቆሻሻ ወደ አስፖልት እና ወንዝ በመልቀቅ 300,000ብር(ሶስት መቶ ሺ) ብር በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዷል።
ህብረተሰቡ በከተማዋ ውስጥ በመንግስትና በህዝብ ሀብት የተገነቡ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ መሠረተ ልማቶችን ደህንነት በመጠበቅ መገልገልና መጠቀም እንደሚገባ አስታውቋል ፡፡
ባለስልጣኑ ህብረተሰቡ ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች መረጃ በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን ያቀርባል።
መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
❤7👍4
በአዋኪ ድርጊቶች እና ብልሹ አሰራርን በመከላከል ዙሪያ የህዝብ ውይይት መድረክ ተካሄደ
30/01/2018 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በኮልፌ ፣ በአራዳ እና በቦሌ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በአዋኪ ድርጊቶችን መከላከል ላይ፣ በደንብ ቁጥር 150/2015 እና በፀረ ሙስና እና ብልሹ አሰራርን በመከላከል ዙሪያ በህዝብ ንቅናቄ መድረክ በማዘጋጀት ለህብረተሰቡ ግንዛቤ መፍጠር ተፈጥሯል ::
በግንዛቤ መድረኮቹ አዋኪ ድርጊቶችን መከላከል እና በስነምግባር እና ብልሹ አሰራር መከላከል በሚል ርዕስ ለህብረተሰቡ የተዘጋጀ ሰነድ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል ።
በመድረኩ ከአዋኪ ድርጊት ጋር በተያያዘ በተለያዩ መንገዶች ግንዛቤ ተፈጥሯል በተለይም ደግሞ በት/ቤቶች ላይ ለተማሪዎች በቅ/መከላከል ባለሙያዎቻችን አማካኝነት በየጊዜው ግንዛቤ የመፍጠር ተግባር እየተከናወነ እንደሚገኝ ተገልጿል ።
ህብረተሰቡ በአሁኑ ሰዓት ህገ ወጥነትን ለመከላከል እያደረገ ያለውን ስራ በማጠናከርና ተባባሪ በመሆን ሊሰሩ እንደሚገባና ከመሰል አዋኪ ተግባራት ልጆቻቸውና ራሳቸውን በማራቅ ለሌሎች አርዓያ መሆን እንደሚገባቸው በመድረኮቹ ተገልጿል ።
የደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ደንቡና መመሪያውን ተፈፃሚ እንዲሆን እና በሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ተደራሽ በማድረግ ለብልሹ አሰራር እና ፀረ ሙስና ተጋላጭነት መቆጣጠር መቻል ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶት ሊሰራበት የሚገባ ጉዳይ መሆኑ ተገልጿል::
በመድረኩ አዋኪ ድርጊትን በመከላከል ህብረተሰቡም ከደንብ ማስከበር ጋር በመቀናጀት የግንዛቤ ስራዎችን አጠናክረው መስራትና እርምጃ እንዲወሰድ የበኩላቸውን ሚና መወጣት እንዳለባቸው ተነግሯል ።
ወጣቱን ከአዋኪ ድርጊቶችን እና ብልሹ አሰራሮችን እንዴት እራሱን መከላከልና መቆጣጠር እንደሚቻል በሰነዱ በዝርዝር ተገልፃል ።
በመጨረሻም ከተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎች በተሰጡ ሀሳብ አስተያየት ጥያቄዎች ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ ከመድረኩ ለተነሱት ሀሳብና አስተያየት ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል።
መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
30/01/2018 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በኮልፌ ፣ በአራዳ እና በቦሌ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በአዋኪ ድርጊቶችን መከላከል ላይ፣ በደንብ ቁጥር 150/2015 እና በፀረ ሙስና እና ብልሹ አሰራርን በመከላከል ዙሪያ በህዝብ ንቅናቄ መድረክ በማዘጋጀት ለህብረተሰቡ ግንዛቤ መፍጠር ተፈጥሯል ::
በግንዛቤ መድረኮቹ አዋኪ ድርጊቶችን መከላከል እና በስነምግባር እና ብልሹ አሰራር መከላከል በሚል ርዕስ ለህብረተሰቡ የተዘጋጀ ሰነድ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል ።
በመድረኩ ከአዋኪ ድርጊት ጋር በተያያዘ በተለያዩ መንገዶች ግንዛቤ ተፈጥሯል በተለይም ደግሞ በት/ቤቶች ላይ ለተማሪዎች በቅ/መከላከል ባለሙያዎቻችን አማካኝነት በየጊዜው ግንዛቤ የመፍጠር ተግባር እየተከናወነ እንደሚገኝ ተገልጿል ።
ህብረተሰቡ በአሁኑ ሰዓት ህገ ወጥነትን ለመከላከል እያደረገ ያለውን ስራ በማጠናከርና ተባባሪ በመሆን ሊሰሩ እንደሚገባና ከመሰል አዋኪ ተግባራት ልጆቻቸውና ራሳቸውን በማራቅ ለሌሎች አርዓያ መሆን እንደሚገባቸው በመድረኮቹ ተገልጿል ።
የደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ደንቡና መመሪያውን ተፈፃሚ እንዲሆን እና በሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ተደራሽ በማድረግ ለብልሹ አሰራር እና ፀረ ሙስና ተጋላጭነት መቆጣጠር መቻል ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶት ሊሰራበት የሚገባ ጉዳይ መሆኑ ተገልጿል::
በመድረኩ አዋኪ ድርጊትን በመከላከል ህብረተሰቡም ከደንብ ማስከበር ጋር በመቀናጀት የግንዛቤ ስራዎችን አጠናክረው መስራትና እርምጃ እንዲወሰድ የበኩላቸውን ሚና መወጣት እንዳለባቸው ተነግሯል ።
ወጣቱን ከአዋኪ ድርጊቶችን እና ብልሹ አሰራሮችን እንዴት እራሱን መከላከልና መቆጣጠር እንደሚቻል በሰነዱ በዝርዝር ተገልፃል ።
በመጨረሻም ከተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎች በተሰጡ ሀሳብ አስተያየት ጥያቄዎች ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ ከመድረኩ ለተነሱት ሀሳብና አስተያየት ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል።
መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
❤3
ባለስልጣኑ "18ተኛውን የሠንደቅ ዓላማ ቀን በድምቀት አከበረ።
03/02/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን "ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጲያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ሉአላዊነታችንና ለኢትዮጲያ ሕዳሴ" በሚል መሪ ቃል 18ተኛውን ብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ ቀንን የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች፣ ኦፊሰሮችና መላሙ የተቋሙ ሰራተኞች በተገኙበት አከበረ።
ክብረ-በዓሉ በብሄራዊ ህዝብ መዝሙር የተጀመረ ሲሆን የባለስልጣኑ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ የዘንድሮውን የሰንደቅ ዓላማ ቀን የህዳሴ ግድብ እና ለሎች በርካታ ሜጋ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ወደ ስራ በገቡበት ወቅትና እንዲሁም ተቋማችን ከፍተኛ ውጤት ባስመዘገበበት ማግስት መሆኑ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል።
ኃላፊው አያይዘውም ሰንደቅ ዓላማችን የክብራችንና የሉአላዊነት መገለጫ አርማችን እንደመሆኑ መጠን ይህንን ቀን ስናከብር አባቶቻችን በደም ጠብቀው ያቆዩልንን ሀገር በስኬት የማንሰራራትና የከፍታ ዘመን የምናስቀጥልበትና በቁርጠኝነት የምንሰራበት ሊሆን እንደሚገባ በአፅንኦት ገልጸዋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
03/02/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን "ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጲያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ሉአላዊነታችንና ለኢትዮጲያ ሕዳሴ" በሚል መሪ ቃል 18ተኛውን ብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ ቀንን የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች፣ ኦፊሰሮችና መላሙ የተቋሙ ሰራተኞች በተገኙበት አከበረ።
ክብረ-በዓሉ በብሄራዊ ህዝብ መዝሙር የተጀመረ ሲሆን የባለስልጣኑ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ የዘንድሮውን የሰንደቅ ዓላማ ቀን የህዳሴ ግድብ እና ለሎች በርካታ ሜጋ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ወደ ስራ በገቡበት ወቅትና እንዲሁም ተቋማችን ከፍተኛ ውጤት ባስመዘገበበት ማግስት መሆኑ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል።
ኃላፊው አያይዘውም ሰንደቅ ዓላማችን የክብራችንና የሉአላዊነት መገለጫ አርማችን እንደመሆኑ መጠን ይህንን ቀን ስናከብር አባቶቻችን በደም ጠብቀው ያቆዩልንን ሀገር በስኬት የማንሰራራትና የከፍታ ዘመን የምናስቀጥልበትና በቁርጠኝነት የምንሰራበት ሊሆን እንደሚገባ በአፅንኦት ገልጸዋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
👍3