የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን Addis Ababa Code Enforcement Authority
1.27K subscribers
2.47K photos
5 videos
1 file
57 links
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
Download Telegram
ባለስልጣኑ በመጀመሪያ ሩብ ዓመት እቅድ አፈፃፀሙ ከጠቅላላ ካውንስል ጋር ገመገመ

27- 01 - 2018ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የእቅድ አፈጻጸሙን ከባለሥልጣኑ ዳይሬክተሮች ጋር የግምገማ መድረክ አካሂዷል ።

የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በመክፈቻው እንዳሉት በዚህ ውይይት በሩብ ዓመቱ በተቋማችን የታዩ ጠንካራ ጎኖች እና ክፍተቶችን ለመፈተሽ ያስችለናል ብለዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2018 ዓ.ም በመጀመሪያ ሩብ ዓመት የተከናወኑ ተግባራት ሰነድ በባለስልጣኑ የእቅድና በጀት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኮለኔል አድማሱ ተክሌ ቀርቧል ።

በሰነዱ እንደተገለጸው የተቋም የአቅም ግንባታና አገልግሎት አሰጣጥን ውጤታማ ከማድረግ አንፃር፣የስራ አከባቢን ለሰራተኛውም ሆነ ለተገልጋይ ምቹ ለማድረግ የሚዲያ ሽፍንን በመጠቀም የተቋም ገፅታ በመገንባትና ከተገልጋይ ጋር መድረክ በመፍጠር ግብዓት ለማግኘት መሠራቱን ገልፀዋል።

ኮነሬል አድማሱ ተክሌ ከሪፖርቱ እንደገለፁት በባለስልጣኑ በቦታ 6808 እንዲሁም በካሬ 11,798,292.38 የሚያህል መሬት እየተጠበቁ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
👍81
ባለስልጣኑ በካይ የፍሳሽ ቆሻሻ ወደ ወንዝ የለቀቀን የንግድ ተቋም 300,000/ሦስት መቶ ሺህ/ ብር መቅጣቱን አስታወቀ

28/01/2018 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 4 እየተሰራ ባለው የአፍንጮ በር የወንዝ ዳርቻ ልማት በካይ ቆሻሻ ወደ ወንዝ የለቀቀን የንግድ ተቋም (ጠጅ ቤት) 3 መቶ ሺ ብር መቅጣቱን አስታውቋል።

የተወሰደውን እርምጃ አስመልክቶ የጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 4 ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ሀላፊ ዋና ሳጅን ውባለም ሽፈራው እንደገለፁት ድርጅቱ በተደጋጋሚ ወደ ወንዝ የሚለቀውን በካይ የፍሳሽ ቆሻሻ እንዲያቆም ግንዛቤ ቢፈጠርለትም ከድርጊቱ መቆጠብ ባለመቻሉ ከክፍለ ከተማው የአካባቢ ጥበቃ ፅ/ቤት ጋር በመሆን የቅጣት እርምጃ መወሰዱን ገልፀዋል።

ባለስልጣኑ መሰል ደንብ መተላለፎች ላይ የሚወሰደው እርምጃ አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑ ገልፀው ደንብ ተላላፊዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳስቧል። እየሰሩም እንደሆነ ገልፀዋል።

ባለስልጣኑ የደንብ መተላለፍን መከላከል የሁሉም ማህበረሰብ ድርሻ በመሆኑ ለማንኛውም የደንብ መተላለፍ ጥቆማዎች 9995 ነፃ የስልክ መስመእንዲጠቀሙ ጥሪውን አቅርቧል።

መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባልስልጣን ኮሙኒኬሽ ዳይሬክቶሬት ነው።
👍103
ባለስልጣኑ የመስከረም ወር መደበኛና ወቅታ ተግባራትን ከክፍለ ከተማ አመራሮች ጋር ገመገመ

መስከረም 28/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የመስከረም ወር በእቅድ አፈፀፀምና ወቅታዊ ስራዎች በተመለከ ከክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች ጋር የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ውይይት አደረገ።

በመድረኩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የመስከረም ወር የአደባባይ በዓላት የነበሩበት ቢሆንም ከዚህ ጎን ለጎን በካስኬዲንግ የወረዱትን ተግባራት በጥራት መስራት መቻሉ ጠቁመዋል።

በውይይቱ የመስከረም ወር እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እያንዳንዱ ክፍለ ከተማ ያቀረበ ሲሆን በወሩ የአደባባይ ሁነቶች ላይ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን ፣ በ9ኙ የደንብ ጥሰቶች የመከላከል ፣የመቆጣጠር እና አስተዳደራዊ እርምጃ የመውሰድ ስራዎች መሰራታቸውን ገልፀዋል።

በመድረኩ በድክመትና በጥንካሬ የታዩ ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰዱ እርምጃዎች በሪፖርቱ በዝርዝር ቀርበዋል።

በወሩ የተሰሩ ስራዎች ጠንካራ እንደነበረ የተገለፀ ሲሆን መሬት ባንክ የገቡ መሬቶች ላይ መረጃ በጥንቃቄ መሰራት እንዳለበት እና አስተዳደራዊ ቅጣቶች የቅጣት ደረሰኝ በትክክል መከፈላቸው መረጋገጥ እንደሚገባ የትኩረት አቅጣጫ በማስቀመጥ መድረኩ ተጠናቋል።

ዘገባው፦ የባለስልጣኑ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
6
በእግረኞች መንገድ በተሽከርካሪ በመሄድ ደንብ የተላለፈው ግለሰብ እና ወንዝን የበከለ ድርጅት መቀጣቱ አስታወቀ

29/01/2018 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በንፋስ ስልክ ላፍቶ በልማት ኮሪደር በተሰራው እግረኞች መንገድ ላይ በመኪና በመሄድ ደንብ ተላልፎ የተሰወረን አሽከርካሪ ከአዲስ አበባ ትራፊክ ፖሊስ ጋር በመተባበር በቁጥጥር ስር በማዋል 5ዐ,000( ሀምሳ ሺህ ) ብር መቅጣቱን አስታወቀ ።

በተያያዘ ዜና የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ፅ/ ቤት በወረዳ 5 ልዪ ቦታ ዘነበ ወርቅ አደባባይ ኤስ አይ ኤም የተባለ ግብረ ሰናይ/NGO/ድርጅት ፍሳሽ ቆሻሻ ወደ አስፖልት እና ወንዝ በመልቀቅ 300,000ብር(ሶስት መቶ ሺ) ብር በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዷል።

ህብረተሰቡ በከተማዋ ውስጥ በመንግስትና በህዝብ ሀብት የተገነቡ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ መሠረተ ልማቶችን ደህንነት በመጠበቅ መገልገልና መጠቀም እንደሚገባ አስታውቋል ፡፡

ባለስልጣኑ ህብረተሰቡ ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች መረጃ በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን ያቀርባል።

መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
7👍4