ባለስልጣኑ “ከጂኦስትራቴጂ ኩስመና ወደ ታደሰ ቁመና” በሚል ርዕስ ውይይት አካሄደ።
27/01/2018ዓ.ም
*አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ሀገራችን ስላለችበት እንዲሁም ከህዝቡ ምን ይጠበቃል፤ ያለንበት የጂኦ ስትራቴጂ ሁኔታ ምን ይመስላል በሚል በተዘጋጀው ሰነድ ዙሪያ የተቋሙ አመራሮች እና መላው ሰራተኞች ውይይት አካሂደዋል።
ከጂኦስትራቴጂ ኩስመና ወደ ታደሰ ቁመና የሚለውን ሰነድ ያቀረቡት የባለስልጣኑ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፍሁን አሉላ እንዳሉት ሀገራችን በተግዳሮቶች ውስጥ አልፋ ወሳኝ የሆነ ተጨባጭ ለውጥ አምጥታለች በዚህ ጊዜ አለም ከሉዓላዊነት ወደ አዲስ ጂኦስትራቴጂያዊ የበላይነት ላይ እየሄደች ነው ኢትዮጵያ ደግሞ በጂኦስትራቴጂያዊ ቁመናቸው ከታደሉ ሀገሮች መካከል አንዷ መሆኖን ገልፀዋል።
አክለውም ከቁጭት ኩስመና ወጥተን እንበልፅግ ነገር ግን ይህን ለማድረግ የምናገለግለውን ህዝብ፣ የምንገነባውን ሀገር ፣የምናስከብረውን ብሔራዊ ጥቅም ታሳቢ ያደረገ ፅኑ አቋም መገንባት ያስፈልጋል ብለዋል።
መድረኩን የመሩት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንዳሉት ሀገራችን ከታላላቅ ሀገራት መካከል የምትመደብ ነበረች የአክሱምን እና የላሊበላ አቢያተ ቤተክርስቲያንን እንደ ማሳያ ማየት እንደሚቻል እናወ ቀደመው ገናናነትዋ ለመመለስ ጠንክሮ መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ይህንን ትልቅነታችንን ለመመለስ ኢትዮጲያዊ የሆነ ሰው በሙሉ የብሔር፣የሀይማኖት የባህል እንዲሁም የተለያዮ ልዮነቶች ቢኖረንም በሀገራችን ጉዳይ ግን አንድ ልንሆን ይገባል ሲሉ ዋና ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል።
በመጨረሻም በቀረበው ሰነድ ላይ ሀሳብ አስተያየቶች ተሰተው ወይይት ተደርጎ መድረኩ ተጠናቋል።
ዘገባው:-የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
27/01/2018ዓ.ም
*አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ሀገራችን ስላለችበት እንዲሁም ከህዝቡ ምን ይጠበቃል፤ ያለንበት የጂኦ ስትራቴጂ ሁኔታ ምን ይመስላል በሚል በተዘጋጀው ሰነድ ዙሪያ የተቋሙ አመራሮች እና መላው ሰራተኞች ውይይት አካሂደዋል።
ከጂኦስትራቴጂ ኩስመና ወደ ታደሰ ቁመና የሚለውን ሰነድ ያቀረቡት የባለስልጣኑ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፍሁን አሉላ እንዳሉት ሀገራችን በተግዳሮቶች ውስጥ አልፋ ወሳኝ የሆነ ተጨባጭ ለውጥ አምጥታለች በዚህ ጊዜ አለም ከሉዓላዊነት ወደ አዲስ ጂኦስትራቴጂያዊ የበላይነት ላይ እየሄደች ነው ኢትዮጵያ ደግሞ በጂኦስትራቴጂያዊ ቁመናቸው ከታደሉ ሀገሮች መካከል አንዷ መሆኖን ገልፀዋል።
አክለውም ከቁጭት ኩስመና ወጥተን እንበልፅግ ነገር ግን ይህን ለማድረግ የምናገለግለውን ህዝብ፣ የምንገነባውን ሀገር ፣የምናስከብረውን ብሔራዊ ጥቅም ታሳቢ ያደረገ ፅኑ አቋም መገንባት ያስፈልጋል ብለዋል።
መድረኩን የመሩት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንዳሉት ሀገራችን ከታላላቅ ሀገራት መካከል የምትመደብ ነበረች የአክሱምን እና የላሊበላ አቢያተ ቤተክርስቲያንን እንደ ማሳያ ማየት እንደሚቻል እናወ ቀደመው ገናናነትዋ ለመመለስ ጠንክሮ መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ይህንን ትልቅነታችንን ለመመለስ ኢትዮጲያዊ የሆነ ሰው በሙሉ የብሔር፣የሀይማኖት የባህል እንዲሁም የተለያዮ ልዮነቶች ቢኖረንም በሀገራችን ጉዳይ ግን አንድ ልንሆን ይገባል ሲሉ ዋና ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል።
በመጨረሻም በቀረበው ሰነድ ላይ ሀሳብ አስተያየቶች ተሰተው ወይይት ተደርጎ መድረኩ ተጠናቋል።
ዘገባው:-የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
❤2👍1
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ከህብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት አዋኪ ተግባራት መከላከል እንዳለበት ተገለፀ
27/ዐ1/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት አዋኪ ድርጊቶችን ለመከላከልና በስነምግባር ና ብልሹ አሰራር ዙሪያ ከወረዳ እስከ ክፍለ ከተማ ከተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር የንቅናቄ መድረክ አካሂዷል ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ መዓዛ ተክሉ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የተሰጠውን ተልዕኮ በመወጣት በዘጠኙም የደንብ መተላለፎች ላይ በመስራት በመከላከል በመቆጣጠርና እርምጃ በመውሰድ እንዲሁም ትውልድ ገዳይ የሆነውን አዋኪ ድርጊት በመከላከል ህብረተሰቡ ከደንብ ማስከበር ጋር በመቀናጀት የግንዛቤ ስራዎችን አጠናክረው መስራትና እርምጃ እንዲወሰድ የበኩላቸውን ሚና መወጣት እንዳለባቸው ተናግረዋል ።
አክለውም ኃላፊዋ ወጣቱን ትውልድ እያጠፍ ከአላማው እያስቀረ ያለውን አዋኪ ድርጊት ተግባር በመቆጣጠር ምንም አይነት የደንብ መተላለፍ እንዳይከሰት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸው ለቀጣይም በዘጠኙም የደንብ መተላለፍ ተግባራት ላይ ሰፊ ስራዎችን እንሰራለን ሲሉ ገልፀዋል።
በመድረኩም አዋኪ ድርጊቶችን መከላከል በስነምግባር እና ብልሹ አሰራር መከላከል በሚል የተዘጋጀውን ሰነድ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የስልጠና ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ወንድማገኝ ቁምላቸው ቀርቧል አዋኪ ተግባራት በክፍለ ከተማው ምን እንደሚመስል ፣ አዋኪ ድርጊቶችን እንዴት መፍታት እና መከላከል እንደሚቻል በሰነዱ በዝርዝር ተገልፃል ።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱት ሀሳብና ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽና አስተያየት በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል ።
27/ዐ1/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት አዋኪ ድርጊቶችን ለመከላከልና በስነምግባር ና ብልሹ አሰራር ዙሪያ ከወረዳ እስከ ክፍለ ከተማ ከተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር የንቅናቄ መድረክ አካሂዷል ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ መዓዛ ተክሉ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የተሰጠውን ተልዕኮ በመወጣት በዘጠኙም የደንብ መተላለፎች ላይ በመስራት በመከላከል በመቆጣጠርና እርምጃ በመውሰድ እንዲሁም ትውልድ ገዳይ የሆነውን አዋኪ ድርጊት በመከላከል ህብረተሰቡ ከደንብ ማስከበር ጋር በመቀናጀት የግንዛቤ ስራዎችን አጠናክረው መስራትና እርምጃ እንዲወሰድ የበኩላቸውን ሚና መወጣት እንዳለባቸው ተናግረዋል ።
አክለውም ኃላፊዋ ወጣቱን ትውልድ እያጠፍ ከአላማው እያስቀረ ያለውን አዋኪ ድርጊት ተግባር በመቆጣጠር ምንም አይነት የደንብ መተላለፍ እንዳይከሰት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸው ለቀጣይም በዘጠኙም የደንብ መተላለፍ ተግባራት ላይ ሰፊ ስራዎችን እንሰራለን ሲሉ ገልፀዋል።
በመድረኩም አዋኪ ድርጊቶችን መከላከል በስነምግባር እና ብልሹ አሰራር መከላከል በሚል የተዘጋጀውን ሰነድ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የስልጠና ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ወንድማገኝ ቁምላቸው ቀርቧል አዋኪ ተግባራት በክፍለ ከተማው ምን እንደሚመስል ፣ አዋኪ ድርጊቶችን እንዴት መፍታት እና መከላከል እንደሚቻል በሰነዱ በዝርዝር ተገልፃል ።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱት ሀሳብና ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽና አስተያየት በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል ።
👍2
ባለስልጣኑ በመጀመሪያ ሩብ ዓመት እቅድ አፈፃፀሙ ከጠቅላላ ካውንስል ጋር ገመገመ
27- 01 - 2018ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የእቅድ አፈጻጸሙን ከባለሥልጣኑ ዳይሬክተሮች ጋር የግምገማ መድረክ አካሂዷል ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በመክፈቻው እንዳሉት በዚህ ውይይት በሩብ ዓመቱ በተቋማችን የታዩ ጠንካራ ጎኖች እና ክፍተቶችን ለመፈተሽ ያስችለናል ብለዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2018 ዓ.ም በመጀመሪያ ሩብ ዓመት የተከናወኑ ተግባራት ሰነድ በባለስልጣኑ የእቅድና በጀት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኮለኔል አድማሱ ተክሌ ቀርቧል ።
በሰነዱ እንደተገለጸው የተቋም የአቅም ግንባታና አገልግሎት አሰጣጥን ውጤታማ ከማድረግ አንፃር፣የስራ አከባቢን ለሰራተኛውም ሆነ ለተገልጋይ ምቹ ለማድረግ የሚዲያ ሽፍንን በመጠቀም የተቋም ገፅታ በመገንባትና ከተገልጋይ ጋር መድረክ በመፍጠር ግብዓት ለማግኘት መሠራቱን ገልፀዋል።
ኮነሬል አድማሱ ተክሌ ከሪፖርቱ እንደገለፁት በባለስልጣኑ በቦታ 6808 እንዲሁም በካሬ 11,798,292.38 የሚያህል መሬት እየተጠበቁ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
27- 01 - 2018ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የእቅድ አፈጻጸሙን ከባለሥልጣኑ ዳይሬክተሮች ጋር የግምገማ መድረክ አካሂዷል ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በመክፈቻው እንዳሉት በዚህ ውይይት በሩብ ዓመቱ በተቋማችን የታዩ ጠንካራ ጎኖች እና ክፍተቶችን ለመፈተሽ ያስችለናል ብለዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2018 ዓ.ም በመጀመሪያ ሩብ ዓመት የተከናወኑ ተግባራት ሰነድ በባለስልጣኑ የእቅድና በጀት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኮለኔል አድማሱ ተክሌ ቀርቧል ።
በሰነዱ እንደተገለጸው የተቋም የአቅም ግንባታና አገልግሎት አሰጣጥን ውጤታማ ከማድረግ አንፃር፣የስራ አከባቢን ለሰራተኛውም ሆነ ለተገልጋይ ምቹ ለማድረግ የሚዲያ ሽፍንን በመጠቀም የተቋም ገፅታ በመገንባትና ከተገልጋይ ጋር መድረክ በመፍጠር ግብዓት ለማግኘት መሠራቱን ገልፀዋል።
ኮነሬል አድማሱ ተክሌ ከሪፖርቱ እንደገለፁት በባለስልጣኑ በቦታ 6808 እንዲሁም በካሬ 11,798,292.38 የሚያህል መሬት እየተጠበቁ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
👍8❤1