ባለስልጣኑ የሆራ ፊንፊኔ ማክበሪያ ቦታ ላይ ፅዳት አካሄደ።
20/01/2018ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2018 ሆራ ፊንፊኔ በዓል ማክበሪያ ቦታ የሆነውን የወንዝ ዳርቻ እንዲሁም የኢሬቻ ፓርክ ጊቢ የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች እና ኦፊሰሮች በጋራ በመሆን አፀዱ።
በቦታው ተገኝተን ያነጋገርናቸው የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ መአዛ እንዳሉት ባለስልጣኑ ከከተማ አስተዳደሩ ከተሰጠው ተግባር እና ኃላፊነት በተጨማሪ እንደነዚህ አይነት ተልእኮዎችን ተቀብሎ በሙሉ ተነሳሽነት እንደሚያከናውን ገልፀዋል።
አክለውም በክፍለ ከተማቸው የሚከበረውን ሆራ ፊንፊኔ ሲከበር ከውስጥም ከውጭም ሀገር ለሚመጡ የበዓሉ አክባሪዎች በእንግዳ ተቀባይነት ባህል ማስተናገድ እንዳለብን አስረድተዋል። በዓሉ በሰላም ተጀምሮ በሰላም እንዲጠናቀቅ ሁሉም አካል የራሱን ድርሻ ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ዘገባው:-የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
20/01/2018ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2018 ሆራ ፊንፊኔ በዓል ማክበሪያ ቦታ የሆነውን የወንዝ ዳርቻ እንዲሁም የኢሬቻ ፓርክ ጊቢ የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች እና ኦፊሰሮች በጋራ በመሆን አፀዱ።
በቦታው ተገኝተን ያነጋገርናቸው የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ መአዛ እንዳሉት ባለስልጣኑ ከከተማ አስተዳደሩ ከተሰጠው ተግባር እና ኃላፊነት በተጨማሪ እንደነዚህ አይነት ተልእኮዎችን ተቀብሎ በሙሉ ተነሳሽነት እንደሚያከናውን ገልፀዋል።
አክለውም በክፍለ ከተማቸው የሚከበረውን ሆራ ፊንፊኔ ሲከበር ከውስጥም ከውጭም ሀገር ለሚመጡ የበዓሉ አክባሪዎች በእንግዳ ተቀባይነት ባህል ማስተናገድ እንዳለብን አስረድተዋል። በዓሉ በሰላም ተጀምሮ በሰላም እንዲጠናቀቅ ሁሉም አካል የራሱን ድርሻ ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ዘገባው:-የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
👍6❤4
ባለስልጣኑ እሬቻ በዓል በሰላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን የቅድመ ዝግጅት በማጠናቀቅ ወደስራ መግባቱ አስታወቀ
22/ዐ1/2018 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የእሬቻ በዓል በሰላም እንዲከበርና እንግዶች ለመቀበል እና በዓሉን ለማክበር የቅድመ ዝግጅት አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን አስታወቀ።
ለበዓሉ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት እየተከናወነ መሆኑን በዓሉ በሚከበርበት ቦታ የጸጥታ ችግር እንዳይፈጠር የተቋሙ አመራሮችና ኦፊሰሮች የተሰጣቸውን ኃላፊነትና ስምሪት በቁርጠኝነት ለመወጣት ዝግጁ በማድረግ ለእንግዶች ምቹነትና ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር አስፈላጊ አገልግሎቶች ለመስጠት መዘጋጀቱ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ገልፀዋል።
ባለስልጣኑ ህብረተሰቡ ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች መረጃ በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን ያቀርባል።
መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
22/ዐ1/2018 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የእሬቻ በዓል በሰላም እንዲከበርና እንግዶች ለመቀበል እና በዓሉን ለማክበር የቅድመ ዝግጅት አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን አስታወቀ።
ለበዓሉ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት እየተከናወነ መሆኑን በዓሉ በሚከበርበት ቦታ የጸጥታ ችግር እንዳይፈጠር የተቋሙ አመራሮችና ኦፊሰሮች የተሰጣቸውን ኃላፊነትና ስምሪት በቁርጠኝነት ለመወጣት ዝግጁ በማድረግ ለእንግዶች ምቹነትና ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር አስፈላጊ አገልግሎቶች ለመስጠት መዘጋጀቱ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ገልፀዋል።
ባለስልጣኑ ህብረተሰቡ ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች መረጃ በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን ያቀርባል።
መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
👍9👏3