ለባለስልጣኑ አመራር እና ኦፊሰሮች በኢትዮጵያ ፓሊስ ዩኒቨርስቲ ስልጠና ለመስጠት የቅድመ ዝግጅት ውይይት ተካሄደ
15/12/ 2017 ዓ.ም
ሰንዳፋ
በአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ምክትል ስራ-አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸዉ የተመራው የልዑካን ቡድን በቀጣይ ለባለስልጣኑ አመራሮች እና ነባር የፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ስልጠና ለመስጠት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ውይይት ተካሄደ፡፡
የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸዉ በዉይይቱ ላይ በቀጣይ ለአመራሩ እና ለነባር ኦፊሰሩ የሚሰጠው ስልጠና በስነ_ ምግባር ፣ በህግ ፣ ከኮምንኬሽንና ተግባቦት ዙሪያ ልማቶችን ደህንነት በመጠበቅና የወንዝ ዳር ብክለትን በመከለከልና በመቆጣጠር ሂደት አዲስ አበባን ከተማ ያማከለ ስልጠና እንደሚሆን ገልፀዋል።
በፓሊስ ዩኒቨርሲቲው ለሰልጣኝ አመራሮቹና ነባር ኦፊሰሮቹ የሚሰጠዉ ስልጠና ለስራቸው አጋዥ ብሎም አበረታች እንደሚሆን በማንሳት የአቅም ግንባታ ስልጠናዎቹ ለአመራሮቹ እና ፈጻሚ አካላት የመፈጸም አቅማቸውን ይበልጥ ለማጎልበት እንደሚረዳ እንዲሁም በቀጣይ ለሚሰጡ ተልእኮዎች ዝግጁ እንደሚያደርጋቸዉ በውይይቱ ላይ ሀሳባቸውን ገልጸዋል፡፡
በውይይቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የስልጠና ምክትል ፕሬዝዳት ረዳት ኮሚሽነር ደረጄ ተስፋዬ ለአባላቱ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ፖሊስ ዩኒቨርሲቲው ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ጋር አብሮ የመስራት ልምዱን ከበፊቱ ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
አክለውም የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ሰልጣኞች በስልጠና ቆይታቸው ስራቸዉን በአግባቡ እንዲያከናውኑ የሚችሉበትን በቂ ዕውቀት የሚያገኙበት ስልጠና ልምድና እውቀቱ ባላቸው አሰልጣኞች እንደሚያዘጋጁ ገልፀዋል፡፡
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የአመራር ስልጠና አቅም ግንባታ ማዕከል መምሪያ ኃላፊ የሆኑት ኮማንደር ፍቃዱ ጌታቸው በውይይቱ ወቅት ከራሱ በላይ ህዝብን ጥቅም የሚያስቀድም ከህዝቡ በፊት እሞታለሁ ብሎ ተጨንቆ ለሀገሩና ለህዝቡ የሚሰራ ሰራተኛ ለመፍጠር እንሰራለን ብለዋል ።
በዉይይቱ የባለስልጣኑ የስልጠና ዳይሬክቶሬት የሆኑት ወ/ሮ ላቀች ሀይሌ በስልጠና አሰጣጥ እና በሚሰጡ የስልጠና ሰነዶች ርዕሶች ዙሪያ ገለፃ አድርገዋል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
15/12/ 2017 ዓ.ም
ሰንዳፋ
በአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ምክትል ስራ-አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸዉ የተመራው የልዑካን ቡድን በቀጣይ ለባለስልጣኑ አመራሮች እና ነባር የፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ስልጠና ለመስጠት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ውይይት ተካሄደ፡፡
የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸዉ በዉይይቱ ላይ በቀጣይ ለአመራሩ እና ለነባር ኦፊሰሩ የሚሰጠው ስልጠና በስነ_ ምግባር ፣ በህግ ፣ ከኮምንኬሽንና ተግባቦት ዙሪያ ልማቶችን ደህንነት በመጠበቅና የወንዝ ዳር ብክለትን በመከለከልና በመቆጣጠር ሂደት አዲስ አበባን ከተማ ያማከለ ስልጠና እንደሚሆን ገልፀዋል።
በፓሊስ ዩኒቨርሲቲው ለሰልጣኝ አመራሮቹና ነባር ኦፊሰሮቹ የሚሰጠዉ ስልጠና ለስራቸው አጋዥ ብሎም አበረታች እንደሚሆን በማንሳት የአቅም ግንባታ ስልጠናዎቹ ለአመራሮቹ እና ፈጻሚ አካላት የመፈጸም አቅማቸውን ይበልጥ ለማጎልበት እንደሚረዳ እንዲሁም በቀጣይ ለሚሰጡ ተልእኮዎች ዝግጁ እንደሚያደርጋቸዉ በውይይቱ ላይ ሀሳባቸውን ገልጸዋል፡፡
በውይይቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የስልጠና ምክትል ፕሬዝዳት ረዳት ኮሚሽነር ደረጄ ተስፋዬ ለአባላቱ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ፖሊስ ዩኒቨርሲቲው ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ጋር አብሮ የመስራት ልምዱን ከበፊቱ ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
አክለውም የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ሰልጣኞች በስልጠና ቆይታቸው ስራቸዉን በአግባቡ እንዲያከናውኑ የሚችሉበትን በቂ ዕውቀት የሚያገኙበት ስልጠና ልምድና እውቀቱ ባላቸው አሰልጣኞች እንደሚያዘጋጁ ገልፀዋል፡፡
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የአመራር ስልጠና አቅም ግንባታ ማዕከል መምሪያ ኃላፊ የሆኑት ኮማንደር ፍቃዱ ጌታቸው በውይይቱ ወቅት ከራሱ በላይ ህዝብን ጥቅም የሚያስቀድም ከህዝቡ በፊት እሞታለሁ ብሎ ተጨንቆ ለሀገሩና ለህዝቡ የሚሰራ ሰራተኛ ለመፍጠር እንሰራለን ብለዋል ።
በዉይይቱ የባለስልጣኑ የስልጠና ዳይሬክቶሬት የሆኑት ወ/ሮ ላቀች ሀይሌ በስልጠና አሰጣጥ እና በሚሰጡ የስልጠና ሰነዶች ርዕሶች ዙሪያ ገለፃ አድርገዋል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
❤11👍3