በቁማር ቤቶች ላይ የተወሰደው እርምጃ በትምህርት ቤቶች አካባቢ እና ከህግ ውጪ ሲሰሩ የነበሩ መሆኑን ተገለፀ።
ታህሰስ 11/2016 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ጉዳዩን አስመልክቶ ከኢቢኤስ ቴሌቪዥን ጋር ቆይታ አድርገዋል።
በቆይታቸው በቁማር ቤቶች ላይ የተወሰደው እርምጃ በትምህርት ቤቶች አቅራቢያ ከ200 ሜትር ራዲየስ በታች የቤትንግ ስፖርት ውርርድ በማጫወት እና በውርርድ ቤት ውስጥ ከተፈቀደው ውጪ ቁማር በማጫወት፣ ጫት በማስቃም፣ ሺሻ በማስጨስ እና አልኮል የሚሸጡ መሆኑን ከህብረተሰቡ ከደረሰ ጥቆማ እና በጥናት መረጋገጡ ገልጸዋል።
ዋና ስራ አስኪያጁ አክለውም ከ21 ዓመት በታች የሆኑ ተማሪዎችና ታዳጊዎችን በማወራረድ ተማሪዎች ትምህርታቸው ከማስተጓጎል በተጨማሪ በሌብነት ውስጥ እንዲገቡ ማድረጉ ከህብረተሰቡ በተደረገው ውይይት መነሳቱ ገልፀዋል።
የደንብ መተላለፎችን በተደጋጋሚ ሲፈጽሙ የተደረሰባቸው ከ3240 በላይ የቤቲንግ እስፖርት አወራራጅ ድርጅቶች የማወራረጃ ቤታቸው የማሸግ እርምጃ የተወሰደ መሆኑን እና ደንብ የማስከበር ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።
በመግለጫቸው በትምህርት ቤቶች አቅራቢያ ከ200 ሜትር ራዲየስ በታች የቤትንግ ስፖርት ውርርድ በማጫወት የተሰማሩ ግለሰቦች የንግድ ዘርፋቸውን በመቀየር በህጋዊ መንገድ የንግድ ስራቸውን እንዲያከናውኑ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመጨረሻም ዋና ስራ አስኪያጁ ህብረተሰቡ መረጃ በመስጠት ላደረገው ከፍተኛ አስተዋፅኦ ምስጋና አቅርበዋል።
ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች ጥቆማ ነፃ የስልክ መስመር 9995 ይጠቀሙ።
ዘገባው :-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ታህሰስ 11/2016 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ጉዳዩን አስመልክቶ ከኢቢኤስ ቴሌቪዥን ጋር ቆይታ አድርገዋል።
በቆይታቸው በቁማር ቤቶች ላይ የተወሰደው እርምጃ በትምህርት ቤቶች አቅራቢያ ከ200 ሜትር ራዲየስ በታች የቤትንግ ስፖርት ውርርድ በማጫወት እና በውርርድ ቤት ውስጥ ከተፈቀደው ውጪ ቁማር በማጫወት፣ ጫት በማስቃም፣ ሺሻ በማስጨስ እና አልኮል የሚሸጡ መሆኑን ከህብረተሰቡ ከደረሰ ጥቆማ እና በጥናት መረጋገጡ ገልጸዋል።
ዋና ስራ አስኪያጁ አክለውም ከ21 ዓመት በታች የሆኑ ተማሪዎችና ታዳጊዎችን በማወራረድ ተማሪዎች ትምህርታቸው ከማስተጓጎል በተጨማሪ በሌብነት ውስጥ እንዲገቡ ማድረጉ ከህብረተሰቡ በተደረገው ውይይት መነሳቱ ገልፀዋል።
የደንብ መተላለፎችን በተደጋጋሚ ሲፈጽሙ የተደረሰባቸው ከ3240 በላይ የቤቲንግ እስፖርት አወራራጅ ድርጅቶች የማወራረጃ ቤታቸው የማሸግ እርምጃ የተወሰደ መሆኑን እና ደንብ የማስከበር ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።
በመግለጫቸው በትምህርት ቤቶች አቅራቢያ ከ200 ሜትር ራዲየስ በታች የቤትንግ ስፖርት ውርርድ በማጫወት የተሰማሩ ግለሰቦች የንግድ ዘርፋቸውን በመቀየር በህጋዊ መንገድ የንግድ ስራቸውን እንዲያከናውኑ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመጨረሻም ዋና ስራ አስኪያጁ ህብረተሰቡ መረጃ በመስጠት ላደረገው ከፍተኛ አስተዋፅኦ ምስጋና አቅርበዋል።
ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች ጥቆማ ነፃ የስልክ መስመር 9995 ይጠቀሙ።
ዘገባው :-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
በአዲሱ ደንብ ቁጥር 150/2015 ላይ ለደንብ ማስከበር በጎ ፍቃደኞች ግንዛቤ ተፈጠረ።
ታህሳስ 12ቀ/2016 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከሁሉም ክፍለ ከተማ ለተውጣጡ በጎ ፍቃደኞች በአዲሱ ደንብ ቁጥር 150/2015 ላይ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ አዳራሽ ግንዛቤ ሰጠ።
የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅና የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ አበባ እሸቴ በመድረኩ መክፈቻ ንግግራቸው ለከተማዋ የደንብ መከበር ከፍተኛ አስተዋፅዖ እያበረከታችሁ ያላችሁ የተከበራችሁ የበጎ ፍቃደኞች ተወካዮቻችን እንኳን ደህና መጣችሁ ብለዋል።
ባለስልጣኑ ባለፉሁት ዓመታት ደንብ ቁጥር 54/2005 ሲያስፈፅም መቆየቱን አስታውሰው፤ አሁን ላይ የከተማዋን እድገት ተከትሎ የሚፈፀመው የደንብ መተላለፍ በመወሳሰቡ ምክንያት ጥናት በማድረግ ደንቡን ማሻሻል አስፈላጊ መሆኑን አስረድተዋል።
በዛሬው መድረክም ከተቋሙ ጋር አጋር በመሆን ከፍተኛ ሀገራዊ ድርሻችሁን ለምትወጡ በጎ ፍቃደኞቻችን አዲሱን ደንብ 150/2015 በዝርዝር በማስጨበጥ በቀጣይም በላቀ መልኩ የደንብ መተላለፍን በጋራ ለመከላከል እንድንተጋ አደራ እያልኩኝ፤ የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፉ በህዝብ ንቅናቄ መድረክ፣ ቤት ለቤትና ቡና በጠጡ እንዲሁም በትምህር ቤትና በሞንታርቦ የሚሰጠውን ግንዛቤ አጠናክሮ በማስቀጠል የደንብ መተላለፍና ህገ-ወጥ ተግባራትን ይከላከል ብለዋል።
አዲሱን ደንብ ቁጥር 150/2015 ሰነዱን የግንዛቤ ማስጨበጥ ባለሙያ ወ/ት አስናቁ አየሁ በዝርዝር አቅርበዋል።
ተሳታፊ በጎ ፈቃደኞችም ደንቡ የሚያሰራና ለሁሉም ህብረተሰብ ማስጨበጥ እንደሚገባ ጠቁመው፤ ከፅዳትና ተያያዥ ጉዳዮች ጋርም እንደ በጎ ፍቃደኛ በተጨባጭ ለውጥ ያመጣ መሆኑን ተናግረዋል።
በጎ-ፈቃደኞቹ ከሽንት ጋር በተያያዘ ቅጣቱ እንዳለ ሆኖ የሚመለከተው አካል የህዝብ መፀዳጃ ቤትን ማስፋት ላይ መስራት እንደሚገባ፤በትምህርት ቤቶች አከባቢ የሚሰጡ የንግድ ፍቃድ ላይ በምንሰጠው ጥቆማ መሠረት በአስቸኳይ እርምት ሊወሰድ እንደሚገባ ተናግረዋል።
ምክትል ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ አበባ እሸቴም ተቋሙ ያለ ህብረተሰቡ እና በጎ ፍቃኞች ተሳትፎ በከተማዋ የሚስተዋለውን የደንብ መተላለፍ መከላከል አይቻልምና በቀጣም በተጠናከረ መልኩ ለመስራት እኛም የምትጠቁሙን እና የምትሰጡንን አስተያየት ተቀብለን በጋራ የደንብ መተላለፍና ህገ ወጥ እንቅስቃሴ እንከላከላለን ብለዋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ታህሳስ 12ቀ/2016 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከሁሉም ክፍለ ከተማ ለተውጣጡ በጎ ፍቃደኞች በአዲሱ ደንብ ቁጥር 150/2015 ላይ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ አዳራሽ ግንዛቤ ሰጠ።
የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅና የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ አበባ እሸቴ በመድረኩ መክፈቻ ንግግራቸው ለከተማዋ የደንብ መከበር ከፍተኛ አስተዋፅዖ እያበረከታችሁ ያላችሁ የተከበራችሁ የበጎ ፍቃደኞች ተወካዮቻችን እንኳን ደህና መጣችሁ ብለዋል።
ባለስልጣኑ ባለፉሁት ዓመታት ደንብ ቁጥር 54/2005 ሲያስፈፅም መቆየቱን አስታውሰው፤ አሁን ላይ የከተማዋን እድገት ተከትሎ የሚፈፀመው የደንብ መተላለፍ በመወሳሰቡ ምክንያት ጥናት በማድረግ ደንቡን ማሻሻል አስፈላጊ መሆኑን አስረድተዋል።
በዛሬው መድረክም ከተቋሙ ጋር አጋር በመሆን ከፍተኛ ሀገራዊ ድርሻችሁን ለምትወጡ በጎ ፍቃደኞቻችን አዲሱን ደንብ 150/2015 በዝርዝር በማስጨበጥ በቀጣይም በላቀ መልኩ የደንብ መተላለፍን በጋራ ለመከላከል እንድንተጋ አደራ እያልኩኝ፤ የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፉ በህዝብ ንቅናቄ መድረክ፣ ቤት ለቤትና ቡና በጠጡ እንዲሁም በትምህር ቤትና በሞንታርቦ የሚሰጠውን ግንዛቤ አጠናክሮ በማስቀጠል የደንብ መተላለፍና ህገ-ወጥ ተግባራትን ይከላከል ብለዋል።
አዲሱን ደንብ ቁጥር 150/2015 ሰነዱን የግንዛቤ ማስጨበጥ ባለሙያ ወ/ት አስናቁ አየሁ በዝርዝር አቅርበዋል።
ተሳታፊ በጎ ፈቃደኞችም ደንቡ የሚያሰራና ለሁሉም ህብረተሰብ ማስጨበጥ እንደሚገባ ጠቁመው፤ ከፅዳትና ተያያዥ ጉዳዮች ጋርም እንደ በጎ ፍቃደኛ በተጨባጭ ለውጥ ያመጣ መሆኑን ተናግረዋል።
በጎ-ፈቃደኞቹ ከሽንት ጋር በተያያዘ ቅጣቱ እንዳለ ሆኖ የሚመለከተው አካል የህዝብ መፀዳጃ ቤትን ማስፋት ላይ መስራት እንደሚገባ፤በትምህርት ቤቶች አከባቢ የሚሰጡ የንግድ ፍቃድ ላይ በምንሰጠው ጥቆማ መሠረት በአስቸኳይ እርምት ሊወሰድ እንደሚገባ ተናግረዋል።
ምክትል ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ አበባ እሸቴም ተቋሙ ያለ ህብረተሰቡ እና በጎ ፍቃኞች ተሳትፎ በከተማዋ የሚስተዋለውን የደንብ መተላለፍ መከላከል አይቻልምና በቀጣም በተጠናከረ መልኩ ለመስራት እኛም የምትጠቁሙን እና የምትሰጡንን አስተያየት ተቀብለን በጋራ የደንብ መተላለፍና ህገ ወጥ እንቅስቃሴ እንከላከላለን ብለዋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ባለስልጣኑ በማህበራዊ ሚድያ አጠቃቀም ዙሪያ ለተቋሙ ሰራተኞች ስልጠና ሰጠ።
ታህሰስ 12/2016 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት የማህበራዊ ሚድያ አጠቃቀምን በተመለከተ ለተቋሙ የማዕከል ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ ስልጠናው ማህበራዊ ሚድያን ተገቢ በሆነ መንገድ እንድንጠቀምና የተሻለ የመግባባት ክህሎት እንድናዳብር አቅም እንደሚፈጥር ተናግረዋል ።
አክለውም በዚህ ዘመን ማህበራዊ ሚድያ ያለው አቅም ከፍተኛ እንደመሆኑ በአግባቡ የማንጠቀም ከሆነ ማህበራዊ ፣ኢኮኖሚያዊ፣ፖለቲካዊ እና ስነልቦናዊ ጉዳት እንደሚያስከትል በመገንዘብ የምንጠቀማቸውን ማህበራዊ ሚድያዎች በጥንቃቄ ልንጠቀምባቸው እንደሚገባ ገልፀዋል ።
በማህበራዊ ሚድያ አጠቃቀም እና በአግባቡ ካልተጠቀምን የሚያመጣው ተጽዕኖ ዙሪያ የተዘጋጀውን ስልጠና የባለስልጣኑ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሲኒየር ባለሙያ በሆኑት በአቶ ሚሊዮን ካሳሁን የተሰጠ ሲሆን የማህበራዊ ሚዲያ ምንነት፣ አይነቶች ፣ የማህበራዊ ሚዲያ መቼ እና ለምን አላማ መጠቀም አንደሚገባ እንዲሁም ኃሰተኛ መረጃዎችን አንዴት በቀላሉ ማወቅ እንደሚቻል በዝርዝር አስረድተዋል ።
የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ አበባ እሸቴ በስልጠናው ማጠቃለያ ንግግራቸው አንደተናገሩት በተለያዩ የአለም ክፋሎች በዚህ ሰዓት ብዙ ቴክኖሎጂ አየተጠቀሙ መሆኑ በመግለፅ የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀሙን በመገንዘብ ለመልካም ነገሮች ስንጠቀም ለሰው ልጆች ያለው ጠቀሜታ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል ።
በተጨማሪም የተቋሙ ሰራተኞች የባለስልጣኑ የሶሻል ሚዲያ ገጾች አባል እና ተከታይ በመሆን በተቋሙ በሚሰሩ ስራዎች ሀሳብና አስተያየት መስጠት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
በመጨረሻም ከስልጠና ተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች በባለሙያው ምላሽና አስተያየት በመስጠት ስልጠናው ተጠናቋል ።
ዘገባው ፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
ታህሰስ 12/2016 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት የማህበራዊ ሚድያ አጠቃቀምን በተመለከተ ለተቋሙ የማዕከል ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ ስልጠናው ማህበራዊ ሚድያን ተገቢ በሆነ መንገድ እንድንጠቀምና የተሻለ የመግባባት ክህሎት እንድናዳብር አቅም እንደሚፈጥር ተናግረዋል ።
አክለውም በዚህ ዘመን ማህበራዊ ሚድያ ያለው አቅም ከፍተኛ እንደመሆኑ በአግባቡ የማንጠቀም ከሆነ ማህበራዊ ፣ኢኮኖሚያዊ፣ፖለቲካዊ እና ስነልቦናዊ ጉዳት እንደሚያስከትል በመገንዘብ የምንጠቀማቸውን ማህበራዊ ሚድያዎች በጥንቃቄ ልንጠቀምባቸው እንደሚገባ ገልፀዋል ።
በማህበራዊ ሚድያ አጠቃቀም እና በአግባቡ ካልተጠቀምን የሚያመጣው ተጽዕኖ ዙሪያ የተዘጋጀውን ስልጠና የባለስልጣኑ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሲኒየር ባለሙያ በሆኑት በአቶ ሚሊዮን ካሳሁን የተሰጠ ሲሆን የማህበራዊ ሚዲያ ምንነት፣ አይነቶች ፣ የማህበራዊ ሚዲያ መቼ እና ለምን አላማ መጠቀም አንደሚገባ እንዲሁም ኃሰተኛ መረጃዎችን አንዴት በቀላሉ ማወቅ እንደሚቻል በዝርዝር አስረድተዋል ።
የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ አበባ እሸቴ በስልጠናው ማጠቃለያ ንግግራቸው አንደተናገሩት በተለያዩ የአለም ክፋሎች በዚህ ሰዓት ብዙ ቴክኖሎጂ አየተጠቀሙ መሆኑ በመግለፅ የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀሙን በመገንዘብ ለመልካም ነገሮች ስንጠቀም ለሰው ልጆች ያለው ጠቀሜታ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል ።
በተጨማሪም የተቋሙ ሰራተኞች የባለስልጣኑ የሶሻል ሚዲያ ገጾች አባል እና ተከታይ በመሆን በተቋሙ በሚሰሩ ስራዎች ሀሳብና አስተያየት መስጠት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
በመጨረሻም ከስልጠና ተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች በባለሙያው ምላሽና አስተያየት በመስጠት ስልጠናው ተጠናቋል ።
ዘገባው ፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ዛሬ የገበታ ለሀገር ፕሮጀክት አካል የሆነውን የጨበራ ዝሆን ዳና ሎጅን መርቀው ከፍተዋል።
በዚሁ ጊዜ የተገኘው እውቁ ዓለም አቀፍ ሼፍ ማርከስ ሳሙኤልሰን፤ የተሰራው ሎጅና በአካባቢው ያለው የተፈጥሮ ኃብት እጅግ የሚደንቅ መሆኑን ተናግሯል።
በአካባቢው ያለው መልክዓ-ምደር፣ የእንስሳት ኃብት እንዲሁም ሌሎች የሕዝቡ ባህል ለሀገሪቱ የቱሪዝም ዘርፍ እድገት ትልቅ ኃብት እንደሚሆን ነው የገለጸው።
ኢትዮጵያ ውስጥ ለቱሪስት መዳረሻነት የሚውሉ በርካታ ሥፍራዎች መኖራቸውን ገልጾ እነዚህን ሥፍራዎች ይበልጥ አልምቶ መጠቀም እንደሚገባ ጠቁሟል።
የኢትዮጵያ የዳያስፖራ አባላት በውጭ ሀገራት ኢትዮጵያን ለተቀረው ዓለም በማስተዋወቅ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽዖ ማድረጋቸውን ጠቁሟል።
አሁን ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ያቀረቡትን ጥሪ ተከትሎ የዳያስፖራው አባላት ወደ ሀገራቸው በመምጣት ያላቸውን ልምድና ክህሎት ማካፈል አለባቸው ብሏል።
የሼፍ ማርከስ ሳሙኤልሰን ባለቤት ማያ ኃይሌ በበኩሏ፤ የጨበራ ዝሆን ዳና ሎጅ የሚገኝበት ሥፍራና እንዲሁም የተሰራው ሎጅ ሳቢ መሆኑን ገልጻለች።
የዳያስፖራው አባላት አሁን ላይ ወደ አገራቸው መጥተው ለሀገራቸው እድገት የበኩላቸውን መወጣት አለባቸው ማለቷን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
መረጃው:- የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ነው።
በዚሁ ጊዜ የተገኘው እውቁ ዓለም አቀፍ ሼፍ ማርከስ ሳሙኤልሰን፤ የተሰራው ሎጅና በአካባቢው ያለው የተፈጥሮ ኃብት እጅግ የሚደንቅ መሆኑን ተናግሯል።
በአካባቢው ያለው መልክዓ-ምደር፣ የእንስሳት ኃብት እንዲሁም ሌሎች የሕዝቡ ባህል ለሀገሪቱ የቱሪዝም ዘርፍ እድገት ትልቅ ኃብት እንደሚሆን ነው የገለጸው።
ኢትዮጵያ ውስጥ ለቱሪስት መዳረሻነት የሚውሉ በርካታ ሥፍራዎች መኖራቸውን ገልጾ እነዚህን ሥፍራዎች ይበልጥ አልምቶ መጠቀም እንደሚገባ ጠቁሟል።
የኢትዮጵያ የዳያስፖራ አባላት በውጭ ሀገራት ኢትዮጵያን ለተቀረው ዓለም በማስተዋወቅ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽዖ ማድረጋቸውን ጠቁሟል።
አሁን ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ያቀረቡትን ጥሪ ተከትሎ የዳያስፖራው አባላት ወደ ሀገራቸው በመምጣት ያላቸውን ልምድና ክህሎት ማካፈል አለባቸው ብሏል።
የሼፍ ማርከስ ሳሙኤልሰን ባለቤት ማያ ኃይሌ በበኩሏ፤ የጨበራ ዝሆን ዳና ሎጅ የሚገኝበት ሥፍራና እንዲሁም የተሰራው ሎጅ ሳቢ መሆኑን ገልጻለች።
የዳያስፖራው አባላት አሁን ላይ ወደ አገራቸው መጥተው ለሀገራቸው እድገት የበኩላቸውን መወጣት አለባቸው ማለቷን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
መረጃው:- የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ታህሳስ 12//04/2016 ዓ.ም ሊሰጥ ለነበረው የቴክኒክና ባህሪ ብቃት ፈተና ለመፈተን በስፍራው ለተገኛችሁ እና የከተማ አስተዳደሩን አቅጣጫ በፍፁም ኢትዮጵያዊ ጨዋነት በመቀበል ውሳኔውን ላከበራችሁ ሰራተኞች በሙሉ የላቀ ምስጋናውን እያቀረበ ለተፈጠረው ችግር ይቅርታ ጠይቋል።
በቀጣይም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተዘጋጀው ፈተና ቅዳሜ ታህሳስ 20/04/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ የሚሰጥ መሆኑንም ቢሮው አስታውቋል።
የከተማ አስተዳደሩ የቴክኒክና ባህሪ ብቃት ፈተና ለአመራሮች ፣ ለባለሙያዎች እና ለሰራተኞች ፈተና እንዲሰጡ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ለኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ኃላፊነት በመስጠት ባሳለፍነው ሳምንት አርብ ቀን ማለትም በ 12/04/2016 ዓ.ም ፈተና ለመፈተን ሙሉ ዝግጅቱን ቢያጠናቅቅም ፈተናው የ አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ባጋጠመው ቴክኒካል ችግር ምከንያት ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙ አይዘነጋም።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን በእለቱ ከረፋዱ 5:00-11:30 በፍጹም ኢትዮጵያዊ ጨዋነት እና በትእግስት የፈተናውን መሰጠት ስትጠባበቁ ለነበራችሁ የ ከተማ አስተዳደሩ ሰራተኞች በሙሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ የላቀ ምስጋናውን እያቀረበ ነገር ግን በእለቱ በሰራተኛው ላይ ለደረሰው መጉላላት እና እንግልት ሁሉ ይቅርታ ጠይቋል።
በተያያዘም ተፈታኞች በተረጋገጠ ሰላም አና በተረጋጋ ስሜት ፈተናውን እንዲወስዱ የተለመደ ኢትዮጵያዊ ጨዋነትን ላሳየው እና የሰላም አርበኛ ለሆነው የመንግስት ሰራተኛ በሙሉ ቢሮው ምስጋናን አቅርቧል።
በተጨማሪም የከተማ አስተዳደሩን አቅጣጫ በመቀበል የትራንስፖርት አቅርቦት በማመቻቸት፣የትራንስፖርት ፍሰቱን በማሳለጥ እና ሰላም እና ፀጥታን በማስጠበቅ ሙሉ ድጋፍ ላደረጋቸው ባለድርሻ አካላት በሙሉ ቢሮ ከፍ ያለ ምስጋናውን አቅርቧል።
በቀጣይም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተዘጋጀው ፈተና ቅዳሜ ታህሳስ 20/04/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ የሚሰጥ መሆኑን እያስታወቀ ተፈታኞች ከዚህ ቀደም በ ኦረንቴሽን ወቅት የተቀመጡ መስፈርቶችን በሙሉ አሟልተው ለፈተና እንዲገኙ ቢሮው ጥሪ አቅርቧል።
በተመሳሳይም የተዘጋጀው ፈተና በቴክኒክ ችግር ምክንያት በመሰረዙ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ይቅርታ መጠየቁም አይዘነጋም።
መረጃው:-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ነው።
በቀጣይም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተዘጋጀው ፈተና ቅዳሜ ታህሳስ 20/04/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ የሚሰጥ መሆኑንም ቢሮው አስታውቋል።
የከተማ አስተዳደሩ የቴክኒክና ባህሪ ብቃት ፈተና ለአመራሮች ፣ ለባለሙያዎች እና ለሰራተኞች ፈተና እንዲሰጡ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ለኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ኃላፊነት በመስጠት ባሳለፍነው ሳምንት አርብ ቀን ማለትም በ 12/04/2016 ዓ.ም ፈተና ለመፈተን ሙሉ ዝግጅቱን ቢያጠናቅቅም ፈተናው የ አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ባጋጠመው ቴክኒካል ችግር ምከንያት ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙ አይዘነጋም።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን በእለቱ ከረፋዱ 5:00-11:30 በፍጹም ኢትዮጵያዊ ጨዋነት እና በትእግስት የፈተናውን መሰጠት ስትጠባበቁ ለነበራችሁ የ ከተማ አስተዳደሩ ሰራተኞች በሙሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ የላቀ ምስጋናውን እያቀረበ ነገር ግን በእለቱ በሰራተኛው ላይ ለደረሰው መጉላላት እና እንግልት ሁሉ ይቅርታ ጠይቋል።
በተያያዘም ተፈታኞች በተረጋገጠ ሰላም አና በተረጋጋ ስሜት ፈተናውን እንዲወስዱ የተለመደ ኢትዮጵያዊ ጨዋነትን ላሳየው እና የሰላም አርበኛ ለሆነው የመንግስት ሰራተኛ በሙሉ ቢሮው ምስጋናን አቅርቧል።
በተጨማሪም የከተማ አስተዳደሩን አቅጣጫ በመቀበል የትራንስፖርት አቅርቦት በማመቻቸት፣የትራንስፖርት ፍሰቱን በማሳለጥ እና ሰላም እና ፀጥታን በማስጠበቅ ሙሉ ድጋፍ ላደረጋቸው ባለድርሻ አካላት በሙሉ ቢሮ ከፍ ያለ ምስጋናውን አቅርቧል።
በቀጣይም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተዘጋጀው ፈተና ቅዳሜ ታህሳስ 20/04/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ የሚሰጥ መሆኑን እያስታወቀ ተፈታኞች ከዚህ ቀደም በ ኦረንቴሽን ወቅት የተቀመጡ መስፈርቶችን በሙሉ አሟልተው ለፈተና እንዲገኙ ቢሮው ጥሪ አቅርቧል።
በተመሳሳይም የተዘጋጀው ፈተና በቴክኒክ ችግር ምክንያት በመሰረዙ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ይቅርታ መጠየቁም አይዘነጋም።
መረጃው:-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ነው።
ለአራት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የነበረው ስልጠና በዛሬው እለት ተጠናቀቀ።
**አዲስ አበባ**
16/04/2016 ዓ.ም
"ከእዳ ወደ ምንዳ" በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ ከተማ የፕብሊክ ሰርቪስ እና የፍትህ ልዩ ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ አባላት ለተካታተይ አራት ቀናት ሲሰጥ የቆየው ስልጠና በዛሬው እለት ተጠናቋል፡፡
ስልጠናው በሃብት ፈጠራ፣ በገዢ ትርክቶች፣ በሰላም እሴት ግንባታ፣ በአገልጋይና ስልጡን ሲቪል ሰርቫንት ግንበታ እና የሰላም ባህልን አመለካከት የመገንባት እና የመምራት ክህሎት ጉዳዮች በተመለከተ ውጤታማ ስልጠናዎች ተሰጥተዋል፡፡
ስልጠናው ሲጠናቀቅ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፍት ቢሮ ኃላፊ አቶ ተክሌ በዛብህ የተኙ ሲሆን አባላቱ ከልዩነት ይልቅ የጋራ የሚያደርጉንን ገዥ ትርክቶችን በማንፀባረቅ ሕብረ-ብሔራዊ አንድናታችንና ሰላማችንን ማጽናት እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡
በስልጠናው የማጠቃለያ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ-አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የበሀገራች ብልጽግና ለማረጋገጥ በርካታ ስራዎች አየተሰሩ መሆኑ በመግለጽ በኢኮኖሚ የበለጸገች ሃገር ለመገንባት በሚደረገው ጥረት አባላቱ የራሱን ድርሻ መወጣት እንዳለበተ አሳስበዋል፡፡
የስልጠናው የተሳታፊ የሆኑ አባላት በበኩላቸው በስልጠናው በቂ ግንዛቤ ማግነታቸውን ገልጸው ሕብረ-ብሄራዊ አንድነትን ለመገንባትና ስልጡን እና ስነምግባር ያለው የሲቪል ሰራተኛ ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ሁሉ በቁርጠንነት ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን በሰጡት አስተያየት ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም አባላቱ በተሰጠው ስልጠና መሠረት በቀጣይ ተግባራዊ የሚደረጉ ባለ አራት ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣትና ለተግባራዊነቱ ቃል በመግባት ስልጠናው ተጠናቋል።
ከስልጠናው መጠናቀቅ በኋላ አባላቱ አንድ ላይ በመሆን የኢትዮጵያ አንድነት ማሳያ የሆነው የአድዋ ዜሮ ዜሮ ፕሮጀክት ጉብኝት አድርገዋል።
በጉብኝቱ የአድዋ ዜሮ ዜሮ ፕሮጀክት ለኢትዮጵያውያንና የጥቁር ህዝብ ቅርስ እና የአንድነት የጀግንነት ማህተም መሆኑ እና ብ
ማሳያ መሆኑ የጉብኝቱ ተሳታፊዎች ገልፀዋል፡፡
መረጃው፦ የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው ።
**አዲስ አበባ**
16/04/2016 ዓ.ም
"ከእዳ ወደ ምንዳ" በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ ከተማ የፕብሊክ ሰርቪስ እና የፍትህ ልዩ ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ አባላት ለተካታተይ አራት ቀናት ሲሰጥ የቆየው ስልጠና በዛሬው እለት ተጠናቋል፡፡
ስልጠናው በሃብት ፈጠራ፣ በገዢ ትርክቶች፣ በሰላም እሴት ግንባታ፣ በአገልጋይና ስልጡን ሲቪል ሰርቫንት ግንበታ እና የሰላም ባህልን አመለካከት የመገንባት እና የመምራት ክህሎት ጉዳዮች በተመለከተ ውጤታማ ስልጠናዎች ተሰጥተዋል፡፡
ስልጠናው ሲጠናቀቅ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፍት ቢሮ ኃላፊ አቶ ተክሌ በዛብህ የተኙ ሲሆን አባላቱ ከልዩነት ይልቅ የጋራ የሚያደርጉንን ገዥ ትርክቶችን በማንፀባረቅ ሕብረ-ብሔራዊ አንድናታችንና ሰላማችንን ማጽናት እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡
በስልጠናው የማጠቃለያ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ-አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የበሀገራች ብልጽግና ለማረጋገጥ በርካታ ስራዎች አየተሰሩ መሆኑ በመግለጽ በኢኮኖሚ የበለጸገች ሃገር ለመገንባት በሚደረገው ጥረት አባላቱ የራሱን ድርሻ መወጣት እንዳለበተ አሳስበዋል፡፡
የስልጠናው የተሳታፊ የሆኑ አባላት በበኩላቸው በስልጠናው በቂ ግንዛቤ ማግነታቸውን ገልጸው ሕብረ-ብሄራዊ አንድነትን ለመገንባትና ስልጡን እና ስነምግባር ያለው የሲቪል ሰራተኛ ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ሁሉ በቁርጠንነት ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን በሰጡት አስተያየት ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም አባላቱ በተሰጠው ስልጠና መሠረት በቀጣይ ተግባራዊ የሚደረጉ ባለ አራት ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣትና ለተግባራዊነቱ ቃል በመግባት ስልጠናው ተጠናቋል።
ከስልጠናው መጠናቀቅ በኋላ አባላቱ አንድ ላይ በመሆን የኢትዮጵያ አንድነት ማሳያ የሆነው የአድዋ ዜሮ ዜሮ ፕሮጀክት ጉብኝት አድርገዋል።
በጉብኝቱ የአድዋ ዜሮ ዜሮ ፕሮጀክት ለኢትዮጵያውያንና የጥቁር ህዝብ ቅርስ እና የአንድነት የጀግንነት ማህተም መሆኑ እና ብ
ማሳያ መሆኑ የጉብኝቱ ተሳታፊዎች ገልፀዋል፡፡
መረጃው፦ የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው ።
በቅርቡ በህገ ወጥ መንገድ ሲሰሩ እርምጃ በተወሰደባቸው የቤቲንግ ቤቶችን በተመለከተ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ተካኔደ።
ታህሳስ 18/4/2016 ዓ.ም (አዲስ አበባ )
የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ በቅርቡ በቤቲንግ ስፖርት ቤቶ ላይ የሚስተዋሉ አላግባብ ጸጥታን የሚያደፈርሱ ከተሰጣቸው ፈቃድ ውጪ ሲንቀሳቀሱ በነበሩ ቤቶች ላይ እርምጃ መውሰዱ የሚታወስ ሲሆን በዛሬው ዕለትም ጉዳዩን አስመልክቶ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በራስ አምባ ሆቴል ውይይት ተካኒዷል።
መድረኩን የመሩት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሀላፊ ክብርት ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ በመድረኩ ላይ እንደገለፁት፦አዲስ አበባ ከተማ በየግዜው የኢኮኖሚ ግብይትን በማዘመን የምትታወቅ ከተማ እንደ መሆኗ መጠን በንግድ ና ነጋዴው መካከል ባለው ስርዓት ውስጥ ሀገራዊ ፍይዳው የጎላ መሆኑን ጭምር በመጠቆም ከቅርብ ግዜ ጀምሮ ግን ህግና ስርዓትን ባልጠበቀ መልኩ የሚንቀሳቀሱ ማህበረሰቡ ላይ ማህበራዊ ጫና በመፍጠር ተቀባይነት የሌላቸው እየተበራከቱ ከመምጣታቸው ባሻገር ከተማውን የሁከት ብጥብጥ የጸረ ሰላም ሀይሎች መሰብሰቢያ የተለያዩ የፖለቲካ አጀንዳ ማስፍፊያ እየሆኑ መምጣታቸውን ጠቁመዋል ።
ሀላፊዋ አያይዘውም ህጋዊ ሆነው ስርዓትን ባልጠበቀ መልኩ በሚሰሩ በቀጣይ እርምጃው እንደሚቀጥል በመጠቆም በቀጣይ እርምጃ የተወሰደባቸውን የቤቲንግ ቤቶቹን በተመለከተ መደረግ ስላለበት ጉዳይ አስፈጻሚው አባል የሚሰጠውን አቅጣጫ እናሳውቃለን ሲሉ ተደምጠዋል ።
በጉዳዩ ላይና በቀረበው ሰነድ ላይ ከተሳታፊዎቹ ለቀረበው ሀሳብና አስተያየት ከሚመለከተው አካል ምላሽ ተሰቶበት ውይይቱ ተጠናቋል።
ዘገባው፦የአዲስ አበባ ከተማ ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ኮሙኒኬሽን ጉዳዩች ነው።
ታህሳስ 18/4/2016 ዓ.ም (አዲስ አበባ )
የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ በቅርቡ በቤቲንግ ስፖርት ቤቶ ላይ የሚስተዋሉ አላግባብ ጸጥታን የሚያደፈርሱ ከተሰጣቸው ፈቃድ ውጪ ሲንቀሳቀሱ በነበሩ ቤቶች ላይ እርምጃ መውሰዱ የሚታወስ ሲሆን በዛሬው ዕለትም ጉዳዩን አስመልክቶ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በራስ አምባ ሆቴል ውይይት ተካኒዷል።
መድረኩን የመሩት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሀላፊ ክብርት ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ በመድረኩ ላይ እንደገለፁት፦አዲስ አበባ ከተማ በየግዜው የኢኮኖሚ ግብይትን በማዘመን የምትታወቅ ከተማ እንደ መሆኗ መጠን በንግድ ና ነጋዴው መካከል ባለው ስርዓት ውስጥ ሀገራዊ ፍይዳው የጎላ መሆኑን ጭምር በመጠቆም ከቅርብ ግዜ ጀምሮ ግን ህግና ስርዓትን ባልጠበቀ መልኩ የሚንቀሳቀሱ ማህበረሰቡ ላይ ማህበራዊ ጫና በመፍጠር ተቀባይነት የሌላቸው እየተበራከቱ ከመምጣታቸው ባሻገር ከተማውን የሁከት ብጥብጥ የጸረ ሰላም ሀይሎች መሰብሰቢያ የተለያዩ የፖለቲካ አጀንዳ ማስፍፊያ እየሆኑ መምጣታቸውን ጠቁመዋል ።
ሀላፊዋ አያይዘውም ህጋዊ ሆነው ስርዓትን ባልጠበቀ መልኩ በሚሰሩ በቀጣይ እርምጃው እንደሚቀጥል በመጠቆም በቀጣይ እርምጃ የተወሰደባቸውን የቤቲንግ ቤቶቹን በተመለከተ መደረግ ስላለበት ጉዳይ አስፈጻሚው አባል የሚሰጠውን አቅጣጫ እናሳውቃለን ሲሉ ተደምጠዋል ።
በጉዳዩ ላይና በቀረበው ሰነድ ላይ ከተሳታፊዎቹ ለቀረበው ሀሳብና አስተያየት ከሚመለከተው አካል ምላሽ ተሰቶበት ውይይቱ ተጠናቋል።
ዘገባው፦የአዲስ አበባ ከተማ ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ኮሙኒኬሽን ጉዳዩች ነው።
ባለስልጣኑ በመንግስት ንብረት አያያዝ እና አወጋገድ ዙሪያ ስልጠና ሰጠ።
**አዲስ አበባ**
18/04/2016 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ ከአስራ አንዱም ክፍለ ከተሞች ለተወጣጡ የንብረት እና የፋይናንስ ባለሙያዎች በመንግስት ንብረት አያያዝ እና አወጋገድ ዙሪያ ስልጠና ሰጠ።
ስልጠናውን የሰጡት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የስልጠና ቡድን መሪ የሆኑት አቶ አዳነ ለገሰ እንደገለጹት ስልጠናው በአዲሱ በመንግስት ንብረት አያያዝና አወጋገድ መመሪያ ቁጥር 2/2015 መሠረት ተደርጎ የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀዋል።
በስልጠናው የተገኙት የባለስልጣኑ የግንዛቤ ማስጨበጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰርካለም ጌታሁን በበኩላቸው ሰልጣኞች በሰለጠኑት መሠረት በመስራት ያለአግባብ የሚባክነው የመንግስት ሃብትና ንብረት ከብክነት ማዳን እንደሚገባ ተናግረዋል።
በስልጠናው የተሳተፉ ባለሙያዎች በበኩላቸው የተሰጠው ስልጠና አስፈላጊ እና ጊዜውን መሠረት ያደረገ መሆኑ በመግለፅ በቀጣይ ህግንና መመሪያ ተከትለን እንድንሠራ በእጅጉ ይረዳናል በማለት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል ፡፡
መረጃው፦ የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዳይሬክቶሬት ነው።
**አዲስ አበባ**
18/04/2016 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ ከአስራ አንዱም ክፍለ ከተሞች ለተወጣጡ የንብረት እና የፋይናንስ ባለሙያዎች በመንግስት ንብረት አያያዝ እና አወጋገድ ዙሪያ ስልጠና ሰጠ።
ስልጠናውን የሰጡት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የስልጠና ቡድን መሪ የሆኑት አቶ አዳነ ለገሰ እንደገለጹት ስልጠናው በአዲሱ በመንግስት ንብረት አያያዝና አወጋገድ መመሪያ ቁጥር 2/2015 መሠረት ተደርጎ የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀዋል።
በስልጠናው የተገኙት የባለስልጣኑ የግንዛቤ ማስጨበጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰርካለም ጌታሁን በበኩላቸው ሰልጣኞች በሰለጠኑት መሠረት በመስራት ያለአግባብ የሚባክነው የመንግስት ሃብትና ንብረት ከብክነት ማዳን እንደሚገባ ተናግረዋል።
በስልጠናው የተሳተፉ ባለሙያዎች በበኩላቸው የተሰጠው ስልጠና አስፈላጊ እና ጊዜውን መሠረት ያደረገ መሆኑ በመግለፅ በቀጣይ ህግንና መመሪያ ተከትለን እንድንሠራ በእጅጉ ይረዳናል በማለት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል ፡፡
መረጃው፦ የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዳይሬክቶሬት ነው።
የባለስልጣኑ የደንብ መተላለፍ የክትትል ቁጥጥር እና እርምጃ አወሳሰድ ዘርፍ የ6 ወር እቅድ አፈጻጸሙን ገመገመ ።
25/04/2016 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የደንብ መተላለፍ ክትትል ቁጥጥር እና እርምጃ አወሳሰድ ዘርፍ የ2016 በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት እቅድ አፈጻጸም ከማዕከል አስከ ወረዳ ካሉ የዘርፋ ኦፊሰሮች ጋር የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት አካሂዷል ።
በመድረኩ የተገኙት የባለስልጣኑ ዋና ሰራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንደተናገሩት በዘርፉ ከማዕከል አስከ ወረዳ የተሰራው ሰራ አበረታች ቢሆንም የሚታዪ ክፍተቶችን በማረም ስራዎች ጠንክሮ በመሰራት የደንብ መተላለፍ የቀነሰ ማድረግ አንደሚገባ ገልፀዋል ።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ ፉፋ አንደተናገሩት በ2016 በጀት ዓመት በስድት ወር ውስጥ ባቀድነው እቅድ መሰረት ያከናወናቸው ተግባራት በጋራ በማየት ጥንካሬዎች ለማስቀጠል የታዪ ክፍተቶችን በመለየት በቀጣይ ክፍተቶችን ለማረምና ያለንን አቅምና እውቀት ተጠቅመን የተሻለ ለውጥ ለማምጣት የዛሬው ውይይት አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል ።
የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርቱ በባለስልጣኑ የደንብ መተላለፍ የቁጥጥር እና አርምጃ አወሳሰድ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ግሩም ወ/መስቀል ቀርቧል።
በሪፖርቱ በ6ወር እቅድ አፈጻጸሙ መሬት ወረራን በማስቆም ፣ ህገወጥ ማስፋፋት አና ህገወጥ ግንባታን ቀደም ሲል ከነበረው እየቀነስ መምጣቱን ተገልጿል ።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ በተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸው የቀጣይ የስራ አቅጣጫ ተቀምጦ መድረኩ ተጠናቋል።
ዘገባው ፦የባለስልጣኑ ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
25/04/2016 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የደንብ መተላለፍ ክትትል ቁጥጥር እና እርምጃ አወሳሰድ ዘርፍ የ2016 በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት እቅድ አፈጻጸም ከማዕከል አስከ ወረዳ ካሉ የዘርፋ ኦፊሰሮች ጋር የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት አካሂዷል ።
በመድረኩ የተገኙት የባለስልጣኑ ዋና ሰራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንደተናገሩት በዘርፉ ከማዕከል አስከ ወረዳ የተሰራው ሰራ አበረታች ቢሆንም የሚታዪ ክፍተቶችን በማረም ስራዎች ጠንክሮ በመሰራት የደንብ መተላለፍ የቀነሰ ማድረግ አንደሚገባ ገልፀዋል ።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ ፉፋ አንደተናገሩት በ2016 በጀት ዓመት በስድት ወር ውስጥ ባቀድነው እቅድ መሰረት ያከናወናቸው ተግባራት በጋራ በማየት ጥንካሬዎች ለማስቀጠል የታዪ ክፍተቶችን በመለየት በቀጣይ ክፍተቶችን ለማረምና ያለንን አቅምና እውቀት ተጠቅመን የተሻለ ለውጥ ለማምጣት የዛሬው ውይይት አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል ።
የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርቱ በባለስልጣኑ የደንብ መተላለፍ የቁጥጥር እና አርምጃ አወሳሰድ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ግሩም ወ/መስቀል ቀርቧል።
በሪፖርቱ በ6ወር እቅድ አፈጻጸሙ መሬት ወረራን በማስቆም ፣ ህገወጥ ማስፋፋት አና ህገወጥ ግንባታን ቀደም ሲል ከነበረው እየቀነስ መምጣቱን ተገልጿል ።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ በተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸው የቀጣይ የስራ አቅጣጫ ተቀምጦ መድረኩ ተጠናቋል።
ዘገባው ፦የባለስልጣኑ ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
"የዓድዋ ዜሮ ዜሮ ኪሎ ሜትር ሙዚየም ታሪኩን በሚመጥን ልክ እየተገነባ ነው።" ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ታህሰስ 26/2016 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
“ታላቁ የዓድዋ ዜሮ ዜሮ ኪሎ ሜትር ሙዚየም የወል ትርክት ለሀገር አንድነት” በሚል ሀሳብ የፓናል ውይይት ተካሄደ።
በፓናል መድረኩ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤን ጨምሮ ሌሎች የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች፣ ከክልሎች የመጡ የስራ ኃላፊዎች፣ የታሪክ ምሁራን እና የኪነ ህንጸ ባለሞያዎች እንዲሁም የሚዲያ አካላት ተሳትፈዋል።
የዓድዋ ድል በደም እና አጥንት የተገኘ ታላቅ ድል መሆኑን የተናገሩት ከንቲባ አዳነች ነገር ግን ይህ ታላቅ ድል ላለፉት ዓመታት በሚገባው ልክ አለመዘከሩን ገልጸዋል።
ዓድዋ የነጻነት አርማ የጥቁር ህዝቦች ሁሉ ድል ነው ያሉት ከንቲባ አዳነች ታላቁ የዓድዋ ዜሮ ዜሮ ኪሎ ሜትር ሙዚየም ታሪኩን በሚመጥን ልክ መገንባቱንም ተናግረዋል።
የዓድዋን ሙዚየም ገነባን ስንል ፕሮጀክት ብቻ ሳይሆን ታሪክም ጭምር ነው የገነባነው ያሉት ከንቲባ አዳነች፣ ገራዊ የጋራ ታሪካችንን እኩል ልንናገረው፣ እኩል ልንኮራበትም ይገባል ብለዋል።
በፓናል ውይይቱ የክልሎች ኮሙኒኬሽን ቢሮ እና የባህል እና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊዎች፣ የታሪክ ምሁራን፣ ስነ-ህንፃ ባለሞያዎች እና የሚዲያ አካላት ተሳትፈዋል።
ታህሰስ 26/2016 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
“ታላቁ የዓድዋ ዜሮ ዜሮ ኪሎ ሜትር ሙዚየም የወል ትርክት ለሀገር አንድነት” በሚል ሀሳብ የፓናል ውይይት ተካሄደ።
በፓናል መድረኩ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤን ጨምሮ ሌሎች የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች፣ ከክልሎች የመጡ የስራ ኃላፊዎች፣ የታሪክ ምሁራን እና የኪነ ህንጸ ባለሞያዎች እንዲሁም የሚዲያ አካላት ተሳትፈዋል።
የዓድዋ ድል በደም እና አጥንት የተገኘ ታላቅ ድል መሆኑን የተናገሩት ከንቲባ አዳነች ነገር ግን ይህ ታላቅ ድል ላለፉት ዓመታት በሚገባው ልክ አለመዘከሩን ገልጸዋል።
ዓድዋ የነጻነት አርማ የጥቁር ህዝቦች ሁሉ ድል ነው ያሉት ከንቲባ አዳነች ታላቁ የዓድዋ ዜሮ ዜሮ ኪሎ ሜትር ሙዚየም ታሪኩን በሚመጥን ልክ መገንባቱንም ተናግረዋል።
የዓድዋን ሙዚየም ገነባን ስንል ፕሮጀክት ብቻ ሳይሆን ታሪክም ጭምር ነው የገነባነው ያሉት ከንቲባ አዳነች፣ ገራዊ የጋራ ታሪካችንን እኩል ልንናገረው፣ እኩል ልንኮራበትም ይገባል ብለዋል።
በፓናል ውይይቱ የክልሎች ኮሙኒኬሽን ቢሮ እና የባህል እና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊዎች፣ የታሪክ ምሁራን፣ ስነ-ህንፃ ባለሞያዎች እና የሚዲያ አካላት ተሳትፈዋል።
የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት‼️
ለአቅመ ደካሞች፣ ለሃገር ባለውለታ አረጋዊያን፣ በዝቅተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ የመንግስት ሠራተኞችና ምንም ገቢ ሌላቸው ከ263 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ነዋሪዎች እንኳን አደረሳችሁ ብለን ማዕድ አጋርተናል። በዚህ የበጎነት ተግባር ላይ የተሳተፋችሁ የከተማችን ባለ ሀብቶች፣ በጋራ ሆነን እምባ እያበስን ፍቅራችንን እና አክብሮታችንን ለህዝባችን መግለጽ ስለቻልን አመሰግናለሁ።
ፈጣሪ በወጣ እጥፍ አድርጎ ይመልስላችሁ!
ለአቅመ ደካሞች፣ ለሃገር ባለውለታ አረጋዊያን፣ በዝቅተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ የመንግስት ሠራተኞችና ምንም ገቢ ሌላቸው ከ263 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ነዋሪዎች እንኳን አደረሳችሁ ብለን ማዕድ አጋርተናል። በዚህ የበጎነት ተግባር ላይ የተሳተፋችሁ የከተማችን ባለ ሀብቶች፣ በጋራ ሆነን እምባ እያበስን ፍቅራችንን እና አክብሮታችንን ለህዝባችን መግለጽ ስለቻልን አመሰግናለሁ።
ፈጣሪ በወጣ እጥፍ አድርጎ ይመልስላችሁ!
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ቀዳማይት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በአዋሬ አካባቢ በ1523.3 ሜትር ካሬ ላይ የተገነባውን ተጨማሪ የአነስተኛ ወጪ ቤትች ግንባታ መርቀዋል።
የተመረቁት ሁለቱ ባለ 11 ወለል ህንፃዎች በሶስት ወራት ጊዜ ተገንብተው የተጠናቀቁ ሲሆኑ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር የ’መደመር ትውልድ መጽሃፍ ሽያጭ ገቢ እና ከኦቪድ ኮንስትራክሽን ግሩፕ ድጋፍ የተገነቡ ናቸው። ህንፃዎቹ ባለአንድ፣ ባለሁለት እና ባለሦስት የመኝታ ክፍሎች ያላቸው 110 ቤቶች እንዲሁም እታችኛው ወለል ላይ 51 የምድር ቤት ክፍሎችን የያዙ ናቸው።
በተጨማሪም የጋራ የእንጀራ እና ዳቦ መጋገሪያ፣ ማብሰያ እና የማጠቢያ አካባቢዎች የተካተቱባቸው ናቸው። ሁለቱ አፓርትመንቶች በጠባብ ቦታ ላይ ለየአገልግሎቱ በልዩ ሁኔታ የመጠቀም ጥበብ ያረፈባቸው ሲሆኑ፣ ሁሉም ቤቶች ሙሉ እቃ ተገጥሞላቸዋል።
ክብር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በንግግራቸው ባለሃብቶች በበጎ አድራጎት እና ፈጠራ የኦቪድ ኮንስትራክሽን ግሩፕን አርዓያነት እንዲከተሉ ጥሪ አቅርበዋል።
#PMOEthiopia
የተመረቁት ሁለቱ ባለ 11 ወለል ህንፃዎች በሶስት ወራት ጊዜ ተገንብተው የተጠናቀቁ ሲሆኑ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር የ’መደመር ትውልድ መጽሃፍ ሽያጭ ገቢ እና ከኦቪድ ኮንስትራክሽን ግሩፕ ድጋፍ የተገነቡ ናቸው። ህንፃዎቹ ባለአንድ፣ ባለሁለት እና ባለሦስት የመኝታ ክፍሎች ያላቸው 110 ቤቶች እንዲሁም እታችኛው ወለል ላይ 51 የምድር ቤት ክፍሎችን የያዙ ናቸው።
በተጨማሪም የጋራ የእንጀራ እና ዳቦ መጋገሪያ፣ ማብሰያ እና የማጠቢያ አካባቢዎች የተካተቱባቸው ናቸው። ሁለቱ አፓርትመንቶች በጠባብ ቦታ ላይ ለየአገልግሎቱ በልዩ ሁኔታ የመጠቀም ጥበብ ያረፈባቸው ሲሆኑ፣ ሁሉም ቤቶች ሙሉ እቃ ተገጥሞላቸዋል።
ክብር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በንግግራቸው ባለሃብቶች በበጎ አድራጎት እና ፈጠራ የኦቪድ ኮንስትራክሽን ግሩፕን አርዓያነት እንዲከተሉ ጥሪ አቅርበዋል።
#PMOEthiopia
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የገና በዓልን አስመልክቶ ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት!
''ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችንና ለመድሀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
የገናን በዓል ክርስቲያኖች ኢየሱስ ክርስቶስ በመወለዱ ሰውና መላዕክት በአንድ ላይ ፈጣሪአቸውን ያመሰገኑበት እለት በማሰብ በደስታና በፍቅር ልደቱን በማሰብ በድምቀት ያከብሩታል።
ከዚህም በመነሳት በዓለ ልደቱ የፍቅር፣ የአብሮነትና የሰላም እንደመሆኑ መጠን ሁላችንም በጋራ ፣በመተሳሰብ፣ በአንድነት ያለንን ለሌላቸው በማካፈል ኢትዮጵያዊ ዕሴቶቻችንን በማጎልበት ሊናከብረው ይገባል።
በዓሉ ስናከብር በከተማው የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎች እና ተያያዥ ህገ ወጥ ተግባራት እንዳይፈጸም ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የበኩልን ድርሻ እንዲወጣ አደራ ማለት እወዳለሁ፡፡
በዓሉ የሰላም ፣የፍቅር፣ የአብሮነት እና የመተሳሰብ እንዲሆን እየተመኘሁ በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ እላለሁ።''
ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ
ታህሳስ 27/2016 ዓ.ም
''ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችንና ለመድሀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
የገናን በዓል ክርስቲያኖች ኢየሱስ ክርስቶስ በመወለዱ ሰውና መላዕክት በአንድ ላይ ፈጣሪአቸውን ያመሰገኑበት እለት በማሰብ በደስታና በፍቅር ልደቱን በማሰብ በድምቀት ያከብሩታል።
ከዚህም በመነሳት በዓለ ልደቱ የፍቅር፣ የአብሮነትና የሰላም እንደመሆኑ መጠን ሁላችንም በጋራ ፣በመተሳሰብ፣ በአንድነት ያለንን ለሌላቸው በማካፈል ኢትዮጵያዊ ዕሴቶቻችንን በማጎልበት ሊናከብረው ይገባል።
በዓሉ ስናከብር በከተማው የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎች እና ተያያዥ ህገ ወጥ ተግባራት እንዳይፈጸም ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የበኩልን ድርሻ እንዲወጣ አደራ ማለት እወዳለሁ፡፡
በዓሉ የሰላም ፣የፍቅር፣ የአብሮነት እና የመተሳሰብ እንዲሆን እየተመኘሁ በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ እላለሁ።''
ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ
ታህሳስ 27/2016 ዓ.ም
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችንና ለመድሀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱ ያስተላልፋል።
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችንና ለመድሀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱ ያስተላልፋል።
👍1