የባለሥልጣኑ 6ኛ ዙር ዕጩ ፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ወደ አፖስቶ የፌደራል ፖሊስ ማሰልጠኛ ኮሌጅ በሰላም ደረሱ
27-07 -2017 ዓ.ም
**ይርጋለም**
ከጠዋቱ 12 ሰዓት ከአዲስ አበባ የተነሱት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን 6ኛ ዙር ምልምል እጩ ፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ወደ አፖስቶ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ማሰልጠኛ ኮሌጅ በሰላም ደረሱ።
ወደ ማሰልጠኛው እንደደረሱ በኮሌጁ ማህበረሰብና አስተባባሪዎች አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
መረጃው፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
27-07 -2017 ዓ.ም
**ይርጋለም**
ከጠዋቱ 12 ሰዓት ከአዲስ አበባ የተነሱት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን 6ኛ ዙር ምልምል እጩ ፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ወደ አፖስቶ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ማሰልጠኛ ኮሌጅ በሰላም ደረሱ።
ወደ ማሰልጠኛው እንደደረሱ በኮሌጁ ማህበረሰብና አስተባባሪዎች አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
መረጃው፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
ለመኪና ፓርኪንግ እየተሰራ ባለው ቦታ ላይ ህገወጥ ንግድ ሲያከናውኑ በነበሩ ግለሰቦች እርምጃ መወሰዱ ተገለፀ
30/07/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
ባለስልጣኑ በአራዳ ክፍለከተማ ወረዳ 05 ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የኦፕሬሽን እቅድ በማውጣት እና ሽፍት በማጠፍ ከጊዮርጊስ ቤተ-ክርስትያን ጀርባ የድሮው አወሊያ ት/ቤት አካባቢ በኮሪደር ልማት የፈረሰው እና ለመኪና ፓርኪንግ እየተሰራ ባለው ቦታ ላይ ህገወጥ ንግድ ሲያከናውኑ በነበሩ ግለሰቦች የወረዳው ደንብ ጽ/ት ሀላፊ ዋና ሳጅን መዝገቡ ዲማ ገለፁ።
ሀላፊው እንደገለፁት በተወሰደው እርምጃው ከፖሊስን አባላት ጋር በመቀናጀት በአይነት ከ35 እና ግምቱ 121,820 ብር በላይ አታክልት እና አልባሳት በመውረስ እርምጃ መወሰዱ ገልፀዋል።
30/07/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
ባለስልጣኑ በአራዳ ክፍለከተማ ወረዳ 05 ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የኦፕሬሽን እቅድ በማውጣት እና ሽፍት በማጠፍ ከጊዮርጊስ ቤተ-ክርስትያን ጀርባ የድሮው አወሊያ ት/ቤት አካባቢ በኮሪደር ልማት የፈረሰው እና ለመኪና ፓርኪንግ እየተሰራ ባለው ቦታ ላይ ህገወጥ ንግድ ሲያከናውኑ በነበሩ ግለሰቦች የወረዳው ደንብ ጽ/ት ሀላፊ ዋና ሳጅን መዝገቡ ዲማ ገለፁ።
ሀላፊው እንደገለፁት በተወሰደው እርምጃው ከፖሊስን አባላት ጋር በመቀናጀት በአይነት ከ35 እና ግምቱ 121,820 ብር በላይ አታክልት እና አልባሳት በመውረስ እርምጃ መወሰዱ ገልፀዋል።
የባለስልጣኑ 6ተኛ ዙር የፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ስልጠና በይፋ ተጀመረ
02/08/2017 ዓ.ም
ይርጋለም /አፖስቶ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ለ6ኛ ዙር የሚያሰለጥናቸውን ከ2000 በላይ ዕጩ የፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮችን ፌደራል ፖሊስ ዩኒቨርስቲ አፖስቶ ካምፓስ የወታደራዊ እና የንድፈ ሃሳብ ስልጠና የመክፈቻ ኘሮግራም አካሄደ።
በፕሮግራሙ የአዲስ አበባ የሠላምና ፀጥታ አስተዳደር ቤሮ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ሊዲያ ግርማና የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች ፣ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት እና የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ም/ኮሚሽነር መስፍን አበባ ፣ የሰላምና ጸጥታ እና የደንብ ማስከበር የክ/ከተማ ጽ/ቤት ኃላፊዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ የሠላምና ፀጥታ አስተዳደር ቤሮ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ ከለውጡ ማግስት ጀምሮ የከተማውን ጸጥታ በማረጋገጥና የደንብ መተላለፎችን የመከላከልና የመቆጣጠር ስራው በአግባቡ በመወጣት ለዜጎቿና ለእንግዶቿ ምቹ እንድትሆን በርካታ ስራዎች የተሰሩና ውጤት የተገኘ መሆኑ ገልጸዋል ።
ባለስልጣኑ የደንብ መተላለፍ ተግባራትን በዘላቂነት ለመከላከል ይቻል ዘንድ ቴክኖሎጂን ዘመናዊ መንገድ በመጠቀም የሚችል ደንብ ማስከበር ኦፊሰርን ለማብቃት መሉ ዝግጅት ተደርጎ በዛሬው ዕለት ስልጠናውን መጀመሩን በማብሰር መልካም የስልጠና ቆይታ ተመኝተዋል ።
ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በ2005 ተቋቁሞ በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎችን ለመከላከል የተቋቋመ ሲሆን አሁን ላይ ራሱን በማዘመንና ሪፎርም በማድረግ 6ኛ ዙር የፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ለማስልጠንና በከተማችን የሚስተዋሉትን የደንብ መተላለፎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ስልጠናውን በዛሬው ዕለት በይፋ መጀመሩን የባለሥልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ገልጸዋል ።
አክለውም ባለስልጣኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት የከተማውን ሰላምና ጸጥታ እያስጠበቀ ይገኛል አንዲሁም በተለያዩ ሰው ተኮር ስራዎችን በመስራት ፣ የአረንጓዴ አሻራ ላይ በመሳተፍ የተለያዩ ተግባራት እያከናወነ ይገኛል ብለዋል ።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት እና የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ም/ኮሚሽነር መስፍን አበበ እንደገለፁት በከተማ ውስጥ ያሉ እንቅስቃሴዎች ሰላማዊ እንዲሆንና በከተማዋ ያሉ የደንብ መተላለፎችን ለመከላከል የኦፊሰሩ ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገልጿል ።
ፕሬዝዳንቱ ስልጠናው ህጎችንና ደንቡ ላይ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ፣ በአካል ብቃት እንዲዳብሩ፣ የህግ የበላይነት እንዲያከብሩና እንዲያስከብሩ የመስክና የክፍል ውስጥ ስልጠና በመሰጠት እጩ ፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ውጤታማና ብቁ ሆኖ እንዲወጡ ዩኒቨርስቲው የበኩሉን እንደሚወጣ ገልጸዋል ።
ዘገባው ፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
02/08/2017 ዓ.ም
ይርጋለም /አፖስቶ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ለ6ኛ ዙር የሚያሰለጥናቸውን ከ2000 በላይ ዕጩ የፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮችን ፌደራል ፖሊስ ዩኒቨርስቲ አፖስቶ ካምፓስ የወታደራዊ እና የንድፈ ሃሳብ ስልጠና የመክፈቻ ኘሮግራም አካሄደ።
በፕሮግራሙ የአዲስ አበባ የሠላምና ፀጥታ አስተዳደር ቤሮ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ሊዲያ ግርማና የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች ፣ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት እና የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ም/ኮሚሽነር መስፍን አበባ ፣ የሰላምና ጸጥታ እና የደንብ ማስከበር የክ/ከተማ ጽ/ቤት ኃላፊዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ የሠላምና ፀጥታ አስተዳደር ቤሮ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ ከለውጡ ማግስት ጀምሮ የከተማውን ጸጥታ በማረጋገጥና የደንብ መተላለፎችን የመከላከልና የመቆጣጠር ስራው በአግባቡ በመወጣት ለዜጎቿና ለእንግዶቿ ምቹ እንድትሆን በርካታ ስራዎች የተሰሩና ውጤት የተገኘ መሆኑ ገልጸዋል ።
ባለስልጣኑ የደንብ መተላለፍ ተግባራትን በዘላቂነት ለመከላከል ይቻል ዘንድ ቴክኖሎጂን ዘመናዊ መንገድ በመጠቀም የሚችል ደንብ ማስከበር ኦፊሰርን ለማብቃት መሉ ዝግጅት ተደርጎ በዛሬው ዕለት ስልጠናውን መጀመሩን በማብሰር መልካም የስልጠና ቆይታ ተመኝተዋል ።
ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በ2005 ተቋቁሞ በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎችን ለመከላከል የተቋቋመ ሲሆን አሁን ላይ ራሱን በማዘመንና ሪፎርም በማድረግ 6ኛ ዙር የፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ለማስልጠንና በከተማችን የሚስተዋሉትን የደንብ መተላለፎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ስልጠናውን በዛሬው ዕለት በይፋ መጀመሩን የባለሥልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ገልጸዋል ።
አክለውም ባለስልጣኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት የከተማውን ሰላምና ጸጥታ እያስጠበቀ ይገኛል አንዲሁም በተለያዩ ሰው ተኮር ስራዎችን በመስራት ፣ የአረንጓዴ አሻራ ላይ በመሳተፍ የተለያዩ ተግባራት እያከናወነ ይገኛል ብለዋል ።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት እና የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ም/ኮሚሽነር መስፍን አበበ እንደገለፁት በከተማ ውስጥ ያሉ እንቅስቃሴዎች ሰላማዊ እንዲሆንና በከተማዋ ያሉ የደንብ መተላለፎችን ለመከላከል የኦፊሰሩ ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገልጿል ።
ፕሬዝዳንቱ ስልጠናው ህጎችንና ደንቡ ላይ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ፣ በአካል ብቃት እንዲዳብሩ፣ የህግ የበላይነት እንዲያከብሩና እንዲያስከብሩ የመስክና የክፍል ውስጥ ስልጠና በመሰጠት እጩ ፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ውጤታማና ብቁ ሆኖ እንዲወጡ ዩኒቨርስቲው የበኩሉን እንደሚወጣ ገልጸዋል ።
ዘገባው ፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
በባለፈው አንድ ወር በወንዞችና የወንዝ ዳርቻ ብክለት መከላከል ላይ የተሰሩ ስራዎች ተገመገሙ።
03/08/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ፣ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን እና የውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ በጋራ በመሆን በወንዝ እና የወንዞች ዳርቻ ብክለት ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ከየካቲት 24 እስከ ሚያዝያ 02/2017 ዓ.ም ድረስ የተሰሩ ስራዎች የተቋማቱ ከፍተኛ አመራሮች እና የክ/ከተማ ጽ/ቤት ኃላፊዎች በተገኙበት ሪፓርት ሪፓርቱ ቀርቦ ተገምግሟል።
በግምገማው ላይ ንግግር ያደረጉት የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በቅንጅት የመስራት ሂደቱ ያመጣው ውጤት መልካም መሆኑን ጠቅሰው፤ በተለይም 2,858 የሚሆኑ የብክለት ድርጊቶች ከሚፅሙት ወንጀል መታቀብ በመቻላቸው ይበል የሚያሰኝ ከፍተኛ ለውጥ መሆኑን እና የሚለቀቁ ፍሳሾች የጉዳት መጠን በላቭራቶሪ በመመርመር እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
በወንዝ ዳርቻ ልማትና ብክለት ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ የተሰሩ ተግባራትን አፈፃፀም ሪፖርት በአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የግንዛቤ ቡድን መሪ አቶ አንበሳው ፈንታ ቀርቧል።
በሪፖርቱም በደንብ ቁጥር 180/2017 ዙርያ 2,354,443 የህብረተሰብ ክፍሎች ግንዛቤ መፈጠረ መቻሉን፣2,858 ከሚፈፅሙት ወንጀል ማስተካከያ መደረጉ እና ህግን ተላልፈው በተገኙ ድርጅቶች እና ግለሰቦችን 68,896,000 (ስልሳ ስምንት ሚሊዮን ስምንት መቶ ዘጠና ስድስት ሺህ ብር ) የገንዘብ ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱ ተገልጿል።
በቀረበው አፈፃፀም ሪፖርት ላይ በአሰራር ላይ ያጋጠሙ አጠቃላይ ሂደቶች በክፍተት በታዩ እና በቀጣይም መስተካከል የሚገባቸው አሰራሮች ላይ ከቤቱ ሀሳቦች ተንሸራሸረዋል። በዚህም የተለያዩ አስተያየት እና ጥያቄዎችን በማንሳት ሰፊ ምክክር ተካሂዷል።
የአዲስ አበባ ከተማ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዲዳ ድሪባ በበኩላቸው የስራ አፈፃፀሙ በጣም ጥሩ መሆኑን ገልፀው፤ ይህም ሊመጣ የቻለው በቅንጅት በመግባባት ስራዎች በመሰራታቸው በመሆኑ ከቀሩ ተቋማት ጋር በቅንጅት መስራት ይበልጥ ለውጥ እንደሚያመጣ ጠቁመዋል።
የአዲስ አበባ ወንዞች ሲፀዱ እኔም ተሳታፊ ነበርኩ የሚል ታሪክ ነጋሪ ለመሆን ወንዞች በዋናነት የሚበክሉት በማን ነው የሚለውን በማየት በቁርጠኝነት ስራዎች በጋራ እንስራ ያሉት ደግሞ የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ ናቸው።
በመጨረሻም በተቋማቱ የበላይ አመራሮች የቀጣይ የአሰራር አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።
ዘገባው፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
03/08/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ፣ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን እና የውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ በጋራ በመሆን በወንዝ እና የወንዞች ዳርቻ ብክለት ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ከየካቲት 24 እስከ ሚያዝያ 02/2017 ዓ.ም ድረስ የተሰሩ ስራዎች የተቋማቱ ከፍተኛ አመራሮች እና የክ/ከተማ ጽ/ቤት ኃላፊዎች በተገኙበት ሪፓርት ሪፓርቱ ቀርቦ ተገምግሟል።
በግምገማው ላይ ንግግር ያደረጉት የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በቅንጅት የመስራት ሂደቱ ያመጣው ውጤት መልካም መሆኑን ጠቅሰው፤ በተለይም 2,858 የሚሆኑ የብክለት ድርጊቶች ከሚፅሙት ወንጀል መታቀብ በመቻላቸው ይበል የሚያሰኝ ከፍተኛ ለውጥ መሆኑን እና የሚለቀቁ ፍሳሾች የጉዳት መጠን በላቭራቶሪ በመመርመር እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
በወንዝ ዳርቻ ልማትና ብክለት ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ የተሰሩ ተግባራትን አፈፃፀም ሪፖርት በአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የግንዛቤ ቡድን መሪ አቶ አንበሳው ፈንታ ቀርቧል።
በሪፖርቱም በደንብ ቁጥር 180/2017 ዙርያ 2,354,443 የህብረተሰብ ክፍሎች ግንዛቤ መፈጠረ መቻሉን፣2,858 ከሚፈፅሙት ወንጀል ማስተካከያ መደረጉ እና ህግን ተላልፈው በተገኙ ድርጅቶች እና ግለሰቦችን 68,896,000 (ስልሳ ስምንት ሚሊዮን ስምንት መቶ ዘጠና ስድስት ሺህ ብር ) የገንዘብ ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱ ተገልጿል።
በቀረበው አፈፃፀም ሪፖርት ላይ በአሰራር ላይ ያጋጠሙ አጠቃላይ ሂደቶች በክፍተት በታዩ እና በቀጣይም መስተካከል የሚገባቸው አሰራሮች ላይ ከቤቱ ሀሳቦች ተንሸራሸረዋል። በዚህም የተለያዩ አስተያየት እና ጥያቄዎችን በማንሳት ሰፊ ምክክር ተካሂዷል።
የአዲስ አበባ ከተማ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዲዳ ድሪባ በበኩላቸው የስራ አፈፃፀሙ በጣም ጥሩ መሆኑን ገልፀው፤ ይህም ሊመጣ የቻለው በቅንጅት በመግባባት ስራዎች በመሰራታቸው በመሆኑ ከቀሩ ተቋማት ጋር በቅንጅት መስራት ይበልጥ ለውጥ እንደሚያመጣ ጠቁመዋል።
የአዲስ አበባ ወንዞች ሲፀዱ እኔም ተሳታፊ ነበርኩ የሚል ታሪክ ነጋሪ ለመሆን ወንዞች በዋናነት የሚበክሉት በማን ነው የሚለውን በማየት በቁርጠኝነት ስራዎች በጋራ እንስራ ያሉት ደግሞ የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ ናቸው።
በመጨረሻም በተቋማቱ የበላይ አመራሮች የቀጣይ የአሰራር አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።
ዘገባው፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
ከ4.5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የአቅመ ደካማ ቤት በትንሣኤ ዋዜማ እርክብክብ ተካሄደ።
07/08/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ከ4.5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በወረዳ 14 ቱሉ አጀርሳ አከባቢ ቤት ገንብቶ ለአርሶ አደር ወ/ሮ ቀጨኔ ሰንበቶ አስረከበ።
በክፍለ ከተማው ስር የሚገኙትን አስራ ሶስት የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ወረዳዎችን በማስተባበር በ120 ቀናት ውስጥ የሰው ተኮር ስራውን ማከናወን ተችሏል።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስከያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በምረቃ መርኃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ባለስልጣኑ ሁሉን አቀፍ በሆነ መልኩ ተልዕኮውን ከመወጣት ባሻገር ባለፉት 9ኝ ወራት ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ 14 ቤቶችን መገንባትና ማደስ መቻሉን አስታውሰው ፤በቀጣይም ሌሎች ቤቶችን ለማስረከብ ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በምረቃ ፕሮግራሙ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወሮ ካባ መብራቱ እንደተናገሩት የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የደንብ መተላለፍችን ከመከላከል ጎን ለጎን ሙሉ ሠራዊቱን በማስተባበር ይህን የመሰለ ሰው ተኮር ስራዎች ላይ ለሚያደርገው አስተዋጽኦ በክፍለ ከተማው ስም የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የህብረተሰብ ተሳትፎና የበጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ኮሚሽነር ይመር ከበደ በመርኃ ግብሩ ተገኝተው የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በሁሉም ክፍለ ከተማዎች ግንባር ቀደም ሆኖ የሚያበረክተው ሰው ተኮሮ ስራዎች የሚደነቁና በጎነትን የሚያፀኑ መሆናቸውን በአፅንኦት ገልፀዋል።
የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ መቶ አለቃ ቦጋለ አለሙ እንደገለፁት የኦፊሰሩን ስነ-መሃንዲሶች እና የአስራ ሶስቱንም ወረዳ ኃላፊና ኦፊሰሮች አሻራ ጥረት ውጤት መሆኑን እና ይህ በጎ ተግባር በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀው፤ ለአርሶ አደር ቀጨኔ የአውደ ዓመት ማዕድ አጋርተዋል።
በተያዘ ዜና በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ብሄረፅጌ አከባበ ከ500ሺህ ብር በላይ በሚገመት ወጪ የ2 አቅመ ደካሞች ቤቶቾን ገንብቶ ማስረከብ የተቻለ ሲሆን በቀጣይም ይህ ሰውተኮር በጎ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጽ/ቤት ኃላፊው መቶ አለቃ ቦጋለ ገልፀዋል።
በመጨረሻም በግንባታ ሂደቱ ላይ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት እውቅ ተሰጥቷል።
ዘገባባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
07/08/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ከ4.5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በወረዳ 14 ቱሉ አጀርሳ አከባቢ ቤት ገንብቶ ለአርሶ አደር ወ/ሮ ቀጨኔ ሰንበቶ አስረከበ።
በክፍለ ከተማው ስር የሚገኙትን አስራ ሶስት የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ወረዳዎችን በማስተባበር በ120 ቀናት ውስጥ የሰው ተኮር ስራውን ማከናወን ተችሏል።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስከያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በምረቃ መርኃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ባለስልጣኑ ሁሉን አቀፍ በሆነ መልኩ ተልዕኮውን ከመወጣት ባሻገር ባለፉት 9ኝ ወራት ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ 14 ቤቶችን መገንባትና ማደስ መቻሉን አስታውሰው ፤በቀጣይም ሌሎች ቤቶችን ለማስረከብ ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በምረቃ ፕሮግራሙ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወሮ ካባ መብራቱ እንደተናገሩት የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የደንብ መተላለፍችን ከመከላከል ጎን ለጎን ሙሉ ሠራዊቱን በማስተባበር ይህን የመሰለ ሰው ተኮር ስራዎች ላይ ለሚያደርገው አስተዋጽኦ በክፍለ ከተማው ስም የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የህብረተሰብ ተሳትፎና የበጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ኮሚሽነር ይመር ከበደ በመርኃ ግብሩ ተገኝተው የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በሁሉም ክፍለ ከተማዎች ግንባር ቀደም ሆኖ የሚያበረክተው ሰው ተኮሮ ስራዎች የሚደነቁና በጎነትን የሚያፀኑ መሆናቸውን በአፅንኦት ገልፀዋል።
የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ መቶ አለቃ ቦጋለ አለሙ እንደገለፁት የኦፊሰሩን ስነ-መሃንዲሶች እና የአስራ ሶስቱንም ወረዳ ኃላፊና ኦፊሰሮች አሻራ ጥረት ውጤት መሆኑን እና ይህ በጎ ተግባር በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀው፤ ለአርሶ አደር ቀጨኔ የአውደ ዓመት ማዕድ አጋርተዋል።
በተያዘ ዜና በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ብሄረፅጌ አከባበ ከ500ሺህ ብር በላይ በሚገመት ወጪ የ2 አቅመ ደካሞች ቤቶቾን ገንብቶ ማስረከብ የተቻለ ሲሆን በቀጣይም ይህ ሰውተኮር በጎ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጽ/ቤት ኃላፊው መቶ አለቃ ቦጋለ ገልፀዋል።
በመጨረሻም በግንባታ ሂደቱ ላይ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት እውቅ ተሰጥቷል።
ዘገባባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።