ለደረቅ ቆሻሻ ሽርክና ጽዳት ማህበራት በደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ግንዛቤ ተፈጠረ::
16/07 /2017 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ለደረቅ ቆሻሻ ሽርክና ጽዳት ማህበራት አመራሮች የወንዝ ዳር ብክለትን ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በባለስልጣኑ አዳራሽ ለሁለት ቀናት ተካሂዷል።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ ኃላፊ እና ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ለህብረተሰቡና ማህበራት በደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ የሚሰጠው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎችን አጠናክሮ በማስቀጠል ከተማዋን ፅዱ ለነዋሪዎቿ ምቹ እና የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ ገልፀዋል።
ህብረተሰቡም የከተማዋን ፅዳት በመጠበቅና የደንብ መተላለፎች ሲመለከት በማውገዝ ከተቋሙ ጎን ሊሰለፍ እንደሚገባ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ ወንዞች ብክለት በአካባቢ እና በጤና ላይ የሚያደርሰው ጉዳት እና መፍትሔዎች እንዲሁም የወንዝ ዳርቻ ልማት እና ብክለት ለመከላከል የተደነገገው ደንብ ቁጥር 180/2017 እንዲሁም የቅጣት ሰንጠረዥ በባለስልጣኑ የቅድመ መከላከልና ኢንስፔክሽን ባለሙያ አቶ ናታን ታዬ በዝርዝር ቀርቦ ግንዛቤ ተፈጥሮበታል።
ህብረተሰቡ ወንዞችን እና የወንዝ ዳርቻ ብክለትን ለመከላከል የወጣውን ደንብ በመገንዘብ በየአካባቢው የሚገኙ ወንዞችን ከብክለት በመጠበቅ የእራሱን እና የሌሎችን ጤና ማስጠበቅ እንደሚገባ የደንብ መተላለፍ መከላከልና የግንዛቤ ማስጨበጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰርካለም ጌታሁን አብራርተዋል።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል።
16/07 /2017 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ለደረቅ ቆሻሻ ሽርክና ጽዳት ማህበራት አመራሮች የወንዝ ዳር ብክለትን ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በባለስልጣኑ አዳራሽ ለሁለት ቀናት ተካሂዷል።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ ኃላፊ እና ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ለህብረተሰቡና ማህበራት በደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ የሚሰጠው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎችን አጠናክሮ በማስቀጠል ከተማዋን ፅዱ ለነዋሪዎቿ ምቹ እና የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ ገልፀዋል።
ህብረተሰቡም የከተማዋን ፅዳት በመጠበቅና የደንብ መተላለፎች ሲመለከት በማውገዝ ከተቋሙ ጎን ሊሰለፍ እንደሚገባ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ ወንዞች ብክለት በአካባቢ እና በጤና ላይ የሚያደርሰው ጉዳት እና መፍትሔዎች እንዲሁም የወንዝ ዳርቻ ልማት እና ብክለት ለመከላከል የተደነገገው ደንብ ቁጥር 180/2017 እንዲሁም የቅጣት ሰንጠረዥ በባለስልጣኑ የቅድመ መከላከልና ኢንስፔክሽን ባለሙያ አቶ ናታን ታዬ በዝርዝር ቀርቦ ግንዛቤ ተፈጥሮበታል።
ህብረተሰቡ ወንዞችን እና የወንዝ ዳርቻ ብክለትን ለመከላከል የወጣውን ደንብ በመገንዘብ በየአካባቢው የሚገኙ ወንዞችን ከብክለት በመጠበቅ የእራሱን እና የሌሎችን ጤና ማስጠበቅ እንደሚገባ የደንብ መተላለፍ መከላከልና የግንዛቤ ማስጨበጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰርካለም ጌታሁን አብራርተዋል።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል።
ባለስልጣኑ በትላንትና በዛሬው እለት ወንዞችና የወንዞች ዳርቻ የበከሉ ድርጅቶችና ግለሰቦችን 5,670,000/ አምስት ሚሊየን ስድስት መቶ ሰባ ሺህ/ ብር መቅጣቱ አስታወቀ
16/07/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣ ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር ወንዞችና የወንዞች ዳርቻ የበከሉ ድርጅቶችና ግለሰቦችን በዛሬው እለትም በደንብ ቁጥር 180/2017 መሰረት በድምሩ 5,670,000/ አምስት ሚሊየን ስድስት መቶ ሰባ ሺህ/ ብር የገንዘብ ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ፡፡
ባለስልጣኑ በየካ ክ/ከተማ 2,350,000 ብር፤ በቦሌ ክ/ከተማ 950,000 ብር ፤ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ 1,050,000
ብር፤በቦሌ ክፍለ ከተማ 600,000 ብር፣ በአራዳ ክፍለ ከተማ 600,000
ብር ቅጣት ተቀጥቷል።
በተያያዘ ዜና በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ 370,000 ብር ፤በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ 300,000 ብር እና በኮልፌ ክፍለ ከተማ 50,000 ብር ቅጣት በመቅጣት ለመንግስት ገቢ ተደርጓል፡፡
ባለስልጣኑ በሁለት ቀናት በአጠቃላይ 14 ድርጅቶች እና 14 ግለሰቦች በድምሩ 5,670,000/ አምስት ሚሊየን ስድስት መቶ ሰባ ሺህ/ ብር ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ወስዷል።
ባለስልጣኑ ወንወዞችና የወንዞች ዳርቻ እንዳይበከሉ ለድርጅቶችና ለግለሰቦች በደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ሰፊ የግንዛቤ ስራ መስራቱ የገለጸ ሲሆን በቀጣይ የግንዛቤና ህግ የማስከበሩ ስራ አጠናክሮ አንደሚቀጥል አስታውቋል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
16/07/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣ ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር ወንዞችና የወንዞች ዳርቻ የበከሉ ድርጅቶችና ግለሰቦችን በዛሬው እለትም በደንብ ቁጥር 180/2017 መሰረት በድምሩ 5,670,000/ አምስት ሚሊየን ስድስት መቶ ሰባ ሺህ/ ብር የገንዘብ ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ፡፡
ባለስልጣኑ በየካ ክ/ከተማ 2,350,000 ብር፤ በቦሌ ክ/ከተማ 950,000 ብር ፤ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ 1,050,000
ብር፤በቦሌ ክፍለ ከተማ 600,000 ብር፣ በአራዳ ክፍለ ከተማ 600,000
ብር ቅጣት ተቀጥቷል።
በተያያዘ ዜና በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ 370,000 ብር ፤በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ 300,000 ብር እና በኮልፌ ክፍለ ከተማ 50,000 ብር ቅጣት በመቅጣት ለመንግስት ገቢ ተደርጓል፡፡
ባለስልጣኑ በሁለት ቀናት በአጠቃላይ 14 ድርጅቶች እና 14 ግለሰቦች በድምሩ 5,670,000/ አምስት ሚሊየን ስድስት መቶ ሰባ ሺህ/ ብር ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ወስዷል።
ባለስልጣኑ ወንወዞችና የወንዞች ዳርቻ እንዳይበከሉ ለድርጅቶችና ለግለሰቦች በደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ሰፊ የግንዛቤ ስራ መስራቱ የገለጸ ሲሆን በቀጣይ የግንዛቤና ህግ የማስከበሩ ስራ አጠናክሮ አንደሚቀጥል አስታውቋል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
የመጋቢታዊያን የለውጥ ፍሬዎችና የነገ ተስፋዎች!!
18/07/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
በአዲስ አበባ ከተማ ብልፅግና ፖርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፐፕሊክና የፍትህ ልዩ ወረዳ 'ትናንት ፣ ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና!' በሚል መሪ ቃል ባለፉት 7 አመታት ከመጋቢት እስከ መጋቢት በተከናወኑ ተግባራትና የተገኙ ስኬቶች በተመለከተ ውይይት ተካሄደ።
በውይይቱ የአዲስ አበባ ከተማ የፐብሊክ ሰርቪስ፣ የፍትህ፣የሠላምና ፀጥታ ቢሮ እና የደንብ ማስከበር ባለስልጣን አመራሮችና አባላቶች ተገኝተዋል።
የመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የልዩ ወረዳው ሰብሳቢ አቶ አሰፋ መብራቴ ከሰባት ዓመት በፊት ሃገሪቱ የነበረችበት ከፓለቲካና ከኢኮኖሚ አዙሪትና መሠረታዊ የሆነ ለውጥ ለማምጣት የተጓዘችበትን እርቀት የምናስታውስበት እንዲሁም የቀጣይ ስራችንን የምናጠናክርበት መሆኑ ገልጸዋል።
በመድረኩ የአዲስ አበባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ የአገልግሎት አሰጣጥና አውት ሶርሲንግ ዘርፍ ኃላፊ አቶ በቀለ ተመስገንአቶ ፓርቲው ባለፉት ሰባት ዓመታት ያፀናቸውን ለውጦችና የተመለከተ የውይይት መነሻ ሰነድ አቅርበዋል።
በሂደቱም የፓለቲካ ለውጥ፣ በኢኮኖሚው ላይ የተደረገው ማሻሻ፣ የተቋማት ሪፎርም እና የዲፕሎማሲው ቱሩፋቶች አበይት የሰባት ዓመቱ የለውጥ ሂደቶች እንደነበር በሰነዱ ተገልጿል።
የሪፍርምና የስርዓት ለውጥ በማምጣት አካታች የሆነ የፓለቲካ ምህዋርን ለማፅናት በርካታ ውስብስብ ፈተናዎች ታልፈው ለዛሬው አንፀባራቂ የብልፅግና ጉዞ ላይ ለመገኘት እንደተቻለና ለነገዋ ኢትዮጵያ ልዕልና በ7/24 እየተሠራ እንደሚገኝ በሰነዱ ተብራርቷል።
የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ ባለፉት የለዉጥ ዓመታት ጉዞ ሀገራችንን በከፍታ ማማ የሚያስቀምጡ በርካታ ውጤቶች የተገኙበት የመጋቢት ፍሬዎችን በአግባቡ ማስገንዘብ አስፈላጊ መሆኑን ተጠቅሷል።
በውይይቱ አመራርና አባላት ባለፉት ዓመታት ፓርቲው ያሳካቸው ውጥኖችና በቀጣይ በትኩረት መሰራት አለበት ባሉት ሃሳቦች ላይ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
በዕለቱ ለተነሱ ሃሳብና አስተያየቶች በልዩ ወረዳው አመራሮች ምላሽና ማብሪሪያ በመስጠቱ መድረኩ ተጠናቋል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
18/07/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
በአዲስ አበባ ከተማ ብልፅግና ፖርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፐፕሊክና የፍትህ ልዩ ወረዳ 'ትናንት ፣ ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና!' በሚል መሪ ቃል ባለፉት 7 አመታት ከመጋቢት እስከ መጋቢት በተከናወኑ ተግባራትና የተገኙ ስኬቶች በተመለከተ ውይይት ተካሄደ።
በውይይቱ የአዲስ አበባ ከተማ የፐብሊክ ሰርቪስ፣ የፍትህ፣የሠላምና ፀጥታ ቢሮ እና የደንብ ማስከበር ባለስልጣን አመራሮችና አባላቶች ተገኝተዋል።
የመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የልዩ ወረዳው ሰብሳቢ አቶ አሰፋ መብራቴ ከሰባት ዓመት በፊት ሃገሪቱ የነበረችበት ከፓለቲካና ከኢኮኖሚ አዙሪትና መሠረታዊ የሆነ ለውጥ ለማምጣት የተጓዘችበትን እርቀት የምናስታውስበት እንዲሁም የቀጣይ ስራችንን የምናጠናክርበት መሆኑ ገልጸዋል።
በመድረኩ የአዲስ አበባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ የአገልግሎት አሰጣጥና አውት ሶርሲንግ ዘርፍ ኃላፊ አቶ በቀለ ተመስገንአቶ ፓርቲው ባለፉት ሰባት ዓመታት ያፀናቸውን ለውጦችና የተመለከተ የውይይት መነሻ ሰነድ አቅርበዋል።
በሂደቱም የፓለቲካ ለውጥ፣ በኢኮኖሚው ላይ የተደረገው ማሻሻ፣ የተቋማት ሪፎርም እና የዲፕሎማሲው ቱሩፋቶች አበይት የሰባት ዓመቱ የለውጥ ሂደቶች እንደነበር በሰነዱ ተገልጿል።
የሪፍርምና የስርዓት ለውጥ በማምጣት አካታች የሆነ የፓለቲካ ምህዋርን ለማፅናት በርካታ ውስብስብ ፈተናዎች ታልፈው ለዛሬው አንፀባራቂ የብልፅግና ጉዞ ላይ ለመገኘት እንደተቻለና ለነገዋ ኢትዮጵያ ልዕልና በ7/24 እየተሠራ እንደሚገኝ በሰነዱ ተብራርቷል።
የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ ባለፉት የለዉጥ ዓመታት ጉዞ ሀገራችንን በከፍታ ማማ የሚያስቀምጡ በርካታ ውጤቶች የተገኙበት የመጋቢት ፍሬዎችን በአግባቡ ማስገንዘብ አስፈላጊ መሆኑን ተጠቅሷል።
በውይይቱ አመራርና አባላት ባለፉት ዓመታት ፓርቲው ያሳካቸው ውጥኖችና በቀጣይ በትኩረት መሰራት አለበት ባሉት ሃሳቦች ላይ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
በዕለቱ ለተነሱ ሃሳብና አስተያየቶች በልዩ ወረዳው አመራሮች ምላሽና ማብሪሪያ በመስጠቱ መድረኩ ተጠናቋል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ባለስልጣኑ መጪው የኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ውይይት አካሄደ ።
19-07 -2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን በቀጣይ የሚከበረውን የኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም ተከብሮ እንዲጠነቀቅ የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ከክ/ከተማ የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች ጋር ውይይት አካሂዷል።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በዓሉን አስመልክቶ ሊያጋጥሙ የሚችሉ የፀጥታ፣የህገወጥ እርዶችንና ሌሎች የደንብ መተላለፎች እንዳይከሰቱ ከወዲሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ማድረግ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
አክለውም በዓሉ በሚከበርበት ወቅት በከተማዋ ላይ የተሰሩትን የኮሪደር መሠሰተ ልማቶች እንዳይበላሹ ህብረተሰቡ የበኩሉን አስተዋጽኦ በማድረግ ከደንብ ማስከበር ኦፊሰሮች ጋር በመቀናጀት ከተማችንን ጽዱ እና ውብ እንድትሆን መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል ።
ለውይይት መነሻ የተዘጋጀው ሰነድ የባለስልጣኑ የደንብ መተላለፍ ክትትል ፣ቁጥጥር እና እርምጃ አወሳሰድ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ግሩም ወ/መስቀል አቅርበው ሰፊ ውይይት ተካሂዷል ።
በመድረኩ በዓሉ ያለምንም የጸጥታ ችግር በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅና በበዓሉን አስመልክቶ አላሰፈላጊ የዋጋ ጭማሪ እንዳይኖርና የግባእት እጥረት እንዳያጋጥም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት መስራት እንደሚያስፈልግ መልዕክት አስተላልፈዋል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ዳሬክቶሬት ነው፡፡
19-07 -2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን በቀጣይ የሚከበረውን የኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም ተከብሮ እንዲጠነቀቅ የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ከክ/ከተማ የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች ጋር ውይይት አካሂዷል።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በዓሉን አስመልክቶ ሊያጋጥሙ የሚችሉ የፀጥታ፣የህገወጥ እርዶችንና ሌሎች የደንብ መተላለፎች እንዳይከሰቱ ከወዲሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ማድረግ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
አክለውም በዓሉ በሚከበርበት ወቅት በከተማዋ ላይ የተሰሩትን የኮሪደር መሠሰተ ልማቶች እንዳይበላሹ ህብረተሰቡ የበኩሉን አስተዋጽኦ በማድረግ ከደንብ ማስከበር ኦፊሰሮች ጋር በመቀናጀት ከተማችንን ጽዱ እና ውብ እንድትሆን መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል ።
ለውይይት መነሻ የተዘጋጀው ሰነድ የባለስልጣኑ የደንብ መተላለፍ ክትትል ፣ቁጥጥር እና እርምጃ አወሳሰድ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ግሩም ወ/መስቀል አቅርበው ሰፊ ውይይት ተካሂዷል ።
በመድረኩ በዓሉ ያለምንም የጸጥታ ችግር በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅና በበዓሉን አስመልክቶ አላሰፈላጊ የዋጋ ጭማሪ እንዳይኖርና የግባእት እጥረት እንዳያጋጥም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት መስራት እንደሚያስፈልግ መልዕክት አስተላልፈዋል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ዳሬክቶሬት ነው፡፡