ባለስልጣኑ ወንዞችና የወንዞች ዳርቻ የበከሉ ድርጅቶችና ግለሰቦችን 4,289,000/ አራት ሚሊየን ሁለት መቶ ሰማኒያ ዘጠኝ ሺህ/ ብር መቅጣቱ አስታወቀ
11/07/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣ ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር ወንዞችና የወንዞች ዳርቻ የበከሉ ድርጅቶችና ግለሰቦችን በዛሬው እለትም በደንብ ቁጥር 180/2017 መሰረት በድምሩ 4,289,000/ አራት ሚሊየን ሁለት መቶ ሰማኒያ ዘጠኝ ሺህ/ ብር የገንዘብ ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ፡፡
ባለስልጣኑ በዛሬው እለት በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ 1,315,000 ብር፤ በአቃቂ ክ/ከተማ 800,000 ብር ፤በየካ ክፍለ ከተማ 600,000
ብር፤በቦሌ ክፍለ ከተማ 600,000 ብር፣ በአራዳ ክፍለ ከተማ 500,000
ብር ቅጣት ተቀጥቷል።
በተያያዘ ዜና በጉለሌ ክፍለ ከተማ 254,000 ብር ፤በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ
170,000 ብር እና በኮልፌ ክፍለ ከተማ 50,000 ብር ቅጣት በመቅጣት ለመንግስት ገቢ ተደርጓል፡፡
ባለስልጣኑ በዛሬው እለት በአጠቃላይ 14 ድርጅቶች እና 22 ግለሰቦች በድምሩ 4,289,000/ አራት ሚሊየን ሁለት መቶ ሰማኒያ ዘጠኝ ሺህ/ብር ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ወስዷል።
ባለስልጣኑ ወንወዞችና የወንዞች ዳርቻ እንዳይበከሉ ለድርጅቶችና ለግለሰቦች በደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ሰፊ የግንዛቤ ስራ መስራቱ የገለጸ ሲሆን ህግ የማስከበሩ ስራ አጠናክሮ አንደሚቀጥል አስታውቋል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
11/07/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣ ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር ወንዞችና የወንዞች ዳርቻ የበከሉ ድርጅቶችና ግለሰቦችን በዛሬው እለትም በደንብ ቁጥር 180/2017 መሰረት በድምሩ 4,289,000/ አራት ሚሊየን ሁለት መቶ ሰማኒያ ዘጠኝ ሺህ/ ብር የገንዘብ ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ፡፡
ባለስልጣኑ በዛሬው እለት በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ 1,315,000 ብር፤ በአቃቂ ክ/ከተማ 800,000 ብር ፤በየካ ክፍለ ከተማ 600,000
ብር፤በቦሌ ክፍለ ከተማ 600,000 ብር፣ በአራዳ ክፍለ ከተማ 500,000
ብር ቅጣት ተቀጥቷል።
በተያያዘ ዜና በጉለሌ ክፍለ ከተማ 254,000 ብር ፤በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ
170,000 ብር እና በኮልፌ ክፍለ ከተማ 50,000 ብር ቅጣት በመቅጣት ለመንግስት ገቢ ተደርጓል፡፡
ባለስልጣኑ በዛሬው እለት በአጠቃላይ 14 ድርጅቶች እና 22 ግለሰቦች በድምሩ 4,289,000/ አራት ሚሊየን ሁለት መቶ ሰማኒያ ዘጠኝ ሺህ/ብር ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ወስዷል።
ባለስልጣኑ ወንወዞችና የወንዞች ዳርቻ እንዳይበከሉ ለድርጅቶችና ለግለሰቦች በደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ሰፊ የግንዛቤ ስራ መስራቱ የገለጸ ሲሆን ህግ የማስከበሩ ስራ አጠናክሮ አንደሚቀጥል አስታውቋል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍12❤2
ሕብረተሰቡ የተቋሙን ስም ለማጠልሸት የሚንቀሳቀሱ ህገ-ወጦችን እንዲያወግዝ ጥሪ ቀረበ
12/07/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በከተማ አስተዳደሩ የተሰጠውን ተልኮ ለማስፈፀም ከሌሎች ባለድርሻ ተቋማት ጋር ተቀናጅቶ በመስራት ተጨባጭ የሆነ ለውጥን በማስመዝገብ ላይ ይገኛል፡፡
ባለስልጣኑ ለህብረተሰቡ ጥቅም ሲባል የሚወጡ ደንቦችን አስቀድሞ ግንዛቤ እያስጨበጠ፤ ሆን ብሎ ደንቡን ተላልፎ በሚገኝ ማንኛውም አካል ላይ አስተዳደራዊ እርምጃዎችን በመውሰድ የደንብ መተላለፍን በመከላከል ላይ ይገኛል፡፡
በዛሬውም ዕለት የተቋሙ ያልሆነ የደንብ ልብስ በመልበስ የሱቅ ማስታወቂያ ሰርተው በማህበራዊ ሚዲያ ያሰራጩ ተጠርጣሪ ግለሰቦችን የአዲስ አበባ ፖሊስ በቁጥጥር ስር እንዲውሉ በማድረግ ተጨማሪ ምርመራ እያካሄደ በመሆኑ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ታላቅ ምስጋናውን ያቀርባል፡፡
ሆኖም ተጠርጣሪዎቹ የለበሱት ዩኒፎርም የቀድሞውንም ሆነ የአሁኑን የተቋሙን የደንብ ልብስና ሎጎ የማይወክል መሆኑን ባለስልጣኑ ያስታውቃል፡፡
ህብረተሰቡም ማንኛውም የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ደንብ አስከባሪ የሆነ ኦፊሰር የተቋሙን ሎጎ ያለበት ዪኒፎርም በመልበስ ደንብ የሚያስከብር መሆኑን በመገንዘብ ህገ ወጥ ግለሰቦች ከሚያደርጉት ማጭበርበር እራሱን እንዲጠብቅ መልዕክት አስተላልፏል።
ባለስልጣኑ ሕብረተሰቡ የተቋሙን ስም ለማጠልሸት የሚንቀሳቀሱ ህገ-ወጦችን እንዲያወግዝ ጥሪ የቀረበ ሲሆን ማንኛውም የሚያጠራጥር ጉዳይ ሲያጋጥመው በ9995 ነፃ የስልክ መስመር እና በክፍለ ከተማና ወረዳ በሚገኝ መዋቅር የደንብ ጽ/ቤት በአካል በመገኘት ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን ያቀርባል፡፡
የአዲስ አበበ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
12/07/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በከተማ አስተዳደሩ የተሰጠውን ተልኮ ለማስፈፀም ከሌሎች ባለድርሻ ተቋማት ጋር ተቀናጅቶ በመስራት ተጨባጭ የሆነ ለውጥን በማስመዝገብ ላይ ይገኛል፡፡
ባለስልጣኑ ለህብረተሰቡ ጥቅም ሲባል የሚወጡ ደንቦችን አስቀድሞ ግንዛቤ እያስጨበጠ፤ ሆን ብሎ ደንቡን ተላልፎ በሚገኝ ማንኛውም አካል ላይ አስተዳደራዊ እርምጃዎችን በመውሰድ የደንብ መተላለፍን በመከላከል ላይ ይገኛል፡፡
በዛሬውም ዕለት የተቋሙ ያልሆነ የደንብ ልብስ በመልበስ የሱቅ ማስታወቂያ ሰርተው በማህበራዊ ሚዲያ ያሰራጩ ተጠርጣሪ ግለሰቦችን የአዲስ አበባ ፖሊስ በቁጥጥር ስር እንዲውሉ በማድረግ ተጨማሪ ምርመራ እያካሄደ በመሆኑ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ታላቅ ምስጋናውን ያቀርባል፡፡
ሆኖም ተጠርጣሪዎቹ የለበሱት ዩኒፎርም የቀድሞውንም ሆነ የአሁኑን የተቋሙን የደንብ ልብስና ሎጎ የማይወክል መሆኑን ባለስልጣኑ ያስታውቃል፡፡
ህብረተሰቡም ማንኛውም የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ደንብ አስከባሪ የሆነ ኦፊሰር የተቋሙን ሎጎ ያለበት ዪኒፎርም በመልበስ ደንብ የሚያስከብር መሆኑን በመገንዘብ ህገ ወጥ ግለሰቦች ከሚያደርጉት ማጭበርበር እራሱን እንዲጠብቅ መልዕክት አስተላልፏል።
ባለስልጣኑ ሕብረተሰቡ የተቋሙን ስም ለማጠልሸት የሚንቀሳቀሱ ህገ-ወጦችን እንዲያወግዝ ጥሪ የቀረበ ሲሆን ማንኛውም የሚያጠራጥር ጉዳይ ሲያጋጥመው በ9995 ነፃ የስልክ መስመር እና በክፍለ ከተማና ወረዳ በሚገኝ መዋቅር የደንብ ጽ/ቤት በአካል በመገኘት ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን ያቀርባል፡፡
የአዲስ አበበ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
👍5
ለተጨማሪ መረጃ፦
የሶሻል ሚዲያ ገፆቻችን ፎሎው፣ላይክ እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
ዌብሳይት ገፃችን፦
https://www.aacea.gov.et/
የፌስ ቡክ ገፃችን፦
https://www.facebook.com/profile.php?id=100082525711518&mibextid
የቲክቶክ አካውንታችን
https://www.tiktok.com/@addisababacodeenforcemen
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/codeenforcement
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/@A.A.C.ACODEENFORCEMENT
የሶሻል ሚዲያ ገፆቻችን ፎሎው፣ላይክ እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
ዌብሳይት ገፃችን፦
https://www.aacea.gov.et/
የፌስ ቡክ ገፃችን፦
https://www.facebook.com/profile.php?id=100082525711518&mibextid
የቲክቶክ አካውንታችን
https://www.tiktok.com/@addisababacodeenforcemen
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/codeenforcement
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/@A.A.C.ACODEENFORCEMENT
www.aacea.gov.et
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን | Home Page
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን 74/2014 ዓ.ም በአንቀጽ 47 መሰረት ተጨማሪ ተግባርና ኃላፊነት ተሰጥቶት ባለስልጣን ሆኖ የተቋቋመ ሲሆን አዋጅ ቁጥር 74/2014 መሰረት በማድረግ ባለስልጣኑ ደንብ ቁጥር 150/2015 በም/ቤት በማጸደቅ እና መዋቅራዊ ክለሳ በማድረግ ተመሠረተ።
ስነምግባር በተላበሰ መልኩ አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ ተገለፀ
12/07/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ለአራዳ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች "ስነ-ምግባርና መልካም አስተዳደር ለተሻለ አገልግሎት አሰጣጥ" በሚል መሪ ቃል የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በክ/ከተማው አዳራሽ ሰጠ።
ስልጠናውን የሰጡት የባለስልጣኑ የስነምግባርና ጸረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዬብ ከበደ የስነምግባርና ብልሹ አሰራር ችግር ለተቋማችን ገጽታ ግንባታ ላይ የሚያሳድረውን ተጽዕኖ በመገንዘብ በዚህ ድርጊት በሚሳተፉ ላይ ጠንካራ የተጠያቂነት ስርዓት በመዘርጋትና በመከላከል ሁሉም አካል ብልሹ አሰራርን ሊጸየፍና ሊታገል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ስነ-ምግባር ለመልካም አስተዳደር መስፈን ያለዉ ፋይዳ የላቀ በመሆኑ ፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ለሌሎች አርኣያ የሚሆን ስነ ምግባር በተላበሰ መልኩ አገልግሎቶችን መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አቶ እዮብ ገልጸዋል ።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የአራዳ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ ሻምበል ኑርልኝ ገ/ኪዳን ኦፊሰሩ ከብልሹ አሠራር እራሱን በመጠበቅ የተሰጠዉን ተልዕኮ በአግባቡ መወጣትና ከዳር ማድረስ እንዳለበት ገልጸዋል።
በመድረኩም ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች ምላሽና አስተያየት ተሰጥቶበታል።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
12/07/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ለአራዳ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች "ስነ-ምግባርና መልካም አስተዳደር ለተሻለ አገልግሎት አሰጣጥ" በሚል መሪ ቃል የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በክ/ከተማው አዳራሽ ሰጠ።
ስልጠናውን የሰጡት የባለስልጣኑ የስነምግባርና ጸረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዬብ ከበደ የስነምግባርና ብልሹ አሰራር ችግር ለተቋማችን ገጽታ ግንባታ ላይ የሚያሳድረውን ተጽዕኖ በመገንዘብ በዚህ ድርጊት በሚሳተፉ ላይ ጠንካራ የተጠያቂነት ስርዓት በመዘርጋትና በመከላከል ሁሉም አካል ብልሹ አሰራርን ሊጸየፍና ሊታገል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ስነ-ምግባር ለመልካም አስተዳደር መስፈን ያለዉ ፋይዳ የላቀ በመሆኑ ፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ለሌሎች አርኣያ የሚሆን ስነ ምግባር በተላበሰ መልኩ አገልግሎቶችን መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አቶ እዮብ ገልጸዋል ።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የአራዳ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ ሻምበል ኑርልኝ ገ/ኪዳን ኦፊሰሩ ከብልሹ አሠራር እራሱን በመጠበቅ የተሰጠዉን ተልዕኮ በአግባቡ መወጣትና ከዳር ማድረስ እንዳለበት ገልጸዋል።
በመድረኩም ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች ምላሽና አስተያየት ተሰጥቶበታል።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
👍12
ባለስልጣኑ በካሳንቺስ አካባቢ የተሰራው አዲስ የኮሪደር ልማት በግዴለሽነት ጉዳት ያደረሰው ድርጅት 510 ሺህ ብር መቅጣቱ ገለፀ
15/07/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በካዛንቺስ የኮሪደር ልማት አዲስ በተሰራው የመንገድ መሠረተ ልማት ሜልኮን ኮንስትራክሽን የተባለ ድርጅት ኃላፊነት በጎደለው ሁኔታ ጉዳት ያደረሰው ድርጅቱ 500 ሺህ ብር እና ሁለት ሹፌሮች እያንዳንዳቸው 5 ሺህ ብር በድምሩ 510,000 ብር መቅጣቱ ገለፀ።
ድርጅቱ በቸልተኝነት የተሰራው የእግረኞች መንገድ ኮንክሪት ስታምፕ በማውደሙ ለፈጸመው ግዴየለሽነት ተግባር የገንዘብ ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዶበታል፡፡
ባለስልጣኑ ድርጅቱ ከገንዘብ ቅጣቱ በተጨማሪ ያወደመውን የእግረኞች መንገድ ከተቀጣበት ሰዓት ጀምሮ በራሱ ወጪ በመገንባት እንዲያስተካክል ውሳኔ የተሰጠው መሆኑንም አሳውቋል።
ህግ በማስከበሩ ሂደት የከተማ አስተዳደሩ አዲስ አበባን እንደ ስሟ አበባ በማድረግ የአፍሪካ ብልጽግና ማዕከል ለማድረግ ቀንና ሌሊት በሚሰራበት በዚህ ሰዓት እንደዚህ አይነት ተግባር መፈፀም አሳፊሪ መሆኑ ተገልጿል።
ባለስልጣኑ በከተማው በልማት ስራ የተሰማሩ ድርጅቶችና ግለሰቦች መሠል ድርጊቶች ከመፈጸም እንዲቆጠቡ እያሳሰበ ደንብ በሚተላለፉት ላይ ደንብ የማስከበሩ ስራ ተጠናክሮ አንደሚቀጥል አስታውቋል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
15/07/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በካዛንቺስ የኮሪደር ልማት አዲስ በተሰራው የመንገድ መሠረተ ልማት ሜልኮን ኮንስትራክሽን የተባለ ድርጅት ኃላፊነት በጎደለው ሁኔታ ጉዳት ያደረሰው ድርጅቱ 500 ሺህ ብር እና ሁለት ሹፌሮች እያንዳንዳቸው 5 ሺህ ብር በድምሩ 510,000 ብር መቅጣቱ ገለፀ።
ድርጅቱ በቸልተኝነት የተሰራው የእግረኞች መንገድ ኮንክሪት ስታምፕ በማውደሙ ለፈጸመው ግዴየለሽነት ተግባር የገንዘብ ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዶበታል፡፡
ባለስልጣኑ ድርጅቱ ከገንዘብ ቅጣቱ በተጨማሪ ያወደመውን የእግረኞች መንገድ ከተቀጣበት ሰዓት ጀምሮ በራሱ ወጪ በመገንባት እንዲያስተካክል ውሳኔ የተሰጠው መሆኑንም አሳውቋል።
ህግ በማስከበሩ ሂደት የከተማ አስተዳደሩ አዲስ አበባን እንደ ስሟ አበባ በማድረግ የአፍሪካ ብልጽግና ማዕከል ለማድረግ ቀንና ሌሊት በሚሰራበት በዚህ ሰዓት እንደዚህ አይነት ተግባር መፈፀም አሳፊሪ መሆኑ ተገልጿል።
ባለስልጣኑ በከተማው በልማት ስራ የተሰማሩ ድርጅቶችና ግለሰቦች መሠል ድርጊቶች ከመፈጸም እንዲቆጠቡ እያሳሰበ ደንብ በሚተላለፉት ላይ ደንብ የማስከበሩ ስራ ተጠናክሮ አንደሚቀጥል አስታውቋል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍12