Christ-centered
1.62K subscribers
18 photos
7 videos
13 files
3 links
​ጤናማ አስተምህሮ ለበሰለ ህይወት መሰረት ነው።
​እውነት ለአእምሮ፣ ጸጋም ለልብ ብርሃን ነው።
Download Telegram
በሕይወት ጉዞዬ ላይ ማዕበሉ ቢበረታ፣ መንገዱ ቢጠብብ፣ እና በምንም ነገር ውስጥ ባልፍ እንኳ በአንድ ነገር እርግጠኛ ነኝ፦
እግዚአብሔር ያበረታኛል፣
እግዚአብሔር ያጽናናኛል፣
እግዚአብሔር ይጠብቀኛል።
የልቤ ስብራት
ሳይሆን፤ የእግዚአብሔር ታማኝነት ታሪኬን ይጽፈዋል።

“እግዚአብሔር ልባቸው ለተሰበረ ቅርብ ነው፥ መንፈሳቸው የተሰበረውንም ያድናቸዋል።”
  — መዝሙር 34፥18

ስለዚህ ዛሬም ሆነ ነገ በምንም ውስጥ ባልፍ፣ የታሪኬ ብዕር ያለው በታማኙ አምላኬ እጅ ስለሆነ የወደፊቱ ሕይወቴ በምስጋናና በድል የተሞላ መሆኑን ሙሉ በሙሉ አምናለሁ!
🙏246👍1🔥1
በገዛ ሥጋዊ ጥረታችንና አቅማችን ኃጢአትን ለማሸነፍና ጽድቅን ለመገንባት መሞከር፣ በገዛ እጃችን አየሩን ጨብጠን ወደ ላይ ለመውጣት የመታገል ያህል ከንቱና ባዶ ስራ ነው። እውነተኛና ዘላቂ የሕይወት ለውጥ የሚጀምረው ከመለኮታዊው የመንፈስ ቅዱስ ስራ ነው።

​መንፈስ ቅዱስ በልባችን ውስጥ ሲሰፍን፣ በመንፈሳዊ ሁኔታ የሞተውን ልባችንን ሕያው ያደርገዋል፤ ለጽድቅ ሕይወት የሚሆን መለኮታዊ ፍላጎትንና የማድረግን አቅምም ይተክላል። እርሱ አሮጌውን በደልና የኃጢአት አኗኗር ደረጃ በደረጃ እያቃጠለና እያደከመ፣ እኛንም በዕለት ተዕለት የቅድስና ሂደት (Sanctification) ወደ ክርስቶስ መልክ የሚለውጥ መለኮታዊ እሳት ነው።

​ይህ የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ግን ለስንፍና ወይም ዝም ብሎ ለመቀመጥ የሚሰጥ ሳይሆን፣ በመንፈሱ ታዝዘንና ተደግፈን ከኃጢአት ጋር እንድንታገል፣ ቅድስናንም በትጋት እንድንከታተል የሚያስችለን መለኮታዊ ሞተር ነው።

"አዲስም ልብ እሰጣችኋለሁ አዲስም መንፈስ በውስጣችሁ አኖራለሁ፤ የድንጋዩንም ልብ ከሥጋችሁ አወጣለሁ የሥጋንም ልብ እሰጣችኋለሁ። መንፈሴንም በውስጣችሁ አኖራለሁ በትእዛዜም አስሄዳችኋለሁ፥ ፍርዴንም ትጠብቃላችሁ ታደርጉትማላችሁ።"
(ሕዝቅኤል 36፥26-27)
18🥰8
መጽሐፍ ቅዱስን በነገረ መለኮት ወይስ ነገረ መለኮትን በመጽሐፍ ቅዱስ?

​የክርስትና እምነትና ትምህርት የመጨረሻና የበላይ ባለሥልጣን እግዚአብሔር በመንፈሱ መሪነት ያስጻፈው ቅዱስ ቃል ብቻ ነው (Sola Scriptura)። ጤናማ ነገረ መለኮት (sound theology) የእግዚአብሔርን ቃል በጥበብ ለመረዳትና ለማደራጀት የሚረዳ መሣሪያ እንጂ፣ ከተሳሳተ ቅድመ-ግምት በመነሳት መጽሐፍ ቅዱስን አጥምዞ የራሱ ባሪያ የሚያደርግ ገዥ መነጽር ሊሆን አይገባም።
መጽሐፍ ቅዱስን በተጣመመ ነገረ መለኮታዊ መነጽር ከማንበብ ይልቅ፣ ነገረ መለኮትን ሁልጊዜም በመጽሐፍ ቅዱስ መነጽር መመዘንና ማረም እጅግ አስፈላጊ ነው።

የትርጓሜ አቅጣጫ፡ Exegesis vs Eisegesis
​መጽሐፍ ቅዱስን በተጫነ ወይም ቅድመ-ግምት ባለው ነገረ መለኮታዊ መነጽር ብቻ ማንበብ አብዛኛውን ጊዜ ወደ Eisegesis ያመራል። ይህም ማለት ቀድመን ያዘጋጀነውን አስተሳሰብ፣ የቤተ እምነት አስተምህሮ ወይም የፍልስፍና መዋቅር ወደ ጽሑፉ በመውሰድ መጽሐፍ ቅዱስ ያላላቸውን ነገሮች እንዲናገር ማስገደድ ነው።

​በተቃራኒው ነገረ መለኮታችንን በመጽሐፍ ቅዱስ መነጽር መመዘን ደግሞ ወደ Exegesis ያመራል። ይህም ከጽሑፉ አውድ፣ ታሪካዊ አመጣጥና የመጀመሪያ መልእክት ተነስተን እውነቱን ማውጣትና የሰዎችን ትምህርት በዚያ ሚዛን መመዘን ነው። በተጨማሪም በስነ-ትርጓሜ መርህ መሠረት "መጽሐፍ ቅዱስ ራሱን በራሱ ይተረጉማል" (Scripture interprets Scripture)፤ በመሆኑም ግልጽ ያልሆኑ ክፍሎችን ግልጽ በሆኑት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች እያበሩ መረዳት የእውነተኛ ነገረ መለኮት መሠረት ነው።

​የሰው ልጅ ነገረ መለኮታዊ ድምዳሜዎች ሁልጊዜም በባህል፣ በዘመንና በቋንቋ ውስንነቶች ሊቃኙ ይችላሉ፤ የእግዚአብሔር ቃል ግን አይለወጥም። ስለዚህ የትኛውም አስተምህሮ ትክክለኛነት የመጨረሻ ዳኛ መሆን ያለበት መጽሐፍ ቅዱስ እንጂ የሰው ነገረ መለኮት አይደለም።

የቀደሙት የቤተ ክርስቲያን አበቶች ምስክርነት
​የቀደሙት የቤተ ክርስቲያን አበቶች ትምህርቶቻቸው ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር የመስማማታቸውን አስፈላጊነት በተደጋጋሚ አስምረውበታል። አበቶች ነገረ መለኮትን ከመጽሐፍ ቅዱስ አውጥተው ከተረዱ በኋላ፣ ማንኛውንም ተፎካካሪና ስሕተት ትምህርት በቅዱሳት መጻሕፍት ሚዛን ይመዝኑት ነበር፦
👉ቅዱስ አትናቴዎስ፦ የአርዮስን የስሕተት ትምህርት በተጋደለበት ወቅት የተጠቀመው ዋነኛ መሣሪያ ቅዱሳት መጻሕፍትን ነበር። በአንዱ መልእክቱ ላይ፡ "ቅዱሳትና መንፈሳውያን መጻሕፍት እውነትን ለማስታወቅ በቂ ናቸው" በማለት መጽሐፍ ቅዱስ የሁሉም ትምህርቶች መፈተሻ ሚዛን መሆኑን አሳይቷል።

👉ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፦ ምእመናን መጽሐፍ ቅዱስን በራሳቸው እንዲመረምሩና ትምህርቶችን እንዲመዝኑ ያበረታታ ነበር። በሐዋርያት ሥራ ስብከቱ ላይ፡ "ማንኛውም ሰው ወደ እናንተ መጥቶ ትምህርት ቢያስተምራችሁ፣ መጽሐፍ ቅዱስን እንደ ሚዛን ተጠቀሙ። ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር የሚስማማውን ተቀበሉ፤ የማይስማማውን ግን አውጥታችሁ ጣሉ" በማለት አስተምሯል።

👉ቅዱስ አውግስጢኖስ፦ ከቅዱሳት መጻሕፍት ውጭ ያሉ የነገረ መለኮት ጽሑፎችንና የራሱንም ጽሑፎች ጨምሮ እንዴት ማየት እንደሚገባ ሲናገር፡ "የእኔንም ሆነ የሌሎችን ጽሑፎች ከቅዱሳት መጻሕፍት ጋር እኩል አታዩ። በእኔ ጽሑፍ ውስጥ ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር የማይስማማ ነገር ካገኛችሁ አትቀበሉት፤ ቅዱሳት መጻሕፍትን ብቻ እንደ ታማኝ እውነት ያዙት" ብሏል።

👉ቅዱስ ሄሬኔዎስ፦ የሁለተኛው ክፍለ ዘመን አባት ሄሬኔዎስ ከእውነተኛው የሐዋርያት ትምህርት የወጡ ግኖስቲኮችን (Gnostics) ሲሞግት፣ መጽሐፍ ቅዱስን አጣሞ ከመተርጎም ይልቅ የቃሉን ተፈጥሮአዊ አውድ መጠበቅ እንደሚገባ አሳይቷል። እሱ እንደሚለው፣ እውነተኛ ነገረ መለኮት ከመጽሐፍ ቅዱስ አጠቃላይ መልእክት ጋር የሚስማማ እንጂ የሚቃረን ሊሆን አይችልም።

👉የቤርያ ሰዎች አርአያነት
​በሐዋርያት ሥራ 17:11 ላይ የተጠቀሱት የቤርያ ሰዎች ትልቅ ምሳሌ ናቸው። ሐዋርያው ጳውሎስ አዲስ ነገረ መለኮትና የክርስቶስን ወንጌል ይዞላቸው የመጣ ቢሆንም፣ እነሱ ግን፡ ነገሩ እንደዚሁ ይሆንን? ብለው ዕለት ዕለት መጻሕፍትን እየመረመሩ ቃሉን በሙሉ ፈቃድ ተቀበሉ” ይላል። ታላቁ ሐዋርያው ጳውሎስ እንኳ ሲያስተምር ትምህርቱን በመጽሐፍ ቅዱስ መነጽር መመዘናቸውን አላቆሙም፤ መጽሐፍ ቅዱስም ይህን ተግባራቸውን "ልበ ሰፊዎች" በማለት አሞግሶታል።

ነገረ መለኮትን በመጽሐፍ ቅዱስ መነጽር የመመዘን ጥቅሞች
👉ከሰዎች ባህልና ፍልስፍና ይጠብቃል፦ ነገረ መለኮት አንዳንዴ በዘመኑ ፍልስፍና ሊበከል ይችላል። መጽሐፍ ቅዱስ ግን የነገረ መለኮቱን ንጽሕና ለመጠበቅ ማጣሪያ ይሆናል።
👉ትሕትናን ያጎናጽፋል፦ ነገረ መለኮታችንን ከቅዱስ ቃል በታች ስናደርግ፣ እግዚአብሔር ከእኛ ሥርዓትና አስተሳሰብ በላይ እንደሆነ እንረዳለን።
👉የእምነት አንድነትን ይፈጥራል፦ ሰዎች የራሳቸውን ነገረ መለኮታዊ ድምዳሜዎች የበላይ ሲያደርጉ መለያየት ይፈጠራል፤ ሁላችንም ወደ ቅዱስ ቃሉ የበላይነት ስንመለስ ግን እውነተኛ አንድነት ይመጣል።

​ነገረ መለኮት የመጽሐፍ ቅዱስ ታማኝ አገልጋይና ማብራሪያ እንጂ የቃሉ ዳኛ ወይም መሪ ሊሆን አይችልም። የቀደሙት አበቶችና የሐዋርያት አስተምህሮ እንደሚያስረዳው፣ ማንኛውም ትምህርት፣ ሥርዓትና የነገረ መለኮት መዋቅር እውነተኛነቱና ተቀባይነቱ የሚረጋገጠው በእግዚአብሔር ቃል ሚዛን ሲመዘን ብቻ ነው።

@christcentered7
17💯5
ወዳጆቼ፣ እግዚአብሔር ያያል! 🥹

​አንዳንድ ጊዜ ሕይወት የሚጭንብን ፈተናና መከራ ከባድ ከመሆኑ የተነሣ ከአቅማችን በላይ ሊሆንብን ይችላል። የሚገጥመን ማዕበል አቅም የሚያሳጣ፣ በሩ ሁሉ የተዘጋና መውጫ የሌለው መስሎ ሊታየን ይችላል። "ለእኔስ ማን አለ? ይህስ መከራ መቼ ያልፋል?" እያልን የተስፋ መቁረጥ ስሜት በውስጣችን ሊመላለስ ይችላል።

​ነገር ግን በዚህ ሁሉ መካከል ልባችን በጽኑ ሊይዘው የሚገባ አንድ ትልቅና አጽናኝ መጽሐፍ ቅዱሳዊ እውነት አለ፦ እግዚአብሔር አያይም፣ አይመለከተኝም፣ አልሰማኝም ብላችሁ በጭራሽ እንዳታስቡ!
​እሱ በሰው ዘንድ የተሰወረውን፣ በምስጢር በውስጣችሁ የሚያለቅሰውን የሕመም እንባ፣ ማንም ያላየውንና ያልተረዳችሁን የልባችሁን ጥልቅ ጩኸት ሁሉ በግልጽ ያያል! ያደምጣልም!

​በራሳችሁ ጉልበት ልትወጡት ያልቻላችሁትን ድካምና ከባድ ሸክም፣ ጌታ ኢየሱስ "እናንተ ሸክም የከበዳችሁ ሁሉ ወደ እኔ ኑ፤ እኔም አሳርፋችኋለሁ" እንዳለ በታላቅ ኃይሉና በምሕረቱ ይሸከምላችኋል። ዓመታት የፈጀ፣ እኔነታችሁን የሚፈታተንና "እኔስ አልቻልኩም" ያላችሁ ማናቸውም ከባድ ሁኔታ በእግዚአብሔር ታላቅነትና ጸጋ ፊት ያንሰል።

ስለዚህ ወዳጆቼ፣ አይዟችሁ! የተጨነቀውንና የደከመው ልባችሁ በጌታ ፊት ይረፍ።

​እግዚአብሔር ዝም ብሎ አይመለከትም፤ በራሱ መልካም ጊዜና ፈቃድ ተዓምሩን ይሠራል፣ በፈተናው መካከል እንኳ ድልንና አጽናኝ ሰላሙን ይሰጣችኋል። እምነታችሁንና ሙሉ ተስፋችሁን በክርስቶስ ላይ ብቻ ጣሉ!

“የአባትህ የዳዊት አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ጸሎትህን ሰምቻለሁ፥ እንባህንም አይቻለሁ እነሆ፥ እፈውስሃለሁ፤”
  (2ኛ ነገሥት 20፥5)


እግዚአብሔር ያያል!🥹
🙏235😢3
ክርስትና የብቸኝነት ጉዞ አይደለም፤ እግዚአብሔር ሰውን የፈጠረውና ያዳነው ለኅብረት ነው። እንደ አንድ አካል ክፍሎች እርስ በእርስ ሳንደጋገፍ፣ በክርስቲያናዊ ህይወታችንና አገልግሎታችን ሙሉ ልንሆን አንችልም። እውነተኛ የአማኞች አንድነት የሚመጣው በጥቅም ወይም በዘር ሳይሆን፣ በክርስቶስ ደም በተመሠረተው መለኮታዊ ቃል-ኪዳን ነው። በአንድነት ስንቆም የጨለማውን ኃይል የሚያሸንፈው ታላቁ የመለኮት ኃይል በመካከላችን ይገለጣል።
24❤‍🔥3🔥3🤝2
ከሳምንቱ ድካም ይልቅ ከቅዱሳን ጋር የሚደረግ ህብረት ነፍስን ያድሳል፤ መንፈስንም ያረካል። ዛሬ ወደ አባታችን ቤት ጎራ ብለን በምስጋና፣ በጸሎትና በፍቅር የምንታደስበት ልዩ ቀን ነው። በህብረት ውስጥ ሰላም አለ፤ በህብረት ውስጥ በረከት አለ።

እንኪያስ ጉዟችንን ወደ ቅዱሳን ህብረት እናድርግ!
31💯8
Audio
አንነቃነቅም እንቆማለን
መሠረታችን ዓለት ነው
ዓለቱም ኢየሱስ ክንደ ብርቱ
16
ቅጥሬ አልፈረሰም መጠበቂያዬ
አለሁ ይለኛል ደጉ ጌታዬ
ቀና ብዬ ሳይ ቀለላት ነፍሴን
ፍቅሩ ስጠራኝ አየሁት እራሴን።
🎶 ደረጄ ከበደ🙏
22🥰5
የሰው ልጅ ታማኝነትና ውለታ እንደ ደመና ተለዋዋጭ ቢሆንም፣ የእግዚአብሔር ኪዳን ግን እንደ ዐለት የጸና ነው። እኛ በጉዞአችን ብንደክም፣ መንገዳችንም ቢጠባብ እንኳ፣ እርሱ ስለ ታላቅ ስሙና ስለ ታማኝነቱ ሲል በሕይወታችን የጀመረውን መልካም ሥራ በድል ይፈጽመዋል።

“በእናንተ መልካምን ሥራ የጀመረው እስከ ኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ድረስ እንዲፈጽመው ይህን ተረድቼአለሁና፤”
— ፊልጵስዩስ 1፥6

የሕይወታችንና የዘላለም መዳናችን ዋስትና የራሳችን ጥንካሬ ወይም መልካምነት ሳይሆን፣ በክርስቶስ ኢየሱስ የተገለጠው የማይለወጠው የእግዚአብሔር ታማኝነትና ጸጋ ብቻ ነው።

ይህ ደግሞ ብርታታችን ነው 🙏
❤‍🔥23🥰73🔥3🙏2
ኢየሱስ ክርስቶስ ማን ነው? ለሚለው መሠረታዊ ጥያቄ የቤተክርስቲያን ትልቁ መሠረት የእርሱ ፍጹም መለኮትነትና ፍጹም ሰውነት ነው።

​ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም አምላክ ፍጹምም ሰው ሆኖ ወደ ምድር የመጣው፣ ቅዱሱን አምላክና በኃጢአት ምክንያት ከእግዚአብሔር ተለይቶ የነበረውን ሰው በመስቀል ላይ በከፈለው መስዋዕትነት ለማስታረቅና ለማገናኘት ነው (1 ጢሞቴዎስ 2:5)።

👉 በሰውነቱ (ፍጹም ሰው) እንደ እኛ መከራን፣ ሕመምን፣ ፈተናንና ጭንቀትን የቀመሰ በመሆኑ አቅማችንንና የልባችንን ስብራት በደንብ ይረዳል (ዕብራውያን 2:18፤ 4:15)።
​ከኃጢአት በቀር በነገር ሁሉ እኛን መስሎ በመመላለሱ፣ በሕይወታችን የምናልፍበትን ማንኛውንም ፈተና የሚረዳ ርኅሩኅ ሊቀ ካህናችን ነው።

👉​ በአምላክነቱ (ፍጹም አምላክ) ደግሞ የኃጢአታችንን ዕዳ የመክፈል፣ የሞትንና የዲያብሎስን ሥልጣን የማሸነፍ፣ እንዲሁም ለተሰበረው ልባችን እውነተኛ ሰላምንና የዘላለም ሕይወትን የመስጠት ሙሉ ሥልጣን አለው (ቆላስይስ 2:9-10፤ ዮሐንስ 14:27)።

የልባችንን ስብራትና ጭንቀት የሚረዳ፣ በሰውነቱ መከራችንን የተካፈለ፣ በአምላክነቱ ደግሞ ከኃጢአትና ከጭንቀት እስራት ሊገላግለን የሚችል አንድ እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው። እርሱ የነፍሳችን አዳኝ፣ የታመነው ወዳጃችንና ብቸኛው መካከለኛችን ነው።
20🔥4👍2
Audio
አቤት እግዚአብሔር አርሱ አምላክ የሆነው
እንዴት ታደለ ምስጉን ሕዝብ ነው

  ጌጃ ቃለሕይወት መዘምራን
🔥17
በሕይወታችን ውስጥ ሁላችንም አልፎ አልፎ የኀዘን፣ የቁጭት እና የንስሐ ስሜቶች ያጋጥሙናል። ነገር ግን ሁሉም ኀዘን አንድ ዓይነት አይደለም፤ ፍሬውም ይለያያል።

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ሰዎች በላከው ሁለተኛ መልእክቱ ላይ፦
​“እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የሆነ ኀዘን ጸጸት የሌለበትን፥ ወደ መዳንም የሚያደርሰውን ንስሐ ያደርጋልና፤ የዓለም ኀዘን ግን ሞትን ያመጣል።”(2ኛ ቆሮንቶስ 7፥10)
​በማለት ሁለት መሠረታዊ የኀዘን ዓይነቶችን እና የሚያስከትሏቸውን ውጤቶች በግልጽ ያሳየናል።

​1. እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የሆነ ኀዘን (መንፈሳዊ ኀዘን)
​ይህ ዓይነቱ ኀዘን ሰው በራሱ ጥረት የሚያመጣው ሳይሆን፣ መንፈስ ቅዱስ በልባችን ውስጥ በሚሰራው የመታደስ ሥራ የሚሰጥ የእግዚአብሔር ነጻ ስጦታ ነው። ሰው ከእግዚአብሔር ጋር ያለው ግንኙነት በመበላሸቱ፣ በፍቅሩ ላይ በመበደሉ ወይም ሕጉን በመጣሱ ምክንያት በልቡ ውስጥ የሚሰማው ጥልቅ እውነተኛ የልብ ስብራት ነው።
👉​ባሕርዩም የራስን ጥፋት አምኖ መቀበልን፣ ትህትናን እና የመንፈስ ቅዱስን የልብ መታደስ ያመጣል።
👉​ውጤቱም የእውነተኛ መዳን እና የልብ መታደስ ፍሬ የሆነውን ንስሐን ያስገኛል። ንስሐ የመዳናችን ምክንያት ወይም ሥራ ሳይሆን፣ በክርስቶስ ኢየሱስ ላገኘነው ነጻ የመዳን ጸጋ የሚሰጥ ትክክለኛ የመንፈስ ቅዱስ ፍሬ ነው። የእግዚአብሔርን ይቅርታ እና ሰላም ስለሚያስገኝ በኋለኛው ጊዜ ምንም የሚያስጸጽት ነገር አይተውም።
👉ምሳሌ“ሐዋርያው ጴጥሮስ ጌታን ሶስት ጊዜ ከካደ በኋላ፣ ጌታ ኢየሱስ አስቀድሞ ስለ እምነቱ በጸለየለትና በሰጠው የመታደስ ጸጋ ምክንያት አልቅሶ ወደ ቀደመው አገልግሎቱና ፍቅሩ ተመለሰ (ማቴ. 26፥75፤ ሉቃ. 22፥32)።”

​2. የዓለም ኀዘን (ሥጋዊ ኀዘን)
​የዓለም ኀዘን የሚመነጨው ከትዕቢት፣ ከራስ ወዳድነት ወይም ደግሞ ጥፋት በመሰራቱ ከሚመጣው ውርደት እና ቅጣት ከመፍራት ነው።
👉​ባሕርዩም ሰዎች ምን ይሉኛል?፣ ስሜ ጠፋ፣ ወይም ጥቅሜ ቀረ ከሚል ስጋት የሚወለድ ነው፤ በኃጢአቱ የተነሳ እግዚአብሔርን በመበደሉ አይቆጭም።
👉​ውጤቱም ተስፋ መቁረጥን፣ ጭንቀትን፣ ምሬትን እና የመንፈስ ሞትን (አንዳንድ ጊዜም አካላዊ ሞትን) ያመጣል።
👉ምሳሌ፡ ይሁዳ ጌታን አሳልፎ ከሰጠ በኋላ ተጸጸተ፤ ነገር ግን ኀዘኑ እግዚአብሔርን ከማሳዘን የመነጨ ሳይሆን ከውርደት እና ከቅጣት ፍርሃት የመጣ የዓለም ኀዘን ስለነበረ፣ ወደ እግዚአብሔር ምሕረት ከመሮጥ ይልቅ ተስፋ ቆርጦ ራሱን ሰቀለ (ማቴ. 27፥3-5)።”

​ውድቀት ወይም ስህተት በገጠመን ጊዜ የሚሰማን ኀዘን ወደ የትኛው መንገድ እየመራን እንደሆነ ማስተዋል አለብን። ኀዘናችን ወደ እግዚአብሔር ምሕረት የሚያቀርበን ከሆነ የእውነተኛ መዳን እና የጸጋው ፍሬ ነው፤ ነገር ግን ወደ ተስፋ መቁረጥ እና ራሳችንን ወደ መኮነን የሚወስደን ከሆነ የዓለም ኀዘን መሆኑን አውቀን፣ ክርስቶስ በመስቀል ላይ በፈጸመው ሥራ ወደተከፈተልን ወደ እግዚአብሔር የጸጋ ዙፋን መሮጥ ይኖርብናል (ዕብ. 4፥16)።

​እግዚአብሔር የመንፈስ ቅዱስ ሥራ የሆነውን የተሰበረውን ልብ አይንቅም። መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚለው፦
​“የእግዚአብሔር መሥዋዕት የተሰበረ መንፈስ ነው፤ የተሰበረውንና የተዋረደውን ልብ እግዚአብሔር አይንቅም።”( መዝሙር 51፥17)
​በክርስቶስ ኢየሱስ የመስቀል ሥራ በተከፈተው መንገድ፣ ኀዘናችን በጸጸት የሚቀር ሳይሆን ወደ ትክክለኛ ንስሐና ወደ እግዚአብሔር እቅፍ የሚመልሰን መንፈሳዊ መንገድ እንዲሆን ሁልጊዜ የእግዚአብሔርን ጸጋና እርዳታ መጠየቅ ያስፈልጋል።

@christcentered7
❤‍🔥134👍2😭1
“በተሰጠንም በመንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ፍቅር በልባችን ስለ ፈሰሰ ተስፋ አያሳፍርም።”
  — ሮሜ 5፥5
22🥰7
ምድራዊ ሕይወታችን በእግዚአብሔር ሉዓላዊ ጸጋ ያገኘነውን የዘላለም ሕይወት፤ በቅድስናና ለእግዚአብሔር ክብር የምንገልጥበት አጭር ምዕራፍ ናት። በክርስቶስ የተመረጥን አማኞች በምድር ላይ የምናደርገው እያንዳንዱ የታዛዥነት ምርጫ በዘላለም አክሊላችንና ዋጋችን ላይ ፍሬ ያፈራል።

ጊዜያዊውን የዓለም ጥቅም ለማተርፍ ሲሉ ዘላለማዊውን የእግዚአብሔርን ክብር ንቆ መተው የታላቁን ሀብት ዋጋ አለማወቅ ነው። ዘላለምንና የእግዚአብሔርን ክብር ታሳቢ ያደረገ ሕይወት፤ የዛሬን ፈተና በደስታ የመሻገር አቅም አለው።

“የማይታየውን እንጂ የሚታየውን ባንመለከት፥ ቀላል የሆነ የጊዜው መከራችን የክብርን የዘላለም ብዛት ከሁሉ መጠን ይልቅ ያደርግልናልና፤ የሚታየው የጊዜው ነውና፥ የማይታየው ግን የዘላለም ነው።”
— 2ኛ ቆሮ 4፥17-18
19🔥6🥰2👌1
ኢሳይያስ 41

⁸ ባሪያዬ እስራኤል፥ የመረጥሁህ ያዕቆብ፥ የወዳጄ የአብርሃም ዘር ሆይ፥
⁹ አንተ ከምድር ዳርቻ የያዝሁህ ከማዕዘንዋም የጠራሁህና፦ አንተ ባሪያዬ ነህ መርጬሃለሁ አልጥልህም ያልሁህ ሆይ፥
¹⁰ እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤ እኔ አምላክህ ነኝና አትደንግጥአበረታሃለሁእረዳህማለሁ፥ በጽድቄም ቀኝ ደግፌ እይዝሃለሁ
¹¹ እነሆ የሚቆጡህ ሁሉ ያፍራሉይዋረዱማል፤ የሚከራከሩህም እንዳልነበሩ ይሆናሉ ይጠፉማል
¹² የሚያጣሉህንም ትሻቸዋለህ አታገኛቸውምም፥ የሚዋጉህም እንዳልነበሩና እንደ ምናምን ይሆናሉ።
¹³ እኔ አምላክህ እግዚአብሔር፦ አትፍራ፥ እረዳሃለሁ ብዬ ቀኝህን እይዛለሁና።

አሜን አሜን 🙏🙌
🙏2510👍2
08 ምህረትህ-Mihreth/Yosef Aschalew
አሐዱ ዜማ Tube
መጸለይ ስከብዳኝ፣ ነፍሴ እጅግ ደክማ፤
ደግሞ ስትበራታ፣ ጸንታ በፈተና፤
ካንታ ንጽህና ስታይ ከውበትህ፤
ደክሜም በረትቼ፣ አልመጥንህም ፊትህ....
         ምህርትህ/ቸርነትህ
         አኖረኝ በቤትህ

Yosef Aschalew
@christcentered7
16🙏2
Christ-centered
አሐዱ ዜማ Tube – 08 ምህረትህ-Mihreth/Yosef Aschalew
እረመድበት ዘንድ፣ ከምርግጣው መሬት
እጅግ ይታመናል የአንታ፤ ምህረት
ከምታነፍሰው ከዚህ ንጽሁ አየር
ቸርነትህ ላኔ ብዙ ነው እግዚአብሔር🥰
24
ቤተክርስቲያን የእግዚአብሔር ቃል የሚታወጅባት፣ ጸጋው የሚገለጥባትና የ አካሉ መገለጫ ናት። እሁድ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን አሸንፎ የተነሣበት የጌታ ቀን ነው!
​በዚህ ታላቅ ቀን ሕያው ቃሉን ልንሰማ፣ ከቅዱሳን ኅብረት ጋር ልንደመር፣ እናም በቃሉና በመንፈሱ በመታደስ አምልኳችንን ለጌታ ልናቀርብ ወደ ቅዱሳን ህብራት (ቤተክርስቲያን) እንሂድ🥰
23🔥4👍2🙏1
በእኛ ወንጌል አማኞች ማህበረሰብ ውስጥ ለአማኙ መንፈሳዊ እድገት፣ ለቤተክርስቲያን አንድነትና ለወንጌል ምስክርነት ሲባል ሊታረሙና ሊስተካከሉ የሚገባቸው ብዬ የማስባቸው ሀሳቦችና ድርጊቶች፦

1. ​የብልጽግና ወንጌል አመለካከት እምነትንና መንፈሳዊነትን ቁሳዊ ሀብት፣ ገንዘብና የዚህ ዓለም ስኬት ማግኛ አድርጎ የመመልከት ዝንባሌ። ክርስቲያናዊ ሕይወት በመስቀሉ መንገድ፣ በትግስቱና በመከራውም ውስጥ ክርስቶስን መከተል እንደሆነ አስተምህሮውን ማመጣጠን ያስፈልጋል።
2. ​መጽሐፍ ቅዱስን ከተቆራረጡ ጥቅሶች ብቻ መረዳት (Proof-Texting)፦ ጥቅሶችን ከቀደም ተከተላቸውና ከተጻፉበት ታሪካዊ/መንፈሳዊ context ውጭ በመውሰድ ለግል ፍላጎት ወይም ለስሜት ማስማማት። መጽሐፍ ቅዱስን በጥልቀትና በስርዓት የማንበብ ባህል ሊጎለብት ይገባል።
3.​አገልጋዮችን ከተገቢው በላይ ማላቀቅ (Hero Worship)፦ ሰዎችን ወይም አገልጋዮችን እንደ እግዚአብሔር ምትክ አድርጎ የመመልከትና የማምለክ ያህል የማክበር አዝማሚያ። ትኩረቱና ክብሩ ሁሉ ወደ ክርስቶስ ብቻ መመለስ አለበት።
4.​ትንቢትንና ተአምራትን ያለመመርመር የሚነገሩ ትንቢቶችንና ተአምራትን ከመጽሐፍ ቅዱስ እውነት ጋር ሳያመዛዝኑ በየዋህነት መቀበል። መጽሐፍ ቅዱስ “መንፈስን ሁሉ አትመኑ” እንደሚል የመንፈስን አመጣጥ የመመርመር ልምድ ያስፈልጋል።
5.​የጸሎትና የአምልኮ አቀራረብ ጸሎትና አምልኮ መንፈሳዊና ግላዊ ግንኙነት እንደመሆኑ መጠን፣ ሌሎች ሰዎችን በሚረብሽ ወይም ከልክ ባለፈ ጫጫታና ግርግር የሚደረጉ ድርጊቶችን መቀነስ።
6.​የፋይናንስ ግልጽነት ማነስ በቤተክርስቲያናትና በአገልግሎት ድርጅቶች ውስጥ የሚሰበሰቡ አስራት፣ በኩራትና ስጦታዎች አጠቃቀም ላይ ግልጽነትና ተጠያቂነት ማነስ።
7.​ለማህበራዊና ለሀገራዊ ጉዳዮች ትኩረት አለመስጠት መንፈሳዊነትን ከዕለት ተዕለት ማህበራዊ ሕይወት፣ ከስራ ባህል፣ ከታማኝነትና ከሀገር እድገት ነጥሎ ማየት። አማኞች በሙያቸውና በማህበራዊ ህይወታቸው የምድር ጨውና የዓለም ብርሃን መሆን አለባቸው።
8.​ሌሎችን የመፍረድና የመንቀፍ አመለካከት ከእኛ እምነት ወይም አሰራር ውጭ ያሉትን ማህበረሰቦች ወይም የሌሎች እምነት ተከታዮችን በፍቅርና በክብር ከመቅረብ ይልቅ የመኮነንና የማግለል አቀራረብ።
9.​የይስሙላ መንፈሳዊነት በቤተክርስቲያን ውስጥ በጣም መንፈሳዊ መስሎ መታየት፣ ነገር ግን በቤት፣ በስራ ቦታና በግል ህይወት የክርስቶስን አምሳል አለማሳየት።
10. ​የህብረትና የአንድነት መሸርሸር በትንሽ ልዩነቶችና በጥቅም ምክንያት የመለያየትና አዳዲስ አብያተ ክርስቲያናትን የመክፈት አዝማሚያ። የመንፈስን አንድነት በሰላም ማሰሪያ ለመጠበቅ መጋደል ይገባል።

ሌሎችን እያያን እንጨምራለን 🙌
@christcentered7
💯15🤝43❤‍🔥21🙏1
​ዛሬ በደካማ ሥጋ ውስጥ ሆነን፣ በኃጢአት ደመናና በሰይጣን ፈተና መካከል ስንጓዝ የጌታ ፍቅር ትንሽ ጠብታ እንኳ በልባችን ሲያርፍ ዓለምን የሚያስረሳ ከሆነ፣ ነገ በትንሣኤ ቀን በክብር ስንነሳ የሚጠብቀን ደስታ ምን ያህል ግዙፍ ይሆን?

በዚያን ቀን፡
➙​የሚከብድ ሥጋ፣ የሚያታልል ሕሊና ወይም የሚስብ ኃጢአት አይኖርም።
➙​ዛሬ በእምነትና በምሳሌ የምናየውን፣ በዚያን ቀን ፊት ለፊት እያየነው በፍቅሩ ባህር እንዋኛለን።

​ስለዚህ፤ ዓለምና ምኞቷ አላፊ ናቸው፤ የእግዚአብሔር ፍቅር ግን ለዘላለም ይኖራል። እግዚአብሔር በጸጋው ልባችንን ለዚህ የክርስቶስ ፍቅር ሲከፍተው፣ የሞት ጥላ ሳይጋርደን የዘላለም ሕይወትን መዓዛና ዘላለማዊውን ሰላም በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ከወዲሁ መለማመድ እንጀምራለን።

1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13:12 (NASV)
¹² ዛሬስ በመስተዋት በድንግዝግዝ እንደምናይ ነን በዚያን ጊዜ ግን ፊት ለፊት እናያለን፤ ዛሬስ ከእውቀት ከፍዬ አውቃለሁ በዚያን ጊዜ ግን እኔ ደግሞ እንደ ታወቅሁ አውቃለሁ።
❤‍🔥236🔥2
"እንግዲህ፥ ወዳጆች ሆይ፥ የዚህ ተስፋ ቃል ካለን፥ በእግዚአብሔር ፍርሃት ቅድስናን ፍጹም እያደረግን ሥጋንና መንፈስን ከሚያረክስ ሁሉ ራሳችንን እናንጻ።"
2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 7:1 (NASV)
19🔥5