በክርስቶስ ( in christ)
708 subscribers
98 photos
33 videos
40 files
38 links
Who is ownership of kingdom
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin
Download Telegram
መልህቅ⚓️ሶስት ጎን ያለው የሚመስል ብረት ነው ። አገልግሎት ለመርከብ ወይም ለጀልባ ነው ። መርከበኞች ብዙ ጊዜ አድማቸው እና ምልክታቸው መልህቅ ነው ። የመርከበኞች እና የመርከብ ህይወት ከመልህቅ ጋር የተቆራኘ ነው ።

መልህቅ መርከቡ እንዲቆም ሲፈለግ ከደረሰበት ቦታ ወይም አደጋ ሲደርስ ወጀብ ማዕበል ሲነሳ ለማረጋጋት አገልግሎት ላይ ይውላል ። ወጀብ ሲነሳ መልህቁ ወደ መሬት ይጣላል .. ብረቱ ስለሆነ ወሃ ስር መሬት ይይዛል ያኔ መርከቡን ይቆማል ..ማዕበሉ ምን ቢገፉው መርከቡን ይነቃነቃል እንጂ ጉዳት አይደርስበትም መልህቁ አንቆ ይዞታላ።

እኛም ክርስቶስ የነፍሳችን መልህቅ ነው ። ከዚህ ምድር ለሚደርስብን እንግልት መከራ የሚታደገን እንደ መልህቁ ወደ ውሃ ውስጥ ሳይሆን ወደ ላይ ወደ አባቱ ዘንድ ወደ ሰማይ ገብቷል ።አሁን መልህቃችን ሰማይ ገብቶ አስገብቶናል መከራ ቢመጣ ይገፋናል እንጂ አያጠፋንም መልህቃችን ኢየሱስ ከሰማይ ጋር አገናኝቶናል !!⚓️

መልህቄ ⚓️ መልህቄ
ኢየሱስ መልህቄ
ላትለቀኝ የያዝከኝ
የእግዚአብሔር ልጅ ፅድቄ
⚓️⚓️⚓️⚓️⚓️⚓️⚓️⚓️

.............


መርከቢቷ አቅቷት
ሚዛኗ ሲዛባ
የነፍስ መልህቅ ⚓️
ሊቁ ቀድሞን ገባ

@ownkin
@cgfsd
በክርስቶስ ያለ ስሙ በኢየሱስ መዝገብ ስር ከህይወት መፀሀፍ ላይ ተፅፆፏል!!
ትኩረት ወደ ኢየሱስ !!
ስርየት
(1ዩሀ 2:12)



በፊሊሞን ነጋ
@ownkin
@cgfsd
#የአብን ቁጣ አበረድክልኝ #የቅጣቱን እጁን ተቀበልክልኝ #ለእኔ የተገባውን ሆኖ በአንተ ላይ #ሆንክልኝ ፅድቄ አብ ፊቱን እንዳይ


ዘማሪ አስቴር አበበ
#በስራ ብዛት ላይ ደምቅ ቤቱ #ያንዴም ለሁሌም ረክቷል አባቱ #የአንድኛ ልጁ ንፅሁ ደም ቀርቦ #ደምቋል ህይወቴ ታይቷል ተውቦ


ዘማሪ አስቴር አበበ
( ከማስታወሻዬ ማስታወሻ)

ከሰሞኑን በተደጋጋሚ የሰማኋቸውን የክርስቶስን የመዋጀት ስራ ላይ በማተኮር የተዘመሩን መዝሙሮች በማስታወሻዬ ፅፌ ነበር ።
................

( አስቴር አበበ)

#የአብን ቁጣ አበረድክልኝ #የቅጣቱን እጁን ተቀበልክልኝ #ለእኔ የተገባውን ሆኖ በአንተ ላይ #ሆንክልኝ ፅድቄ አብ ፊቱን እንዳይ
................
(ሰላም ደስታ)

#ፀጋው በእምነት አድኖኝ ....
#ኢየሱስ ፅድቁን አልብሶኝ...
#ስለእኔ በአብ ፊት ታይቶ ....
#ፈፅሞታል ስራዬን ጨርሶ..
..........

(ሰላም ደስታ)

........ #የበግ ደም አይደለም ያነፃኝ
#አብን እንዳየው ፀጋው ነው የረዳኝ

..............
(ህሊና ዳዊት )

#እኔም ኢየሱስን ለብሼ #አብ ፊት ሞገስ አገኘው !!
.................
(መስከረም ጌቱ)

#ኢየሱስ ያድናል #አዎን አድኖናል
ከፊት እየመራ 😍
ወደ ፅዮን ያደርሰናል

..............
(ዘመናይ ጎሳዬ)

#አባትነት ከሚሰየምበት #ከአብ ፊት እንበረከካለሁ #በልጁ ለሚያየኝ የልቤን አስታወቀዋለሁ
...................
( አዲሱ ወርቁ )

#እኔ በበኩሌ ከእኔ ነው የምለው
ምንም ታሪክ የለኝ
#በመስቀል ላይ ሁኖ ተጠማሁኝ
ያለው የደሙ ፍሬ ነኝ

.........................
(በረከት መገርሳ)

#ከህይወቱ ብዙ መማሬ ሳያንሰኝ
#ትንሳኤ ድጋሚ ወደድኩት አነፀኝ
አቤት የኔ ረቡኒ .....

@ownkin
@cgfsd
ሕይወት ተገልጧል እኔ አይቻለሁ
#በአንድ ልጁ ሞት ተዋጅቻለሁ #ስለ አብ ፍቅር ተሰልፊያለሁ !!

(ሀዋዝ)
የመጀመሪያው አዳም ምድርን እንዲገዛ ተስጥቶት ነበር ቢሆንም በውድቀት ሳቢያ በፍፅምና ሊገዛ አልተቻለው !!! የኋለኛው አዳም (ክርስቶስ) ግን በማያልፍ ሃይል በማይገረሰስ ጉልበት ድል በመንሳቱ ከዘላለም እስከ ዘላለም ይገዛል እኛም እንገዛለታለን!!!
ህብረትን ማጣጣም
መዝ133

ክርስቶስ የመሰረተው ህብረት ግሩም መአዛ እና የሚያወድ ጠረን አለው ።እሱን እናጣጥም !!!

በፊሊሞን ነጋ
@ownkin
@cgfsd
#መልካሙን የእምነት ገድል ተጋድዬ🏃‍♂ #እንዳልፍ እርዳኝ ኢየሱስ ጌታዬ🙏
ክርስቶስ ገብቶበት ትርጉም የማይሰጥ የህይወት እንቆቅልሽ የለም ።

Aman shalom
ደቀመዛሙርትነት ዘወትር በመምህሩ ኢየሱስ ክርስቶስ እየተገረሙ እና እየተደነቁ መኖር !!
ክርስቶስ ማለት የተቀባ ማለት ነው ስለዚህ የተቀባውን ክርስቶስ ስንጠራ ቀቢውን አብን.. ቅባቱን መንፈስ ቅዱስም እያነሳን መሆኑን ማወቅ አለብን ።

(ሙሽሪትን ለሙሽራ በሔኖክ ኢሳይያስ )
ክርስቶስ ወደ እራሱ አደረሰን !!!እሰይ እሰይ ራሱ ክርስቶስ በራሱ ስራ ፣በራሱ ደም፣ በራሱ ፀጋ፣ በራሱ አቅም ፣በራሱ ምህረት ፣ በራሱ ፍቅር ወደ ራሱ አደረሰን !!!

ዕብራውያን 12 (Hebrews)
24፤ የአዲስም ኪዳን መካከለኛ ወደሚሆን ወደ ኢየሱስ፥ ከአቤልም ደም ይልቅ የሚሻለውን ወደሚናገር ወደ መርጨት ደም ደርሳችኋል።


@ownkin
@cgfsd
( ውብ ትዕዛዙ 📖 )


1 ዮሐንስ 2 (1 John)
3፤ ትእዛዛቱንም ብንጠብቅ በዚህ እንዳወቅነው እናውቃለን።

ዩሀንስ ትዕዛዝ ፣ትዕዛዙን የሚሉ ቃላት በወንጌልም በዚህም መልዕክት ውስጥ በተደጋጋሚ ይጠቀማል ።ትዕዛዝን ብቻ አይደለም እወቁ ፣ማወቅ፣እናውቀቃለን የሚለው ቃል ብዙ ጊዜ ፅፎታል ። ዕውቀትን የፃፈበት ምክኒያት ኖስቲዝም አስተማሪዎች እውቀት ብቻ ነው የሚያድነው ብለው ለሚያስተምሩ ነው ።ኖስቲዝም ማለት እራሱ ዕውቀት ማለት ነው ትርጉሙ ። ስለዚህ እነዚህን ቃላት ደጋግሟል በትክክል ለማስረዳት ነው ።እንደ ኖስቲዝም እግዚአብሔር ማወቅ የአይምሮ እውቀት የጠለቀቀ ማብራራት ፣ሀሳባዊነት ብቻ ሳይሆን ዩሀንስ የሚነግረን እግዚአብሔር ማወቅ ከውስጥ በመነጨ ትዕዛዙን በመጠበቅ ነው ።እግዚአብሔር ማወቅ ከንባብ ወይም ከመማር የሚመጣ "ፐ" የሚያስብል ምጥቀት አይደለም ። እግዚአብሔር ማወቅ ከህብረት (fellowship ) ነው የሚጀምረው ። ትዕዛዙን የጠበቀ በእርግጥ እግዚአብሔርን ያውቃል ።

እግዚአብሔር ማወቅ = ኢየሱስን ማመን + መታዘዝ + በፍቅር መመላለስ

ትዕዛዜን ጠብቁ ሲል ታዛዥ ሁኑ ታዘዙ እያለ ነው ። በእንደ ክርስቲያን መታዘዝ የእምነት ውጤት ነው ። ክርስቶስ እንደ ግል አዳኙ ያረገ ሰው እሱ እግዚአብሔርን ታዟል ። የመጀመሪያው የታዘዝነው ኢየሱስን እንደ ግል አዳኛችን ያመንን ጊዜ ነው ።ያኔ በእምነት ለሚገኘው መታታዝ እጃችን ሰጠን ። ለእሱ ለመኖር ጀመርን ታዘዝን በእምነት ምክኒያት ።

አንድ ሰው በሚሰራበት መስሪያ ቤት ፣በሚማርበት ትምህርት ቤት፣ በሚኖርበት ቤት ..አለቃ ለሰራተኛው ፣አስተማሪ ለተማሪ ፣ ወላጅ ለልጆች የሚያዙት ትዕዛዝ አለ ያንን መፈፀም አለባቸው እንዲፈፅሙ የሚያስችላቸው እንዲታዘዙም የሚያደርጋቸው በመካከላቸው ያለው ህብረት ነው ያ ህብረት እና ግንኙነት እንዲታዘዙ ግድ ይላችኋል ። እኛም ከአባት ከልጁም ከኢየሱስ ጋር ህያው ህብረት ስላለን ወደደን እንታዘዛለን ።

ትዕዛዙ ግን ምንድን ነው ????

ትዕዛዝ ሲባል ቀድሞ የሚታወቀው መካከል 10ቱ ትዕዛዛት ነው ። እነዚህ ትዕዛዝ ለእስራኤል ሲሰጥ ከሰው ከእግዚአብሔር ጋር ህብረት ለማረግ እነዚህን ትዕዛት እየፈፀመ ነው ።

አሁን ዩሀንስ ሊነግረን የፈለው ትዕዛዝ አለ !!!ያ ትዕዛዝ ፍቅር ነው !!!!!😍😍 ፍቅር ፣ፍቅር ፣ፍቅር ነው ትዕዛዙ ። እግዚአብሔር ግን ምን አይነት አምላክ ነው ያዘዘን ፍቅርን ነው ።
ዮሐንስ 15 (John)
12፤ እኔ እንደ ወደድኋችሁ እርስ በርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ ትእዛዜ ይህች ናት።

ዮሐንስ 13 (John)
34፤ እርስ በርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ፥ እንደ ወደድኋችሁ እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ አዲስ ትእዛዝ እሰጣችኋለሁ።
35፤ እርስ በርሳችሁ ፍቅር ቢኖራችሁ፥ ደቀ መዛሙርቴ እንደ ሆናችሁ ሰዎች ሁሉ በዚህ ያውቃሉ።

ዮሐንስ 15 (John)
9፤ አብ እንደ ወደደኝ እኔ ደግሞ ወደድኋችሁ፤ በፍቅሬ ኑሩ።
10፤ እኔ የአባቴን ትእዛዝ እንደ ጠበቅሁ በፍቅሩም እንደምኖር፥ ትእዛዜን ብትጠብቁ በፍቅሬ ትኖራላችሁ።

ጌታ የሰጠን ትዕዛዝ ይቺ ናት 👉 በፍቅሬ ኑሩ !!! በፍቅር ኑሩ ሲባል ሌላ ፍቅር እንዳንፈልግ እራሱን ፍቅሩን ሰጠን ፣ፍቅሩን አቀመሰን ወደ እኛ አስጠጋው እና በቀመሳችሁት በእኔው ፍቅር ኑሩ አለ ። ፍቅሬ ኑሩ አለ ይሔ ነው በቃ ትዕዛዙ ። አንድ ሰው እግዚአብሔር ማወቁ የሚተወቀው በእውቀት ጥልቁ ሳይሆን በፍቅር ስፋቱ ነው ። እግዚአብሔርን ይወዳል ወይ ??? ሰውን ይወዳል ወይ ??አዎ ከሆነ መልሱ እግዚአብሔርን ያውቃል ። ለምን ፍቅር እግዚአብሔር ማወቂያ መንገድ ሆነ??እግዚአብሔር ፍቅር ነዋ እኛን ያዳነን በፍቅሩ ነው ፍቅር ግድ ብሎት ነው ።

የእግዚአብሔር ፍቅር በደንብ ወደ እኛ ሊደርስ የቻለው ሁሉ በክርስቶስ መታዘዝ ነው ። ክርስቶስ የመታዘዝ ጥግ ነው ። መስቀል የመታዘዙ ወጤት ነው ...መዳናችን የመታዘዙ ውጤት ነው....ወደ ምድር መምጣቱ የመታዘዝ ውጤቱ ነው ...መሞቱ የመታዘዙ ውጤት ነው ። ኢየሱስ አባቱን አባ የታዘዘው ፍቅር ግድ ስላለው ነው። አባቱን ይወደዋል ደግሞም እኛም ይወደናል ። የመታዘዝ ምሳሌያችን ኢየሱስ ነው። እኛም ትዕዙዙን(ፍቅሩ )እንታዘዛለን ደቀመዛሙርት ነን እና

10ቱ ትዕዛዝ ሆነም ሌላው ትዕዛዝ ህግ ዋና አለማቸው ፍቅር ነው ። አስርቱ ትዕዛዝ ሲጨመቁ የሚወጣቸው እንዲህ የሚል ነው ..

ማቴዎስ 22 (Matthew)
36፤ መምህር ሆይ፥ ከሕግ ማናቸይቱ ትእዛዝ ታላቅ ናት? ብሎ ጠየቀው።
37፤ ኢየሱስም እንዲህ አለው፡— ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ በፍጹም ነፍስህም በፍጹም አሳብህም ውደድ።
38፤ ታላቂቱና ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት።
39፤ ሁለተኛይቱም ይህችን ትመስላለች፥ እርስዋም፡— ባልንጀራህን እንደ ነፍስህ ውደድ የምትለው ናት።
40፤ በእነዚህ በሁለቱ ትእዛዛት ሕጉም ሁሉ ነቢያትም ተሰቅለዋል።

#ትዕዛዙ ፍቅር ነው ያልነው በዚሁ አግባብ ነው ።

ሮሜ 13 (Romans)
8፤ እርስ በርሳችሁ ከመዋደድ በቀር ለማንም ዕዳ አይኑርባችሁ፥ ሌላውን የሚወድ ሕግን ፈጽሞታልና።
9፤ አታመንዝር፥ አትግደል፥ አትስረቅ፥ በውሸት አትመስክር፥ አትመኝ የሚለው ከሌላይቱ ትእዛዝ ሁሉ ጋር በዚህ፡— ባልንጀራህን እንደ ነፍስህ ውደድ፥ በሚለው ቃል ተጠቅልሎአል።
10፤ ፍቅር ለባልንጀራው ክፉ አያደርግም፤ ስለዚህ ፍቅር የሕግ ፍጻሜ ነው።

...እንዋደድ !!! ትዕዛዙም ያ ነው !!!
በፍቅሩ እንኑር🏃‍♂እንመላለስ🚶

@ownkin
@cgfsd
(ኢየሱስን ልናይ እንወዳለን !!)
ዩሀ 12:20

ክርስትና ኢየሱስን በማየት የምንመላለስበት ህይወት ነው ።


በፊሊሞን ነጋ
@cgfsd
@ownkin
ያንተ ልታደርገን 🤗 እኛን ለመሰልከው🙏 ክበር
ለሰላም ፣ለፍቅር ፣ ለተስፋ ፣ለማዳን፣ ለማፅደቅ ፣የራሱ ለማረግ ፣ ወዳጅነት ለመፍጥር ደም የተቃባው አምላካችን እግዚአብሔር ብቻ ነው !!!
የትኛው ደም መፍትሔ ሲሆን አልታየም ። እንደው እርስ በእርስ መጠራጠሪያ ፣ እርስ በእርስ በበቀል ፣ ለመገዳደል የሚያነሳሳ ...የሚያቅበዘብዝ ፣ ሰውን ከሰው የሚያራርቅ ፣ በአንዱን ከሌላው የሚያናክስ ።
የመድሃኒታችን ኢየሱስ ደም በዘላለም መንፈስ የቀረበ ሰውን ከአምላኩ ጋር በሰላም ያወዳጀ ፣ የሰውን ኩነኔ ወደ ፅድቅ የለወጠ ፣ ኑ ብሎ ወደ እግዚአብሔር ያቀረበ ፣ ከሀጢያት የሚያነፃ ፣ መተማመኛ ዋስትና ያለው፣ ከወርቅ የከበረ ከብር የተወደደ፣ ንፁህ ደም ነው ።
ኢየሱስ ኢየሱሴ መገረሜ ነህ መደነቄ