Amhara Region revenue bureau
4.28K subscribers
2.24K photos
70 videos
270 files
272 links
Amhara region revenue bureau Main office
Download Telegram
የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ግብር አከፋፈል
በ “AGOA” መታገድ ምክንያት የተፈጠረ የገበያ እጥረት በአምራቾች ላይ የፈጠረውን ጫና መቀነስ እንዲቻል የ “AGOA” ተጠቃሚ የሆኑ በኢንደስትሪ ፓርክ ውስጥ የሚገኙ አምራች ላኪዎች ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት አስፈላጊውን የጉምሩክ፣ ቀረጥና ታክስ ከፍለው ምርቶቻቸውን በአገር ውስጥ ገበያ እንዲሸጡ ለ6 (ልስድስት) ወራት የተራዘመ መሆኑን ገቢዎች ሞኒስቴር አሳወቀ።
የሲሚንቶ ፋብሪካ የበር መሸጫ ዋጋ ይፋ ሆነ
የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ.pdf
3.8 MB
በኤሌክትሪክ ተሽከርሪዎች ላይ የታክስ ማስተካከያ መደረጉን ገንዘብ ሚኒስቴር ኣሰወቀ
ከአፋር ክልል የገቢ መ/ቤትና ባለድርሻ መ/ቤቶች ተወክሎ የመጣ ቡድን ከገቢዎች ቢሮ ተሞክሮ ልውውጥ አካሄደ፡፡
መስከረም 27/2015 ዓ.ም
የተሞክሮ ቡድኑ በገቢ ተቋሙ አወቃቀርና አደረጃጀት፣ የግብር ህግ ተገዥነትን ለማሳደግ የምንከተላቸውን ስልቶች፣ ገቢያችንን ለማሳደግ እየተሠሩ ያሉ ሥራዎች፣ የከተማ አገልግሎት ገቢ አሰባሰባችንን (ትላልቅ የፌዴራል መ/ቤቶችን ከማስከፈል አኳያ) በሰነድ የታገዘ ማብራርያ ተደርጎላቸዋል።
የኦዲት አሠራራችንን ፣ ከፌዴራል ገቢዎችና ከሌሎች ክልሎች ጋር ያለውን የጋራ ገቢ ትልልፍ በተመለከተ፣ በዋናናት ደግሞ ከአጋርና ባለድርሻ አካላት ጋር ያለንን ቅንጅት በተመለከተ ያሉንን ተሞክሮዎች ተለዋውጠናል፡፡
ከዚህም ባሻገር ሁለቱ ክልሎች በተለያዩ ጉዳዮች ለመደጋገፍ ያላቸውን ተነሳሽነት ግልፀዋል፡፡
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለነብዩ መሀመድ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!
የ1 ሺህ 497 የነብዩ መሀመድ ልደት (መውሊድ) በዓል ስናከበር የነቢዩ መሐመድን በረከቶችን በማስተዋልና መንገዳቸውን በማሰብ መሆን አለበት። ክብረት ማህሙድ ምክትል ቢሮ ኃላፊ