ብራና ሚድያ - Birana Media
664 subscribers
1.66K photos
40 videos
4 files
572 links
+ የወጣቶች መንፈሳዊ ሕይወት
+ ገዳማትና ታሪካዊ ስፍራዎች
+ የቅዱሳን አበው መንፈሳዊ ተጋድሎና ታሪክ
+ እንዲሁም በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች የውይይት መድረክ በማዘጋጀት ወደ እናንተ ውድ ተከታታዮች መንፈሳዊ ይዘቱን ጠብቆ በየእለቱ ይቀርባል።
ቻናላችንን Subscribe በማድረግ ይቀላቀሉን።
https://www.youtube.com/c/BiranaMedia
ጥያቄ ካሎት በዚህ ይጻፉልን @birana259
Download Telegram
በዋግ ኽምራ ሀገረ ስብከት ለተከተሰተው ድርቅ ከ315 ሺ በላይ ዜጎች አስቸኳይ የምግብ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው ተገለጸ።

ጥቅምት 23 ቀን 2016 ዓ.ም (ብ.ሚ/ አዲስ አበባ)

በዋግ ኽምራ ሀገረ ስብከት ለተከተሰተው ድርቅ ከ315 ሺ በላይ ዜጎች አስቸኳይ የምግብ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው ብፁዕ አቡነ በርናባስ ገለጹ።

ብፁዕ አቡነ በርናባስ የዋግ ኽምራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እንደገለጹት በሀገረ ስብከቱ ባሉ 3 ወረዳዎች ከፍተኛ ድርቅ መከሰቱን ገልጸው በተከሰተው ከፍተኛ ድርቅ ዜጎችን ለረሃብ ከመዳረጉ ባለፈ ከብቶች በመሞት ላይ እንደሚገኙ ነው የገለጹት።

ብፁዕነታቸው አክለውም በዋግ ኸምራ ሀገረ ስብከት በተከሰተው ከፍተኛ ድርቅ ምክንያት በሥሩ የሚገኙ 65 አብያተክርስቲያናት ለከፋ ችግር መጋለጣቸውን ጠቁመዋል።

በአማራ ክልል የዋግ ኽምራ ሀገረ ስብከትን ጨምሮ በሌሎች አካባቢዎችም በተከሰተው ከፍተኛ ድርቅ ለተጎዱ ወገኖች መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሊረዱ እንደሚገባም ብፁዕነታቸው ገልጸዋል።
©EOTCTV

#Ethiopia 
#Birana_Media
#BM_Addia_Ababa

ብራና ሚዲያ
የኦርቶዶክሳዊያን ድምፅ

የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/c/BiranaMedia

የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፤ ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ
https://t.me/birana3

በፌስቡክ ገጻችን ትምህርቶች እና ወቅታዊ መረጃዎችን ያግኙ
https://www.facebook.com/birana22

አጫጭር ትምህርታዊ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቲክ ቶክ አማራጫችንን ይመልከቱ
https://www.tiktok.com/@birana16

የኢንስታግራም ገጻችንን
www.Instagram.com/birana96
"ለማኅበራዊ ሚዲያ ማድመቂያ በማኅሌቱ የሚታየው የሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ጥሰት ሊቆም ይገባል " ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ

ጥቅምት 24 ቀን 2016 ዓ.ም (ብ.ሚ./አዲስ አበባ)

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከምትታወቅባቸው እና ከምትገለገልባቸው የማይዳሰሱ ሀብቶቿ መካከል አንዱ እና ዋነኛው ሥርዓተ ማኅሌት ነው ሲሉ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ገልጸዋል።

ብፁዕነታቸው በገለጻቸው ቤተክርስቲያን ሥርዓተ አምልኮዋን በማኅሌት ታቀርባለች ፤ ይሁን እንጂ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ይዘቱን በለቀቀ መልኩ አቀራረቡ ተለይቶ ማኅሌት በማይመስል መልኩ ባልተገባ ሁኔታ ሥርዓቱን ባልጠበቀ አቀራረብ ሲቀርብ እየተመለከትን ነው ብለዋል።

በዚህ ሁኔታ በአሁን ወቅት በተለያዩ የሶሻል ሚዲያዎች የቤተ ክርስቲያኗን ስልት እና ሥርዓት በትክክል በሚገልጽ መልኩ ሲገለገሉ አይታይም ይህን ነገር እግዚአብሔር አይቀበለውምና ሊቀር ይገባል ብለዋል ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ።

አሁን ያለው ሥርዓት ከእግዚአብሔር ጋር አያገናኘንም ቤተክርስቲያንንም አይገልጻትም የጥንት አባቶቻችን ሥርዓት በልክ ተሰርቶ ተቀምጦ ያለው ከሚፈልገው መንገድ ወጥቷልና የሚመለከታቸው አካላት ሊቃውንትን ጨምሮ ይህን እንቅስቃሴ በጊዜ ሊያስቆሙ ይገባል ነው ያሉት።
©eotc tv

#Ethiopia 
#Birana_Media
#BM_Addia_Ababa

ብራና ሚዲያ
የኦርቶዶክሳዊያን ድምፅ

የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/c/BiranaMedia

የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፤ ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ
https://t.me/birana3

በፌስቡክ ገጻችን ትምህርቶች እና ወቅታዊ መረጃዎችን ያግኙ
https://www.facebook.com/birana22

አጫጭር ትምህርታዊ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቲክ ቶክ አማራጫችንን ይመልከቱ
https://www.tiktok.com/@birana16

የኢንስታግራም ገጻችንን
www.Instagram.com/birana96
ከስልጤ ዞን ቅበት ከተማ ተሰደው በቡታጅራ የነበሩት ኦርቶዶክሳውያን እና አብሮ የተሰደደው የቅድስት ድንግል ማርያም ጽላት ወደ አካባቢያቸው ተመለሱ።

ጥቅምት 26 ቀን 2016 ዓ.ም (ብ.ሚ./ አዲስ አበባ)

ከስልጤ ዞን ቅበት ወረዳ በደረሰባቸው ጥቃት ምክንያት የተሰደዱት ኦርቶዶክሳውያን እና አብሮ የተሰደደው የቅድስት ድንግል ማርያም ጽላት ወደ አካባቢያቸው መመለሳቸውን የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ የሆኑት መልአከ ሕይወት ቀሲስ ንጉሤ ባወቀ ለተሚማ ገልጸዋል።

መልአከ ሕይወት ቀሲስ ንጉሤ ባወቀ የሀድያና ስልጤ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ከተ.ሚ.ማ ጋር ባደረጉት የስልክ ቆይታ እንደገለጹት  ከአዲስ አበባ 130 ኪ.ሜ ከስልጤ ዞን 12 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምትገኘው ቡታጅራ ደብረ ጽዮን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ተጠልለው ለ2 ወራት የቆዩት ኦርቶዶክሳውያን በሙሉ ወደ አካባቢያቸው ገብተዋል ብለዋል።

ከስልጤ ዞን ቅበት ወረዳ በደረሰባቸው ጥቃት ምክንያት የተሰደዱት ከ1500 በላይ ኦርቶዶክሳውያን መካከል አብዛኞቹ ህጻናት ፣ ሲሆኑ አዛውንት ፣ ወጣቶች ፣ ጎልማሶች እና አራስ እናቶች እንደሚገኙበት ተ.ሚ.
ማ በቦታው ተገኝቶ መዘገቡ አይዘነጋም።

ሥራ አስኪያጁ በገለጻቸው ወደ ቀያቸው የተመለሱት ኦርቶዶክሳውያን በዞኑ የሚገኙ ጽንፈኞች መኖርያ ቤቶቻቸውን አቃጥለውባቸው እና ዘርፈውባቸው ስለነበር መታደስ እና መስተካከል የሚችሉ ቤቶችን ዞኑ እንደሚያስተካክል እና ካሳ እንደሚሰጣቸው ፤ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸውን ቤቶች በድጋሚ እስኪሰሩ ድረስ ዞኑ ቤት ተከራይቶላቸው እንደሚቆይ አክለዋል።

በስልጤ ዞን ቅበት ወረዳ በሚኖሩ ኦርቶዶክሳውያን ላይ ያለው ስጋት አሁንም እንደሚኖር ገልጸው ከዚህ በኋላ ከፌደራል ጀምሮ ጥብቅ ክትትል እንደሚደረግ እና ምንም አይነት ጥቃት እንደማይደርስባቸው የዞኑ የመንግሥት አካላት ፣ የከተማው አስተዳደር እና የሀገር ሽማግሌዎቹ ዋስትና እንደሚወስዱ ቃል ገብተዋል ነው ያሉት ሥራ አስኪያጁ።

በመጨረሻም መልአከ ሕይወት ቀሲስ ንጉሤ ባወቀ የሀድያና ስልጤ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ የተፈናቀሉት ኦርቶዶክሳውያንን ለመርዳት ለተደረገው ርብርብ በመላው ዓለም የሚገኙ ምዕመናንን ፣ የመንግስት አካላትን ፣ በቦታው ድረስ በመገኘት እርዳታ ላደረጉ ሊቃነ ጳጳሳት ፣ ለሚዲያ አካላት ፣ ቡታጅራ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያንን እና የቡታጅራ ነዋሪዎችን አመስግነዋል።

©️ተ.ሚ.ማ.

#Ethiopia 
#Birana_Media
#BM_Addia_Ababa

ብራና ሚዲያ
የኦርቶዶክሳዊያን ድምፅ

የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/c/BiranaMedia

የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፤ ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ
https://t.me/birana3

በፌስቡክ ገጻችን ትምህርቶች እና ወቅታዊ መረጃዎችን ያግኙ
https://www.facebook.com/birana22

አጫጭር ትምህርታዊ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቲክ ቶክ አማራጫችንን ይመልከቱ
https://www.tiktok.com/@birana16

የኢንስታግራም ገጻችንን
www.Instagram.com/birana96
በብዙ ልፋት የተሰሩ ብዙ ታሪክን ሰንደው የያዙ ገዳማት በጦርነቱ ምክንያት እየወደሙ እንደሚገኙ ተገለጸ።

ጥቅምት 28 ቀን 2016 ዓ.ም (ብ.ሚ/አዲስ አበባ)

በብዙ ልፋት የተሰሩ ብዙ ታሪክን ሰንደው የያዙ ገዳማት በጦርነቱ ምክንያት እየወደሙ እንደሚገኙ መጋቤ ካህናት አባ ሀብተጊዮርጊስ አስራት ለተ.ሚ.ማ ገለጹ።

ገዳማት እና ገዳማውያን  በሀገሪቱ አሁናዊ የሰላም ሁኔታ ምክንያት አገልግሎት መስጠት እንዳልቻሉ መጋቤ ካህናት አባ ሀብተጊዮርጊስ አስራት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የገዳማት አስተዳደር መምሪያ ዋና ኃላፊ ከተ.ሚ.ማ ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ጀምሮ ያለው ተዋረድ የተገኙት እና መፍለቂያቸው ገዳም ነው ያሉት ኃላፊው የገዳማት አገልግሎት የሚቋረጥ እና የሚዘጉ ከሆነ የቤተ ክርስቲያን ህልውና አደጋ ውስጥ የሚገባ ነውም ብለዋል።

መጋቤ ካህናት አባ ሀብተጊዮርጊስ አስራት አክለውም በትግራይ አካባቢ ያሉ ገዳማት ከዚህ ቀደም በነበረው ጦርነት ጉዳት ደርሶባቸው እና "መንበረ ሰላማ" በማለት ራሳቸውን በነጠሉ አካላት ምክንያት አገልግሎት እየሰጡ አይደለም ነው ያሉት።

በጦርነቱ ምክንያት በገዳም ውስጥ ያሉ ገዳማውያን የልማት ሥራን ሠርተው ራሳቸውን ማስተዳደር ፣ መብል ማግኘት አለመቻላቸውን እንዲሁም በሸዋ ፣ በወሎ ፣ በጎጃም እና በጎንደር ብዙ ደቀመዛሙርት እና ጸበልተኞች በገዳም ውስጥ ሆነው መሞታቸውን ፤ ገዳማት እንዳልነበሩ ሆነው እየወደሙም መሆኑን ገልጸዋል ኃላፊው።

በመጨረሻም የተቸገሩ ገዳማትን ለመርዳት እና ወደ ቀድሞ ሁኔታቸው ለመመለስ ሰላም በእጅጉ ያስፈልገናል ያሉት ኃላፊው በችግር ላይ የሚገኙ ገዳማትን እና ገዳማውያንን መርዳት የሁላችንም ኃላፊነት ነውና ገዳማት ራሳቸውን እንዲችሉ ሁሉም የበኩሉን ለመወጣት እና ለማገዝ መረባረብ እንደሚገባ አሳስበዋል።


#Ethiopia 
#Birana_Media
#BM_Addia_Ababa

ብራና ሚዲያ
የኦርቶዶክሳዊያን ድምፅ

የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/c/BiranaMedia

የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፤ ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ
https://t.me/birana3

በፌስቡክ ገጻችን ትምህርቶች እና ወቅታዊ መረጃዎችን ያግኙ
https://www.facebook.com/birana22

አጫጭር ትምህርታዊ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቲክ ቶክ አማራጫችንን ይመልከቱ
https://www.tiktok.com/@birana16

የኢንስታግራም ገጻችንን
www.Instagram.com/birana96
በአማራ ክልል ባለው ጦርነት ምክንያት የደብረ ሮሃ ቅዱስ ላሊበላ አብያተ ክርስቲያናት ደኅንነት አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ ተገለጸ።

ጥቅምት 29 ቀን 2016 ዓ.ም (ብ.ሚ/አዲስ አበባ)

በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በአማራ ክልል እየተካሄደ በሚገኘው ጦርነት ምክንያት የደብረ ሮሃ ቅዱስ ላሊበላ አብያተ ክርስቲያናት ደኅንነት አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን  የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል።

የላሊበላ አካባቢ ነዋሪዎች እንደገለጹት በአብያተ ክርስቲያናቱ ዙሪያ ያለው ተኩስ የጥንታውያኑን አብያተ ክርስቲያናት ደኅንነት አደጋ ላይ እንደሆነ ነው የተናገሩት።

ለደብረ ሮሃ ቅዱስ ላሊበላ አብያተ ክርስቲያናት መጠለያነት የተሠሩ የብረት ሽፋኖች በተባራሪ ጥይቶች መመታታቸውን ፤ ሁሉንም ዓይነት የጦር መሳሪያዎች እየተጠቀሙ መሆኑን እና "የተኩሱ ንዝረት ይሰማኛል” በማለት ውጊያው በከተማዋ ውስጥ የፈጠረውን ስጋት እና የደቀነውን አደጋ የሮይተርስ የዜና ወኪል ያናገረው አገልጋይ ገልጸዋል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል።

ጉዳዩን በተመለከተ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነትን ብንጠይቅም ከሀገረ ስብከቱ መረጃው እንዳልደረሰው የተገለጸልን ሲሆን ወደ ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ያደረግነው የስልክ ሙከራም አልተሳካም።

#Ethiopia 
#Birana_Media
#BM_Addia_Ababa

ብራና ሚዲያ
የኦርቶዶክሳዊያን ድምፅ

የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/c/BiranaMedia

የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፤ ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ
https://t.me/birana3

በፌስቡክ ገጻችን ትምህርቶች እና ወቅታዊ መረጃዎችን ያግኙ
https://www.facebook.com/birana22

አጫጭር ትምህርታዊ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቲክ ቶክ አማራጫችንን ይመልከቱ
https://www.tiktok.com/@birana16

የኢንስታግራም ገጻችንን
www.Instagram.com/birana96
የደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያንን እድሳት ለማስጀመር ታቦተ ሕጉ ወደ ተዘጋጀለት ማረፊያ መቃኞ ቤተ ክርስቲያን በክብር ገባ !

ኅዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም (ብ.ሚ /አዲስ አበባ)

የደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያንን እድሳት ለማስጀመር ታቦተ ሕጉ  ወደ ተዘጋጀለት ማረፊያ መቃኞ ቤተ ክርስቲያን በዛሬው ዕለት ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት በደማቅ ስነ ሥርዓት በክብር ገብቷል ።

ታሪካዊው የደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን በጊዜ ብዛት ከመሠረቱ ጀምሮ እስከ ጣሪያው ድረስ ከፍተኛ ጉዳት የደረስበት ሲሆን ፤ አስቸኳይ እድሳት እንደሚያስፈልግ በመወሰኑ እድሳቱን የማስጀመር ሥራ የተከናወነ ሲሆን ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ምእመናን ሁሉም በጸሎት እና በሀሳብ እንዲተባበሩ፣ በእድሳት ሂደት ሁሉ መለኮታዊ መመሪያን እና ጥንካሬን እንዲፈልጉ ጥሪ በማቅረብ የተከበረውን የእግዚአብሔር መልአክ የቅዱስ ዑራኤልን ቤት ለመመለስ የጋራ ርብርብ አስፈላጊ መሆኑን በማሳየት ማህበረሰቡ በሚያደርገው የማይናወጥ ድጋፍ ላይ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

ሕንፃ ቤተክርስቲያኑ ለዚህን ያህል ዓመታት አገልግሎት መስጠቱ የደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያንን የሰሩት አባቶቻችን እና ምእመናን  የነበራቸውን ጽናት ፣ እምነት የሚያሳይ ነው ያሉት ብፁዕነታቸው እድሳቱ ተጠናቅቆ ወደ ቀደመው የአምልኮ ሥርዓት በቅርብ እንደሚመለስ እምነታቸው ገልጸዋል።


#Ethiopia 
#Birana_Media
#BM_Addia_Ababa

ብራና ሚዲያ
የኦርቶዶክሳዊያን ድምፅ

የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/c/BiranaMedia

የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፤ ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ
https://t.me/birana3

በፌስቡክ ገጻችን ትምህርቶች እና ወቅታዊ መረጃዎችን ያግኙ
https://www.facebook.com/birana22

አጫጭር ትምህርታዊ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቲክ ቶክ አማራጫችንን ይመልከቱ
https://www.tiktok.com/@birana16

የኢንስታግራም ገጻችንን
www.Instagram.com/birana96
ቀደም ሲል ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ መሠረት በመላው ዓለም ለሚገኙ ሕዝበ ክርስቲያን የታወጀውን አዋጅ አስተላልፈዋል፡፡ በዚሁ መሠረት ያለፈውን በይቅርታና በምህረት ዘግተን በእውነተኛ ንሥሓ ልቅሶና በምህላ፣ በጾምና በጸሎት ወደ ፈጣሪ እንድንቀርብ፣ በመካከላችንም ፍቅርና አንድነት እንዲመጣ ይኽንን ጾመ ነቢያት ወይም የገና ጾም በልዩ ሁኔታ እንድንጾም መንፈሳዊ አዋጅ ተላልፏል፡፡ 

ይኽ ጥንታዊ የአዋጅ ጾም ሁለት አበይት ታሪኮችን የያዘ ነው፡፡ የመጀመሪያው ክፍል ቅዱስ አብርሃም ሶርያዊ የተባለ ጻድቅ አባት በጸሎት፣ በጾምና በምኅላ ተራራን ከመሬት ከፍ በማድረጉ ኃይለ ጸሎቱና ክብረ አምለኩ የሚዘከርበት ነው፡፡ በሁለተኛው ክፍል ነቢያት የጌታችንን ሰው መሆን እያፈለጉ፣ ድህነትንና ሰላምን በመሻት መጾማቸው ይዘከራል፡፡ (፩ኛ ጴጥ ፩፡፲) እኛም ይኽንን አብነት አድርገን ታላቋ ቤተ ክርስቲያን፣ ኃላፊነቷን እንድትወጣ ስለችግራችን፣ ስለሀገር ሰላምና ስለ ሕዝቡ ደኅንነት በአንድነት ሆነን ወደፈጣሪያች እንድንጮኽ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በጥቅምት ወር ፳፻፲ወ፮ ዓ/ም ወስኖ መግለጫ ሰጥቷል፡፡

ሀገራችን እንድትፈወስ፣ የወገን በወገን ደም መፋሰስ እንዲቀር፣ ያለፈውን በይቅርታና በንሥሓ ዘግቶ ለወደፊቱ ብሩህ ዘመንን እንዲመጣ በንሥሓና በፍጹም ለቅሶ፣ በቁመትና በሰጊድ፣ በሰፊሕና በአንቅአድዎ፣ ወደፈጣሪ እንድንቀርብ የምልኣተ ጉባኤውን ውሳኔ መሠረት በማድረግ ቋሚ ሲኖዶስ በኅዳር ወር ፳፻፲ወ፮ዓ/ም የሚከተለውን ዝርዝር አፈጻጸም አውጥቷል፡፡

፩ኛ. የጾሙ የመጀመሪያ ሳምንት ከቅዳሜ ኅዳር ፲፭ እስከ ኅዳር ፳፩ ቀን ፳፻፲ወ፮ ዓ/ም በሁሉም የሀገራችን ክፍልና ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ባለችበት በመላው ዓለም የንሥሓ፣ የጾም፣ የጸሎትና የምኅላ ሳምንት እንዲሆን፤
 
፪ኛ. በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ በአድባራት አስተዳዳሪዎች፣ በአጥቢያ አለቆችና በገዳም አበምኔቶች መሪነት ሁሉም ዲያቆናት፣ ቀሳውስት፣ መነኰሳት፣ ሰባክያንና ሊቃውንት በሙሉ በየመዐርጋቸው ልብሰ ተክህኖና ወጣት የሰንበት ትምህርት ቤት ዩኒፎርማቸው ለብሰው፣ ሁሉም ምእመናን ጋር በአንድነት በዐውደ ምህረት ጸሎተ ምኅላውን እንዲያደርሱ፤ 

፫ኛ. በላው ሕዝበ ክርስቲያን ከሊቅ እስከ ደቂቅ፣ ሕፃናት፣ ወጣቶች፣ እናቶች አባቶች አረጋውያን ሁሉ የቻለ በቤተ ክርስቲያን፣ ያልቻለ በያለበት ሆኖ የተጣላ ታርቆ፣ በፍቅርና በአንድነት፣ በእውነተኛ ንሥሓና ጸጸት በምኅላው እንዲሳተፍ፤ በማእከል የሚደረገው ጸሎተ ምኅላ በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ መሪነት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት በተገኙበት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ገዳም ሆኖ በመገናኛ ብዙኀን የቀጥታ ሥርጭት ለመላው ዓለም እንዲተላለፍ፤

፬ኛ. በመጀመሪያው የሱባኤ ቀን ኅዳር ፲፭ ቀንና፣ በሰባተኛው ቀን ኅዳር ፳፩ ቀን በጸሎተ ምኅላው በሚደረግበት ጊዜ ታቦቱ ከመንበሩ ተነሥቶ በዐውደ ምኅረት በቀሳውስት እንዲከብር ሆኖ፤ በሁሉም የምኅላው ቀናት ሥዕለ ማርያም፣ ወንጌልና መስቀል ወጥቶ በአራቱ መዐዝን ሥርዓተ ጸሎተ ምኅላው ከጸሎተ ወንጌል ጋር በየቀኑ በነግህና በሠርክ የሥራ ሰዓትን በማይነካ ሁኔታ እንዲፈጸም፤

፭ኛ. በየዕለቱ የሚነበቡት የወንጌል ክፍሎችን ስለ ሰላም፣ ስለንሥሓና ጸጸት፣ ስለ ፍቅርና አንድነት፣ ስለ በጎነትና መደማመጥ፣ ስለመሰማማትና ጥላቻን ስለማራቅ እንዲሆን፤

፮ኛ. በሰፊህና በአንቀዓድዎ፣ በሰጊድና በአስተብርኮ፣ ምኅላው ከደረሰና፣ ጸሎተ ወንጌል ደርሶ ዕለቱ ወንጌል ከተነበበ በኋላ በአንድነት የንሥሓ መዝሙር በመዘመር፣ ሕዝበ ክርስቲያን ስለሀገራቸውና ስለሰው ልጆ ደኅንነት እያሰቡ ወደቤታቸው እንዲሄዱ፤

፯ኛ. ከመጀመሪው ሳምንት በኋላ እስከ በዓለ ልደት ድረስ የሰርክ ምህላ ሳይቋረጥ መደበኛው ሥርዓተ ጾምና ጸሎት እንዲቀጥል፣ የቤተ ክርስቲያንን ታላቅነት፣ የአበውን ተቀባይነት በሚገለጽ፣ በቀጣይም ሁሉም ኦርቶዶክሳውያን በመንፈሳዊ ጽናት የሰላም ልዑካን ሆነው እንዲቀጥሉ በሚያደርግ ሁኔታ እንዲፈጸም፤ 
 
፰ኛ. አስቀድሞ የደረሰውንና፣ እየደረሰብን ያለው ችግር የጦርነትና የግጭት ብቻ ሳይሆን የረሀብ፣ የድርቅ፣ የኑሮ ውድነት፣ የመፈናቀልና የስደት ጭምር ስለሆነ ከጸሎትና ምኅላችን ጎን ለጎን መረዳዳትና መተዛዘን፣ ርኅራሄና መደጋገፍ አብሮ እንዲፈጸም፤   

፱ኛ. ይኽንኑ መልእክት መላው ዓለም እንዲውቀው፣ በተለይም የኦሬንታል ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት በጸሎት እንዲያስቡን፣ የጸሎታችንና የምኅላችን መነሻ ምክንያቱ የሀገራችን ወቅታዊ ችግር ቢሆንም የምንጸልየው ለመላው ዓለም መሆኑ ተገልጾ በደብዳቤ እንዲላክ እንዲደረግ፣ በማለት ቅዱስ ሲኖዶስ ጥብቅ መመሪያ አስተላልፏል፡፡ 

እግዚአብሔር አምላካችን በእንባና በንሥሓ የምናቀርበውን ጸሎተ ምኅላችንን በምህረቱ ተቀብሎ ሀገራችንን ሰላም ያድርግልን፣ ሕዝባችንን ይጠብቅልን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 
ቅዱስ ሲኖዶስ

#Ethiopia 
#Birana_Media
#BM_Addia_Ababa

ብራና ሚዲያ
የኦርቶዶክሳዊያን ድምፅ

የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/c/BiranaMedia

የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፤ ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ
https://t.me/birana3

በፌስቡክ ገጻችን ትምህርቶች እና ወቅታዊ መረጃዎችን ያግኙ
https://www.facebook.com/birana22

አጫጭር ትምህርታዊ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቲክ ቶክ አማራጫችንን ይመልከቱ
https://www.tiktok.com/@birana16

የኢንስታግራም ገጻችንን
www.Instagram.com/birana96
የማኀበረ ቅዱሳን ዋና ማእከል ምዕራፍ ሁለት የሕንጻ ግንባታ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተከናወነ

ኅዳር 16 ቀን 2016 ዓ.ም (ብ.ሚ/አዲስ አበባ)

ማኅበረ ቅዱሳን ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ ቤተ ክርስቲያን በኹለንተናዊ አቅሟ እንድትጠናከር ለማድረግ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። አገልግሎቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰፋ የመጣው ማኅበሩ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት የቤተ ክርስቲያንን ተልእኮ ማስፈጸም የሚችሉ ማእከላት በማቋቋም ተግባራዊ እንቅስቃሴ ማድረግ ላይ ይገኛል።

ማኅበሩ ዘመኑ የሚጠይቀውን የአገልግሎት መንገድ በመከተል በዘመናዊ አሠራር ቤተ ክርስቲያንን ማገዝ የሚችሉ በርካታ አሠራሮችን ወደ ተግባር እያስገባ ሲሆን ለዚህ ተግባር የሚያግዙ የሰው ኃይል እና የግብዓት ማሟላት ላይ በትኩረት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።ለዚህ ማሳያ የሚሆነው ደግሞ አሁን ግባታውን ለመጀመር በዝግጅት ላይ የሚገኘው የምዕራፍ ሁለት የማኅበሩ ሕንጻ ማስፋፊያ ነው።

ማኅበሩ ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት ለመስጠት ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ የተነገረለት አዲሱ የማኅበሩ ሕንጻ የመሬት ወለልን ጨምሮ 14 ወለሎች እንደሚኖረው የተነገረለት ሲሆን ኅዳር 15 ቀን 2016 ዓ.ም ግንባታውን ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተከናውኗል።

በመርሐ ግብሩ ላይ ጸሎተ ወንጌልን ጨምሮ ሌሎች ዝግጅቶችም የቀረቡ ሲሆን በቦታው ለተገኙ ታዳሚዎች የሕንጻውን ግንባታ እና ያካተታቸውን አገልግሎቶች በተመለከተ ማብራሪያ ተሰጥቷል።በተጨማሪም የማኅበሩ ሰብሳቢ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ስዩም እንደተናገሩት ማኅበረ ቅዱሳን ቤተ ክርስቲያን የጣለችበትን ኃላፊነት ለመወጣት ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ነው ያሉ ሲሆን ይህንን ሕንጻም አባላቱ እና በጎ አድራጊ አጋር አካላት በመተባበር ወደ ፍጻሜ እንዲያደርሱት የአደራ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

በቀጣይ ጥቂት ሳምንታት ውስጥ  ግንባታው እንደሚጀመር የተነገረለት አዲሱ የማኅበሩ ሕንጻ የአርክቴክቸራል እና ስትራክቸራል ዲዛይን ሥራዎቹ እና ወደ ግንባታ ለመግባት የሚያስፈልጉ ቅድመ ዝግጅቶች በሙሉ መጠናቀቃቸው ተገልጿል።


#Ethiopia 
#Birana_Media
#BM_Addia_Ababa

ብራና ሚዲያ
የኦርቶዶክሳዊያን ድምፅ

የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/c/BiranaMedia

የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፤ ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ
https://t.me/birana3

በፌስቡክ ገጻችን ትምህርቶች እና ወቅታዊ መረጃዎችን ያግኙ
https://www.facebook.com/birana22

አጫጭር ትምህርታዊ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቲክ ቶክ አማራጫችንን ይመልከቱ
https://www.tiktok.com/@birana16

የኢንስታግራም ገጻችንን
www.Instagram.com/birana96
በደብረ ታቦር ከተማ የደብረ በረከት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን በከባድ መሳሪያ መመታቱ ተገለጸ!

ኅዳር 17 ቀን 2016 ዓ.ም (ብ.ሚ/አዲስ አበባ)

በአማራ ክልል እየተካሄደ ባለው ጦርነት በደብረ ታቦር ከተማ በሚገኘው ደብረ በረከት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን በከባድ መሳሪያ መመታቱ ተገልጿል።

ጥቃቱ የደረሰው  ኅዳር 15 ቀን 2016 ዓ.ም  ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ገደማ  የሥርዓት ቅዳሴ አገልግሎት በመጠናቀቅ  ላይ ሳለ ሲሆን በጥቃቱ አንድ ዲያቆንና አንድ ምእመን  መሞታቸው ፣ ስምንት አገልጋዮችና ምእመናን ተጎድተው በሕክምና ላይ እንደሚገኙ ፣ ቤተክርስቲያኑም  ከባድ  ጉዳት  እንደደረሰበት ተጠቁሟል።

© ማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት

#Ethiopia 
#Birana_Media
#BM_Addia_Ababa

ብራና ሚዲያ
የኦርቶዶክሳዊያን ድምፅ

የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/c/BiranaMedia

የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፤ ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ
https://t.me/birana3

በፌስቡክ ገጻችን ትምህርቶች እና ወቅታዊ መረጃዎችን ያግኙ
https://www.facebook.com/birana22

አጫጭር ትምህርታዊ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቲክ ቶክ አማራጫችንን ይመልከቱ
https://www.tiktok.com/@birana16

የኢንስታግራም ገጻችንን
www.Instagram.com/birana96
በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ከ 36 በላይ ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸው ተገለጸ !

ኅዳር 19 ቀን 2016 ዓ.ም (ብ.ሚ. /አዲስ አበባ)

በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ሽርካ ወረዳ በሕገ ወጥ ታጣቂ ኃይሎች ባለፉት 3 ቀናት ብቻ በደረሰ ጥቃት ከ 36 በላይ ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸው ተገልጿል።

ለደህንነታቸው ሲባል ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉት ለማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን መረጃ ያደረሱት ተጎጂዎች እንደገለጹት ከሆነ በሶሌ መድኃኔዓለም እና ሴሮ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ኅዳር 13 ቀን በተፈጸመው አሰቃቂ ግድያ 28 ኦርቶዶክሳዊን መገደላቸው በመጠቆም ኅዳር 17 ቀን 2016 ዓ.ም ደግሞ 8 ምእመናን በድምሩ 36 ምእመናን መገደላቸው ጠቅሰዋል፡፡ በርካቶችም ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው ተጠቁሟል፡፡ 

በሽርካ ወረዳ በተደጋጋሚ ጊዜ በደረሰው ጥቃት ነፍሰጡር ሴትን ጨምሮ ጨቅላ ሕጻናት የተገደሉ ሲሆን የሟቾች ቁጥር አሁንም ሊጨምር እንደሚችል ገልጸዋል።

በአካባቢው ምእመናን ላይ እንዲህ ዓይነት መሰል ጥቃት ሲፈጸም በአንድ ሳምንት ውስጥ ለሶስተኛ ጊዜ በ 2016  ዓ.ም ደግሞ ለአራተኛ ጊዜ መሆኑንም ተናግረዋል ። ጥቃቱ የደረሰባቸው ምእመናን በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ ስጋት ውስጥ የሚገኙ ሲሆን በአካባቢው እየደረሰ ያለውን አሰቃቂ ግድያ አስመልክቶ ለሚመለከታቸው የመንግሥት የጸጥታ አካላት ሀገረ ስብከቱ የማሳወቅ ስራ እንደሚሰራ ተገልጿል ።

#Ethiopia 
#Birana_Media
#BM_Addia_Ababa

ብራና ሚዲያ
የኦርቶዶክሳዊያን ድምፅ

የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/c/BiranaMedia

የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፤ ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ
https://t.me/birana3

በፌስቡክ ገጻችን ትምህርቶች እና ወቅታዊ መረጃዎችን ያግኙ
https://www.facebook.com/birana22

አጫጭር ትምህርታዊ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቲክ ቶክ አማራጫችንን ይመልከቱ
https://www.tiktok.com/@birana16

የኢንስታግራም ገጻችንን
www.Instagram.com/birana96
የደብረ ፀሐይ  ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በከባድ መሣሪያ ተደብድቦ ዘጠኝ ሰዎች ላይ ጉዳት ደረሰ !

ኅዳር 19 ቀን 2016 ዓ.ም (ብ.ሚ. /አዲስ አበባ)

በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሀብሩ-መርሣ ወረዳ ቤተክህነት ጋቲራ ደብረ ፀሐይ  ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በከባድ መሣሪያ ተደብድቦ ዘጠኝ ሰዎች ላይ ጉዳት ደረሰ።

ኅዳር 18 ቀን 2016 ዓ.ም ምሽት 11:00 በሰሜን ወሎ ዞን ውርጌሳ ከተማ ጋቲራ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን የሠርክ ጉባኤ ትምህርት ላይ እያሉ ወደ ቤተክርስቲያኑ በተተኮሰ ከባድ መሣሪያ ዘጠኝ ካህናትና ጸበልተኞች መቁሰላቸውን ወረዳ ቤተክህነቱ ገልጧል።

በትምህርታዊ ጉባኤ ላይ እያሉ በቤተክርስቲያኑ ቅጽረ ግቢ፣ በቤተ ልሔሙና በጸበልተኛ መጠለያ ቤቶች በርካታ ከባድ መሣሪያ ያረፈ ሲሆን በደብሩ አስተዳዳሪ፣ ሰባኬ ወንጌልና በጸበልተኛ ህሙማን ላይ ከባድና ቀላል የመቁሰል አደጋ መድረሱን ከወረዳ ቤተ ክህነቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖች በውርጌሣ ጤና ጣቢያ መታከማቸውንና 3 ሰዎች ለከፍተኛ ህክምና ወደ ደሴ እና ወልድያ ሪፈራል ሆስፒታሎች መላካቸውን ታውቋል።

የከባድ መሣሪያ ተኩሱ በአካባቢው ዛሬም መቀጠሉን የተገለጸ ሲሆን የአብነት ተማሪዎችና ለጸበል የመጡ ህሙማን ከቤተክርስቲያን ወጥተው ተበትነዋል ተብሏል።

በተመሳሳይ በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ጋዞ ወረዳ ቤተክህነት ብርአፋፍ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ኅዳር 16 ቀን 2016 ዓ.ም በከባድ መሣሪያ ጥቃት ሦስት ካህናት ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል።

ዘገባው የሰሜን_ወሎ_ሀገረስብከት_ ሚዲያ ነው

#Ethiopia 
#Birana_Media
#BM_Addia_Ababa

ብራና ሚዲያ
የኦርቶዶክሳዊያን ድምፅ

የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/c/BiranaMedia

የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፤ ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ
https://t.me/birana3

በፌስቡክ ገጻችን ትምህርቶች እና ወቅታዊ መረጃዎችን ያግኙ
https://www.facebook.com/birana22

አጫጭር ትምህርታዊ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቲክ ቶክ አማራጫችንን ይመልከቱ
https://www.tiktok.com/@birana16

የኢንስታግራም ገጻችንን
www.Instagram.com/birana96
የኅዳር ጽዮንን በዓል አክብረው በተመለሱ ሦስት ኦርቶዶክሳውያን ላይ ግድያ ተፈጸመ !

ኅዳር 23 ቀን 2016 ዓ.ም (ብ.ሚ /አዲስ አበባ)

በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በሮቤ ወረዳ ቤተ ክህነት  ወልተኢ  ቀበሌ ገበሬ ማኅበር በደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም  የኅዳር ጽዮንን በዓል አክብረው በሚመለሱ  ሦስት ኦርቶዶክሳውያን ምእመናን ላይ  ግድያ መፈጸሙን ሀገረ ስብከቱ አስታውቋል።

ግድያው የተፈጸመው  ትናንት ኅዳር 21 ቀን 2016 ዓ.ም  ከክብረ በዓሉ ፍጻሜ በኋላ ምሽት 12:00 ሰዓት አካባቢ መሆኑም ተገልጿል።
በግፍ ከተገደሉት ኦርቶዶክሳውያን መካከል አባትና ልጅ የሚገኙበት ሲሆን  ስማቸውም
       1.አቶ ቃኛው ይልማ
       2.አቶ ሙላቱ ቱሉ
       3.አቶ ጌቲ ሙላት  የሚባሉ ሲሆኑ በምሥራቅ አርሲ ዞን በሮቤ ወረዳ ወልተኢ ቀበሌ ገበሬ ማኅበር ነዋሪዎች የነበሩ ናቸውም ተብሏል።

ሀገረ ስብከቱ  የመከራውን ግፍና ኦርቶዶክሳውያን ላይ ያነጣጠሩ ግድያዎች እንዲቆሙ በተደጋጋሚ ለመንግሥት የጸጥታ አካላት እያሳወቀ ቢሆንም እስካሁን ግን ምንም  ሊሻሻል አለመቻሉንም  ገልጿል።

በቅርብ  ወራት ወስጥ በምሥርቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ሥር  በዴራ አማኑኤል  የካህናት ግድያ ፣ ባሳለፍነው ሳምንት ከ ኅዳር 14 ቀን እስከ ኅዳር 17 ቀን 2016 ዓ.ም  በሦስት ቀናት ውስጥ  በተለያዩ ቀበሌዎች 36 ኦርቶዶክሳውያን የተገደሉ ሲሆን  ከነዚህም  ከአንድ ቤተሰብ ብቻ 8 ኦርቶዶክሳውያን በጅምላ መገደላቸው  የሚታወስ ነው።

መረጃው የምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ነው

#Ethiopia 
#Birana_Media
#BM_Addia_Ababa

ብራና ሚዲያ
የኦርቶዶክሳዊያን ድምፅ

የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/c/BiranaMedia

የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፤ ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ
https://t.me/birana3

በፌስቡክ ገጻችን ትምህርቶች እና ወቅታዊ መረጃዎችን ያግኙ
https://www.facebook.com/birana22

አጫጭር ትምህርታዊ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቲክ ቶክ አማራጫችንን ይመልከቱ
https://www.tiktok.com/@birana16

የኢንስታግራም ገጻችንን
www.Instagram.com/birana96
በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት አምስት ኦርቶዶክሳውያን በታጣቂ ኃይሎች በአሰቃቂ ሁኔታ  ተገደሉ።

ኅዳር 24 ቀን 2016 ዓ.ም (ብ.ሚ/አዲስ አበባ)

በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ሽርካ ወረዳ ሄላ ጢጆ ሴሮ ቀበሌ አምስት ኦርቶዶክሳውያን በታጣቂ ኃይሎች በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ።

ግድያው የተፈጸመው ዛሬ ኅዳር 24 ቀን 2016 ዓ.ም ማለዳ ላይ ሲሆን ከሟቾቹም መካከል የ21 ዓመት ወጣትና የ70 ዓመት የእድሜ ባለጸጋ እናት እንደሚገኙበት ከአካባቢው ምእመናን በስልክ ያገኘነው  መረጃ  ይጠቁማል።

ምእመናን ጨምረው እንደገለጹት እስካሁን ማንኛውም የመንግሥት አካል የወሰደው እርምጃ  የለም።

በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ሺርካ ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች ከኅዳር 13 ቀን ጀምሮ ለተከታታይ ቀናት በምእመናኑ ላይ አሰቃቂ ግድያ እየተፈፀመ እንደሚገኝ  መዘገባችን ይታወሳል።
©ማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት

#Ethiopia 
#Birana_Media
#BM_Addia_Ababa

ብራና ሚዲያ
የኦርቶዶክሳዊያን ድምፅ

የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/c/BiranaMedia

የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፤ ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ
https://t.me/birana3

በፌስቡክ ገጻችን ትምህርቶች እና ወቅታዊ መረጃዎችን ያግኙ
https://www.facebook.com/birana22

አጫጭር ትምህርታዊ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቲክ ቶክ አማራጫችንን ይመልከቱ
https://www.tiktok.com/@birana16

የኢንስታግራም ገጻችንን
www.Instagram.com/birana96
ባለፈው ዓመት በሕገወጥ መንገድ "ጵጵስና  ተሹመናል በማለት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ አካላት በዛሬው ዕለት በዚሁ ሕገወጥ መንገድ በመቀጠል "መንበረ ጴጥሮስ" የተባለ ሕገወጥ ቤተ ክህነት መሥርተናል አሉ !

ጥር 14 ቀን 2016 ዓ.ም (ብ.ሚ./አዲስ አበባ)


በኦሮሚያ ክልል ፖለቲካዊ ካባ የደረበ አጀንዳ ይዘው የኢትዮጵቻ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ለመከፋፈል እየተንበሳበሱ የሚገኙት በቀድሞ ስማቸው "አባ" ገ/ማርያም ነጋሳ እና ግብረ አበሮቻቸው ሕገወጥ ተግባራቸውን በመቀጠል "መንበረ ጴጥሮስ" የተባለ ቀኖናዊ መሠረት የሌለው እና ሕገወጥ የሆነ ቤተ ክህነት መሥርተናል ሲሉ ስትራቴጂክ አጋሮቻቸው በሆኑ የሚዲያ ተቋማት አማካይነት በሰጧቸው መግለጫዎች አስታውቀዋል።

 
በቋንቋችን ለመማር እና በነጻነት ለማምለክ ለዘመናት ተከልክለናል በሚል ሀሰተኛ ሽፋን ይህን እንቅስቃሴ እያደረጉ የሚገኙት ነውጠኛ መነኮሳት በመንግስት አደራዳሪነት ችግሩ ተፈትቷል ከተባለ በኋላ የሚያደርጓቸው እንቅስቃሴዎች ስምምነቱን የጣሰ እና በሚዲያዎች እና ቤተ ክርስቲያንን ለማጥፋት በሚጥሩ ኃይሎች ድጋፍ እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ማሳያ ነው።

ልክ የዛሬ ዓመት ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም ሕገኸጥ ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳት በመፈፀም የኦሮሚያና የብሔር ብሔረሰቦች ሲኖዶስ በሚል "አብዮታዊ ዴሞክራሲን" እናት ፍልስፍና አድርጎ ተመሠረተ የተባለው የመነኮሳት ስብስብ በአሁኑ ወቅትም ከ5 በማይበልጡ የቀድሞ መነኮሳት የቤተ ክርስቲያንን አንድነት ለማፍረስ የውክልና እንቅስቃሴ ላይ መሆናቸውን በዛሬው ዕለት ይፋ አድርገዋል።

"ለትግራይና ለአማራ ሲኖዶስ እንዲቋቋም ተፈቅዷል" በማለት ሀሰተኛ እና በቤተ ክርስቲያኒቱ ያልተደረገን ነገር ማስተላለፋቸው ሳያንስ "ለ5 ኪሎ ሲኖዶስ" እንዳትገዙ በማለት ጭምር ሕዝብን በሕዝብ ለማነሳሳት ከፍተኛ ቅስቀሳ እና የጦርነት አዋጅ እያወጁ ይገኛሉ።

#Ethiopia 
#Birana_Media
#BM_Addia_Ababa

ብራና ሚዲያ
የኦርቶዶክሳዊያን ድምፅ

የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/c/BiranaMedia

የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፤ ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ
https://t.me/birana3

በፌስቡክ ገጻችን ትምህርቶች እና ወቅታዊ መረጃዎችን ያግኙ
https://www.facebook.com/birana22

አጫጭር ትምህርታዊ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቲክ ቶክ አማራጫችንን ይመልከቱ
https://www.tiktok.com/@birana16

የኢንስታግራም ገጻችንን
www.Instagram.com/birana96
የደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን የሕንጻ እድሳት ሥራ ተጠናቆ በብፁዕ ወቅዱስ  ፓትርያርኩ ቡራኬ ቅዳሴ ቤቱ ተከበረ።

(አዲስ አበባ / ብ.ሚ. / የካቲት ፱ /፳፻፲፮ ዓ/ም)

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጥንታዊው የደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን የሕንጻ ዕድሳት ሥራ ተጠናቆ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ተባርኮ ታቦተ ሕጉ ከመቃኞ ቤተመቅደስ ወደ ጥንታዊ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን በዛሬ ዕለት  ገብቷል።

በክብረ በዓሉ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የባሕርዳርና ሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት  ሊቀ ጳጳስ፣ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣  እንዲሁም በርካታ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የጠቅላይ ቤተክህነት የመምሪያ ሐላፊዎች ፣ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስቅዱስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣  የሀገረ ስብከቱ እና የክፍላተ ከተማው የክፍል ኃላፊዎችና ሠራተኞች፣ የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች ምእመናንና እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

ለረጅም ዓመታት ዕድሳት ሳይደረግለት በመቆየቱ ለጉዳት የተዳረገው ጥንታዊውና ታሪካዊው የደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን ኅዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም ታቦታቱ ወደ አዲሱ መቃኞ ቤተክርስቲያን ገብቶ ጥንታዊ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን እድሳት ሲደረግለት መቆየቱ ይታወቃል።

የደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን ፲፰፻፸፭(1875) ዓ/ም በወቅቱ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት በነበሩት  በአፄ ምኒልክ ዳግማዊ  አማካኝነት እንደተሠራ ታሪክ ያስረዳል።


#Ethiopia 
#Birana_Media
#BM_Addia_Ababa

ብራና ሚዲያ
የኦርቶዶክሳዊያን ድምፅ

የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/c/BiranaMedia

የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፤ ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ
https://t.me/birana3

በፌስቡክ ገጻችን ትምህርቶች እና ወቅታዊ መረጃዎችን ያግኙ
https://www.facebook.com/birana22

አጫጭር ትምህርታዊ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቲክ ቶክ አማራጫችንን ይመልከቱ
https://www.tiktok.com/@birana16

የኢንስታግራም ገጻችንን
www.Instagram.com/birana96
ሰበር መረጃ

በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በሚገኘው ጥታዊው የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም እራሱን ኦነግ ሸኔ ብሎ በሚጠራው ቡድን የገዳሙን መጋቢ ጨምሮ አራት አባቶችን መግደሉን ገዳሙ አስታውቋል፡፡
ሰኞ የካቲት 11 ቀን 2016 ዓመተ ምሕረት ታጣቂዎቹ ሦስት አባቶችን አግተው ወደ በረሃ ከወሰዱ በኋላ የታገቱትን ለማስለቀቅ ገዳሙ ጥረት በሚያርግበት ወቅት የካቲት 13 ቀን 2016 ዓ.ም ተጨማሪ አባቶችን በመያዝ
1.  የገዳሙ መጋቢ አባተክለማርያም ዐሥራት
2.  የገዳሙ ጸሐፊ አባ ኪዳነ ማርያም ጥላሁን
3.  የገዳሙ የመጽሐፍ መምህርና ቀዳሽ አባ ገ/ማርያም አበበ
4.  በአመክሮ የሚኖሩ መናኝ ኃይለማርያም ወልደሰንበት
የተባሉት የገዳሙ የሥራ ኃላፊዎች እንደተገደሉና አብረው ከነበሩት አንድ አባት ብቻ ማምለጥ መቻላቸውን እንደተረዱ የገዳሙ ኃላፊዎች ለኢኦተቤ ቴቪ (EOTC TV) ገልጸዋል፡፡
የገዳሙ የሥራ ኃላፊዎች ቡድኑ ከዚህ ቀደም ገዳሙን በመዝረፍ ለከፋ ችግር አጋልጦት መቆየቱን አስታውሰው ገዳሜ ጸጥታውን የሚያስከብረበት  መሣሪያች በቡድኑ በመወረሳቸው ለከፋ የጸጥታ ችግር መጋለጡን ገልጸዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ገዳማውያ በስጋት ላይ መሆናቸውንና የመንግሥት የጸጥታ አካላትን እገዛ እንደሚሹ አስታውቀው መረጃውንም በየደረጃው ለሚገኙ የሀገረ ስብከቱና የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ማሳወቃቸውን ገልጸዋል፡፡
©️EOTC TV

#Ethiopia 
#Birana_Media
#BM_Addia_Ababa

ብራና ሚዲያ
የኦርቶዶክሳዊያን ድምፅ

የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/c/BiranaMedia

የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፤ ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ
https://t.me/birana3

በፌስቡክ ገጻችን ትምህርቶች እና ወቅታዊ መረጃዎችን ያግኙ
https://www.facebook.com/birana22

አጫጭር ትምህርታዊ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቲክ ቶክ አማራጫችንን ይመልከቱ
https://www.tiktok.com/@birana16

የኢንስታግራም ገጻችንን
www.Instagram.com/birana96
በታላቁ ዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም የተፈፀመውን ጥቃት አስመልክቶ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ በተገኙበት ከመንግሥት አካላት ጋር ውይይት ተካሄደ፡፡

 የካቲት 15 ቀን 2016 ዓ.ም. ( ብ.ሚ./ አዲስ አበባ )       

በጥንታዊውና ታሪካዊ ዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም የተፈፀመውን የመነኮሳት ግድያ   አስመልክቶ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት በምሥራቅ ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አባቡ ዋቆ መሪነት ተካሂዷል።

በውይይቱ  የምሥራቅ ሸዋ ዞን የጸጥታ ክፍል ከፍተኛ ኃላፊዎች፣ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ም/ሥራ አስኪያጅ በሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኮነን የተመራ ልዑክ፣የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም አበምኔትና የገዳሙ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የሀገረ ስብከቱ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡

በግፍ የሰማዕትነትን ጽዋ የተቀበሉ አባቶች መርዶ በትናንትናው ዕለት የተሰማ ሲሆን በመላው ዓለም የሚገኙ ኦርቶዶክሳውያን ሀዘናቸውን በመሪር እንባ እየገለጹ ይገኛሉ።

የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከትም ከገዳሙ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በትኩረት ጉዳዩን ሲከታተል የቆየ ሲሆን በዛሬ ዕለትም በቢሾፍቱ ከተማ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ አየር ኃይል ግቢ ዐራት ሰዓታትን የፈጀ ሰፊ ውይይት ሲደረግ ቆይቷል፡፡

በውይይቱ የተቀመጡ የመፍትሔ ሃሳቦች፡-

1ኛ፡- በመንግሥት የፀጥታ አካላት አማካኝነት  የሰማዕታቱን አስክሬን ከወደቁበት አንስቶ በክብር ወደ ገዳሙ በማምጣት ሥርዓተ ቀብር እንዲፈፀምላቸው

2ኛ-  በቋሚነት በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሀገር መከላከያ ሠራዊትና በኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ጸጥታ መዋቅር ገዳሙንና ገዳማውያንን በዘላቂነት መጠበቅ እንዲቻል

3ኛ፡- በመንግሥትና በሀገረ ስብከቱ እንዲሁም በቤተክርስቲያን አባቶች ልባቸው የተሠበረና የተጎዱ የገዳሙ አባቶችና እናቶችን በጋራ ማጽናናት እንዲችል፡፡

የውይይቱ  የውሳኔ ሃሳቦች ሲሆኑ ይኼው ግብረ ኃይል ከሀዘኑ በኋላ ዳግም ተገናኝቶ በተሠሩ ሥራዎችና ወደ ፊት አስተማማኝ ሰላም በሚሠፍንበት ጉዳይ ላይ ለመመካከር ቀጠሮ ተይዞ በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የዕለቱ ውይይት በጸሎት ተዘግቷል፡፡

     ዘገባው የሀገረ ስብከቱ ሐመረ ተዋሕዶ ሚዲያ ነው

#Ethiopia 
#Birana_Media
#BM_Addia_Ababa

ብራና ሚዲያ
የኦርቶዶክሳዊያን ድምፅ

የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/c/BiranaMedia

የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፤ ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ
https://t.me/birana3

በፌስቡክ ገጻችን ትምህርቶች እና ወቅታዊ መረጃዎችን ያግኙ
https://www.facebook.com/birana22

አጫጭር ትምህርታዊ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቲክ ቶክ አማራጫችንን ይመልከቱ
https://www.tiktok.com/@birana16

የኢንስታግራም ገጻችንን
www.Instagram.com/birana96
ኪዳነ ምሕረት

በድንቅ ጥበቡ እግዚአብሔር አምላክ ዓለምን ያደነው እጅጉን መሐሪ ስለሆነ ነው፡፡ የቀደሙት የብሉይ ኪዳን ኪዳናት ሕዝቡን ከሲኦል መታደግ አልቻሉም ነበር፡፡ ፍጹም የሆነው ኪዳን የተደረገው በሰባተኛው ኪዳን ይህም ለሰው ዘር ምሕረትን ባስገኝች በንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም ነው፡፡  
 
የምሕረት ቃል ኪዳን የተሰጠችውን እናታችንንም ‹‹ኪዳነ ምሕረት›› እያልን የምንማጸናት ለዚህ ነው፡፡ ለአዳም የተገባለት የምሕረት ቃል በእርሷ ተፈጽሟልና፡፡ እመቤታችን አምላክን በድንግልና ፀንሳ በድንግልና ወልዳዋለችና፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መከራን ተቀብሎ እንዲሁም በመስቀል ተሰቅሎ ዓለምን ያዳነው ከእርሷ በነሣው ሥጋና ነፍስ ነውና፡፡  
 
በነገረ ማርያም ተጽፎ እንደምናገኘው ከጌታችን ከመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዕርገት በኋላ እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ልጇ መቃብር ቦታ ጎልጎታ እየሄደች ትጸልይ ስለ ነበር  በየካቲት ፲፮ ቀን በጸለየችው ጸሎት ቃል ኪዳን ገብቶላታል፡፡ ጸሎቷም እንዲህ የሚል ነበር፤ ‹‹ልጄ ወዳጄ ሆይ፥ ከሥጋዬ ሥጋ ከነፍሴ ነፍስ ነሥተህ ሰው በመሆንህ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በቻለችህ ማኅፀኔ ከአንተ ጋር ሀገር ለሀገር ስለ መሰደዴ መጥተህ ልመናዬን ትሰማኝ ዘንድ እለምንሃለሁ፡፡››
 
ጌታችንም ምን ሊያደርግላት እንደምትሻ ሲጠይቃት በስሟ ለሚማጸኑ፣ መታሰቢያዋን ለሚያደርጉ፣ ለችግረኛ ለሚራሩ፣ በስሟ ቤተ ክርስቲያን ለሚያንጹ፣ ዕጣን፣ ዘይትና መብአ ለቤተ ክርስቲያን ለሚሰጡ ምሕረትን እንዲያደርግላቸው ጨምራ ጠየቀችው፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በየካቲት ፲፮ ዕለት የገባላትን ቃል ኪዳን እንዲህ በማለት በመሐላ አጽንቶታል፡፡  ‹‹መሐልኩ ለኪ በርእስየ ወበአቡየ ወበመንፈስ ቅዱስ ሕያው፤ በራሴ፣ በአባቴ እና በመንፈስ ቅዱስ ማልኩልሽ፡፡›› 

የምሕረት ቃል ኪዳን የተሰጠበት ይህ ዕለት ታላቅ ነውና ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በድምቅት ታከብረዋለች፡፡ ቀድሞ ለነበሩ ኪዳናት ማለትም ኪዳነ አዳም፣ ኪዳነ ኖህ፣ ኪዳነ መልከ ጸዴቅ፣ ኪዳነ አብርሃም፣ ኪዳነ ሙሴና ኪዳነ ዳዊት መደምደሚያ ነውና፡፡ ዘለዓለማዊ ስለ ሆነው የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳን እየታሰበም በመዝሙር፣ በማኅሌትና በቅዳሴ ይከበራል፡፡
 
በክርስቶስ ክርስቲያን ለምንባል ለእኛ የሐዲስ ኪዳን የቤተ ክርስቲያን ልጆችም ይህ አዲስ ውል የተደረገልን ለነፍሳችን ድኅነት በመሆኑ በስሟ እየተማጸንን እንዲሁም መታሰቢያዋን እያደረግን ለተራቡት ማብላት፣ ለተጠሙት ማጠጣትና ችግረኛ መርዳት ይገባናል፡፡  

የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ጸሎት፣ አማላጅነትና ተረዳኢነት አይለየን፤ አሜን! 


#Ethiopia 
#Birana_Media
#BM_Addia_Ababa

ብራና ሚዲያ
የኦርቶዶክሳዊያን ድምፅ

የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/c/BiranaMedia

የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፤ ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ
https://t.me/birana3

በፌስቡክ ገጻችን ትምህርቶች እና ወቅታዊ መረጃዎችን ያግኙ
https://www.facebook.com/birana22

አጫጭር ትምህርታዊ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቲክ ቶክ አማራጫችንን ይመልከቱ
https://www.tiktok.com/@birana16

የኢንስታግራም ገጻችንን
www.Instagram.com/birana96
"ግብረ ሰዶማውያን ንስሐ እስኪገቡ ድረስ ማስጠንቀቂያ ሊሰጣቸውና ከሕብረት ሊከለከሉ ይገባል" የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ

የካቲት 29 ቀን 2016 ዓ.ም (ብ.ሚ./አዲስ አበባ)

የኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በትናንትናው እለት በዋዲ አል ናትሩ በሚገኘው አባ ቢሾይ ገዳም ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ በልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ ያሳለፈ ሲሆን በአጀንዳነት ከያዛቸው ጉዳዮች መካከል የግብረሰዶማውያን ጉዳይን የተመለከተው አጀንዳ ይገኝበታል።

ቅዱስ ሲኖዶሱ ግብረሰዶማዊነትን አጥብቆ እንደሚቃወም እና ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለው ከሰው ተፈጥሯዊ ባሕርይ ውጭ የሆነ ፣ ከሕገ እግዚአብሔር የራቀ መሆኑን በመግለጫው አመላክቷል።

በግብረ ሰዶም ተግባር የወደቀ ማንኛውም ሰው እውነተኛ ንስሐ ፣ መንፈሳዊ እና ሥነ ልቦናዊ ክትትል ያስፈልጋቸዋል ያለው ቅዱስ ሲኖዶሱ መንፈሳዊና ሥነ ልቦናዊ ድጋፍን አለመቀበል እና በግብረ ሰዶማዊነት ለመቀጠል እና የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ለመጣስ የሚሞክር በዝሙት ከሚኖር ሰው ይልቅ ሁኔታው ​​ይከፋል ያለ ሲሆን ስለዚህ በዚህ ሕይወት የሚኖሩ ሰዎች ንስሐ እስከሚገቡ ድረስ ማስጠንቀቂያ ሊሰጣቸውና ከሕብረት ሊከለከሉ ይገባል በማለት ገልጿል።

ቤተክርስቲያን ተመሳሳይ ጾታ ባላቸው ሁለት ሰዎች መካከል ያለውን የጾታ ግንኙነት ታወግዛለች ፣ ታስጠነቅቃለች ፣ ትከለክላለች  ያለው ቅዱስ ሲኖዶሱ የኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በግብረሰዶም ዝንባሌ የሚሰቃዩ ልጆቿን ከዚህ ሕይወት እንዲወጡ በመርዳት ረገድ ያላትን የኖላዊነት ሚና ፣ እንዲሁም እነሱን ባሉበት ሁኔታ አለመቀበሏን ወይም እንዲወጡ ድጋፍና እገዛን በማድረጓ ሥነ ልቦናዊና መንፈሳዊ ፈውስ ለመስጠት የምታደርገውን ጥረት በመደገፍ እምነትዋን በጽናት ታረጋግጣለች ብሏል።


#Ethiopia 
#Birana_Media
#BM_Addia_Ababa

ብራና ሚዲያ
የኦርቶዶክሳዊያን ድምፅ

የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/c/BiranaMedia

የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፤ ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ
https://t.me/birana3

በፌስቡክ ገጻችን ትምህርቶች እና ወቅታዊ መረጃዎችን ያግኙ
https://www.facebook.com/birana22

አጫጭር ትምህርታዊ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቲክ ቶክ አማራጫችንን ይመልከቱ
https://www.tiktok.com/@birana16

የኢንስታግራም ገጻችንን
www.Instagram.com/birana96
"#የትናንት ሊቃውንት አባቶቻችን ጦም እያደሩ  የጠበቋትን ቤተ ክርስቲያን እኛ እየበላን አሳልፈን መስጠት አይገባም"  ብፁዕ አቡነ አብርሃም

ከ200 በላይ የአብነት መምህራን የተሳተፉበት የምክክር ጉባኤ በመንበረ ፓትርያርክ ጽርሐ ተዋሕዶ እየተካሔደ ይገኛል።

አዲስ አበባ (ግንቦት ፲፭/፳፻፲፮ ዓ/ም / ብራና ሚድያ )

በመንበረ ፓትርያርክ ትምህርትና ማሰልጠኛ መምሪያ ከሊቃውንት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው  ሀገር አቀፍ የምክክርና የውይይት ጉባኤ ማካሔዱን ጀምሯል።

በመርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ የበላይ ሊቀ ጳጳስ፣የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ሐላፊዎች  ከየ አህጉረ ስብከቱ የመጡ ከ200 በላይ ሊቃውንት ቤተ ክርስቲያንና የጉባኤ መምህራን  ተገኝተዋል።

ጉባኤው በጸሎተ ወንጌል የተጀመረ ሲሆን በማስከተልም የደብረ ምሕረት ሰአሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያምና ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ካቴድራል ሊቃውንት
"ያሬድ ካህኑ ለእግዚአብሔር
ትርድአነ ነዐ በህየ መካኑ ያሬድ ነዐ ትርድአነ" የሚለውን ወረብ አቅርበዋል።

የመምሪያው ሐላፊ  መልአከ መዊዕ ሳሙኤል እሸቱ ሊቃውንቱ ከየጉባኤ ቤቱ የመጡትን ሊቃውንት አስተዋውቀዋል።
በዚህም የድጓ፣ የዝማሬ መዋስዕት ፣ የቅኔ ፣የአቋቋም ፣ የሐዲሳትና የብሉያት  መጻሕፍት ትርጓሜ መምህራን መሆናቸው ተገልጿል።

መልአከ መዊዕ ሳሙኤል እሸቱ ለጉባኤ መሳካት የበኩሉን ድርሻ የተወጡትን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የትምህርትና ስልጠና ዋና ክፍልንና ሌሎችን አመስግነዋል።

አክለውም ጉባኤ  ሁልጊዜ በየዓመቱ ከግንቦቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት ከመጀመሩ በፊት ጉባኤ እንዲዘጋጅና እውቅና እንዲሰጠው ጥያቄ አቅርበዋል።

የእንኳን ደህና መጣችሁ አባታዊ መልእክት ያስተላለፉት ብፁዕ አቡነ አብርሃም  ብዙ ኪሎ ሜትሮችን አልፈው ወቅታዊ የሀገሪቱ ሁኔታ ተቋቁመው   የተገኙትን ሊቃውንት እንኳን ደህና መጣችሁ ያሉ ሲሆን የምክክር ጉባኤውን  ያሰናደውን የትምህርት ማሰልጠኛ መምሪያ  አመስግነዋል።

ብፁዕነታቸው  አክለውም ለዘመናት የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን አባቶች ቤተ ክርስቲያናችንን በበላይነት በሚመሩበት ጊዜ  "አማኙን ከሀገሩ" "እምነቱን ከታሪኩ" ጠብቀው ያቆዩ ሊቃውንት መሆናቸውን በማስታወስ አሁንም የበኩላችሁን የሊቅነት ድርሻችሁን በመወጣት ቤተ ክርስቲያናችንን ልታስከብሩ ይገባል ብለዋል።

በዚህ ዘመን በሕይወት የሚያገለግሉትን ሊቃውንት በኑሯቸውም ልናስባቸውና የት አሉ ልንል ይገባልም ብለዋል።

"የትናንት ሊቃውንት አባቶቻችን ጦም እያደሩ  የጠበቋትን ቤተ ክርስቲያን እኛ እየበላን አሳልፈን መስጠት አይገባም" ሲሉ ገልጸዋል።

ስለሆነም ሊቅነትን ከቤተ ክርስቲያን ተልእኮ ውጤት ጋር በማጣመር ዘመኑን የዋጀና ትውልዱን የሚያተርፍ  አገልግሎት እንድታገለግሉ ወደፊት መምጣት ይገባችኋል ብለዋል።
 
ጉባኤው ለሁለት ቀናት የሚቆይ እንደሆነ ከወጣው መርሐ ግብር ለማወቅ ተችሏል።
#Ethiopia 
#Birana_Media
#BM_Addia_Ababa

ብራና ሚዲያ
የኦርቶዶክሳዊያን ድምፅ

የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/c/BiranaMedia

የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፤ ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ
https://t.me/birana3

በፌስቡክ ገጻችን ትምህርቶች እና ወቅታዊ መረጃዎችን ያግኙ
https://www.facebook.com/birana22

አጫጭር ትምህርታዊ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቲክ ቶክ አማራጫችንን ይመልከቱ
https://www.tiktok.com/@birana16

የኢንስታግራም ገጻችንን
www.Instagram.com/birana96