ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ Balderas for Democracy
2.03K subscribers
951 photos
14 videos
3 files
138 links
Political party
Download Telegram
አቶ ናትናኤል ያለምዘውድ ነገ ፍ/ቤት ይቀርባሉ

የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ እና የስራአስፈፃሚ አባል የሆኑት አቶ ናትናኤል ያለምዘውድ በብልፅግና አገዛዝ የፀጥታ ሀይሎች ከታፈኑ ከሁለት ወራት በላይ መቆየታቸው ይታውሳል።

የግፍ እስረኛው በአገዛዙ ከታፈኑበት መጋቢት 27/2016 ዓ.ም እስከ መጋቢት 30/2016 ዓ.ም በቀጨኔ ፖሊስ ጣቢያ እና በጉለሌ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ (ላዛሪስት) የቆዩ ቢሆንም፣ ከመጋቢት 30/2016 ዓ.ም ጀምሮ ግን ወደ አዋሽ አርባ የእስረኞች ማጎሪያ ተወስደው ሲጉላሉ ቆይተዋል። ፖሊስ የግፍ እስረኛውን በግንቦት 30/2016 ዓ.ም በድጋሚ ወደ አ.አ አምጥቷቸዋል።

አቶ ናትናኤል በአዋሽ ፣ሸርባ በቆዩበት ጊዜያት ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት የደረሰባቸው ሲሆን፣ በጤንነታቸውም ላይ ከፍተኛ እክል ገጥሟቸዋል።

የግፍ እስረኛው ናትናኤል ያለምዘውድ ከአዋሽ አርባ ተመልሰው ትላንት ሰኔ 3/2016 ዓ.ም ፍ/ቤት የቀረቡ ሲሆን፤  ከሌሎች 8 እስረኞች ጋር 'ሁከት እና ብጥብጥ በማነሳሳት መንግስት እና ህገመንግስታዊ ስርአት ለማናድ' የሚል ውንጀላ በፖሊስ ቀርቦባቸዋል። ፖሊስ በተጨማሪም የእስከ አሁኑን መጉላላት ሳይቆጥር ተጨማሪ 14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ጠይቆባቸዋል።

የተከሳሾቹ ጠበቆች በበኩላቸው የግፍ እስረኞቹ ከታሰሩ ከ70 እስከ 80 ቀናት መቆየታቸውን ጠቅሰው፣ ፖሊስ በዚህ ጊዜ ውስጥ ያላሳካውን ምርመራ ከዚህ በኋላም ተጨማሪ  ጊዜ ቢሰጠው ሊፈፅም እንደማይችል አስረድተዋል።

ጠበቆቹ በተጨማሪም ፖሊስ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ያዝኳቸው ያላቸውን ሰዎች ከግንቦት 27 ጀምሮ ፍ/ቤት እያቀረበ ቢሆንም እነአቶ ናትናኤልን  ግን ለይቶ  እስከ ሰኔ 3/2016 ዓ.ም ድረስ አንዳላቀረባቸው ገልፀዋል። ይህም ፖሊስ በህገ መንግስቱ ላይ የተቀመጠውን በ48 ሰአታት ውስጥ ፍ/ቤት የመቅረብ መብታቸውን መንፈጉን ያሳየ እንደሆነ ጥቅሰው ተከራክረዋል። ጠበቃዎቹ አክለውም "ፖሊስ ህገመንግስቱን እየጣሰ መልሶ እነ አቶ ናትናኤልን ሕገመንግስታዊ ስርአት በመናድ በሚል በሀሰት ከሷል"  በማለት አስረድተዋል።

ስለሆነም ፖሊስ የጠየቀው ተጨማሪ የምርመራ ቀናት በፍፁም መፈቀድ የለበትም ሲሉ ተከራክረዋል።

ፖሊስ ከሁለት ወራት በላይ በግፍ እስር ላይ የቆዩት አቶ ናትናኤልን በ48 ሰዓታት ውስጥ ለምን ፍ/ቤት እንዳላቀረበ ሲጠየቅ፣ ምንም እንኳን ከአዋሽ አርባ-አዲስ አበባ የ5 ወይም 6 ሰአታት ጊዜ ብቻ
ቢፈጅም" እስረኛውን ለማጓጓዝ ጊዜ ስለፈጀብኝ ነው" በሚል አስተባብሏል።

ፍ/ቤቱ ፖሊስ የጠየቀውን የ14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እና የጠበቆችን የተቃውሞ ክርክር ከሰማ በኋላ ብይን ለመስጠት ለነገ ሰኔ 5/2014 ዓ.ም ቀጥሯል።
አቶ ናትናኤል ያለምዘውድ ነገ ፍ/ቤት ይቀርባሉ

የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ እና የስራአስፈፃሚ አባል የሆኑት አቶ ናትናኤል ያለምዘውድ በብልፅግና አገዛዝ የፀጥታ ሀይሎች ከታፈኑ ከሁለት ወራት በላይ መቆየታቸው ይታውሳል።

የግፍ እስረኛው በአገዛዙ ከታፈኑበት መጋቢት 27/2016 ዓ.ም እስከ መጋቢት 30/2016 ዓ.ም በቀጨኔ ፖሊስ ጣቢያ እና በጉለሌ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ (ላዛሪስት) የቆዩ ቢሆንም፣ ከመጋቢት 30/2016 ዓ.ም ጀምሮ ግን ወደ አዋሽ አርባ የእስረኞች ማጎሪያ ተወስደው ሲጉላሉ ቆይተዋል። ፖሊስ የግፍ እስረኛውን በግንቦት 30/2016 ዓ.ም በድጋሚ ወደ አ.አ አምጥቷቸዋል።

አቶ ናትናኤል በአዋሽ ፣ሸርባ በቆዩበት ጊዜያት ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት የደረሰባቸው ሲሆን፣ በጤንነታቸውም ላይ ከፍተኛ እክል ገጥሟቸዋል።

የግፍ እስረኛው ናትናኤል ያለምዘውድ ከአዋሽ አርባ ተመልሰው ትላንት ሰኔ 3/2016 ዓ.ም ፍ/ቤት የቀረቡ ሲሆን፤  ከሌሎች 8 እስረኞች ጋር 'ሁከት እና ብጥብጥ በማነሳሳት መንግስት እና ህገመንግስታዊ ስርአት ለማናድ' የሚል ውንጀላ በፖሊስ ቀርቦባቸዋል። ፖሊስ በተጨማሪም የእስከ አሁኑን መጉላላት ሳይቆጥር ተጨማሪ 14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ጠይቆባቸዋል።

የተከሳሾቹ ጠበቆች በበኩላቸው የግፍ እስረኞቹ ከታሰሩ ከ70 እስከ 80 ቀናት መቆየታቸውን ጠቅሰው፣ ፖሊስ በዚህ ጊዜ ውስጥ ያላሳካውን ምርመራ ከዚህ በኋላም ተጨማሪ  ጊዜ ቢሰጠው ሊፈፅም እንደማይችል አስረድተዋል።

ጠበቆቹ በተጨማሪም ፖሊስ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ያዝኳቸው ያላቸውን ሰዎች ከግንቦት 27 ጀምሮ ፍ/ቤት እያቀረበ ቢሆንም እነአቶ ናትናኤልን  ግን ለይቶ  እስከ ሰኔ 3/2016 ዓ.ም ድረስ አንዳላቀረባቸው ገልፀዋል። ይህም ፖሊስ በህገ መንግስቱ ላይ የተቀመጠውን በ48 ሰአታት ውስጥ ፍ/ቤት የመቅረብ መብታቸውን መንፈጉን ያሳየ እንደሆነ ጥቅሰው ተከራክረዋል። ጠበቃዎቹ አክለውም "ፖሊስ ህገመንግስቱን እየጣሰ መልሶ እነ አቶ ናትናኤልን ሕገመንግስታዊ ስርአት በመናድ በሚል በሀሰት ከሷል"  በማለት አስረድተዋል።

ስለሆነም ፖሊስ የጠየቀው ተጨማሪ የምርመራ ቀናት በፍፁም መፈቀድ የለበትም ሲሉ ተከራክረዋል።

ፖሊስ ከሁለት ወራት በላይ በግፍ እስር ላይ የቆዩት አቶ ናትናኤልን በ48 ሰዓታት ውስጥ ለምን ፍ/ቤት እንዳላቀረበ ሲጠየቅ፣ ምንም እንኳን ከአዋሽ አርባ-አዲስ አበባ የ5 ወይም 6 ሰአታት ጊዜ ብቻ
ቢፈጅም" እስረኛውን ለማጓጓዝ ጊዜ ስለፈጀብኝ ነው" በሚል አስተባብሏል።

ፍ/ቤቱ ፖሊስ የጠየቀውን የ14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እና የጠበቆችን የተቃውሞ ክርክር ከሰማ በኋላ ብይን ለመስጠት ለነገ ሰኔ 5/2014 ዓ.ም ቀጥሯል።
የግፍ እስረኛው አቶ ናትናኤል ያለምዘድ ላይ 12 ቀናት ተሰጠባቸው

በግፍ እስር ላይ ይሚገኙት የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ እና የስራ አስፈፃሚ አባል አቶ ናትናኤል ያለምዘውድ ለዛሬ ፍ/ቤት እንደሚቀርቡ መዘገባችን ይታወሳል። በቀጥሯቸው መሰረትም ዛሬ ሰኔ 5/2016 ዓ.ም በአራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርበዋል።

ችሎቱ ከትላንት በስቲያ ፖሊስ የጠየቀውን የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜና የእስረኞች ጠብቆች ያቀረቡትን መቃወሚያ መርምሮ ብይን ለመስጠት ነበር የተሰየመው። በዚህም መሰረት ፍ/ቤቱ በእነ አቶ ናትናኤል ያለምዘውድ ላይ ተጨማሪ 12 ቀናት የምርመራ ጊዜ ፈቅዶባቸዋል።

ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ በስራ አፈፃሚ አባሉ አቶ ናትናኤል ያለምዘውድ ፣ በሚዲያ ክፍል ጋዜጠኛው ወንድምነው አድማስ እንዲሁም በሌሎች የግፍ እስረኞች ላይ እየደረሰ የሚገኘውን በደል እና ኢ-ሠብአዊ ድርጊት አጥብቆ ያወግዛል። በአስቸኳይ እንዲፈቱም ያሳስባል።

የግፍ እስረኞች ይፈቱ!
እነ ናትናኤል ያለምዘውድ ለሰኞ ተቀጠሩ

ከትላንት በስቲያ የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ እና የስራ አፈፃሚ አባል የሆኑት አቶ ናትናኤል ያለምዘውድ 12 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እንደተሰጠባቸው መዘገባችን ይታወሳል።  ይህንን የፍ/ቤቱን ውሳኔ በመቃወም የተከሳሾቹ ጠበቆች ይግባኝ ብለው ነበር።

በዚህም መሰረት በግፍ እስር ከሁለት ወራት በላይ የቆዩት አቶ ናትናኤል ያለምዘውድና ሌሎች በአባሪነት የተያዙ 8 ሰዎች ዛሬ በአራዳ ምድብ የይግባኝ ሰሚ ችሎት ቀርበዋል። በችሎቱ ፖሊስ ለቀረበው ይግባኝ መልስ ነው ያለውን በፅሁፍ ይዞ የቀረበ ሲሆን፤ ፖሊስ ባቀረበው መልስ ላይም የቃል ክርክር ተደርጎበታል።

የግፍ እስረኞቹ ጠበቆች ፖሊስ በፅሁፍ ይዞ የቀረበው መልስ አሳማኝ አለመሆኑን አስረድተዋል። እንደ ማሳያም ፖሊስ ከተቋማት የምጠብቀው ደብዳቤዎች አሉ ያለው ምክንያት ልክ እንዳልሆነ ጠቅሰዋል።

ፖሊስ እየተሰበሰበ ያለውን ማስረጃ ማስተንተን ይቀረኛል በሚል ያቀረበውን ምላሽ በሚመለከት የስነ ስርዐት ህጉ ማስረጃ እስኪሰበሰብ ድረስ ለምርመራ አላማ ብቻ ተጠርጣሪዎች  በእስር ሆነው ምርመራ ሊከናወን ይችላል እንጂ የተሰበሰበውን ማስረጃ ማስተነተን ይቀረኛል በሚል ጊዜ ቀጠሮ መጠየቁ ኢ-ስነስርዐታዊ ነው በሚል ከጠበቆቹ ምላሽ ተሰጥቷል፡፡  ሌላው ያልተያዙ አባሪዎችን እስክንይዝ ድረስ ይግባኝ ባዮች በእስር ይቆዩልኝ የሚለው መከራከሪያም ፖሊስ በውጪ ሀገር የሚገኙ አባሪዎችን ብሎ በጠቀሰበት ሁኔታ፤ አባሪዎችን ከውጪ እስኪያመጣ ድረስ በሚል ይግባኝ ባዮች በእስር የሚቆይበት የህግ መሠረትየለም የሚል ክርክር ቀርቧል፡፡

ፖሊስ "ከተቋማት የምጠብቀው የምርመራ ውጤት አለ" የሚለው በፍፁም ልክ ያልሆነ መከራከሪያ እንዳልሆነ ጠቅሰዋል። መረጃዎች አንዴ ተሰብስበው ከሄዱ በኋላ የግፍ እስረኞቹ በዋስ ቢወጡ እንኳን፤ በእነዚህ ትላልቅ ተቋማት ላይ ምንም አይነት ተፅዕኖ ማድረግ እንደማይችሉ እና ደብዳቤ ለመሰብሰብም የእነርሱ በእስር መቆየት አላስፈላጊ መሆኑን የተከሳሽ ጠበቆች አንስተው ተከራክረዋል።

በተጨማሪም የተከበሩ ጠበቆች የግፍ እስረኞቹ ከ70 እስከ 80 ቀናት በእስር ላይ ቢቆዩም ምርመራው ምንም አይነት እድገት ያላሳየ ሲሆን፣ ፖሊስ በእስር በቆዩበት ጊዜ አዋሽ አርባ ድረስ ሄዶ ቃል መቀበሉ እና በቂ የምርመራ ጊዜ እንደነበረው አስረድተዋል።

ጠበቆቹ አክለውም ፓሊስ ለክስ መነሻ ሆኖኛል የሚለው ሶሻል ሚዲያው ሆኖ ሳለ እና በሶሻል ሚዲያ ላይ ተጋርተው የነበሩ ልጥፎችን አንዴ ከወሰደ በኋላ መረጃ ያጠፋሉ ማለት ልክ አለመሆኑን ጠቅሰው ተከራክረዋል።

አያይዘውም ከዚህ በፊት በክሱ ላይ ከተዘረዘሩት የግፍ እስረኞች መሀል ስድስቱ ፍ/ቤት ቀርበው ጉዳያቸው እየታየ ከነበረበት፣ ሂደቱ ተቋርጦ ወደ አዋሽ አርባ መጋዛቸውን ተናግረዋል። አያይዘውም የግፍ እስረኛው ናትናኤል ያለምዘውድም አካልን ነፃ የማውጣት ክስ ተከፍቶ ውሳኔ ከተሰጠ በኋላ፤ ውሳኔው ሳይከበር ወደ አዋሽ አርባ መውሰዳቸውን አስታውሰዋል።

የተከበሩ ጠበቆች ከላይ የተጠቀሱትን እና ሌሎች የመከራከሪያ ነጥቦችን ካስረዱ በኋላ፤ የስር ፍ/ቤቱ ያስተላለፈው ውሳኔ ተሽሮ የግፍ እስረኞቹ በዋስ እንዲለቀቁ ጥያቄ አቅርበዋል። ግራ ቀኙን የሰማው ችሎቱ ውሳኔ ለመስጠት ለሰኞ 5 ሰዓት ቀጥሯል።
#ሰበር

አቶ ናትናኤል ያለምዘውድ በ30 ሺህ ብር ዋስ እንዲወጡ ተወሰነ

የባልደራስ ፓርቲ የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ እና የስራ አስፈፃሚ አባል የሆኑት አቶ ናትናኤል ያለምዘውድ ለዛሬ ሰኔ 10/2016 ዓ.ም በዋስትና ላይ ውሳኔ ለመስጠት መቀጠራቸውን መዘገባችን ይታወሳል።

የግፍ እስረኛው በቀጠሯቸው መሰረት አብረዋቸው ከታሰሩት ሌሎች 8 የግፍ እስረኞች ጋር ፍ/ቤት የቀረቡ ሲሆን። ዘጠኙም የግፍ እስረኞች እያንዳንዳቸው በ20 እና በ30 ሺህ ብር ዋስ እንዲወጡ ተወስኖላቸዋል።

የግፍ እስረኛው ናትናኤል ያለምዘውድ ከሁለት ወራት በላይ በአዋሽ አርባ ከፍተኛ ስቃይ ሲደርስባቸው የቆየ ሲሆን፣ በግፍ እስሩ ምክንያትም ለወባ በሽታ ተጋልጠዋል።

ባልደራስ ፓርቲ በአቶ ናትናኤል ላይ የደረሰውን በደል እያወገዘ ሌሎች በግፍ እስር ላይ የሚገኙ ንፁሀንም በአስቸኳይ እንዲፈቱ ያሳስባል።

የግፍ እስረኞች ይፈቱ!
የግፍ እስረኞቹ ናትናኤል ያለምዘውድ እና ወንድምነው አድማስ ለሀሙስ እና አርብ ተቀጥሩ

#አቶ_ናትናኤል_ያለምዘውድ

የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ የስራአስፈፃሚ አባል እና የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ የሆኑት አቶ ናትናኤል ያለምዘውድ በ10/10/2016 ዓ.ም  በይግባኝ ሰሚ ችሎት መቅረባቸው ይታወሳል። ችሎቱም የግፍ እስረኛውን ጨምሮ ሌሎች ስምንት የግፍ እስረኞችን እያንዳንዳቸውን በሃያ እና ሰላሳ ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቁ ውሳኔ መስጠቱን ዘግበን ነበር።

ሆኖም ፖሊስ የግፍ እስረኞቹን ሳይለቅ በመቅረት፣ ለጠቅላይ ፍ/ቤት ይግባኝ ብሏል። በዚህም መሰረት የግፍ እስረኞቹ ዛሬ በጠቅላይ ፍ/ቤት የቀረቡ ሲሆን፤ ፍ/ቤቱ ፖሊስ ያቀረበው ይግባኝ ያስቀርባል/አያስቀርብም የሚለውን መርምሮ ውሳኔ ለመስጠት ለአርብ 14/10/2016 ዓ.ም ቀጥሯል።

#ጋዜጠኛ_ወንድምነው_አድማስ

በግፍ እስር ላይ የሚገኙት የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ የሚዲያ ክፍል ጋዜጠኛ የሆኑት ወንድምነው አድማስ ከሌሎች 20 እስረኞች ጋር የሽብር ክስ በፖሊስ እንደቀረበባቸው ይታወሳል። ከዚህ ቀደም በ28/09/2016 ዓ.ም  በዋለው ችሎት ፖሊስ ለምርመራ በሚል 14 ቀናት ጠይቆ፣ ፍ/ቤቱም ይህንኑ የፖሊስ ጥያቄ በመቀበል ሙሉ 14 ቀናትን እንደፈቀደለት ዘግበን ነበር።

የግፍ እስረኛውን ወንድምነው አድማስን ጨምሮ ሌሎች በመዝገቡ የተከሰስት 20 ሰዎች ዛሬ በቀጠሯቸው መሠረት ፍ/ቤት ቀርበዋል። ሆኖም ፖሊስ በድጋሚ 14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ይሰጠኝ ሲል ጠይቋል። የተከሳሾች ጠበቆችም ይህንን የፖሊስ አላግባብ የግፍ እስረኞችን በግፍ እስር ለማቆየት የሚያደርገውን ተግባር ተቃውመው ተከራክረዋል። ጠበቆቹ አክለውም የግፍ እስረኞቹ የዋስ መብት እንዲከበር ጠይቀዋል።

ፍ/ቤቱም ግራ ቀኙን ከሰማ በኋላ ፖሊስ በጠየቀው ተጨማሪ የምርመራ ቀናት እና በጠበቆች የዋስትና ጥያቄ ላይ መርምሮ ውሳኔ ለመስጠት ለነገ 13/40/2016 ዓ.ም ቀጥሯል።
#መረጃ
ጋዜጠኛ ወንድምነው አድማስ ለሰኔ 26 ተቀጠሩ

❗️የመሀል ዳኛው ለአራተኛ ጊዜ ተቀይረዋል

በኦህዴድ-ብልፅግና ሀይሎች ታፍነው በግፍ እስር ላይ የሚገኙት የባልደራስ ፓርቲ የሚዲያ ክፍል ጋዜጠኛ ወንድምነው አድማስ ትናንት ሰኔ 12/2016 ፍ/ቤት መቅረባቸው ይታወሳል። ፖሊስ ከዚህ ቀደም እንደሚያደርገው በአቶ ወንድምነው እና በሌሎች አብረዋቸው በተከሰሱ የግፍ እስረኞች ላይ ተጨማሪ 14 የምርመራ ቀናት መጠየቁን እና የተከሳሾች ጠበቆችም ይህንን ተቃውመው መከራከራቸውን ዘግበን ነበር።

በዚህም መሰረት ፍ/ቤት ፖሊስ በጠየቀው ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ላይ እና የግፍ እስረኞቹ ጠበቆች ባቀረቡት የዋስትና መብት ላይ መርምሮ ውሳኔ ለመስጠት ለዛሬ ሰኔ 13/2016 ዓ.ም ቀጥሮ ነበር።

ጋዜጠኛ ወንድምነው አድማስ እና ሌሎች የግፍ እስረኞች በቀጠሯቸው መሰረት ዛሬ ፍ/ቤት የቀረቡ ሲሆን ፍ/ቤቱ ፖሊስ ያቀረበውን 14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ፈቅዷል። በዚህም መሰረት የግፍ እስረኞቹ በሰኔ 26/2016 ዓ.ም ፍ/ቤት እንደሚቀርቡ ይጠበቃል።

🔴 በተያያዘ የግፍ እስረኞቹ ፍ/ቤት መቅረብ ከጀመሩበት ከግንቦት 28/2016 ዓ.ም ጀምሮ የእነ ጋዜጠኛ ወንድምነውን ጉዳይ ከሚያዩት ዳኞች ውስጥ የመሀል ዳኛው ለአራተኛ ጊዜ ተቀይረዋል። ይህም በፍርድ ስርዓቱ ላይ ያልተለመደ እና ጥያቄ የሚያስነሳ ነው።

ባልደራስ ጋዜጠኛ ወንድምነው አድማስ፣ አቶ ናትናኤል ያለምዘውድ፣ አቶ ስንታየሁ ቸኮልን ጨምሮ ሌሎች በግፍ እስር ላይ የሚገኙ ንፁሀን በአስቸኳይ እንዲፈቱ ያሳስባል።

የግፍ እስረኞች ይፈቱ!
#ሰበር
አቶ ናትናኤል በ30 ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቁ ጠቅላይ ፍ/ቤቱ አፀና

የግፍ እስረኛው አቶ ናትናኤል ያለምዘውድ ከዚህ ቀደም በሰኔ 5/2016 ዓ.ም አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ተጨማሪ 12 የምርመራ ቀን ፈቅዶባቸው እንደነበረና፣ የግፍ እስረኞች ጠበቆችም ይህንን በመቃወም ለይግባኝ ሰሚ ችሎት ይግባኝ ማለታቸው ይታወሳል። ይግባኝ ሰሚ ችሎቱም አቶ ናትናኤል እና አብረዋቸው የታሰሩ 8 ሰዎች እያንዳንዳቸው በሀያ እና ሰላሳ ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቁ ወስኖ ነበር።

ፖሊስ በበኩሉ ይህንን የይግባኝ ሰሚ ችሎት በመቃወም ለጠቅላይ ፍ/ቤት በግፍ እስረኞቹ ላይ ይግባኝ እንዳለ መረጃውን ማድረሳችን ይታወሳል። ጠቅላይ ፍ/ቤቱም በቀረበለት ይግባኝ ላይ መዝገብ መርምሮ ውሳኔ ለመስጠት ለአርብ 14/10/2016 ዓ.ም ቀጥሮ የነበረ ቢሆንም፣ መዝገቡን ለመርምሮ ውሳኔ ለመስጠት በቂ ጊዜ ባለማግኘቱ ለዛሬ 17/10/2016 ዓ.ም ቀጠሮውን አዙሮ ነበር።

እነ አቶ ናትናኤል ያለምዘውድ ዛሬ በቀጠሯቸው መሰረት ፍ/ቤት የቀረቡ ሲሆን፣ ጠቅላይ ፍ/ቤቱ የይግባኝ ሰሚ ችሎቱ የወሰነውን የሀያ እና ሰላሳ ሺህ ብር ዋስ አፅድቆታል። በዚህም መሰረት አቶ ናትናኤል ያለምዘውድ ከሰባ ቀናት በላይ ከቆዩበት የግፍ እስር በሰላሳ ሺህ ብር ዋስ ይወጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።

አቶ ናትናኤል በተለይም አዋሽ አርባ የእስረኞች ማጎሪያ በግፍ እስር በቆዩበት ወቅት በወባ በሽታ ተጠቅተዋል። ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ በግፍ እስር ላይ የሚገኙ ንፁሀን በአስቸኳይ እንዲፈቱ ያሳስባል።

የግፍ እስረኞች ይፈቱ!
#ሰበር

የግፍ እስረኛው አቶ ናትናኤል ያለምዘውድ ተፈተዋል

ከ27/7/2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ሶስት ወር ገደማ በግፍ እስር ላይ የቆዩት የባልደራስ ፓርቲ የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ እና የስራ አስፈፃሚ አባል የሆኑት ናትናኤል ያለምዘውድ ዛሬ በ 30 ሺህ ዋስ ተፈተዋል።

አቶ ናትናኤል በተለይም አዋሽ አርባ በቆዩበት ወቅት ከፍተኛ ስቃይ የደረሰባቸው ሲሆን፣ በከፍተኛ የወባ በሽታም ተጠቅተዋል።

የግፍ እስረኞች ይፈቱ!
በግፍ እስር ላይ የሚገኘው የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ የሚዲያ ክፍል ጋዜጠኛ ወንድም ነው አድማስ፦

🔴 ግንቦት 14/2016 ዓ.ም  በኦህዴድ-ብልፅግና ኃይሎች ታፈነ።

🔴 እስከ 28/09/2016 ዓ.ም ድረስ ፍ/ቤት አልቀረበም።

🔴 በ28/09/2016 ዓ.ም ከሌሎች የግፍ እስረኞች ጋር በፖሊስ "የሽብር ክስ" ቀርቦባቸዋል።

🔴 የግፍ እስረኞቹ ለሁለት ተከታታይ ጊዜያት፣ 14 ቀናት የምርመራ ጊዜ (በድምሩ 28 ቀናት) ተሰጥቶባቸዋል።

🔴 የግፍ እስረኛው ጋዜጠኛ ወንድምነው በኦህዴድ-ብልፅግና ኃይሎች ከታፈነ 40 ቀናት ገደማ ሆኖታል፤

🔴 ጋዜጠኛ ወንድምነው በአሁኑ ሰአት በፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ (ሜክሲኮ) በግፍ እስር ላይ ይገኛል።
በጋዜጠኛ ወንድምነው አድማስ እና በሌሎች የግፍ እስረኞች ላይ 15 ቀናት ተሰጠባቸው

በኦህዴድ-ብልፅግና የፀጥታ ሀይሎች ታፍኖ ከግንቦት 14/2016 ዓ.ም ጀምሮ በግፍ እስር ላይ የሚገኘው የባልደራስ ፓርቲ የሚዲያ ክፍል ጋዜጠኛ ወንድምነው በትላንትናው እለት (26/10/2016 ዓ.ም) በቀጠሮው መሰረት ፍ/ቤት ቀርቦ ነበር።

በጋዜጠኛ ወንድምነው ላይ እና በሌሎች አብረው በታሰሩ የግፍ እስረኞች ላይ ለተደጋጋሚ ጊዜ 14 ቀናትን ፖሊስ ሲጠይቅ መቆየቱ ይታወቃል፣ አሁን ደግሞ አቃቢ ህግ ለክስ መመስረቻ በሚል ተጨማሪ 15 ቀናትን ጠይቆባቸዋል። ፍርድ ቤቱም አቃቤህግ የጠየቀውን የ15 ቀናት የክስ መመስረቻ ጊዜ ተቀብሎታል። በዚህም መሰረት በግፍ እስግ ላይ የሚገኙት እነ ወንድምነው አድማስ ለተጨማሪ 15 ቀናት በግፍ እስር ላይ የሚቆዩ ይሆናል።

የግፍ እስረኛው ወንድም ነው አድማስ በግፍ ከታሰረ ከ40 ቀናት በላይ ሆኖቷል። ጋዜጠኛ ወንድምነው በአሁን ሰአት ሜክሲኮ በሚገኘው የፌደራል ወንጀል ምርመራ በግፍ እስር ላይ ይገኛል።

የግፍ እስረኞች ይፈቱ!
ዘመናዊ ባርነት በኢትዮጵያ መንግሥት ሠራተኞች ላይ

ዘመናዊ ባርነት አንድን ሰው በማስፈራራት፣ በአመጽ፣ በማስገደድ፣ በማታለል ወይም ሥልጣንን አላግባብ በመጠቀም ምክንያት እምቢ ማለት ወይም መተው የማይችልበትን የብዝበዛ ሁኔታዎችን ያመለክታል።

ባለፈው ሳምንት በሸገር ሬድዮ የኢትዮጵያ መንግሥት ሠራተኞችን ሁኔታ በግልፅ የሚያብራራ መርሀግብር አዳምጫለሁ ከላይ የተገለፀውን ፍቺ ያሟላል።

በርካታ ሰራተኞች የቤት ኪራይ መክፈል ባለመቻላቸው ቤታቸውን አጥተዋል፣ በቂ ምግብ መግዛት አይችሉም ፣ አብዛኛዎቹ ለልጆቻቸው መሠረታዊ ፍላጎቶች እንኳን ማሟላት አይችሉም። ከአቅም በላይ ይሰራሉ። በርካቶች ደሞዛቸው በጊዜ ክፍያ እየተከፈላቸው አይደለም። እንዲሁም ብዙ ሠራተኞች ለወራቶች ያልተከፈለ ደሞዝ አላቸው። መንግሥት ብልፅግና ፓርቲን እንዲቀላቀሉ በማስገደድ ነፃነታቸውን እየገፈፈ ይገኛል።

የሠራተኞች ኮንፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት መረጃ እንደሚያመለክተው ወደ 4 ሚሊዮን የሚጠጉ የተደራጁ እና ያልተደራጁ ሠራተኞች አሉ። በአማካይ አንዱ ሰራተኛ የሚያስተዳድራቸውን ቤተሰቦች ብዛት አራት ናቸው ብለን ብንወስድ፣ በትንሹ ወደ 16 ሚሊዮን ሰዎች በእነርሱ ስር ይተዳደራሉ እንደማለት ነው። ከዚህ የበለጠ ትኩረት የሚሻ ነገር ከየት ይመጣል?!

የሠራተኛውንና የቤተሰቡን ደህንነት ለማሻሻል መስራት ያለባቸው ብዙ የመንግሥት፣ የግል እና ማህበር ተቋማት አሉ። እነዚህ ተቋማትና መሪዎቻቸው በጥቅማ ጥቅም ፣ በጉዞ አበል ፣ በስብሰባ፣ በቦርድ አባልነት ፣ ድጎማ፣ በሙስና በሚያግበሰብሱት ገንዘብ ገበታቸው ስለሚሞላ የሌላዉም ገበታ እንዲሁ ሞልቶ የሚተርፍ እየመሰላቸው መሆን አለበት ከራሳቸው በቀር ለሌላው ማሰብ ተስኗቸው እንቅልፋቸዉን ሚለጥጡት።

አምሀ ኃይለማርያም፣ ከሰሜን አሜሪካ ድጋፍ ሰጪ ማህበር
#አሳዛኝ
በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ ከ230 በላይ የወገኖቻችን ሞት ፓርቲያችን ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ እጅጉን አዝኗል።

የሞቱትን ነፍስ እንዲምር እና ለቤተሰቦቻቸውም መፅናናትን ይመኛል።
የሀዘን መግለጫ

ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በተፈጥሮ አደጋ ሕይዎታቸው ባለፉ ንፁሐን የተሰማውን መሪር ሀዘን ይገልፃል

የኢትዮጵያ ሕዝብ በሰው ሰራሽ ችግሮች ምክንያት በእየቀኑ ከሕፃናት እስከ አዛውንት መቀጠፋቸው ሳያቆም የተፈጥሮ አደጋ ደግሞ በመቶች የሚቆጠሩ ዜጎችን ሕይዎት መቀማቱ የሀገሪቱን ሕዝብ ሀዘን እጅግ መሪር አድርጎታል፡፡ በዚህም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ ሀምሌ 15 /2016 ዓ.ም ከረፋዱ 4:00 ሰዓት አካባቢ በጀመረው ድንገተኛ የመሬት ናዳ እስካሁን የሟቾች ቁጥር ከ2መቶ አልፏል፡፡

ለአደጋው ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ የማይሰራበት ከሆነ የሟቾች ቁጥር በአዛሳኝ ሁኔታ ሊጨምር እንደሚችል ለባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራስ ፓርቲ የደረሰው መረጃ ያመላክታል፡፡ ባልደራስ ለአውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ በንፁሐን ዜጎች ላይ የደረሰውን ሰቅጣጭ አደጋ በቅርበት ሲከታተለው የቆየ ሲሆን አሁንም አደጋው የመጨረሻ መፍትሄ እስከሚያገኝ በጥብቅ እየተከታተለ መሆኑን ማሳወቅ እንወዳለን፡፡

የተፈጥሮ አደጋ ተፈጥሮአዊ ከመሆኑ አንፃር አደጋዎችን ፈፅሞ ማስቀረት የማይታሰብ ቢሆንም መከላከል እና ጉዳቶችን መቀነስ ግን የመንግሥት ተቀዳሚ ተግባሩ ነው፡፡ አንዳንድ የተፈጥሮ አደጋዎች የወቅቶችን መፈራረቅ መሰረት አድርገው የሚከሰቱ በመሆናቸው ቀድሞ ማወቅ እና ዝግጅት ማድረግ የሚቻል በመሆኑ በሰዎች እና በንብረት ላይ የሚደርሱ አደጋዎችን መከላከል ይቻላል፡፡ የተፈጥሮ አደጋዎችን መካከል የሚችሉ ተቋማት በሚገባቸው ልክ አለመዘጋጀት እና ግዴለሽነት ለንፁሐን ዜጎች ሞት እና ንብረት ውድመት የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡

በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ያለቁበትን የተፈጥሮ አደጋ እንደ ቀላል ጉዳይ ማየት እና ለአደጋው የሚመጥን መፍትሔ በአፋጣኝ አለመስጠት እጅግ አሳዛኝ ነገር ነው፡፡ ይህን አደጋ ተከትሎ መንግሥት የሀዘን መግለጫ ያወጣው፤ በኢትዮጵያ የሚገኙ የውጭ ሀገር ዲፕሎማቲክ ኮንሱላዎች የሀዘን መግለጫዎች ካወጡ በኋላ መሆኑ ፤ ገዥው ፓርቲ እና መንግሥት ለኢትዮጵያዊያን ዜጎች ደህንነት ደንታ የሌላቸው መሆኑን ያመለክታል፡፡

ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰ ድንገተኛ የመሬት ናዳ አደጋ ሕይዎታቸው ላለፍት ዜጎች የተሰማውን መረሪ ሀዘን እየገለፀ የሚከተሉትን ጥሪዎችን ያስተላልፋል፤

1. ገዥው መንግሥት በአደጋው ለተጎዱ ወገኖች የሚሆን አስቸኳይ እርዳታ እና የአደጋውን ዘግናኝነት ለኢትዮጵያ ሕዝብ ብሎም ለዓለም ሕዝብ በማሳዎቅ አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጥ፣

2.በተፈጥሮ አደጋው ሳቢያ የደረሰው የዜጎች ሞት እና የንብረት ወድመቱ እጅግ ከባድ በመሆኑ ሁሉም አካላት ለተጎጅዎች እንዲደርስላቸው ጥሪ እናቀርባለን፣

3. የሚዲያ አካላት እና በአደጋው ዙሪያ በልዩ ትኩረት እና በኃላፊነት የምትንቀሳቀሱ ተቋማት የዐደጋውን አሳዛኝ ሁኔታ በግልፅ በማሳወቅ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ ጥሪ እናቀርባለን፣

4. መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት፣ የእምነት ተቋማት እና ግለሰቦች ለተጎጅ ዜጎች የሚቻላችሁን ትብብር እንድታደርጉ ጥሪ እናቀርባለን

5. የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ዝቅ ብሎ እንዲውለበለብ እንጠይቃለን፣

በመጨረሻም በተፈጥሮ እና በሰው ሰራሸ አደጋዎች ሳቢያ በሁሉም የሀገሪቱ አቅጣጫ ሕይዎታቸው እየተቀጠፉ ላሉ ንፁሐን ነፍሳቸው በአፀደ ገነት ያሳርፍ እንላለን ለሟች ቤተሰቦች እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ መፅናናትን እንመኛለን፡፡

የባልደራስ ብሔራዊ ስራአስፈፃሚ ኮሚቴ
ሐምሌ 19/2016 ዓ.ም
የባልደራስ ፓርቲ የብሔራዊ ምክር ቤት አባል አቶ ፋሲል ማሞ በብልፅግና ሀይሎች ታፈኑ

አቶ ፋሲል ፈረንሳይ ከሚገኘው አንቀፀ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ፣ ዓመታዊ የቅዱስ ገብርኤል በዓልን አክብሮ በመመለስ ላይ እያለ በፖሊስ መታሰሩን ቤተሰቦቹ አስታውቀዋል፡፡

ሀምሌ 19/11/2016 ዓ.ም ከረፋዱ 5፡00 አካባቢ ከንግስ በዓል ሲመለስ የአዲስ አበባ ፖሊሶች ትፈለጋለህ በሚል ከወሰዱት በኋላ፣ በአዲስ አበባ ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ አስረውታል፡፡

አቶ ፋሲል የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ የብሔራዊ ምክር ቤት አባል ሆኖ በሰላማዊ ፖለቲካ እንቅስቃሴ የሚሳተፍ መሆኑ ይታወቃል፡፡

የአገዛዙ ፖሊሶች በተደጋጋሚ የባልደራስ ፓርቲ አባላትን እና አመራሮችን በማሰር ለከፍተኛ እንግልት እና ስቃይ የሚዳርጉ መሆናቸው አይዘነጋም፡፡

የግፍ እስረኞች ይፈቱ!