ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ Balderas for Democracy
1.68K subscribers
985 photos
14 videos
3 files
138 links
Political party
Download Telegram
#የሀዘን_መግለጫ

የባልደራስ ፓርቲ - የሰሜን አሜሪካ ድጋፍ ሰጪ ማህበር መስራች አባል የነበሩት እና በኦዲት እና ቁጥጥር በኃላፊነት ያገለገሉት አቶ ወንድወሰን መኮንን በትላንትናው እለት ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል።

ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ በአቶ ወንድወሰን መኮንን ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ሀዘን እየገለፀ ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጆቹ እና ለትግል አጋሮቹ መፅናናትን ይመኛል።

ነፍስ ይማር!
😢16
ከስራቸው የተፈናቀሉ ሰራተኞች በአስቸኳይ ወደ ስራ ገበታቸው ይመለሱ

ከባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ

በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የአንበሳ አውቶቡስ እና የኢትዮ ፖስታ አገልግሎት ሰራተኞችን ጨምሮ ሌሎች የመንግሥት መስሪያ ቤት ሰራተኞች በግፍ ከስራቸው እየተባረሩ መሆናቸውን ባልደራስ ከደረስው የህዝብ ቅሬታ አረጋግጧል፡፡ ባለፉት ሁለት ሳምንት ብቻ ከአዲስ አበባ ከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት ከ480 በላይ ሠራተኞች አለ አግባብ ከስራቸው ሲባረሩ ፣ከኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት ደግሞ እንደዚሁ ተመሳሳይ 450 በላይ ሰራተኞች ተባረዋል፡፡ ለፓርቲያችን የሚደርሱት የሕዝብ ጥቆማዎች እንደሚያመላክቱት ከሆነ ምን አልባትም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰራተኞች ከስራ ገበታቸው ሊፈናቀሉ ይችላሉ፡፡
ከአንድ ዓመት በፊት የመንግሥት ሰራተኞች ብሔራቸውን በመጥቀስ ፎርም ሞልተው የብቃት  መመዘኛ በሚል ፈተና መሰጠት ሲጀመር ፣ሆነ ተብሎ  የአማራ ተወላጆችን እና የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን ከስራ የማፈናቀል ተግባር መሆኑን አጋልጠናል፡፡‘’የብቃት መመዘኛ‘’እየተባለ የሚሰጠው ፈተና ለዓመታት ብቸኛ መፈተኛ ቋንቋ ሁኖ ሲያገለግል በቆየው  የአማርኛ ቋንቋ ተፈትነው በአንድ መስሪያ ቤት ሲሰሩ የኖሩ ሰራተኞችን ፣በተለያዩ ቋንቋዎች እንዲፈተኑ የተደረገበት ስልታዊ የማባረሪያ ምክንያት  ነበር፡፡ በተጨባጭ መረጃዎች እንደሚያመላክቱት ከስራ ገበታቸው እንዲፈናቀሉ የተደረጉት አብዛኞቹ በአማርኛ ቋንቋ ፈተና የወሰዱት ናቸው፡፡

በነገድ ላይ የተመሰረተው አገዛዝ ሆነ ብሎ የአንድን ማሕበረሰብ አባል ለማጥቃት የሚጠቀምበት መሳሪያውም የብሔር ብረሰቦች እና ሕዝቦች የሚባለውን’’ ሕገ መንግሥት’’ ነው፡የኦሕዴድ/ኦነግ/  ብልፅግና ፖለቲከኖች የፌዴራል የመንግሥት መስሪያ ቤት ‘’በአንድ ማሕበረሰብ ተይዟል’’ በሚል ሲለፉት የነበረውን የጥላቻ አካሄድ ተግባራዊ እያደረጉት ነው፡፡ በዚህ ኢ ህገ - መንግሥታዊ አካሄድ የአዲስ አበባን ሕዝብ ጨምሮ የአማርኛ ቋንቋ ተናገሪውን  ሕዝብ ግንባር ቀደም የጥቃቱ ሰለባ አድርገዋል፡፡ ይህ አይነቱ አካሄድ ደግሞ በሀገር እና በሕዝብ ላይ ከባድ መከራን ከማስከተል እና ሀገርን ከማውደም የዘለለ ለማንም ቡድን ወይንም ግለሰብ የሚሰጠው ዘላቂ ጥቅም አይኖርም፡፡

ባልደራስ ለአውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ በተለያዩ መስሪያ ቤቶች ለአስርት ዓመታት ያገለገሉ ሰራተኞች እና ቤተሰቦቻቸውን ጎዳና ላይ የሚጥል ውሳኔ በአገዛዙ መሰጠቱን አጥብቆ ይቃወማል፡፡ ፓርቲያችን ባልደራስ በዚህ የግፍ ውሳኔ ተጠቂ የሆኑ ወገኖቻችን ፍትሕ እንዲያገኙ እና ህዝብን አደጋ ላይ የሚጥሉ አሰራሮች በአስቸኳይ እንዲቆሙ የሚከተሉትን ጥሪዎች ያቀርባል።

1. በግፍ ከስራቸው የተፈናቀሉ ሰዎች በአስቸኳይ ወደ ቀድሞ ስራቸው እንዲመለሱ እናሳስባለን፤

2. ሁሉም ኢትዮጵያዊ ዜጋ ከስራቸው ከተባረሩ ዜጎች ጎን ቁሞ  ሰላማዊ ተቃውሞ እንዲያሰማ ጥሪ እናቀርባለን፤

3.  ከስራቸው የተፈናቀሉ ዜጎች ለሚያደርጉት ማንኛውም ሰላማዊ ተቃውሞ ፓርቲያችን ሙሉ ድጋፉን ይሰጣል፤

4.  የሚመለከታችሁ የሰብአዊ መብት ጥበቃ ላይ የምትስሩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እና የሚዲያ አካላት የመስራት መብት በፈረንጆች አቆጣጠር በ1966 በተባበሩት መንግሥታት አጠቃላይ ጉባኤ ላይ የፀደቀው የአለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች መግለጫ (United Nation Universal Declaration of Human Rights) (UNDHR)በአንቀፅ 23 ንዑስ አንቀፅ አንድ (1)ላይ ሰፍሮ የሚገኘውን የዜጎች መብት እንዲሁም በዓለም አቀፍ የኢኮኖሚያዊ ፣የማሕበራዊ እና ባህላዊ መብቶች (The International Covenant on Economic, Social and Cultural Rights) (ICESCR) ቃል ኪዳን  ውስጥ የተካተተውን መሠረታዊ መብት ግልፅ በሆነ ሁኔታ የሚጥስ በመሆኑ ፣ይህን  ህገ ወጥ ድርጊት ለዓለም በማጋለጥ ለመብቶች መከበር እየተደረገ ላለው ሀገራዊ ትግል የበኩላችሁን አስተዋፅኦ እንድታበረክቱ እና የሰላማዊ ለውጡ  አካላት በሙሉ የዜጎችን ከስራ መፈናቀል በፅኑ በመቃወም የሰላማዊ ትግሉ አካል እንድትሆኑ  ፓርቲያችን ባልደራስ አበክሮ ይጠይቃል፡፡

የባልደራስ ለአውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ  
የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ
👍3😢1
በአፋር ወገኖቻችን ላይ የደረሰውን ጥቃት በጥብቅ እናወግዛለን

ከባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ይርተሰጠ መግለጫ

በጥር 22/2017 ዓ.ም በአውሲ ራሱ ዞን ኤሊዳር ወረዳ ኪያሩ ቀበሌ በደረሰ የድሮን ጥቃት ቢያንስ ስምንት የሚሆኑ የአፋር ወገኖቻችን መሞታቸው ታውቋል። ጥቃቱ የተፈፀመው  በጎረቤት ሀገር ጅቡቲ ድሮን መሆኑን የጅቡቲ መንግስት ያመነ ሲሆን፣ ነገር ግን በራሱ ግዛት ላይ እንደተፈፀመ አሳውቋል። እንደ ምክንያት የጠቀሰውም የሽብር ጥቃትን ለመከላከል እንደሆነ ገልጿል። የአፋር ክልል ነዋሪዎች እና ባለስልጣናት ጭምር ግን ጥቃቱ በአፋር ክልል ላይ እንደተደረገ እና በጥቃቱም ንፁሀን እንደተገደሉ እማኝነታቸውን ገልፀዋል።

ሆኖም የኦህዴድ-ብልፅግና አገዛዝ ጉዳዩን አስመልክቶ እስካሁን ምንም አይነት መግለጫ አልሰጠም። ይህም አገዛዙ በህዝብ ላይ ለሚደርስ ሞት እና ውዥንብር ደንታ ቢስ መሆኑን በግልፅ የሚያሳይ ነው። ይህ በርሀብ፣ በኑሮ ውድነት፣ በሙስና፣ በመልካም አስተዳደር እጦት... ወ.ዘ.ተ ፍዳውን እየበላ የሚገኝ ህዝብ ላይ ተጨማሪ የድሮን ድብደባ ሲደርስበት እጅግ አሳዛኝ ነው። ከደረሰው ግድያ ባልተናነሰ በተለይ አደጋው በሚመለከታቸው ተቋማት ትኩረት ሳይሰጠው መቅረቱ አሳዛኝነቱን ያጎላዋል።

ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ በወገኖቻችን ላይ በደረሰው ሞት እና ጉዳት እያዘነ  ፤ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መፅናናትን ይመኛል።  አገዛዙም በአስቸኳይ በንፁሀን ላይ ለደረሰው ግድያ እውቅና እንዲሰጥ እና በአስቸኳይ ግልፅ ማብራሪያ እንዲያቀርብ ፓርቲው ያሳስባል።

የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ
የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ
👍81
አምስት አመታትን ለህዝብ በመታመን

ከክልል አቀፍ ፓርቲነት እስከ ሀገር አቀፍ ፓርቲነት!

ድል ለኢትዮያ!
ድል ለዲሞክራሲ!
👍15
ታስረው ፍርድ ቤት ስለማይቀርቡ እና በታጣቂዎች እየታገቱ ስላሉ ዜጎች ከባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ የተሠጠ መግለጫ

1. ታስረው ፍርድቤት እንዳይቀርቡ ስለተደረጉ ዜጎች

የኦህዴድ/ብልፅግና አገዛዝ ወደ ስልጣን ከመጣበት ጊዜ አንስቶ እንዲሁም የህወሓት/ኢህአዴግ አገዛዝ በስልጣን ላይ በቆየባቸው አመታት፣ "ሕገመንግስቱን ማስከበር¡" የሚል የዳቦ ስም በተሰጠው ቅፅል አፈናዎች፣ የኃይል እርምጃዎች እና ግድያዎች ሲፈፅሙ ቆይተዋል አሁንም እያደረጉት ይገኛል። ነገር ግን በእነዚህ 34 አመታት ውስጥ ሕገመንግስቱንም ሆነ ሌሎች ሕጎችን በመጣስ አራት ኪሎን ተቆጣጥረው የቆዩት ኢህአዴግ ቁጥር አንድ እና ሁለትን የሚወዳደር የለም። ለዚህም ከቁጥር በላይ ምስክሮችን ማቅረብ ይቻላል። ለአብነት በቅርቡ ከተለያዩ ቦታዎች የተያዙ እና አድራሻቸው የጠፉ ወጣቶችን መጥቀስ ይቻላል።

በአገዛዙ ኃይሎች ከመኖሪያ ቤት፣ ከመንገድ ላይ እና ከስራ ቦታቸው የተወሰዱ እነዚህ ዜጎች ከተያዙ ብዙ ቀናትን ቢያስቆጥሩም እስካሁን ድረስ ግን ፍርድ ቤት እንዳልቀረቡ ቤተሰቦቻቸው ተናግረዋል። ይህም አገዛዙ 'እመራበታለሁ እና አስከብረዋለሁ' በሚለው ሕገመንግስት አንቀፅ 19 (3) ላይ የተፃፈውን "የተያዙ ሰዎች በአርባ ስምንት ሰዓታት ውስጥ ፍርድ ቤት የመቅረብ መብት አላቸው" የሚለውን አንቀፅ ፍፁም የሚደፈጥጥ ነው።

2. በታጣቂዎች ታግተው አድራሻቸው ስለሚጠፉ ንፁሀን

ባለፉት ከሰላሳ በላይ አመታት አማራን በአማራነቱ ብቻ መግደል፣ ማገት እና ማፈናቀል የተፈቀደ ስራ መስሎ ቀጥሏል፡፡ በተለይም የብልፅግና አገዛዝ በትረ ስልጣን ከጨበጠ ጀምሮ እጅግ በከፋ መልኩ ብሶ ቀጥሏል።

በአገዛዙ ደረጃ ወደ ዋና ከተማዋ አዲስ አበባ እንዳይገባ የተከለከለው የአማር ህዝብ አሁን ላይ ተንቀሳቅሶ እንኳን እንዳይሰራ በህገወጥ ታጣቂዎች እየተገደለ፣ እየታገተና ገንዘብ እየተጠየቀበት ይገኛል። ይህ በአማራው ሕዝብ ላይ እየደረሰ ያለው መከራ በተለያየ መጠን በሌላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ላይም እየተፈፀመ መሆኑን ፓርቲያችን ባልደራስ ይገነዘነባል፡፡
ከአይን እማኞች እንደተገኘው መረጃ፣ በመጋቢት 27/2017 ዓ.ም ከአማራ ክልል ርዕሰ መዲና ባሕርዳር መነሻውን ያደረገ በተለምዶ ''ታታ'' ተብሎ የሚጠራ የሕዝብ ማመላለሻ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ወረ ጃርሶ ወረዳ በጎሀጽዮን እና ቱሉ ሚልኪ ከተሞች መካከል በሚገኝ ሥፍራ ላይ ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ በርካታ ሰዎች ሲገደሉ አብዛኛዎቹ ተሳፋሪዎች ደግሞ ቆስለዋል፡፡ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን አካባቢ በአማራ ተወላጆች ላይ የሚፈፀመው ግድያ ፣ዘረፋ እና እገታ ተባብሶ መቀጠሉን ከጥቃት የተረፉ የአማራ ተወላጆች አብራርተዋል፡፡ አካባቢው ላይ በርካታ የሚባል የመንግስት ታጣቂ ሀይል ቢኖርም፣ በአማራ ተወላጆች ላይ የሚፈፀመውን ግድያ እና እገታ መታደግ አለመቻሉ እንዳሳዘናቸው የተጎጅ ቤተሰቦች ተናግረዋል። "ፅንፈኛ ታጣቂዎች በሚንቀሳቀሱበት፣ በአማራ ክልልና በኦሮሚያ ክልል አዋሳኝ አካባቢ የአማራ ተወላጆች መንቀሳቀስ ባለመቻላችን፣ የአውሮፕላን ቲኬት መግዛት የማንችል ሰዎች በሕይታቸው ፈርደን የምንሄድበት የግድያ ቀጠና ሆኖብናል" ብለዋል፡፡

ከቀናት በፊት በዚሁ አካባቢ በታጠቁ ሀይሎች ''ፈለገ ግዮን'' በተባለ አገር አቋራጭ አውቶቡስ ላይ ተመሳሳይ እገታ ተፈጽሞ ከ50 በላይ የሚሆኑ ተሳፋሪዎች ታፍነው መወሰዳቸውን ባልደራስ ለአውነተኛ ዲሞክራሲ በመግለጫ ማስታወቁ አይዘነጋም።

እንደዚህ ያሉ ተደጋጋሚ ክስተቶች አማራን ከአዲስ አበባ ከተማ የማገድ ሴራ እንደሆነ፣ ሁነቶቹን አትኩሮ ለሚከታተል ሁሉ ግልፅ ነው። ከዚህ ቀደም በአገዛዙ የፀጥታ ሀይሎች ጭምር የአማራ ተወላጆች ወደ አዲስ አበባ ከተማ እንዳይገቡ ክልከላ ሲደረግባቸው እንደነበር የሚታወስ ነው። ባልደራስ ፓርቲም ድርጊቱን በቪዲዮ ጭምር ማጋለጡ ይታወቃል። ከዚህ ድርጊት ተቀፅላ በሚመስል መልኩ አሁን ላይ የታጠቁ ሕገወጥ ሀይሎችም ሲያሻቸው እየገደሉ፣ ሲያሻቸው ደግሞ አግተው ገንዘብ በመቀበል የአማራውን ስቃይ እያባባሱት ይገኛሉ። ከሁሉ በላይ የሚያሳዝነው በህዝብ ገንዘብ የሚተዳደሩ እና የሚደጎሙ ሚዲያዎች ስለ ጉዳዩ አልሰማንም ብለው ማለፋቸው ነው።

ባልደራስ ለእውነተና ዲሞክራሲ ፓርቲ ከላይ በገለፁት ጉዳዮች ላይ የሚከተሉትን አቋሟቹን ያንፀባርቃል።

1. ከተለያዩ ቦታዎች የተያዙ እና ፍርድ ቤት ያልቀረቡ ዜጎቻችን በአስቸኳይ ፍ/ቤት ቀርበው ሕጋዊ ፍትሕ እንዲያገኙ፣

2. አገዛዙ ተደጋጋሚ እገታዎች በሚፈፀምባቸው ቦታዎች ላይ ልዩ ስምሪት በማድረግ እንገታዎችን እንዲያስቆም፣ የታገቱ ንፁሀንንም በአስቸኳይ እንዲያስለቅቅ፣

3. ሚዲያዎች ለእንደዚህ አይነት አሳሳቢ ጉዳዮች የበለጠ ትኩረት በመስጠት ለህዝብ ትክክለኛ ድምፅ እንዲሆኑ፣

4. መላው የኢትዮጵያ ህዝብ የትኛውም ሕገወጥ ድርጊቶች ነገ የእያንዳንዳችን ቤት ሊያንኳኳ የሚችሉ መሆኑን አውቀን ካሁኑ ድርጊቶቹን እንዲያወግዝ እና እንዲቆሙ ጫና እንዲያደርግ ባልደራስ ያሳስባል።

ባልደራስ በታጣቂ ሀይሎች ለተገደሉ ንፁሀን ነፍስ ይማር እያለ ለመላ ቤተሰቦቻቸው መፅናናትን ይመኛል፡፡

የባልደስራ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ
የሥራአስፈፃሚ ኮሚቴ
👍71😢1
ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ሁለተኛውን ዙር ውይይት ከደቡብ ኢትዮጵያ እና ከደቡብ-ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የፓርቲ-መዋቅር ተወካዮች ጋር አደረገ።

ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ወደ ሀገር አቀፍ ፓርቲነት ማደጉን ተከትሎ፣ በተለያዩ የሀራችን ክፍሎች መዋቅሩን እየዘረጋ መሆኑ ይታወቃል። በዚህም መሰረት በሲዳማ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ እና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎች እያከናወነ ያለውን የመዋቅር ዝርጋታ ተከትሎ ከሲዳማ ክልል በመቀጠል ሁለተኛውን ዙር እሁድ ሚያዚያ 5/2017 ዓ.ም የፓርቲው ስራአስፈፃሚ ወኪሎች፣ ከደቡብ እና ደቡብ-ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የመዋቅር ወኪሎች ጋር በፓርቲው ፖለቲካዊ እና አደረጃጀት ጉዳዮች ላይ ተወያይቷል።

የባልደራስ ፓርቲ ፕሬዝዳንት አቶ አምሀ ዳኜው፣ የፓርቲው ምክትል ፕ/ት ዶ/ር በቃሉ አጥናፉን ጨምሮ ሌሎች የስራ አስፈፃሚ አባላት ለወኪሎቹ የ"እንኳን ደህና መጣችሁ" መልዕክት አስተላልፈዋል። የባልደራስ ፓርቲ ፕሬዝዳንት አቶ አምሃ ዳኘው ለተወያዮቹ ፣የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝብ ኢትዮጵያዊነቱን አስከብሮ የኖረ ጠንካራ ህዝብ ሲሆን ባልደራስም በደቡብ ኢትዮጵያ ትልቅ መሰረት ያለው መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ፕሬዝዳንቱ አክለውም፣ የፓርቲው የአደረጃጀት መዋቅር በሁሉም አካባቢዎች ተደራሽ እንደሚሆን እና በኢትዮጵያ አንድነት ከሚያምኑ ፓርቲዎች ጋር በጋራ ለመስራት እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን ለተሳታፊዎቹ ገልፀዋል፡፡

በስልጠናው ላይ የተሳተፉ የፓርቲው አደራጆች በበኩላቸው፣ ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ በሀገር አቀፍ ደረጃ መንቀሳቀሱ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ትልቅ ድል  መሆኑን ተናግረዋል። ባልደራስ ለአውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ በተለያዩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች የአደረጃጀት መዋቅር መዘርጋቱ  በሕዝቡ ዘንድ ከፍተኛ ደስታ እና ትልቅ ተስፋ መስጡትን ተወያዮቹ አብራርተው ፓርቲው ይዞት የተነሳውን አላማ እንዲሳካ እና የኢትዮጵያ ሕዝብ አንድነት እውን እንዲሆን ጠንክረን እንሰራለን ብለዋል፡፡

በዕለቱ የፓርቲው አደረጃጀት እና ፖለቲካ ስራዎች ላይ ከተከበሩ የመዋቅር ወኪሎች ጋር ሰፊ ውይይት ተካሂዷል። መርሀ ግብሩ ሙሉ ቀን የቆየ ሲሆን ከውይይት ባለፈም፣ የተለያዩ አደረጃጀታዊ እና ፖለቲካዊ አቅጣጫዎች የተወሰዱ ሲሆን በሲዳማ፣ በደቡብ ኢትዮጵያና  ደቡብ-ምእራብ ኢትዮጵያ ክልል ያላችሁ ሀገር ወዳድ ዜጎች ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲን በመቀላቀልና በተለያየ መልኩ ድጋፍ በማድረግ ሰላማዊ ትግሉን እንድታጠናክሩ ባልደራስ ጥሪውን ያስተላልፋል።

ድል ለዲሞክራሲ!
ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ!
👏5👍41
የሕክምና ባለሙያዎችን ጥያቄ እና እስር አስመልክቶ
ከባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ

በሀገራችን በኢትዮጵያም ሆነ በሌሎች ሀገራት የሕክምና ት/ቤቶች (Medical Colleges) ለመግባት፣ ብዙ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል። ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃም የሕክምና ት/ቤት የሚገቡ ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል የመልቀቂያ ፈተናን በከፍተኛ ውጤት የሚያልፉ ተማሪዎች ናቸው። እነዚህ ተማሪዎች፣ በዩኒቨርስቲ ቆይታቸውም ሆነ በትምህርቱ ይዘት ምክንያት ከአብዛኛው የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በላቀ ሁኔታ የትምህርት ጫና የሚበዛባቸው እና ይህንንም ተወጥተው ለመመረቅ የሚደርሱ ናቸው። ከሌሎች የትምህርት ዘርፎች በተለየ መልኩ ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ ቢሰላ እንኳ ተምሮ ለመመረቅ በትንሹ 19 አመታትን በትምህርት ያሳልፋሉ።

ነገር ግን በዚህ ሁሉ ፈተና ውስጥ ያለፉና ክቡር የሆነውን የሰው ሕይወት ለማትረፍ ቀን ከሌት ደፋ ቀና የሚሉ የሕክምና ባለሙያዎች የሚያገኙት ገቢ ከሙያ ችሎታቸው ጋር የማይመጥን እጅግ ዝቅተኛ ደሞዝ ነው፡፡ በተለይም የብልፅግና አገዛዝ የመንግሥትን መንበረ ስልጣን ላይ ከተቆጣተረ ጀምሮ የምግብ እና የመሰረታዊ መገልገያዎች ዋጋ በአራት እና በአምስት እጥፍ አያሻቀበ ባለበት ሁኔታ፣ በነዳጅ ጭማሪ ምክንያት የትራንስፖርት ዋጋ ጣራ በነካበት፣ የቤት ኪራይ ዋጋ አልቀመስ ባለበት ሁኔታ፣ አይደለም የወር ደሞዝን ጠብቆ ለሚኖር፣ አትራፊ ለሆኑ ነጋዴዎችም ኑሮን መግፋቱ ከባድ ሆኗል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ "መኖር ከበደን፣ የደሞዝ ጭማሪ እና የጥቅማ ጥቅም ጥያቄዎቻችን ይከበሩ!" ብለው ተቃውሟቸውን ፍፁም ሰላማዊ በሆን መንገድ ላሰሙ የሕክምና ባለሙያዎች፣ አገዛዙ የሰጠው ምላሽ እጅግ አሳፋሪ ሆኗል። አገዛዙ የመኖር እና የእንጀራ ጥያቄን "ፓለቲካዊ ነው፣ የፅንፈኛ ፖለቲካ ሃይሎች ግፊት ነው፤ የጠላት እጅ አለበት" ወ.ዘ.ተ በማለት ለማፈን እየሞኮረ ይገኛል። የዚህ አሳፋሪ ድርጊቱ ዋንኛ መገለጫ ደግሞ በእስር እና እንግልት ላይ የሚገኙ ሀኪሞች እና የጤና ባለሙያዎች ጉዳይ ነው። የጤና ባለሙያዎቹ ጥያቄያቸው የመኖርና ያለመኖር ጉዳይ እንጂ ሌላ ምንም ዓይነት የፖለቲካ ይዘት ወይም ከስልጣን ጥያቄ ጋር የተያያዘ የፖለቲካ እንድምታ ያለው አይደለም፡፡ ለዓመታት ለጥያቄያቸው ተገቢው ምላሽ እንዲሰጣቸው በሰለጠነ መልኩ ሲያሳስቡ ቆይተዋል። የጤና ባለሙያዎች ጥያቄዎቻቸውን ያቀረቡበት ፍፁም ሰላማዊ በሆነ በሰለጠነ መንገድ ነው፡፡ ለጥያቄያቸውም መደመጥ ያሳዩት በአንድነት የመቆም ፅናት በእጅጉ የሚያስደንቅ ነው።

በአንፃሩ የብልጽግና አገዛዝ በአደባባይ ወጥቶ ሰላማዊ ጥያቄ ያቀረበ የጤና ባለሙያን በማሰር እና ጥያቄውን በተሳሳተ መንገድ በመፈረጅ የመረጠው አካሄድ የለመደውን የጦርነት መንገድ እንጅ ከሰላማዊ ትግል ጋር ጨርሶ የተፋታ እና የማይተዋወቅ መሆኑን በገሃድ አስመስክሮበታል፡፡ አገዛዙ በተደጋጋሚ እንደሚታየው በሰላማዊ መልኩ የሚቀርቡ ጥያቄዎችን ሁሉ በኃይል ለማፈን የማይፈነቅለው ጉድጓድ እንደሌለ እያሳዬ ነው። ይህም ህዝብ በፍራቻ ከላይ የሚወርድ ትዛዝ እንጂ ወደላይ የሚቀርብ ጥያቄ እንደሌለ እንዲያምን እና በፍራቻ ተቀፍድዶ እንዲኖር ለማድረግ በአገዛዙ የተሸረበ ሴራ ነው። እንዲህ አይነቱ ተግባር ደግሞ በተደጋጋሚ ጊዜ በተለያዩ የአምባገነን መንግስታት ሲደረግ የቆየ እና አሁንም በብልፅግና አገዛዝ እየተፈፀመ ያለ ድርጊት ነው።

አገዛዙ ባለሙያዎቹ ያቀረቡትን ጥያቄ ተቀብሎ በተሰጠው ጊዜ ውስጥ አግባብ ባለው ኹኔታ መልስ ባለመስጠቱ በባለሙያዎቹ በኩል የሥራ ማቆም እርምጃው ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል። በዚህም በመንግሥት ቸልተኝተኝነት ሰፊው የኢትዮጵያ ሕዝብ ለከባድ አደጋ እንዲጋለጥ እየተደረገ መሆኑን ባልደራስ ተገንዝቧል። አገዛዙ የጤና ባለሙያዎችን ጥያቄ አፋጣኝ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ የተለመለደውን የሚዲያ ቅጥፈት ማስተጋባት መጀመሩ ለሕዝብ ጥያቄዎች ያለውን ንቀት ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። በጤና ባለሙያዎች ጥያቄ ዙሪያ አገዛዙ በእልህ እና በማንአለብኝነት እያስተላለፋቸው ያሉ ውሳኔዎች ኢትዮጵያን ከባድ አረንቋ ውስጥ የሚከቱ ናቸው።

ቀድሞውን በችግር መጫኛ የተተበተበው የኢትዮጵያ የጤና ስርዓት አሁን ላይ በመንግሥት ግብዝ አካሄድ ወደ ሞት አፋፍ እየተገፋ ነው። የጤና ባለሙያዎች መኖር ሳይችሉ የሚኖር የጤና ስርዓት የለም። ዛሬ በጅምላ የሚታሰሩ እና ለዳቦ ጥያቄ ምላሽ የተነፈጋቸው የጤና ባለሙያዎችን ነገ ለምልክት እንኳ ማግኘት ሊከብድ የሚከብድበት ጊዜ ሊመጣ ይችላል።

ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ የጤና ባለሙያዎች ሲያደርጉት የቆዩትን እና እያደረጉት ያሉትን ፍፁም ሰላማዊ ተቃውሞ ተከትሎ በጉዳዩ ላይ ሀሳብ ከመስጠት በመቆጠብ በጥንቃቄ ሲከታተል ቆይቷል።
ፓርቲው ይህንን ያደረገበት ምክንያት አገዛዙ ሰላማዊ እና ሙያዊ ጥያቄን ፖለቲካዊ መልክ ሰጥቶ ማፈን መፈለጉን በመረዳቱ በሃኪሞች ጥያቄ ላይ አገዛዙ ለሚሰነዝረው የሃሰት ፍረጃ ምክንያት መሆን ስላልፈለገ ነው።
ይሁን እንጂ አሁን ላይ በጤና ባለሙያዎች ላይ የሚደርሰው እስር እና በተገልጋዩ ሕዝብ ላይ እየደረሰ ያለው መጉላላት በመባባሱ በጉዳዩ ላይ መግለጫ ለመስጠት ተገዷል ። በዚህም መሠረት ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ የሚከተሉትን ማሳሰቢያዎች ያቀርባል።

1. የታሰሩ የሕክምና ዶክተሮች ለሌሎች የጤና ባለሙያዎች በአስቸኳይ እንዲፈቱ፤
2. የሕክምና ዶክተሮቹ እና መላ የጤና ባለሙያዎች የሚያነሷቸውን ጥቄዎች ፍፁም ከፍረጃ በራቀ መልኩ እንዲሰሙ እና ጥያቄዎቻቸው አግባብነት ባለው መልኩ እንዲመለሱላቸው፤
3. የብልፅግና አገዛዝ እስካሁን በጤናው አገልግሎት መተጓገል ምክንያት ህክምና ላላገኙ ታካሚዎች ይፋዊ ይቅርታ እንዲጠይቅ
4. መንግሥት ሁሉንም ፖለቲካዊ ያልሆነ የጥቅማጥቅም ጥያቄ ከስልጣን ቆይታው ጋር በማያያዝ ለሕዝብ ስቃይ ደንታቢስ በመሆን የሕዝብን መከራ ከሚያራዝሙ ግብዝ አካሄዶች እንዲታቀብ ፓርቲያችን ያሳስባል።

በመጨረሻም በዚህ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆናችሁ ጥያቄዎቻችሁን በዘመናዊ፣ በሰለጠነ እና ሰላማዊ በሆነ የተቃውሞ ዘይቤ በመጠቀም ላቀረባችሁ የጤና ባለሙያዎች ባልደራስ ያለውን አክብሮት እየገለፀ፣ ጥያቄዎቻችሁ በአስቸኳይ እንዲመለሱ ገዥውን መንግሥት በአፅንኦት ያሳስባል።

የባልደስራ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ
የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ
👍136