Forwarded from Ashara Media - አሻራ ሚዲያ
አሻራ ሪፖርተር ልዩ የቀጥታ ስርጭት መርሐ ግብር አሁን
ገባ ገባ በሉ
👇👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/live/earovQlE-8Y?si=jMF-TqyIRaxZCsIZ
ገባ ገባ በሉ
👇👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/live/earovQlE-8Y?si=jMF-TqyIRaxZCsIZ
YouTube
አርበኛው ለምን ተሰዋ? የአገዛዙ ስልታዊ አጋሮችና ሴራ | ከሕልውና ጥያቄ ወደ ሐገራዊ መዋቅር | የዲፕሎማሲው ባዶነት እና የውጭ ኃይሎች ዝምታ
Journalistic & Legal Disclaimer
EDITORIAL CONTEXT: This video is a professional news report produced for Educational and Documentary (EDSA) purposes.
Our objective is to provide factual, on-the-ground reporting and independent analysis of current events…
EDITORIAL CONTEXT: This video is a professional news report produced for Educational and Documentary (EDSA) purposes.
Our objective is to provide factual, on-the-ground reporting and independent analysis of current events…
👍27❤19😭14🤬6🤯4😢3😱2
ሰበር ዜና
የአፋብን ቴዎድሮስ እዝ እና ምኒልክ ዕዝ አሃዶች በጥምረት #መርጦለ_ማርያም_ከተማን ተቆጣጠ
ከቴዎድሮስ ዕዝ እና ከምኒልክ ዕዝ የተውጣጡ የ105ኛ ኮር ስር የሚገኙ የ45ኛ እና የ29ኛ ክፍለ ጦር አሃዶች በምስራቅ ጎጃም ዞን በኩል መርጦለ ማርያም ከተማን ጨምሮ አካባቢው ላይ የሚገኙ ቁልፍ ቦታዎችን በመቆጣጠር ላይ ይገኛሉ::
በዛሬው ዕለት ሚያዝያ 19 ቀን 2018 ዓ.ም የብፅግናው የሰራዊት አባላት ሰፍረውባቸው በነበሩት፣በእነብሴ ሳር ምድር ፣በወሪያ መስቀል እና በሰኞ ከተማ አካባቢዎች ምንም ዓይነት የተኩስ ልውውጥ ሳይደረግ፣ በደረሰባቸው ከፍተኛ ስጋትና ድንጋጤ ምክንያት የያዙትን ወታደራዊ ቁሳቁስና ንብረት እየጣሉ አካባቢውን ለፋኖ ለቀው ወጥተዋል።
በተጋድሎው በሁለቱ የአፋብን ዕዝ አሃዶች መርጦለ ማርያም ከተማን መቆጣጠር የተቻለ ሲሆን የቡድን መሳሪያን ጨምሮ በርካታ የነፍስ ወከፍ ክላሽ ከጠላት ላይ ተማርኳል:: ዝርዝር መረጃውን ይዘን እንመለሳለን!
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
©አፋብን ምኒልክ ዕዝ ህ/ግንኙነት መምሪያ!
ሚያዚያ 19/2018 ዓ.ም
የአፋብን ቴዎድሮስ እዝ እና ምኒልክ ዕዝ አሃዶች በጥምረት #መርጦለ_ማርያም_ከተማን ተቆጣጠ
ከቴዎድሮስ ዕዝ እና ከምኒልክ ዕዝ የተውጣጡ የ105ኛ ኮር ስር የሚገኙ የ45ኛ እና የ29ኛ ክፍለ ጦር አሃዶች በምስራቅ ጎጃም ዞን በኩል መርጦለ ማርያም ከተማን ጨምሮ አካባቢው ላይ የሚገኙ ቁልፍ ቦታዎችን በመቆጣጠር ላይ ይገኛሉ::
በዛሬው ዕለት ሚያዝያ 19 ቀን 2018 ዓ.ም የብፅግናው የሰራዊት አባላት ሰፍረውባቸው በነበሩት፣በእነብሴ ሳር ምድር ፣በወሪያ መስቀል እና በሰኞ ከተማ አካባቢዎች ምንም ዓይነት የተኩስ ልውውጥ ሳይደረግ፣ በደረሰባቸው ከፍተኛ ስጋትና ድንጋጤ ምክንያት የያዙትን ወታደራዊ ቁሳቁስና ንብረት እየጣሉ አካባቢውን ለፋኖ ለቀው ወጥተዋል።
በተጋድሎው በሁለቱ የአፋብን ዕዝ አሃዶች መርጦለ ማርያም ከተማን መቆጣጠር የተቻለ ሲሆን የቡድን መሳሪያን ጨምሮ በርካታ የነፍስ ወከፍ ክላሽ ከጠላት ላይ ተማርኳል:: ዝርዝር መረጃውን ይዘን እንመለሳለን!
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
©አፋብን ምኒልክ ዕዝ ህ/ግንኙነት መምሪያ!
ሚያዚያ 19/2018 ዓ.ም
👍91❤71😢16🤬13🤯5😭4👏2😱2
ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 47ኛ ክፍለ ጦር አማራ ሳይንት አጅባር ከተማ ታላቅ ጀብድ ፈፅመው ድል አስመዘገቡ::
ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 47ኛ ክፍለ ጦር ታቦር ተራራ ሻለቃ ሚያዚያ 18/2018 ዓ.ም ምሽት አማራ ሳይንት ወረዳ አጅባር ከተማ በመግባት የጠላትን ጥምር ሰራዊት በመደምሰስና የነፍስ ወከፍ መሳሪያ በመማረክ ታላቅ ድል አስመዝግበዋል:: በተጋድሎው ታብር ተራራ ሻለቃ አጅባር ከተማ መግቢያ ያለውን ነሆር ሜዳ ኮንክሪት ምሽግ በመደምሰስ ከተማውን ሙሉ ለሙሉ ተቆጣጥረዋል::
ታቦር ተራራ ሻለቃ በተጋድሎው በርካታ ሆድ አደር ሚሊሻ እና የብልፅግና መከላከያ ሰራዊት በመደምሰስ ከ13 በላይ የነፍስ ወከፍ ክላሽ ማርከዋል:: ከዚህ ጋር ተያይዞም የፋሽስቱን ሰራዊት ፍርፋሪ እየለቀሙ ወገናቸው የአማራ ህዝብ ላይ ዘር ማጥፋት እየፈፀሙ የነበሩ ከ14 በላይ ሚሊሻዎች ተደምስሰዋል:: ከእነዚህ መካከል፦
1.ሚሊሻ ውባለም አያሌው አጅባር ከተማ 03 ቀበሌ ተጠርንፎ የነበረ
2.ሚሊሻ አለሙ እንዳለ አጅባር ከተማ 011 ቀበሌ ተጠርንፎ የነበረ
3.ሚሊሻ ሰይድ አድማሱ አጅባር 01 ቀበሌ ተጠርንፎ የነበረ
4.ሚሊሻ መላኩ አበበ አጅባር ከተማ 06 ቀበሌ ተጠርንፎ የነበረ
5.ሚሊሻ ሽመልስ ጌቶ አጅባር ከተማ 028 ቀበሌ ተጠርንፎ የነበረ እና ሌሎች ለጊዜው በስም ያልታወቁ ዘጠኝ ሚሊሻዎችን ጨምሮ አጠቃላይ 14 ሆድ አደር ሚሊሻ ተደምስሷል:: በተጨማሪም መከለከያ እና አድማ ብተና ጠቅላላ ከ28 በላይ የሚሆኑ በታቦር ተራራ ሻለቃ ተደምስሰዋል::
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ
ሚያዚያ 20/2018 ዓ.ም
ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 47ኛ ክፍለ ጦር ታቦር ተራራ ሻለቃ ሚያዚያ 18/2018 ዓ.ም ምሽት አማራ ሳይንት ወረዳ አጅባር ከተማ በመግባት የጠላትን ጥምር ሰራዊት በመደምሰስና የነፍስ ወከፍ መሳሪያ በመማረክ ታላቅ ድል አስመዝግበዋል:: በተጋድሎው ታብር ተራራ ሻለቃ አጅባር ከተማ መግቢያ ያለውን ነሆር ሜዳ ኮንክሪት ምሽግ በመደምሰስ ከተማውን ሙሉ ለሙሉ ተቆጣጥረዋል::
ታቦር ተራራ ሻለቃ በተጋድሎው በርካታ ሆድ አደር ሚሊሻ እና የብልፅግና መከላከያ ሰራዊት በመደምሰስ ከ13 በላይ የነፍስ ወከፍ ክላሽ ማርከዋል:: ከዚህ ጋር ተያይዞም የፋሽስቱን ሰራዊት ፍርፋሪ እየለቀሙ ወገናቸው የአማራ ህዝብ ላይ ዘር ማጥፋት እየፈፀሙ የነበሩ ከ14 በላይ ሚሊሻዎች ተደምስሰዋል:: ከእነዚህ መካከል፦
1.ሚሊሻ ውባለም አያሌው አጅባር ከተማ 03 ቀበሌ ተጠርንፎ የነበረ
2.ሚሊሻ አለሙ እንዳለ አጅባር ከተማ 011 ቀበሌ ተጠርንፎ የነበረ
3.ሚሊሻ ሰይድ አድማሱ አጅባር 01 ቀበሌ ተጠርንፎ የነበረ
4.ሚሊሻ መላኩ አበበ አጅባር ከተማ 06 ቀበሌ ተጠርንፎ የነበረ
5.ሚሊሻ ሽመልስ ጌቶ አጅባር ከተማ 028 ቀበሌ ተጠርንፎ የነበረ እና ሌሎች ለጊዜው በስም ያልታወቁ ዘጠኝ ሚሊሻዎችን ጨምሮ አጠቃላይ 14 ሆድ አደር ሚሊሻ ተደምስሷል:: በተጨማሪም መከለከያ እና አድማ ብተና ጠቅላላ ከ28 በላይ የሚሆኑ በታቦር ተራራ ሻለቃ ተደምስሰዋል::
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ
ሚያዚያ 20/2018 ዓ.ም
❤61👏7😭7🤯4😱3🤬3😢3
አሳዛኝ መረጃ
ጋይንት ላይ በኦሮሙማ ወታደሮች ንፁሀን እየተ*ጨፈ**ጨፈ ነው።
ንፍስ መውጫ ከተማ ላይ 303ኛ ኮር 59 ክፍለ ጦር አዛዥ ኮረኔል አለሜ ታደለ በህዝባችን ላይ እየሰራው ያለው ግ*ፍ:-
1)ከየትኛውም ቦታ በነፍስ መውጫ ከተማ ሲያልፍ ወጣት ከሆንክ ጥፊ እርግጫ ዱላ ተቀ*ጥቅጦ ደስ ያላቸውን ወደ ማጎሪያ ይወሰደል የት እንደሚደርስ አይታወቅም ይሰውራሉ ።
2) ከምሽቱ 12 ስዓት በኋላ የሚንቀሳቀስ የከተማው ነዋሪ ትዝታ ሆቴል (ጅምር ህንፃ) ድብ*ደባ ይፈጸም*በታል ይረ**ሸናል።
3) ስላሴ ቤተክርስቲያን በድምፅ ማጉያ መቀደሰ አይችሉም ማስጠንቀቂያ ተሰጧቸዋል። በጣም የሚያበ*ሳ*ጨው ገና ሳሊ ቄስ ሞት ብላችሁ ነው ገና ሁላችሁም ይደርሳችኋል በማለት ማስጠንቀቂያ ተሰጧቸዋል።
4) ከቀኑ 10 ስዓት በኋላ ወደ ስላሴ ቤተክርስቲያን መሄድ ተከል*ክሏል ።
5) ሁለት በካሮ (የእጅ ጋሪ) ስራ የሚተዳደሩ ወጣቶች ፀጉራቸውን በኮርኪ( በቢራ ጠርሙስ ክዳን) በደረቁ ተላጭተው እየተንሰ*ፈሰፉ ይገኛሉ።
6) ከመኳቢያ እና ከግድም እንዲሁም ከቀበሌ 13 የመጡ ወጣቶች አስተዳደር ቢሮ ጀርባ እና ወደ አቡነሃራ ፀበል አካባቢ ተረሽ*ነዋል ቁጥራቸውም እስካሁን 9 ደርሰዋል።
ድል ለአማራ ህዝብ !!!
ድል ለአማራ ፋኖ !!!
የ206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር ቃል አቀባይ ክፍል!!!
ጋይንት ላይ በኦሮሙማ ወታደሮች ንፁሀን እየተ*ጨፈ**ጨፈ ነው።
ንፍስ መውጫ ከተማ ላይ 303ኛ ኮር 59 ክፍለ ጦር አዛዥ ኮረኔል አለሜ ታደለ በህዝባችን ላይ እየሰራው ያለው ግ*ፍ:-
1)ከየትኛውም ቦታ በነፍስ መውጫ ከተማ ሲያልፍ ወጣት ከሆንክ ጥፊ እርግጫ ዱላ ተቀ*ጥቅጦ ደስ ያላቸውን ወደ ማጎሪያ ይወሰደል የት እንደሚደርስ አይታወቅም ይሰውራሉ ።
2) ከምሽቱ 12 ስዓት በኋላ የሚንቀሳቀስ የከተማው ነዋሪ ትዝታ ሆቴል (ጅምር ህንፃ) ድብ*ደባ ይፈጸም*በታል ይረ**ሸናል።
3) ስላሴ ቤተክርስቲያን በድምፅ ማጉያ መቀደሰ አይችሉም ማስጠንቀቂያ ተሰጧቸዋል። በጣም የሚያበ*ሳ*ጨው ገና ሳሊ ቄስ ሞት ብላችሁ ነው ገና ሁላችሁም ይደርሳችኋል በማለት ማስጠንቀቂያ ተሰጧቸዋል።
4) ከቀኑ 10 ስዓት በኋላ ወደ ስላሴ ቤተክርስቲያን መሄድ ተከል*ክሏል ።
5) ሁለት በካሮ (የእጅ ጋሪ) ስራ የሚተዳደሩ ወጣቶች ፀጉራቸውን በኮርኪ( በቢራ ጠርሙስ ክዳን) በደረቁ ተላጭተው እየተንሰ*ፈሰፉ ይገኛሉ።
6) ከመኳቢያ እና ከግድም እንዲሁም ከቀበሌ 13 የመጡ ወጣቶች አስተዳደር ቢሮ ጀርባ እና ወደ አቡነሃራ ፀበል አካባቢ ተረሽ*ነዋል ቁጥራቸውም እስካሁን 9 ደርሰዋል።
ድል ለአማራ ህዝብ !!!
ድል ለአማራ ፋኖ !!!
የ206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር ቃል አቀባይ ክፍል!!!
❤38😭12🤯3😢2
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ከሚያዝያ 17/2018 ዓ.ም ጀምሮ የህዝብ ንቅናቄ መድረኮችን በማከናወን ላይ ይገኛል።
በተደራጀ የፖለቲካ ስራ የአማራ ህዝብ ብሔራዊ ንቃት ይዳብራል፤ ህልውናውም ይረጋገጣል! በሚል መሪ ቃል ሚያዚያ ከሚያዚያ 17/2018 ዓ.ም እስከ ሚያዚያ 20/2018 ዓ.ም በእነማይ ዲማ ከተማ፣ የቀብሀና፣ ደብረቅዱሳን ወንደሳ፣ ቁስቋም ቀሸምሽ፣ ሰቀላ ቀበሌ እና በሸበል በረንታ አራጢ፣ ከወይንየ፣ ከወረጎና አካባቢው፣ ከገደያሱ፣ ከአባሰልማ ፣ከየጠሃና፣ ከቦንያ ሰቀላ ቀበሌ የተሰባሰቡ የማህበረሰብ ክፍል በቁጥቋጥ ቀበሌ ላይ ሰፊ ህዝባዊ ውይይት ተካሂዶል።
በፖለቲካ ግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት የህዝብ አስተዳደርን፣ የፍትህ አሰጣጥን፣ የድርጅቱን አሁናዊ ቁመና በመዳሰስ በ201ኛ ኮር እና የ64ኛ ክፍለ ጦር አመራሮች ሰፊ የፖለቲካ ግንዛቤ ተሰጥቷል።
በአፋብን በተሰጠ አቅጣጫ መሰረት የ201ኛ ኮር አመራሮች 64ኛ ክ/ጦር በተቆጣጠራቸው ነፃ ቀጠናዎች ከክ/ጦሩ አመራሮች እና ከወረዳ ጊ/መንግስት አመራሮች ጋር በመሆን የህዝብ መድረክ እያካሄዱ ይገኛሉ።
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!
ሚያዚያ 20/2018 ዓ.ም
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ህዝብ ግንኙነት
በተደራጀ የፖለቲካ ስራ የአማራ ህዝብ ብሔራዊ ንቃት ይዳብራል፤ ህልውናውም ይረጋገጣል! በሚል መሪ ቃል ሚያዚያ ከሚያዚያ 17/2018 ዓ.ም እስከ ሚያዚያ 20/2018 ዓ.ም በእነማይ ዲማ ከተማ፣ የቀብሀና፣ ደብረቅዱሳን ወንደሳ፣ ቁስቋም ቀሸምሽ፣ ሰቀላ ቀበሌ እና በሸበል በረንታ አራጢ፣ ከወይንየ፣ ከወረጎና አካባቢው፣ ከገደያሱ፣ ከአባሰልማ ፣ከየጠሃና፣ ከቦንያ ሰቀላ ቀበሌ የተሰባሰቡ የማህበረሰብ ክፍል በቁጥቋጥ ቀበሌ ላይ ሰፊ ህዝባዊ ውይይት ተካሂዶል።
በፖለቲካ ግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት የህዝብ አስተዳደርን፣ የፍትህ አሰጣጥን፣ የድርጅቱን አሁናዊ ቁመና በመዳሰስ በ201ኛ ኮር እና የ64ኛ ክፍለ ጦር አመራሮች ሰፊ የፖለቲካ ግንዛቤ ተሰጥቷል።
በአፋብን በተሰጠ አቅጣጫ መሰረት የ201ኛ ኮር አመራሮች 64ኛ ክ/ጦር በተቆጣጠራቸው ነፃ ቀጠናዎች ከክ/ጦሩ አመራሮች እና ከወረዳ ጊ/መንግስት አመራሮች ጋር በመሆን የህዝብ መድረክ እያካሄዱ ይገኛሉ።
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!
ሚያዚያ 20/2018 ዓ.ም
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ህዝብ ግንኙነት
❤52🤯5😱3😭3😢2👍1🤬1
Ashara Media - አሻራ ሚዲያ
Photo
ሰበር የድል ዜና
ቢቡኝ ወረዳ የመሸገውን የአረመኔው ሰራዊት ሲደቆስ ውሏል
=============================
ሚያዚያ19/2018ዓ.ም
የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ
ቢቡኝ ወረዳ የመሸገውን የአብይ አህመድ ሰራዊት ምሽጉ ድረስ በመሄድ ሲያናግሩት ውለዋል።
የ201ኛና የ109ኛ ኮር የ54ኛና የ99ኛ ክ/ጦር ሻለቆች የጨመቆትንና የሙገር ምሽግን በመጠጋት የጠላትን መከላከል ሰብሮ በመግባት ጠላት ላይ ታሪክ ሰርተዋል።
ድጎፅዮን ቀጠና ጨመቆትና ሙገር ሉባ ምሽግ በኩል
የተደመሰሰ
1ኛ ምትኩ ሹመቴ -ሚኒሻ
2ኛ ዮሀንስ ሞላ-ሚኒሻ
3ኛ ደሴ አለማየው-ሚኒሻ
4ኛ አባ ደነቀው -ሚኒሻ
5ኛ ሞላ -ሚኒሻ
6ኛ አየነው ፍቃዴ-ሚኒሻ
7ኛ የኃላው መርሻ -ሚኒሻ
8ኛ በስም ያልታወቀ-ሚኒሻ
9ኛ አንድ ፖሊስ የቆሰለ
10ኛ, 04መከላከያ
12 ክላሽና በቁጥር ያልታወቀ ተተኳሽ
የ201ኛ ኮር 33ኛ ክ/ጦርና የ54ኛ ክ/ጦርን 04ሻለቃን ቃኝ በማድረግ ወይንውሃ የመሸገውን የጠላት ሰራዊት ምሽጉን በመደምሰስ ጠላትን ተራራ ላይ ሰቅሎታል።
በወይንውሃ ቀጠና
1ኛ, ጤናው አማረ-ሚኒሻና ሻለቃ መሪ
2ኛ, ይርጋ አለሙ- ሚኒሻ
3ኛ, ይበልጣል --ሚኒሻ
4ኛ,ጌቴ ዘገዬ-ሚኒሻ
5ኛ, መሌ አባተ-ሚኒሻ
6ኛ, ወንዴ ንጋቱ-ሚኒሻ
7ኛ,መቶ ዓለቃ መከለያ
ከባድ ቁስለኛ
1-ምህረቱ እውነቴ -ሚኒሻ
2-ደሴ አበበ--ሚኒሻ
እንዲሁም
11ክላሽና በወል ያልታወቀ ተተኳሽ ተማርኳል
የ201ኛ ኮር 54ኛ ክ/ጦር የሻለቃ 4 ምክትል ሻለቃ አዛዥ ታዘብ አንሙት ሁለት ክላሽ ማርኳል
ይቀጥላል ------------------
የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
ቢቡኝ ወረዳ የመሸገውን የአረመኔው ሰራዊት ሲደቆስ ውሏል
=============================
ሚያዚያ19/2018ዓ.ም
የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ
ቢቡኝ ወረዳ የመሸገውን የአብይ አህመድ ሰራዊት ምሽጉ ድረስ በመሄድ ሲያናግሩት ውለዋል።
የ201ኛና የ109ኛ ኮር የ54ኛና የ99ኛ ክ/ጦር ሻለቆች የጨመቆትንና የሙገር ምሽግን በመጠጋት የጠላትን መከላከል ሰብሮ በመግባት ጠላት ላይ ታሪክ ሰርተዋል።
ድጎፅዮን ቀጠና ጨመቆትና ሙገር ሉባ ምሽግ በኩል
የተደመሰሰ
1ኛ ምትኩ ሹመቴ -ሚኒሻ
2ኛ ዮሀንስ ሞላ-ሚኒሻ
3ኛ ደሴ አለማየው-ሚኒሻ
4ኛ አባ ደነቀው -ሚኒሻ
5ኛ ሞላ -ሚኒሻ
6ኛ አየነው ፍቃዴ-ሚኒሻ
7ኛ የኃላው መርሻ -ሚኒሻ
8ኛ በስም ያልታወቀ-ሚኒሻ
9ኛ አንድ ፖሊስ የቆሰለ
10ኛ, 04መከላከያ
12 ክላሽና በቁጥር ያልታወቀ ተተኳሽ
የ201ኛ ኮር 33ኛ ክ/ጦርና የ54ኛ ክ/ጦርን 04ሻለቃን ቃኝ በማድረግ ወይንውሃ የመሸገውን የጠላት ሰራዊት ምሽጉን በመደምሰስ ጠላትን ተራራ ላይ ሰቅሎታል።
በወይንውሃ ቀጠና
1ኛ, ጤናው አማረ-ሚኒሻና ሻለቃ መሪ
2ኛ, ይርጋ አለሙ- ሚኒሻ
3ኛ, ይበልጣል --ሚኒሻ
4ኛ,ጌቴ ዘገዬ-ሚኒሻ
5ኛ, መሌ አባተ-ሚኒሻ
6ኛ, ወንዴ ንጋቱ-ሚኒሻ
7ኛ,መቶ ዓለቃ መከለያ
ከባድ ቁስለኛ
1-ምህረቱ እውነቴ -ሚኒሻ
2-ደሴ አበበ--ሚኒሻ
እንዲሁም
11ክላሽና በወል ያልታወቀ ተተኳሽ ተማርኳል
የ201ኛ ኮር 54ኛ ክ/ጦር የሻለቃ 4 ምክትል ሻለቃ አዛዥ ታዘብ አንሙት ሁለት ክላሽ ማርኳል
ይቀጥላል ------------------
የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
❤93🤬5😭5😢3👍2🤯2😱1
የጋይንት ሕዝብ ጭፍጨፋና የጅምላ መቃብሮች መገኘታቸው ተሰማ
የምሥራቅ ዕዝ ውስጥ ኮሎኔል ዓለሜ ታደለ የሚመራው 33ኛ ክፍለ ጦር የጋይንት ምድርን ከረገጠ ጀምሮ አያሌ የአደባባይ እና የስውር ጅምላ ግድያዎች እየተካሄዱ ይገኛሉ። ቀሳውስትና ዲያቆናት ከቤተ መቅደስ (ቅዳሴ) ውስጥ ወጥተው ተገድለዋል። መነኮሳት ተገድለዋል። አደባባይ ላይ መረሸን አልበቃ ብሎ ወጣቶች ከቤታቸው እየወጡ ሌሊት ላይ በመረሸን ላይ ናቸው። ታፍሰው የሚወሰዱ ወጣቶች በሌሊት እያስወጡ በነፋስ መውጫ ከተማ እና በዙሪያዋ ባሉ አካባቢዎች ማለትም ቅድሥት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ግቢ ውስጥ፣ ኮሶ ሜዳ በታች፣ ክታክታ ጫካ፣ የኩሩጣ ማርያም አካባቢዎች ጅምላ መቃብሮች እና ሳይቀበሩ የቀሩ የብዙ ወጣቶች አስከሬን እየተገኘ ይገኛል። አሁንም ወጣቶች እየታፈሱ ይገኛሉ።
የክፍለ ጦሩ ዋና አዛዥ በጭካኔው የታወቀና ወጣቶች ታፍሰው ሲደበደቡና ሲረሸኑ እንኳን ፊት ለፊት ሆኖ ይስቃል አሉ። ሲመገብም ብቻውን ነው አሉ። ከጋርዶቹ ጋር እንኳን ተመግቦ አያውቅም ነው የሚሉት። በስሩ ያሉት የአማራ ተወላጅ የሆኑ የመከላከያ አባላት ሲናገሩ "ሰውየው ፍጹም ጭራቅ ነው። ከዚህ በፊት፥ አማራ ክልል ላይ በተንቀሳቀሰባቸው ቀጠናዎች አያሌ ግፎች የሠራ፣ ወጣቶችን የረሸነ ነው። በጭካኔውና ጨፍጫፊነቱ የተነሳ ነው ጠንካራ የፋኖ መሠረት ወዳለበት እንዲንቀሳቀስ የሚታዘዘው። አካባቢውን ለቀን ወደ ሌላ ግዳጅ ቀጠና እስከምንሄድ ወጣቶች ተሰደዱ" ነው ያሉት።
የዚሁ የ33ኛ ክፍለ ጦር እና አዛዡ ሞጣ ከተማ በነበረበት ሠዓት አያሌ ግፎችን ሲሠራ የነበረ ሲሆን፣ ወደ ደብረ ታቦር ተዛውሮ የለመደውን ግፍ ፈጽሞ ሲያበቃ ወደ ጋይንት ከተዘዋወበት ጀምሮ ሕዝብ እያለ ይገኛል።
ከትናንት በፊት 17፣ 2018 ዓ.ም "ደምበጣ ሚካኤል" ከተባለ አካባቢ ከእናቱ ጋር ተነስቶ ወደ ነፋስ መውጫ ከተማ ቅዳሜ ገበያ የሄደ ወጣት እስከነ ሕይወቱ በእሳት አቃጥለውታል። ከእናቱ ጋር ወደ ገበያው የሄደው ወጣት ጸጉሩን ያሳደገ ነው። ወደ ገበያው ውስጥ እንደገባ የመከላከያ አባላት ያዙት። ወደ ኮሎኔል ዓለሜ ወሰዱት። ከዚያም "ጸጉርህን ያሳደከው ፋኖ ለመሆን ነው" ብሎ በጸጉሩ ላይ ነዳጅ አርከፍክፎ እሳት ለቀቀበት። የወጣቱ ሕይወት አላልፍ ብሎ ለሁለት ሠዓታት ያክል ተሰቃይቷል። የተቃጠለውን አስከሬን ቤተሰቦቹ ቢጠይቁም የት እንዳደረሱት አይታወቅም።
የምሥራቅ ዕዝ ውስጥ ኮሎኔል ዓለሜ ታደለ የሚመራው 33ኛ ክፍለ ጦር የጋይንት ምድርን ከረገጠ ጀምሮ አያሌ የአደባባይ እና የስውር ጅምላ ግድያዎች እየተካሄዱ ይገኛሉ። ቀሳውስትና ዲያቆናት ከቤተ መቅደስ (ቅዳሴ) ውስጥ ወጥተው ተገድለዋል። መነኮሳት ተገድለዋል። አደባባይ ላይ መረሸን አልበቃ ብሎ ወጣቶች ከቤታቸው እየወጡ ሌሊት ላይ በመረሸን ላይ ናቸው። ታፍሰው የሚወሰዱ ወጣቶች በሌሊት እያስወጡ በነፋስ መውጫ ከተማ እና በዙሪያዋ ባሉ አካባቢዎች ማለትም ቅድሥት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ግቢ ውስጥ፣ ኮሶ ሜዳ በታች፣ ክታክታ ጫካ፣ የኩሩጣ ማርያም አካባቢዎች ጅምላ መቃብሮች እና ሳይቀበሩ የቀሩ የብዙ ወጣቶች አስከሬን እየተገኘ ይገኛል። አሁንም ወጣቶች እየታፈሱ ይገኛሉ።
የክፍለ ጦሩ ዋና አዛዥ በጭካኔው የታወቀና ወጣቶች ታፍሰው ሲደበደቡና ሲረሸኑ እንኳን ፊት ለፊት ሆኖ ይስቃል አሉ። ሲመገብም ብቻውን ነው አሉ። ከጋርዶቹ ጋር እንኳን ተመግቦ አያውቅም ነው የሚሉት። በስሩ ያሉት የአማራ ተወላጅ የሆኑ የመከላከያ አባላት ሲናገሩ "ሰውየው ፍጹም ጭራቅ ነው። ከዚህ በፊት፥ አማራ ክልል ላይ በተንቀሳቀሰባቸው ቀጠናዎች አያሌ ግፎች የሠራ፣ ወጣቶችን የረሸነ ነው። በጭካኔውና ጨፍጫፊነቱ የተነሳ ነው ጠንካራ የፋኖ መሠረት ወዳለበት እንዲንቀሳቀስ የሚታዘዘው። አካባቢውን ለቀን ወደ ሌላ ግዳጅ ቀጠና እስከምንሄድ ወጣቶች ተሰደዱ" ነው ያሉት።
የዚሁ የ33ኛ ክፍለ ጦር እና አዛዡ ሞጣ ከተማ በነበረበት ሠዓት አያሌ ግፎችን ሲሠራ የነበረ ሲሆን፣ ወደ ደብረ ታቦር ተዛውሮ የለመደውን ግፍ ፈጽሞ ሲያበቃ ወደ ጋይንት ከተዘዋወበት ጀምሮ ሕዝብ እያለ ይገኛል።
ከትናንት በፊት 17፣ 2018 ዓ.ም "ደምበጣ ሚካኤል" ከተባለ አካባቢ ከእናቱ ጋር ተነስቶ ወደ ነፋስ መውጫ ከተማ ቅዳሜ ገበያ የሄደ ወጣት እስከነ ሕይወቱ በእሳት አቃጥለውታል። ከእናቱ ጋር ወደ ገበያው የሄደው ወጣት ጸጉሩን ያሳደገ ነው። ወደ ገበያው ውስጥ እንደገባ የመከላከያ አባላት ያዙት። ወደ ኮሎኔል ዓለሜ ወሰዱት። ከዚያም "ጸጉርህን ያሳደከው ፋኖ ለመሆን ነው" ብሎ በጸጉሩ ላይ ነዳጅ አርከፍክፎ እሳት ለቀቀበት። የወጣቱ ሕይወት አላልፍ ብሎ ለሁለት ሠዓታት ያክል ተሰቃይቷል። የተቃጠለውን አስከሬን ቤተሰቦቹ ቢጠይቁም የት እንዳደረሱት አይታወቅም።
❤77😢24😭16🤯6👍5😱3🤬3🥰1
ብልፅግና ያዝኩት ብሎ ካሰራጨው የኮሎኔል አለሙ ሞላ መረጃ ጋር ተያይዞ መሬት ላይ ያለው ሐቅ!
ኮሎኔል አለሙ ሞላ በቀድሞው ምስራቅ አማራ ፋኖም ይሁን በአሁኑ ምኒልክ ዕዝ ምንም አይነት ሃላፊነት የሌለውና ከ2016 ዓ.ም ክረምት ጀምሮ ትግሉ ላይም ያልነበረ ሲሆን ሃብሩ ወረዳ ጊራና ዙሪያ ልዩ ስሙ ጎራርባ የተባለ ቦታ ላይ ትዳር መስርቶ ወልዶ እየኖረ የነበረ ነው::
መሬት ላይ ያለው እውነታ ኮሎኔሉ ከብልፅግና መከላከያ ሰራዊትም ይሁን ከፋኖ ነፃ ሆኖ የግል ህይወቱን እየኖረ ባለበት ሁኔታ ለፖለቲካና ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ለማዋል ሲባል ከእውነት የራቀ ነገር ማሰራጨቱ ከብልፅግና አገዛዝ የሚጠበቅና ከተለመደ ህዝብን የማደናገር ተግባር የተለየ አይደለም::
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ
ሚያዚያ 20/2018 ዓ.ም
ኮሎኔል አለሙ ሞላ በቀድሞው ምስራቅ አማራ ፋኖም ይሁን በአሁኑ ምኒልክ ዕዝ ምንም አይነት ሃላፊነት የሌለውና ከ2016 ዓ.ም ክረምት ጀምሮ ትግሉ ላይም ያልነበረ ሲሆን ሃብሩ ወረዳ ጊራና ዙሪያ ልዩ ስሙ ጎራርባ የተባለ ቦታ ላይ ትዳር መስርቶ ወልዶ እየኖረ የነበረ ነው::
መሬት ላይ ያለው እውነታ ኮሎኔሉ ከብልፅግና መከላከያ ሰራዊትም ይሁን ከፋኖ ነፃ ሆኖ የግል ህይወቱን እየኖረ ባለበት ሁኔታ ለፖለቲካና ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ለማዋል ሲባል ከእውነት የራቀ ነገር ማሰራጨቱ ከብልፅግና አገዛዝ የሚጠበቅና ከተለመደ ህዝብን የማደናገር ተግባር የተለየ አይደለም::
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ
ሚያዚያ 20/2018 ዓ.ም
❤38😭6👍4🤯3🤬3✍2😢2😱1
Ashara Media - አሻራ ሚዲያ
Photo
ሰበር ዜና!!
አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ጀብደኛው ምኒልክ ዕዝ የምስራቅ አማራ 102ኛ ኮር በሰሜን ወሎ ዞን ራያ ቆቦ ወረዳ በቀዩ ጋሪያ፣በአረቋቲና በሮቢት ከተማ ህዝባችንን በማንገላታት የሚታወቀው የአብይ አህመድን ወንበር ጠባቂ ወታደር እርምጃ ወሰደበት።
የአማራ ፋኖ ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ የምስራቅ አማራ 102ኛ ኮር ዛሬም እንደ ትናንቱ የብልፅግና መራሹ አገዛዝ ላይ አስደናቂ የሆነ መብረቃዊ ጥቃት ፈፀመበት ።
ህዝባችንን በሀይል በመደብደብ ለ7ኛው የአምባገነኑ ብልፅግና ምርጫ የምርጫ ካርድ በአስገዳጅ ሁኔታ ለማስወጣት በቀዩ ጋሪያ፣በአረቋቲና በሮቢት ከተማ ሙከራ ቢያደርግም ልማደኛው የምስራቅ አማራ102ኛ ኮር 12ኛ ክ/ጦር 3ኛ ሻለቃ በአረቋቲ፣ 65ኛ ክ/ጦር በቀዩ ጋሪያ፣ 49ኛ ክ/ጦር በሮቢት ከተማ አቅራቢያ ምሽግና ኬላውን በማስለቀቅ በጥላት ላይ የስነ-ልቦና ስብራት በማድረስ በራያ ቆቦ ዙሪያ ያሉ ቀበሌዎችን ቀጠናውን በማስፋት በቁጥጥር ስር አውሏል።
በተጨማሪም የምስራቅ አማራ102ኛ ኮር አውደ ውጊያ ባደረገባቸው በሁሉም ቀጠናዎች ዘልቆ በመግባት 45 የመከላከያ ሰራዊት አባል 10 የፌደራል ፖሊስ አባል በተከታታይ የሞርተርና የድሽቃ ጥቃት በማድረግ የጌታቸው ረዳን ራሱን ሐራ መሬት እያለ የሚጠራውን የሰራዊት አባል በደጋሜ ደምስሷል።
በዚህ ዘመቻ የነበሩት የምስራቅ አማራ102ኛ ኮር ወታደራዊ አዛዦችና ወታደራ ዘመቻ መሪዎች በሚገርም መናበብና ጦርነቱን እንደተለመደው በተሻለ ብቃት በጥላት ላይ አስደማሚ ገድል መፈፀሙን የ102ኛ ኮር የህዝብ ግንኙነት ገልጿል።
ጠላት ከሰዓት ጀምሮ በድሮን፣ በቢ-ኤም፣በዙ-23፣ በመድፍና በታንክ የተጠናከረ ማጥቃት ቢያደርግም የ102ኛ ኮር አመሻሽ ላይ የ12ኛ ክ/ጦር በሀብተማሪያም መንበሩ የምትመራው የ3ኛ ሻለቃ ዋና አዛዥ የአርበኛ ዝናቤ አማረን ልጆች አይበገሬዎቹን ማቆም ተስኖት ውሏል።
ከሰዓት የጀመረው አውደ ውጊያ በአገዛዙ ላይ ወታደራዊና ፖለቲካዊ የስበት ማዕከሉን በመለየት የምስራቅ አማራ 102ኛ ኮር የ65ኛ ክ/ጦር በአስር አለቃ ሻምበል ተሾመ የምትመራውና የ49ኛ ክ/ጦር በለገሰ ሰማው የምትመራው በጋራ በመሆን የሀይል የበላይነትን በመውሰድ ከላይ የተጠቀሱትን የገጠር ቀበሌዎችንና ከተሞች በቁጥጥር ስር አውሏል።
ከሰዓት የጀመረው ዘመቻ የምስራቅ አማራ102ኛ ኮር የ49ኛ ክ/ጦር በሮቢት ከተማ አቅራቢያ በነበረው አውደ ውጊያ የጥላትን ድሽቃ በወገን ሞርተር ሙሉ በሙሉ በመውደሙ በአገዛዙ በኩል ከፍተኛ ድንጋጤ ተፈጥሯል።
በመጨረሻም የአማራ ፋኖን ጥቃት መቋቋም ያቃተውና ቤተ-ክርስቲያን በማውደም የሚታወቀው አገዛዝ ሆርማት ሆኖ በግምት ባስወነጨፈው መዲፍ በተለምዶ ታችኛው ጎለሻ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ አንድት እናት ከቤቷ ላይ በማረፉ የ3 አመት ልጅ እንዳዘለች ህይወቷን ቀጥፋል።
በአውደ ውጊያው የተገኘ ሞርኮና አጠቃላይ ድሎችን ዘገባውን አጠናቅረን የምንመለስ ይሆናል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ የምስራቅ አማራ102ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
ሚያዚያ 20/2018ዓ/ም
አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ጀብደኛው ምኒልክ ዕዝ የምስራቅ አማራ 102ኛ ኮር በሰሜን ወሎ ዞን ራያ ቆቦ ወረዳ በቀዩ ጋሪያ፣በአረቋቲና በሮቢት ከተማ ህዝባችንን በማንገላታት የሚታወቀው የአብይ አህመድን ወንበር ጠባቂ ወታደር እርምጃ ወሰደበት።
የአማራ ፋኖ ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ የምስራቅ አማራ 102ኛ ኮር ዛሬም እንደ ትናንቱ የብልፅግና መራሹ አገዛዝ ላይ አስደናቂ የሆነ መብረቃዊ ጥቃት ፈፀመበት ።
ህዝባችንን በሀይል በመደብደብ ለ7ኛው የአምባገነኑ ብልፅግና ምርጫ የምርጫ ካርድ በአስገዳጅ ሁኔታ ለማስወጣት በቀዩ ጋሪያ፣በአረቋቲና በሮቢት ከተማ ሙከራ ቢያደርግም ልማደኛው የምስራቅ አማራ102ኛ ኮር 12ኛ ክ/ጦር 3ኛ ሻለቃ በአረቋቲ፣ 65ኛ ክ/ጦር በቀዩ ጋሪያ፣ 49ኛ ክ/ጦር በሮቢት ከተማ አቅራቢያ ምሽግና ኬላውን በማስለቀቅ በጥላት ላይ የስነ-ልቦና ስብራት በማድረስ በራያ ቆቦ ዙሪያ ያሉ ቀበሌዎችን ቀጠናውን በማስፋት በቁጥጥር ስር አውሏል።
በተጨማሪም የምስራቅ አማራ102ኛ ኮር አውደ ውጊያ ባደረገባቸው በሁሉም ቀጠናዎች ዘልቆ በመግባት 45 የመከላከያ ሰራዊት አባል 10 የፌደራል ፖሊስ አባል በተከታታይ የሞርተርና የድሽቃ ጥቃት በማድረግ የጌታቸው ረዳን ራሱን ሐራ መሬት እያለ የሚጠራውን የሰራዊት አባል በደጋሜ ደምስሷል።
በዚህ ዘመቻ የነበሩት የምስራቅ አማራ102ኛ ኮር ወታደራዊ አዛዦችና ወታደራ ዘመቻ መሪዎች በሚገርም መናበብና ጦርነቱን እንደተለመደው በተሻለ ብቃት በጥላት ላይ አስደማሚ ገድል መፈፀሙን የ102ኛ ኮር የህዝብ ግንኙነት ገልጿል።
ጠላት ከሰዓት ጀምሮ በድሮን፣ በቢ-ኤም፣በዙ-23፣ በመድፍና በታንክ የተጠናከረ ማጥቃት ቢያደርግም የ102ኛ ኮር አመሻሽ ላይ የ12ኛ ክ/ጦር በሀብተማሪያም መንበሩ የምትመራው የ3ኛ ሻለቃ ዋና አዛዥ የአርበኛ ዝናቤ አማረን ልጆች አይበገሬዎቹን ማቆም ተስኖት ውሏል።
ከሰዓት የጀመረው አውደ ውጊያ በአገዛዙ ላይ ወታደራዊና ፖለቲካዊ የስበት ማዕከሉን በመለየት የምስራቅ አማራ 102ኛ ኮር የ65ኛ ክ/ጦር በአስር አለቃ ሻምበል ተሾመ የምትመራውና የ49ኛ ክ/ጦር በለገሰ ሰማው የምትመራው በጋራ በመሆን የሀይል የበላይነትን በመውሰድ ከላይ የተጠቀሱትን የገጠር ቀበሌዎችንና ከተሞች በቁጥጥር ስር አውሏል።
ከሰዓት የጀመረው ዘመቻ የምስራቅ አማራ102ኛ ኮር የ49ኛ ክ/ጦር በሮቢት ከተማ አቅራቢያ በነበረው አውደ ውጊያ የጥላትን ድሽቃ በወገን ሞርተር ሙሉ በሙሉ በመውደሙ በአገዛዙ በኩል ከፍተኛ ድንጋጤ ተፈጥሯል።
በመጨረሻም የአማራ ፋኖን ጥቃት መቋቋም ያቃተውና ቤተ-ክርስቲያን በማውደም የሚታወቀው አገዛዝ ሆርማት ሆኖ በግምት ባስወነጨፈው መዲፍ በተለምዶ ታችኛው ጎለሻ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ አንድት እናት ከቤቷ ላይ በማረፉ የ3 አመት ልጅ እንዳዘለች ህይወቷን ቀጥፋል።
በአውደ ውጊያው የተገኘ ሞርኮና አጠቃላይ ድሎችን ዘገባውን አጠናቅረን የምንመለስ ይሆናል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ የምስራቅ አማራ102ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
ሚያዚያ 20/2018ዓ/ም
❤25😢8😱3🤬3😭2👍1🤯1
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር አንበሳው ጋይንት ክፍለ ጦር በምርኮ የተያዙ የመከላከያ ፣የአድማ ብተና፣የፖሊስ እና ሚኒሻ አካላት ተገቢውን የተሀድሶ ስልጠና በመስጠት ተለቀዋል።
መጋቢት 09/2018 ዓ.ም ጋይንት ንፋስ መውጫ ከተማ የተማረኩት አባላቶቹ በቆይታቸው ተገቢውን በክፍለ ጦር የፖለቲካ ዘርፍ ክፍል ፣ በኮሩ የህግ ክፍልና በሌሎች ስራ አስፈጻሚዎች የፖለቲካ የግንዛቤ ተሰጥቷቸው ወደ ማህበረሰቡ እንዲቀላቀሉ ተደርጓል።
አስተያየት እንዲሰጡ የተጠየቁት ምርኮኞቹ በነበራቸው ቆይታ ተገቢውን እንክብካቤ እንደተደረገላቸው በመግለጽ ለማህበረሰቡ ፣ለክፍለ ጦሩ አመራር እና ለመላው አባላቱ ምስጋና አቅርበዋል።
ድል ለአማራ ህዝብ !!!
ድል ለአማራ ፋኖ !!!
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር ቃል አቀባይ ክፍል!!!
መጋቢት 09/2018 ዓ.ም ጋይንት ንፋስ መውጫ ከተማ የተማረኩት አባላቶቹ በቆይታቸው ተገቢውን በክፍለ ጦር የፖለቲካ ዘርፍ ክፍል ፣ በኮሩ የህግ ክፍልና በሌሎች ስራ አስፈጻሚዎች የፖለቲካ የግንዛቤ ተሰጥቷቸው ወደ ማህበረሰቡ እንዲቀላቀሉ ተደርጓል።
አስተያየት እንዲሰጡ የተጠየቁት ምርኮኞቹ በነበራቸው ቆይታ ተገቢውን እንክብካቤ እንደተደረገላቸው በመግለጽ ለማህበረሰቡ ፣ለክፍለ ጦሩ አመራር እና ለመላው አባላቱ ምስጋና አቅርበዋል።
ድል ለአማራ ህዝብ !!!
ድል ለአማራ ፋኖ !!!
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር ቃል አቀባይ ክፍል!!!
❤46👍19🤬11😭9😢3😱2🤯1
በአርሲ ዞን ሮቤ ዲዳዓ ወረዳ በንጹሐን ላይ የተፈጸመው ጥቃት
በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ሮቤ ዲዳዓ ወረዳ ባሳለፍነው ሰኞ ሚያዚያ 12 ቀን 2018 ዓ.ም. አንድ የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ከሁለት ወንድሞቻቸው ጋር ባልታወቁ ታጣቂዎች መገደላቸውን ቤተሰቦች እና የቤተክስቲያን አገልጋዮች ገለጹ። ሙልዬ ፍሰኃ የተባሉት ለዓመታት በዚያ የኖሩ አገልጋይ በተጠቀሰው ቀን አመሻሹ ላይ ከሁለት ወንድሞቻቸው ጋር ከቤታቸው ተጠርተው ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ግድም ወደ ጫካ ተወስደው እንደተገደሉ ነው የተሰማው።
አስተያየታቸውን ለዶይቼ ቬለ የሰጡ የሟች አቶ ሙልዬ ፍሰኃ ቤተሰብ ግድያው የተፈጸመበትን ሂደት ሲያስረዱ «አደጋው የደረሰው በዕለቱ 12 ምሽት አካባቢ ነው» ነው ያሉት። አስተያየት ሰጪው የቤተሰብ አባል አክለውም፤ ታጣቂዎቹ በዚያ ሰዓት እንደገቡ ሟቹንና ሌሎች ሁለት ሰዎችንም ጨምረው ይዘዋቸው በመውጣት ወደ ምሽት ሦስት ሰዓት አከባቢ የመሳሪያ ድምጽ መሰማቱን ገልጸዋል።
ሌላው ለደኅንነታቸው ሲባል ስማቸው እንዳይገለጽ ጠይቀው አስተያየት የሰጡን በአካባቢው የጄና መብሩቁ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ፤ ሰኞ ዕለት ከቤታቸው ተወስደው የተገደሉት አቶ ሙልዬ ፍሰኃ፤ በታጠቁ አካላት ከመኖሪያ ቤታቸው ተወስደው ነው ብለዋል። «ጄና መብሩቅ ቅዱስ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ነው የሚኖሩት» ያሉት አስተያየት ሰጪው፤ ቤተ ክርስቲያኑን ለብዙ ዓመታት ማገልገላቸውንም ገልጸዋል። ሰኞ ሚያዚያ 12 ቀን ለ13 አጥቢያ ምሽቱን አንድ ሰዓት አካባቢ ወደ ቤታቸው የመጡ «ያልታወቁ» ያሏቸው የታጠቁ አካላት በቤተ ክርስቲያኑ ደጃፍ በሚገኝ መኖሪያ ቤታቸው ገና ከብት አጉረው ወደ ቤታቸው እንደገቡ ይዘዋቸው ወጥተዋል ነው ያሉት።
አስተያየት ሰጪው የሃይማኖት አባት እንዳሉት በዕለቱ ምሽቱን የተገደሉት አቶ ሙሉዬ ፍሰኃ ከሁለት ወንድሞቻቸው ጋር ጭምር ወደ ጫካ ተወስደው እንደሆነም ነው የገለጹት። «ሙስሊም ሁለት ወንድሞች አሏቸው፤ እሳቸው ክርስቲያን ናቸው፤ ሦስቱንም ነው ወደ ጫካ ወስደው የገደሏቸው» ብለዋል። አስከሬናቸውም በማግስቱ ጠዋት ተገኝቶ መቀበሩን ገልጸዋል።
በዚህ አካባቢ ብቻ ከ2017 ዓ.ም. ወዲህ እንኳ በተለያዩ ጊዜያት ወደ 46 ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ምዕመናን በታጣቂዎች መገደላቸውን የገለጹት አስተያየት ሰጪው የቤተ ክርስቲን አገልጋይ፤ ምዕመናንም በተለያዩ ቀበሌያት ለመፈናቀል መገደዳቸውን አስረድተዋል። «በተመሳሳይ ሁኔታ አቶ ፍቅሬ የተባሉ አንድ ግለሰብ መጋቢት 16 ተገድለው ከአሁኑ ጋር ከ2017 ወዲህ በተመሳሳይ መልኩ የተገደሉ ሰላማዊ ዜጎች ቁጥን ወደ 46 አድርሶታል፤» ብለዋል።
ይህ በተደጋጋሚ የሚከሰተው ሰላማዊ ዜጎች ላይ ያነጣጠረው የታጣቂዎች ጥቃት ደግሞ በርካታ ሰዎችን ከሃብት ቄዬያቸው ማፈናቀሉንም እንዲሁ አስተያየት ሰጪው አስረድተው፤ ስጋቱ አሁንም አለማባራቱን ተናግረዋል። «በየዘመዱ በከተማ ከቀዬያቸው ተፈናቅለው የተጠለሉ በርካታ ናቸው» ያሉት አስተያየት ሰጪው የሃይማኖት አባት፤ ስጋቱ እየተገታም እንዳልሆነ በአስተያየታቸው ገልጸዋል።
ዶይቼ ቬለ ነዋሪዎቹ ከጸጥታው ሁኔታ ጋር ተያይዞ ስላነሱት ጥቃትና ተፈጽሟል ስለተባለው ግድያ ከወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ባያን ቃሲም ተጨማሪ አስተያየት ለማግኘት በእጅ ስልካቸው በመደወልና እና የጽሑፍ መልዕክት በመላክም ያደረግነው ጥረት ለዛሬ ምላሽ አላገኘም።
ከዚህ በፊት በአርሲ ዞን በተለያዩ አካባቢዎች ሰላማዊ ዜጎች ላይ የሚፈጸመው ጥቃት እንዲቆም መንግሥት በተጠናከረ መልኩ የጸጥታ አካላትን በማሰማራት ንጹሐን ዜጎችን እንዲጠብቅ መንግሥታዊው የ ኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን መጠየቁ ይታወሳል።
ዘገባው የጆይቼ ቬለ ነው።
በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ሮቤ ዲዳዓ ወረዳ ባሳለፍነው ሰኞ ሚያዚያ 12 ቀን 2018 ዓ.ም. አንድ የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ከሁለት ወንድሞቻቸው ጋር ባልታወቁ ታጣቂዎች መገደላቸውን ቤተሰቦች እና የቤተክስቲያን አገልጋዮች ገለጹ። ሙልዬ ፍሰኃ የተባሉት ለዓመታት በዚያ የኖሩ አገልጋይ በተጠቀሰው ቀን አመሻሹ ላይ ከሁለት ወንድሞቻቸው ጋር ከቤታቸው ተጠርተው ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ግድም ወደ ጫካ ተወስደው እንደተገደሉ ነው የተሰማው።
አስተያየታቸውን ለዶይቼ ቬለ የሰጡ የሟች አቶ ሙልዬ ፍሰኃ ቤተሰብ ግድያው የተፈጸመበትን ሂደት ሲያስረዱ «አደጋው የደረሰው በዕለቱ 12 ምሽት አካባቢ ነው» ነው ያሉት። አስተያየት ሰጪው የቤተሰብ አባል አክለውም፤ ታጣቂዎቹ በዚያ ሰዓት እንደገቡ ሟቹንና ሌሎች ሁለት ሰዎችንም ጨምረው ይዘዋቸው በመውጣት ወደ ምሽት ሦስት ሰዓት አከባቢ የመሳሪያ ድምጽ መሰማቱን ገልጸዋል።
ሌላው ለደኅንነታቸው ሲባል ስማቸው እንዳይገለጽ ጠይቀው አስተያየት የሰጡን በአካባቢው የጄና መብሩቁ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ፤ ሰኞ ዕለት ከቤታቸው ተወስደው የተገደሉት አቶ ሙልዬ ፍሰኃ፤ በታጠቁ አካላት ከመኖሪያ ቤታቸው ተወስደው ነው ብለዋል። «ጄና መብሩቅ ቅዱስ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ነው የሚኖሩት» ያሉት አስተያየት ሰጪው፤ ቤተ ክርስቲያኑን ለብዙ ዓመታት ማገልገላቸውንም ገልጸዋል። ሰኞ ሚያዚያ 12 ቀን ለ13 አጥቢያ ምሽቱን አንድ ሰዓት አካባቢ ወደ ቤታቸው የመጡ «ያልታወቁ» ያሏቸው የታጠቁ አካላት በቤተ ክርስቲያኑ ደጃፍ በሚገኝ መኖሪያ ቤታቸው ገና ከብት አጉረው ወደ ቤታቸው እንደገቡ ይዘዋቸው ወጥተዋል ነው ያሉት።
አስተያየት ሰጪው የሃይማኖት አባት እንዳሉት በዕለቱ ምሽቱን የተገደሉት አቶ ሙሉዬ ፍሰኃ ከሁለት ወንድሞቻቸው ጋር ጭምር ወደ ጫካ ተወስደው እንደሆነም ነው የገለጹት። «ሙስሊም ሁለት ወንድሞች አሏቸው፤ እሳቸው ክርስቲያን ናቸው፤ ሦስቱንም ነው ወደ ጫካ ወስደው የገደሏቸው» ብለዋል። አስከሬናቸውም በማግስቱ ጠዋት ተገኝቶ መቀበሩን ገልጸዋል።
በዚህ አካባቢ ብቻ ከ2017 ዓ.ም. ወዲህ እንኳ በተለያዩ ጊዜያት ወደ 46 ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ምዕመናን በታጣቂዎች መገደላቸውን የገለጹት አስተያየት ሰጪው የቤተ ክርስቲን አገልጋይ፤ ምዕመናንም በተለያዩ ቀበሌያት ለመፈናቀል መገደዳቸውን አስረድተዋል። «በተመሳሳይ ሁኔታ አቶ ፍቅሬ የተባሉ አንድ ግለሰብ መጋቢት 16 ተገድለው ከአሁኑ ጋር ከ2017 ወዲህ በተመሳሳይ መልኩ የተገደሉ ሰላማዊ ዜጎች ቁጥን ወደ 46 አድርሶታል፤» ብለዋል።
ይህ በተደጋጋሚ የሚከሰተው ሰላማዊ ዜጎች ላይ ያነጣጠረው የታጣቂዎች ጥቃት ደግሞ በርካታ ሰዎችን ከሃብት ቄዬያቸው ማፈናቀሉንም እንዲሁ አስተያየት ሰጪው አስረድተው፤ ስጋቱ አሁንም አለማባራቱን ተናግረዋል። «በየዘመዱ በከተማ ከቀዬያቸው ተፈናቅለው የተጠለሉ በርካታ ናቸው» ያሉት አስተያየት ሰጪው የሃይማኖት አባት፤ ስጋቱ እየተገታም እንዳልሆነ በአስተያየታቸው ገልጸዋል።
ዶይቼ ቬለ ነዋሪዎቹ ከጸጥታው ሁኔታ ጋር ተያይዞ ስላነሱት ጥቃትና ተፈጽሟል ስለተባለው ግድያ ከወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ባያን ቃሲም ተጨማሪ አስተያየት ለማግኘት በእጅ ስልካቸው በመደወልና እና የጽሑፍ መልዕክት በመላክም ያደረግነው ጥረት ለዛሬ ምላሽ አላገኘም።
ከዚህ በፊት በአርሲ ዞን በተለያዩ አካባቢዎች ሰላማዊ ዜጎች ላይ የሚፈጸመው ጥቃት እንዲቆም መንግሥት በተጠናከረ መልኩ የጸጥታ አካላትን በማሰማራት ንጹሐን ዜጎችን እንዲጠብቅ መንግሥታዊው የ ኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን መጠየቁ ይታወሳል።
ዘገባው የጆይቼ ቬለ ነው።
❤5😢3😭3🤯2🤬2