ASD AJ LAH
755 subscribers
1.73K photos
194 videos
3 files
487 links
ካነበብኩት…
Download Telegram
ዶክተር ዛኪር ናይክ 4.5 milion ተከታይ ባለው የፌስቡክ ፔጁ ይህን መልዕክት አስተላልፏል።
«ولا تلمزوا أنفسكم»
«ነፍሶቻችሁንም አታነውሩ፡፡» ሱረቱል‐ሑጁራት ፥ 11
:
ሱረቱል‐ሑጁራት የስነምግባር ድንጋጌዎች እና አዳቦችን በመላው የምእራፉ አንጓዎች ላይ የዳሰሰች ሱራ ናት። በአስራ አንደኛው አንቀፅ መካከል ያለችው ይች ቃል ግን ዐጂብ ናት። የስነምግባር መዘውርን በሁለት ቃላት አሳጥራው አርፋለች። «ነፍሶቻችሁንም አታነውሩ፡፡»
:
ይችው አንቀፅ አስቀድማ ምን አለች: ‐
⚀ «እናንተ ያመናችሁ ሆይ!»:‐ በአላህና በመልክተኛው [ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም] አምኛለሁ ለሚል ሁሉ የተላለፈ ጥሪ ነው። ሙእሚን የግብረገብ ደንቡን የሚወስደው ከፈጣሪው ብቻ ነው! የሙእሚን ክብሩም ግብሩም ይኸው ነው!

⚀ «ወንዶች ከወንዶች አይቀልዱ፡፡ ከእነርሱ የበለጡ ሊኾኑ ይከጀላልና፡፡ ሴቶችም ከሴቶች (አይሳለቁ)፡፡ ከእነርሱ የበለጡ ሊኾኑ ይከጀላልና፡፡»: ‐ ወንድንም ሆነ ሴትን ያለ ልዩነት በሰው ላይ መሳለቅን ከለከለ። አንዳችን በሌላው ላይ ለመሳለቅ የሚያበቃው ልዩነት የለም። በብሄርህ፣ በገንዘብህ፣ በስልጣንህ በቀለምህ ማንንም አትበልጥምና አትበልጥምና በሌላው ላይ ለመሳለቅ የሚያበቃ መሰረት የለህም። እንደው በተቅዋህ ልትበልጥ ከቻልክ ነበር መሳለቅ ደግሞ የተቂዮች ጠባይ አይደለም!

⚀ «ነፍሶቻችሁንም አታነውሩ፡፡» ይች በአንቀጿ ላይ ያለችው ትኩረቴን የሳበችው አረፍተ ነገር ናት። ሙእሚኖች እንደ አንድ አካል መሆናቸውን ትበይናለች። «አንድ አካሉ ከታመመ ሌላው የአካል ክፍል በትኩሳትና እንቅልፍ በማጣት ይጠራራል።» ሙእሚኖች «እንደ ግንብም ናቸው። አንዱ ሌላውን ይደግፋል።» በወንድምህ ላይ የምትጥሰው ገደብ በነፍስህ ላይ እንደምትፈፅመው በደል ነው።

በሌላ በኩል «በነፍስህ ላይ እንዲፈፀም የማትሻውን በሌላው ላይ አትፈፅም።» ማለትም ነው። ዛሬ በሌሎች ላይ የምትፈፅመው በደል ነገ በራስህ ላይ እንዲፈፀም እንደመፍቀድ ይቆጠራል። "በሰፈሩት ቁና መሰፈር አይቀርም!"

አንቀጿ በማስከተል እንዲህ ትላለች: ‐
«በመጥፎ ስሞችም አትጠራሩ፡፡ ከእምነት በኋላ የማመጽ ስም ከፋ፡፡ ያልተጸጸተም ሰው እነዚያ እነርሱ በዳዮቹ ናቸው፡፡»
ደህና እደሩ!

ተውፊቅ ባሕሩ
አ በ በ
በ ቀ ለ
በ ለ ጠ
----
እስቲ ወደቀኝም ወደታችም አንብቡት፡፡

አፈንዲ
🗓 #በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#አልኽሚስ 18 #ዙልሒጃ 1444 ሂ
አሰላሙዓለይኩም
የነሲሓ ቲቪ የማህበራዊ ሚድያ ኦፊሽያል ገፅና ቻናሎቻችንን በተመለከተ፤ በፌስቡክ ቴሌግራምና ዩትዩብ ብቻ በ @nesihatv አድራሻ የምንገኝ መሆኑን እየገለፅን፤ ድጋፍ የምንጠይቅባቸው ሒሳቦቻችንም በ ibnu Masoud Islamic Center ስም ብቻ የተመዘገቡ መሆናቸውን ለተከበራችሁ የነሲሓ ቤተሰቦች ማሳወቅ እንወዳለን።

ሰኔ 28/2015

ነሲሓ ቲቪ
Just pray…
ከአላህ የሆነ ግዜ ጠይቀሀው ባለመሳካቱ ረስተሀው የነበረው ነገር በድንገት እፊትህ ታገኘዋለህ ምናልባት ረስተሀው ሊሆን ይችላል ጀሊሉ ግን አልረሳውም…

በቃ ዱዐእህን ወደላይ🤲

አንድ ቀን የሠራኸው ስፖርት ጤናማ እና የተስተካከለ የአካል ብቃት እንዲኖርህ አያደርግም። አንድ ቀን የወሰድከው መድሐኒት ከህመምህ አያድንህም። አንድ ቀን ያነበብከው መፅሐፍም የዕዉቀት ባለፀጋ አያደርግህም። ነገር ግን አላህ ዘንድ የላካት ዱዐእ በንፁህ ልብ ማድረግህ ብቻ በቂ ነው።
ይሄ ኳስ እብድም ጅልም ያደረጋችሁ …

ሚሊንየም ሚሊንየም ስላችሁ ደግሞ ሚሊንየም ትምህርት ቤት የተማራችሁ እሚመስላችሁ… አይደለም እሺ
ASD AJ LAH
ይሄ ኳስ እብድም ጅልም ያደረጋችሁ … ሚሊንየም ሚሊንየም ስላችሁ ደግሞ ሚሊንየም ትምህርት ቤት የተማራችሁ እሚመስላችሁ… አይደለም እሺ
ስለኳስ ከተነሳ አይቀር…

የሰፈር ውስጥ የእግር ኳስ ጨዋታ ህጎች

1 ቋሚ ዳኛ አይኖርም(ምናልባት ቀጣይ እሚገባ ከሆነ)
2 ወይ በድካም ወይ ደግሞ በመጝሪብ አዛን ጨዋታው ያበቃል
3 ተጫዋቹ በአላህ ስም ከማለ ኢሊጎሬ ይሰጣል
4 ወፍራሙ ተጫዋች ሁሌም በረኛ ይሆናል
5 የኳሱ ባለቤት ከተቆጣ ወይም ከተሸነፈ ኳሱን ይዞ ይሄዳል
6 አንድ ጥፋት ጥፋት እሚባለው ጥፋት መሆኑን ሁለቱም ቡድን ሲያምን ብቻ ነው።
7 ምንግዜም "በረኛ ተቀይሯል" ብሎ ወፍራሙን በረኛ እሚቀይር ጎበዝ በረኛ አለ።
8 ደግሞ ጉልቤዎች አሉ "እኛም እንጫወታለን አልያ እናንተም አትጫቱም እሚሉ"
9 ኣ ደግሞ ሁለቱ ቡድኖች ካልተጣጣሙ አንዱ ቡድን ላይ ሌላ ሰው ይጨመራል
10 ኳሱ ከአቅም በላይ ካለፈ ለመወሰን ቢያንስ አምስት ደቂቃ በጭቅጭቅ ያልፋል
11 ሁሌም የኳሱ ባለቤት ጠንካራው ቡድን ላይ ነው እሚጫወተው


ሰላም ለእነዚያ ይህን ላይፍ ላሳለፉ

https://t.me/asdajlahh
ለአላህ ሱብሀነሁ ወተዐላ የተተው ጉዳዮች ሁሉ ዋስትና ያላቸው ናቸውና ጉዳዮቻችሁን በሙሉ ለአላህ ተውት። ነገራቶቻችሁን በሙሉ ለጥሩ ነገር ጌታ ለሆነው ተውት ታድያ ሁሌ ለአንተ ለአንቺ ጥሩን ነገር እንደሚሰጥህም እንደሚሰጥሽም እርግጠኛ ሁን ሁኚ። ጉዳዮቻችሁን በሙሉ ለአላህ ስጡ አላህ እኮ ከፈለገ ከእናንተ ከራሳችሁ ከአባታችሁ ከእናታችሁ በላይ አዛኝ እና ጉዳዮችን ልባችን ባሻት መልኩ ፈፃሚ ጌታ ነው። ነገራቶችንም እናንተ ለእርሱ በተዋችሁት ግዜ እና ሁኔታ መዝኖ ይተገብረዋል። የእናንተ ጉዳይ ልባችሁ ባሻው መልኩ ይሳካ ዘንድ አላህ እንደፈለገው ሊያደርገው ተውት።

اللهم صل وسلم وبارك على سيدنا وحبيبنا ونبينا محمد صلى الله عليه وآله وصحبه أجمعين

ነገሮች የቱን ያህል ከባድ ቢሆኑብንም በአላህ ከተውነው የማይሸነፍ አንድም ብርቱ ሀይል የለም ከአላህ ጋር ያሰብነው የሚሳካበት በሱራህ አልካህፍ በዱዓ በሰለዋት የተዋበ ምርጥዬ ጁምዓ ይሁንልን

https://t.me/asdajlahh
ዩኒፎርም ያልሰቀላችሁ እየተማራችሁ…
May Allah give all of us the opportunity to perform Hajj in our life time.
ታናሽ ወንድሜ በፍልስፍና መፅሀፎች በመለከፉ አወራሩም ላይ ጭምር እሚያስቀይም ፍልስፍና ይጨማምርበት ነበር…
ምሳሌ ምግብ ሲፈልግ ለእናቴ እንዲህ ይላት ነበር
"አንቺ የተከበረ ሰው ልጅ የታማኝ
ረሐብ ከሀዲ ነው ደስታዬን ቀማኝ"

ገንዘብ ሲፈልግ ደግሞ አባቴን" አንተ የውዱ አያቴ ልጅ ሆይ ድሕነት አጥቅቶህ ነው ወይስ የኔን ድሕነት እያጣጣምክ አመሸህ"
ከታናሽ እህቴ ደግሞ የሆነን ነገር ሲፈልግ "የአንድ ህዝብ አገልጋይ የህዝቡ አለቃ ነው እና የኔ አለቃ ልትሆኚ ትችያለሽ? "
እና እናቴ ፈገግ ትል እና ምግብ ታዘጋጅለት ነበር አባቴም ይስቅ እና ገንዘቡን ይሰጠው ነበር።እህቴም ትስቅ ጉዳዩን ታሟላለት ነበር።

የተተረጎመ

https://t.me/asdajlahh
ASD AJ LAH
የማለዳ ማስታወሻ 34 ዑቅባህ ኢብን ናፊዕ አስር ሺህ ጦር ይዞ ቁጥራቸው ሰማንያ ሺህ ከሚገመተው የሮም ሰራዊት ጋር ለጦርነት በሚወጣ ግዜ ሚስቱ ፍልሚያው ሲጋጋል የት ነው እማገኝህ ስትለው የሮም ሰራዊት መምሪያ ድንኳን ውስጥ አልያ ጀነት ውስጥ አላት። ምን ለማለት ነው ሩቅ አስቡ… https://t.me/asdajlahh
የማለዳ ማስታወሻ 35

ህይወት ከእርሷ ስንመኘው የነበረውን ነገር እኛ ከእርሷ ምንም እንደማንፈልግ በወሰንበት ሁናቴ ምኖቶቻችንን በሙሉ እውን ማድረጓን ትጀምራለች

ምን ለማለት ነው ምንግዜም የተስፋ ብርሀን ከልባችን እንዳይጠፋ እንታገል
… እ

https://t.me/asdajlahh
🗓 #በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#ጁምዓ 19 #ዙልሒጃ 1444 ሂ
ባለፈው የተመረቁት ፓስተሮች የሰሩት ነው አሉ…🤷

አሉ ነው
ሁለቱንም ባንኮቻችንን አላህ በረካ ያድርግልን።

ግን አካውንት ከፍታችኋል?