።፨።ልዩ ፍቅር።፨።
እንደበግ ተቅበዝብዤ፣
የመጥፊያዬን መንገድ ይዤ፣
ሙት የነበርኩ በሀጥያቴ፣
የማልጠቅም ምናምንቴ፣
የማስተውል አልነበረ፣
የሚገባኝ ሞት ነበረ።
እንዳይቀጣኝ በእውነቱ፣
ይቅር አለኝ በም'ረቱ፣
ይቅርታው ሳያንሰኝ፣
በደሙ ቀደሰኝ፣
እኔን እያወቀኝ፣
በጸጋው አጸደቀኝ።
ሀጥአን ለይ አለመፍረድ፣
ፃድቃን ለይ መፍረድ
በሱ ዘንድ ሁለቱ፣
የማይገመቱ።
ጻድቅ ፈራጅም ነው፣
ያረገው ይሄን ነው።
በደሌን ጠቅላላ፣
ሀጢአቴን በሞላ፣
ወረደና ከላይ፣
አኖረ ራሱ ላይ፣
ተጨነቀ ነፍሱ፣
በኔ ምትክ እሱ፣
የሰው ስጋ ለብሶ፣
በሀሰት ተከሶ፣
በደዌ ደቀቀ፣
በህማም ማቀቀ፣
በስቃይ ቃተተ፣
የመስቀል ሞት ሞተ።
ዘላለም ሚደነቅ፣
የሚያልፍ ከመታወቅ፣
ያለና ሚኖረው፣
ልዩ ፍቅር አለው።
እንደበግ ተቅበዝብዤ፣
የመጥፊያዬን መንገድ ይዤ፣
ሙት የነበርኩ በሀጥያቴ፣
የማልጠቅም ምናምንቴ፣
የማስተውል አልነበረ፣
የሚገባኝ ሞት ነበረ።
እንዳይቀጣኝ በእውነቱ፣
ይቅር አለኝ በም'ረቱ፣
ይቅርታው ሳያንሰኝ፣
በደሙ ቀደሰኝ፣
እኔን እያወቀኝ፣
በጸጋው አጸደቀኝ።
ሀጥአን ለይ አለመፍረድ፣
ፃድቃን ለይ መፍረድ
በሱ ዘንድ ሁለቱ፣
የማይገመቱ።
ጻድቅ ፈራጅም ነው፣
ያረገው ይሄን ነው።
በደሌን ጠቅላላ፣
ሀጢአቴን በሞላ፣
ወረደና ከላይ፣
አኖረ ራሱ ላይ፣
ተጨነቀ ነፍሱ፣
በኔ ምትክ እሱ፣
የሰው ስጋ ለብሶ፣
በሀሰት ተከሶ፣
በደዌ ደቀቀ፣
በህማም ማቀቀ፣
በስቃይ ቃተተ፣
የመስቀል ሞት ሞተ።
ዘላለም ሚደነቅ፣
የሚያልፍ ከመታወቅ፣
ያለና ሚኖረው፣
ልዩ ፍቅር አለው።
ያ ......ትሁቱ ሻማ
።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨።
ያ ትሁቱ ሻማ፤
መስዋዕት ለመሆን ራሱን ባዶ ያረገ፣
ከደረቅ መሬት ለይ እንደ ስር ያደገ፣
መልክ ዉበት የሌለዉ በደዌ የደቀቀ፣
በሰዉ የተጠላ በሰዉ የተናቀ፣
ያ .....ትሁቱ ሻማ
ያ ትሁቱ ሻማ፤
ቤዛ ሆኖ ሊከፍል የሰውን ሁሉ እዳ፣
አንዳች ሳይናገር ለእሳት ሲነዳ፣
በጭንቅ ነበልባል ሲነድ በብዙ፣
እንደ ደም ሲወርድ ሲንጠባጠብ ወዙ፣
ያ .....ት ሁቱ ሻማ
ያ ትሁቱ ሻማ፤
በተከተሉት ፊት ሲሸነፍ ሲረታ፣
ምራቅ ሲተፋበት በጥፊ ሲመታ፣
ብረት ባለዉ ጠፍር በሃይል ሲገረፍ፣
ቆዳዉ ሲገሸለጥ ደሙ ሲጉረፈረፍ፣
ያ......ትሁቱ ሻማ
ያ ትሀቱ ሻማ፤
በሾህ ጉንጉን አክሊል ግንባሩ ሲበሳ፣
መስቀል ተሸክሞ ሲወድቅ ሲነሳ፣
በረዣዠም ምስማር እጅ እግሩ ሲጠረቅ፣
መጠማቱ ሲያይል አፍ ጉሮሮዉ ሲደርቅ፣
ያ...... ትሁቱ ሻማ
ያትሁቱ ሻማ፤
አልባሱ ተገፎ በ'ንጨት ሲንጠለጠል፣
በህማሙ ንዳድ ሲቃትት ሲቃጠል፣
ጅማተ አጥንቱ በ'ሳት ተለኩሷል፣
ሰዉነቱ ቀልጧል በፍም ተገማምሷል።
ያ....... ትሁቱ ሻማ
ያ ትሁቱ ሻማ፤
ከቆሰለ አካሉ ደሙ እየወረደ፣
ብርሃን ያበራልን እሱ እየነደደ፣
አበቃለት ሲሉ መቼ ቀረ ቀልጦ?!
በ ሶስተኛ ቀኑ ታይቷል ሁሉን በልጦ።
✍ @artopian
።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨።
ያ ትሁቱ ሻማ፤
መስዋዕት ለመሆን ራሱን ባዶ ያረገ፣
ከደረቅ መሬት ለይ እንደ ስር ያደገ፣
መልክ ዉበት የሌለዉ በደዌ የደቀቀ፣
በሰዉ የተጠላ በሰዉ የተናቀ፣
ያ .....ትሁቱ ሻማ
ያ ትሁቱ ሻማ፤
ቤዛ ሆኖ ሊከፍል የሰውን ሁሉ እዳ፣
አንዳች ሳይናገር ለእሳት ሲነዳ፣
በጭንቅ ነበልባል ሲነድ በብዙ፣
እንደ ደም ሲወርድ ሲንጠባጠብ ወዙ፣
ያ .....ት ሁቱ ሻማ
ያ ትሁቱ ሻማ፤
በተከተሉት ፊት ሲሸነፍ ሲረታ፣
ምራቅ ሲተፋበት በጥፊ ሲመታ፣
ብረት ባለዉ ጠፍር በሃይል ሲገረፍ፣
ቆዳዉ ሲገሸለጥ ደሙ ሲጉረፈረፍ፣
ያ......ትሁቱ ሻማ
ያ ትሀቱ ሻማ፤
በሾህ ጉንጉን አክሊል ግንባሩ ሲበሳ፣
መስቀል ተሸክሞ ሲወድቅ ሲነሳ፣
በረዣዠም ምስማር እጅ እግሩ ሲጠረቅ፣
መጠማቱ ሲያይል አፍ ጉሮሮዉ ሲደርቅ፣
ያ...... ትሁቱ ሻማ
ያትሁቱ ሻማ፤
አልባሱ ተገፎ በ'ንጨት ሲንጠለጠል፣
በህማሙ ንዳድ ሲቃትት ሲቃጠል፣
ጅማተ አጥንቱ በ'ሳት ተለኩሷል፣
ሰዉነቱ ቀልጧል በፍም ተገማምሷል።
ያ....... ትሁቱ ሻማ
ያ ትሁቱ ሻማ፤
ከቆሰለ አካሉ ደሙ እየወረደ፣
ብርሃን ያበራልን እሱ እየነደደ፣
አበቃለት ሲሉ መቼ ቀረ ቀልጦ?!
በ ሶስተኛ ቀኑ ታይቷል ሁሉን በልጦ።
✍ @artopian
Forwarded from Artopian🎨
፨፨ተረቱና እውነቱ፨፨
ላልነገረ ህመሙን፣
መድሃኒት የለውም፣
ተብሎ ሲተረት፣
ምሳሌና ተረት፣
መድሃኒት ብትሻ፣
ከ'መም መፈወሻ፣
መናገር ቢያቅታት፣
ግፊያውም ቢያግዳት...
አልያም ምናልባት፣
ሰው ስለበዛባት፣
ህመሟን ለማውራት፣
ቢሆን ያሳፈራት፣
ምንም ሳትናገር፤
ጨርቁን ስትዳስሰው፣
የውስጧን የሚያውቀው፤
ህመሟን ፈወሰው።
ልክ እንደተረቱ፣
ቢሆን ኖሮ እውነቱ፣
ሚያስጨንቀን ነገር፣
ሲሆን ማይነገር፣
ማውራት ሳንችል ስንቀር፣
ምን ይውጠን ነበር?!
✏️unknown
✍artopian
#repost
ላልነገረ ህመሙን፣
መድሃኒት የለውም፣
ተብሎ ሲተረት፣
ምሳሌና ተረት፣
መድሃኒት ብትሻ፣
ከ'መም መፈወሻ፣
መናገር ቢያቅታት፣
ግፊያውም ቢያግዳት...
አልያም ምናልባት፣
ሰው ስለበዛባት፣
ህመሟን ለማውራት፣
ቢሆን ያሳፈራት፣
ምንም ሳትናገር፤
ጨርቁን ስትዳስሰው፣
የውስጧን የሚያውቀው፤
ህመሟን ፈወሰው።
ልክ እንደተረቱ፣
ቢሆን ኖሮ እውነቱ፣
ሚያስጨንቀን ነገር፣
ሲሆን ማይነገር፣
ማውራት ሳንችል ስንቀር፣
ምን ይውጠን ነበር?!
✏️unknown
✍artopian
#repost