Forwarded from Yedidiya Art Gallery via @like
It's all about him
It's all about the baby boy that saved the world
The one that gives Joy to the world.
It's not about the food we eat the pictures we take or the gifts we receive from our beloved ones it's all about the king
🎄Merry Christmas🎄
📌 @Art_works_Jed
@Art_works_Jed
📌 @yedi_T
It's all about the baby boy that saved the world
The one that gives Joy to the world.
It's not about the food we eat the pictures we take or the gifts we receive from our beloved ones it's all about the king
🎄Merry Christmas🎄
📌 @Art_works_Jed
@Art_works_Jed
📌 @yedi_T
።፨።ልዩ ፍቅር።፨።
እንደበግ ተቅበዝብዤ፣
የመጥፊያዬን መንገድ ይዤ፣
ሙት የነበርኩ በሀጥያቴ፣
የማልጠቅም ምናምንቴ፣
የማስተውል አልነበረ፣
የሚገባኝ ሞት ነበረ።
እንዳይቀጣኝ በእውነቱ፣
ይቅር አለኝ በም'ረቱ፣
ይቅርታው ሳያንሰኝ፣
በደሙ ቀደሰኝ፣
እኔን እያወቀኝ፣
በጸጋው አጸደቀኝ።
ሀጥአን ለይ አለመፍረድ፣
ፃድቃን ለይ መፍረድ
በሱ ዘንድ ሁለቱ፣
የማይገመቱ።
ጻድቅ ፈራጅም ነው፣
ያረገው ይሄን ነው።
በደሌን ጠቅላላ፣
ሀጢአቴን በሞላ፣
ወረደና ከላይ፣
አኖረ ራሱ ላይ፣
ተጨነቀ ነፍሱ፣
በኔ ምትክ እሱ፣
የሰው ስጋ ለብሶ፣
በሀሰት ተከሶ፣
በደዌ ደቀቀ፣
በህማም ማቀቀ፣
በስቃይ ቃተተ፣
የመስቀል ሞት ሞተ።
ዘላለም ሚደነቅ፣
የሚያልፍ ከመታወቅ፣
ያለና ሚኖረው፣
ልዩ ፍቅር አለው።
እንደበግ ተቅበዝብዤ፣
የመጥፊያዬን መንገድ ይዤ፣
ሙት የነበርኩ በሀጥያቴ፣
የማልጠቅም ምናምንቴ፣
የማስተውል አልነበረ፣
የሚገባኝ ሞት ነበረ።
እንዳይቀጣኝ በእውነቱ፣
ይቅር አለኝ በም'ረቱ፣
ይቅርታው ሳያንሰኝ፣
በደሙ ቀደሰኝ፣
እኔን እያወቀኝ፣
በጸጋው አጸደቀኝ።
ሀጥአን ለይ አለመፍረድ፣
ፃድቃን ለይ መፍረድ
በሱ ዘንድ ሁለቱ፣
የማይገመቱ።
ጻድቅ ፈራጅም ነው፣
ያረገው ይሄን ነው።
በደሌን ጠቅላላ፣
ሀጢአቴን በሞላ፣
ወረደና ከላይ፣
አኖረ ራሱ ላይ፣
ተጨነቀ ነፍሱ፣
በኔ ምትክ እሱ፣
የሰው ስጋ ለብሶ፣
በሀሰት ተከሶ፣
በደዌ ደቀቀ፣
በህማም ማቀቀ፣
በስቃይ ቃተተ፣
የመስቀል ሞት ሞተ።
ዘላለም ሚደነቅ፣
የሚያልፍ ከመታወቅ፣
ያለና ሚኖረው፣
ልዩ ፍቅር አለው።
ያ ......ትሁቱ ሻማ
።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨።
ያ ትሁቱ ሻማ፤
መስዋዕት ለመሆን ራሱን ባዶ ያረገ፣
ከደረቅ መሬት ለይ እንደ ስር ያደገ፣
መልክ ዉበት የሌለዉ በደዌ የደቀቀ፣
በሰዉ የተጠላ በሰዉ የተናቀ፣
ያ .....ትሁቱ ሻማ
ያ ትሁቱ ሻማ፤
ቤዛ ሆኖ ሊከፍል የሰውን ሁሉ እዳ፣
አንዳች ሳይናገር ለእሳት ሲነዳ፣
በጭንቅ ነበልባል ሲነድ በብዙ፣
እንደ ደም ሲወርድ ሲንጠባጠብ ወዙ፣
ያ .....ት ሁቱ ሻማ
ያ ትሁቱ ሻማ፤
በተከተሉት ፊት ሲሸነፍ ሲረታ፣
ምራቅ ሲተፋበት በጥፊ ሲመታ፣
ብረት ባለዉ ጠፍር በሃይል ሲገረፍ፣
ቆዳዉ ሲገሸለጥ ደሙ ሲጉረፈረፍ፣
ያ......ትሁቱ ሻማ
ያ ትሀቱ ሻማ፤
በሾህ ጉንጉን አክሊል ግንባሩ ሲበሳ፣
መስቀል ተሸክሞ ሲወድቅ ሲነሳ፣
በረዣዠም ምስማር እጅ እግሩ ሲጠረቅ፣
መጠማቱ ሲያይል አፍ ጉሮሮዉ ሲደርቅ፣
ያ...... ትሁቱ ሻማ
ያትሁቱ ሻማ፤
አልባሱ ተገፎ በ'ንጨት ሲንጠለጠል፣
በህማሙ ንዳድ ሲቃትት ሲቃጠል፣
ጅማተ አጥንቱ በ'ሳት ተለኩሷል፣
ሰዉነቱ ቀልጧል በፍም ተገማምሷል።
ያ....... ትሁቱ ሻማ
ያ ትሁቱ ሻማ፤
ከቆሰለ አካሉ ደሙ እየወረደ፣
ብርሃን ያበራልን እሱ እየነደደ፣
አበቃለት ሲሉ መቼ ቀረ ቀልጦ?!
በ ሶስተኛ ቀኑ ታይቷል ሁሉን በልጦ።
✍ @artopian
።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨።
ያ ትሁቱ ሻማ፤
መስዋዕት ለመሆን ራሱን ባዶ ያረገ፣
ከደረቅ መሬት ለይ እንደ ስር ያደገ፣
መልክ ዉበት የሌለዉ በደዌ የደቀቀ፣
በሰዉ የተጠላ በሰዉ የተናቀ፣
ያ .....ትሁቱ ሻማ
ያ ትሁቱ ሻማ፤
ቤዛ ሆኖ ሊከፍል የሰውን ሁሉ እዳ፣
አንዳች ሳይናገር ለእሳት ሲነዳ፣
በጭንቅ ነበልባል ሲነድ በብዙ፣
እንደ ደም ሲወርድ ሲንጠባጠብ ወዙ፣
ያ .....ት ሁቱ ሻማ
ያ ትሁቱ ሻማ፤
በተከተሉት ፊት ሲሸነፍ ሲረታ፣
ምራቅ ሲተፋበት በጥፊ ሲመታ፣
ብረት ባለዉ ጠፍር በሃይል ሲገረፍ፣
ቆዳዉ ሲገሸለጥ ደሙ ሲጉረፈረፍ፣
ያ......ትሁቱ ሻማ
ያ ትሀቱ ሻማ፤
በሾህ ጉንጉን አክሊል ግንባሩ ሲበሳ፣
መስቀል ተሸክሞ ሲወድቅ ሲነሳ፣
በረዣዠም ምስማር እጅ እግሩ ሲጠረቅ፣
መጠማቱ ሲያይል አፍ ጉሮሮዉ ሲደርቅ፣
ያ...... ትሁቱ ሻማ
ያትሁቱ ሻማ፤
አልባሱ ተገፎ በ'ንጨት ሲንጠለጠል፣
በህማሙ ንዳድ ሲቃትት ሲቃጠል፣
ጅማተ አጥንቱ በ'ሳት ተለኩሷል፣
ሰዉነቱ ቀልጧል በፍም ተገማምሷል።
ያ....... ትሁቱ ሻማ
ያ ትሁቱ ሻማ፤
ከቆሰለ አካሉ ደሙ እየወረደ፣
ብርሃን ያበራልን እሱ እየነደደ፣
አበቃለት ሲሉ መቼ ቀረ ቀልጦ?!
በ ሶስተኛ ቀኑ ታይቷል ሁሉን በልጦ።
✍ @artopian