Artopian🎨
551 subscribers
238 photos
10 videos
2 files
4 links
The fear of the Lord is the beginning of wisdom.
@El_knows
Download Telegram
My first acrylic painting on canvas🎨
🔘Size (60*80)cm
🔘title- ''yeselam liguam''
🤔መስቀል አንደበት ቢኖረው ምን ይነግረን ነበር?
፨፨፨፨፨፨


ከመስቀሉ አንደበት 🗣

"ባይነ ህሊናዬ የኋሊት ገስግሼ፣
በትዝብት በቁጭት ያኔን አስታውሼ፣
የርግማን ምልክት የሆንኩ ከፍጥረቴ ፣
የተከወነውን ላውራ ባንደበቴ።

ሰው ያላከበረው ፈጽሞ የተናቀ፣
ከቶ የተጠላ ደዌንም ያወቀ፣
ራሱን ባዶ ያረገ ከሰማይ ወረደ፣
በከብቶች ማደሪያ በረት ተወለደ።
ለሁሉ ደቀቀ ለሁሉ ታመመ፣
የብዙውን በደል ሀጢአት ተሸከመ፣
የ'ጆቹ ፍጥረት ግን ልባቸው ደንድኖ፣
ማስተዋል ጎድሏቸው ክፋታቸው ገኖ፣
በሀሰት ከሰውት ተላልፎ ተሰቶ ፣
ንጹኹ ሊታሰር በርባን ግን ተፈቶ፣
"ስቀለው ስቀለው" አሉት ጲላጦስን፣
አልቀበል ብለው ጠልተው ክርስቶስን።
ጲላጦስም ገርሞት የሀሰት ክሳቸው፣
እጆቹን ተጣጥቦ ሊገድሉት ሰጣቸው።
እየዘበቱበት ቀይ ልብስ አልብሰውት፣
አይኖቹን ሸፍነው በጥፊ መተውት፣


ትንቢት ተንብይ ሲሉ ተዘባበቱበት፣
የሾህ አክሊል ጎንጉነው ራሱ ላይ ደፉበት፣
በመቃ እየመቱት ጎሰሙት ተፉበት::
ብረት ባለው ጠፍር ገርፈው አቁስለዉት፣
ከሁለት ወንበዴዎች መሀል ለይ ሰቅለውት፣
እሱ ግን ይቅር ባይ ምህረት የወደደ፣
አመጻቸውን አይቶም ለህዝቡ ማልደ።

"ክርስቶስ አይደለህ አድነህ ራስህን
እስቲ እኛንም አድን እንየው ሀይልህን።"

ሲል አንዱ ወንጀለኛ ህዝቡም ሲተባበር፣
ግን ደሞ ሌላኛው መልሱ እንደዚህ ነበር።
" እኛስ በድለን ነዉ እሱ ምን በደለ፣
ክፋትን ሳይሰራ ነው የተሰቀለ።"

የተረገመን ነዉ በኔ ሚሰቅሉቱ፣
ተብሎም ተጽፏል ይሄ ነው እውነቱ።
የአማልክት አምላክ ጻድቁ ቅዱሱ፣
እርግማን የሆነው ለሁሉ ነው እሱ።

በተማሪዎቹ ፊት ረቡኒ በሚሉት፣
አልባሱን ገፈውት በርቃኑ የሰቀሉት፣
ማን እንደሚወስድ- አውቀው ሊካፈሉ፣
እጀ ጠባቡ ለይ እጣ ተጣጣሉ።

ተጠማው ሲላቸው በደከመ ድምጹ፣
መች ልባቸው ራራ ይብሱን አመጹ።
በሰፍነግ ሆምጣጤ አረስርሰው ሰጡት፣
ደሞ ብለው ብለው ጎኑን በጦር ወጉት።
የተረገመን ነው በኔ ሚሰቅሉቱ፣
ተብሎም ተጽፏል ይሄ ነዉ እውነቱ፣
የአማልክት አምላክ ጻድቁ ቅዱሱ፣
እርግማን የሆነው ለሁሉ ነው እሱ።''

@artopian
"The tongue is like a sharp knife: it kills without drawing blood. "

#Learn_how_and_when_to_use_it.

#inktober #inktober2020 #blade #prompt5

@artopian
🐭 #rodents have a pair of upper & a pair of lower teeth that never stop growing.They must chew on things constantly to wear their teeth down & survive.

#inktober2020 #rodent
@artopian
🎨The painting, titled "Yeselam Liguam", is aimed at illustrating the role of a young person in the peace of a country.
1⃣A young man washing his father's feet...
This is to show that a young person should respect his family, be first and foremost obedient and humble to his family.
👨‍🦳 Besides a father should rebuke & guide his son to go in a righteous path.
🏡The basis for peace is home.
2⃣ We see the young man giving something to the needy. A young man who respects his family & is obedient can easily share love & what he has with others.
3⃣ We see the young man with his arm stabbed & bleeding, embracing the man who stabbed him.
❇️ This is to show a young man should learn how to forgive before he asks for forgiveness . Needless to say, he is a man & also makes mistakes.
A young man who knows how to forgive can easily reconcile differences among people.
4⃣ The young man is trying to resolve conflict between two people.
5⃣ We see a guy dressed in black inviting something to the young man & the young man refuses.
❇️The guy with black dress is to show that he is inviting something which has tragic consequences.
The use of drugs is a risk factor for illegal activities, and a young person addicted to various drugs will have the courage to do something illegal.
👏The young man did a good thing by rejecting this invitation.
6⃣Since one person's contribution is not enough,lots of people inspite of their differences have to take part for one common goal, the peace of a country.
🌝 Generally speaking, what I believe is that a young man who wants to contribute towards peace should go through this basic process without compromising to follow the above direction.

@artopian
የኖረው ሲሞት ነው
፨፨፨፨፨፨፨፨

ነፍሱ ከስጋው ላይ
ያኔ ሳትለያይ
እስትንፋሱ ሳለ
በምድር እያለ
አልን በ'ይወት አለ።
ሚጠይቀው ጠፍቶ
ዘመድ ወዳጅ አጥቶ
ኖሮ በሰቀቀን
ከለታት አንድ ቀን
ያቺ አንድ ነፍሱ
ስትጠፋ ከሱ
ሲበድን አካሉ
''ወይኔ ሞተ'' አሉ
ከዛም እንዳረፈ
በ'ድር ተለፈፈ።
ሰው ተሰበሰበ
ቤት ጊቢው ጠበበ
መሞቱን ሲሰማ መኖሩን የረሳ
የሟች ባህሪውን አስታውሶ አወሳ
ስራው ተነገረ
ስሙ ተዘከረ
ታድያ ነፍሱ እያለ 'አለ' ማለት ምነው?
አልገባንም እንጂ የኖረው ሲሞት ነው።

2005 ዓ.ም
@artopian
#repost