፨፨፨፨
በህይወት ጎዳና ለኑሮው ሲዳዳ፣
ወድቆ ሲቀር ስንቱ በወረርሽኝ ሜዳ፣
መኖር በሞት ጥላ ሂደቱ ሲዛነፍ፣
የሰው ነፍስ በዋዛ እንደ ቅጠል ሲረግፍ፣
ቀባሪ አስቀባሪ የሚሆን ሲጠፋ፣
ሚታየው ሚሰማው ቀን በቀን ሲከፋ፣
ስልጡን ባለጸጋ ሃያላን ነን ያሉ፣
ሚጨብጡት ሲያጡ ሽንፈት ስር ሲውሉ፣
ጠቢባን ምሁራን ሊቃውንት ስመጥር፣
ማወቅ ሲሳናቸው የ ኮቪዱን ሚስጥር፣
አይን ሲንከራተት ተራራ ሲወጣ፣
አወይ ጣር ሰቀቀን ረዳት ከየት ይምጣ?
......
ሰማይና ምድርን በቃሉ የፈጠረው፣
ረዳትማ እሱ ያለና ሚኖረው።
የሀገሬ ድንኳን እጅግ ተጨንቃለች፣
እግዚኦ ማረን ብላ እጇን ዘርግታለች።
ጎልያድ በጠጠር የመውደቁ ነገር፣
አምላክ በ'ስራኤል ዘንድ እንዳለ ሊነገር።
በኛም ዘንድ ኤሎሄ መኖሩ ይታወቅ፣
ይ' ባይን ማይታይ በጾም ጸሎት ይውደቅ።
፨፨፨፨
✍ሃና መለሰ
@artopian
@artopian
በህይወት ጎዳና ለኑሮው ሲዳዳ፣
ወድቆ ሲቀር ስንቱ በወረርሽኝ ሜዳ፣
መኖር በሞት ጥላ ሂደቱ ሲዛነፍ፣
የሰው ነፍስ በዋዛ እንደ ቅጠል ሲረግፍ፣
ቀባሪ አስቀባሪ የሚሆን ሲጠፋ፣
ሚታየው ሚሰማው ቀን በቀን ሲከፋ፣
ስልጡን ባለጸጋ ሃያላን ነን ያሉ፣
ሚጨብጡት ሲያጡ ሽንፈት ስር ሲውሉ፣
ጠቢባን ምሁራን ሊቃውንት ስመጥር፣
ማወቅ ሲሳናቸው የ ኮቪዱን ሚስጥር፣
አይን ሲንከራተት ተራራ ሲወጣ፣
አወይ ጣር ሰቀቀን ረዳት ከየት ይምጣ?
......
ሰማይና ምድርን በቃሉ የፈጠረው፣
ረዳትማ እሱ ያለና ሚኖረው።
የሀገሬ ድንኳን እጅግ ተጨንቃለች፣
እግዚኦ ማረን ብላ እጇን ዘርግታለች።
ጎልያድ በጠጠር የመውደቁ ነገር፣
አምላክ በ'ስራኤል ዘንድ እንዳለ ሊነገር።
በኛም ዘንድ ኤሎሄ መኖሩ ይታወቅ፣
ይ' ባይን ማይታይ በጾም ጸሎት ይውደቅ።
፨፨፨፨
✍ሃና መለሰ
@artopian
@artopian
፨፨ተረቱና እውነቱ፨፨
ላልነገረ ህመሙን፣
መድሃኒት የለውም፣
ተብሎ ሲተረት፣
ምሳሌና ተረት፣
መድሃኒት ብትሻ፣
ከ'መም መፈወሻ፣
መናገር ቢያቅታት፣
ግፊያውም ቢያግዳት...
አልያም ምናልባት፣
ሰው ስለበዛባት፣
ህመሟን ለማውራት፣
ቢሆን ያሳፈራት፣
ምንም ሳትናገር፤
ጨርቁን ስትዳስሰው፣
የውስጧን የሚያውቀው፤
ህመሟን ፈወሰው።
ልክ እንደተረቱ፣
ቢሆን ኖሮ እውነቱ፣
ሚያስጨንቀን ነገር፣
ሲሆን ማይነገር፣
ማውራት ሳንችል ስንቀር፣
ምን ይውጠን ነበር?!
✏️unknown
✍@artopian
ላልነገረ ህመሙን፣
መድሃኒት የለውም፣
ተብሎ ሲተረት፣
ምሳሌና ተረት፣
መድሃኒት ብትሻ፣
ከ'መም መፈወሻ፣
መናገር ቢያቅታት፣
ግፊያውም ቢያግዳት...
አልያም ምናልባት፣
ሰው ስለበዛባት፣
ህመሟን ለማውራት፣
ቢሆን ያሳፈራት፣
ምንም ሳትናገር፤
ጨርቁን ስትዳስሰው፣
የውስጧን የሚያውቀው፤
ህመሟን ፈወሰው።
ልክ እንደተረቱ፣
ቢሆን ኖሮ እውነቱ፣
ሚያስጨንቀን ነገር፣
ሲሆን ማይነገር፣
ማውራት ሳንችል ስንቀር፣
ምን ይውጠን ነበር?!
✏️unknown
✍@artopian
