Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች
አንድ በአሜሪካ የሚገኝ የኮፕቲክ(የግብጽ) ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እሑድ እለት ከቅዳሴ ቀጥሎ ይመስለኛል እዛው ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሕዝቡ በጴንጤ መዝሙር ሲያመልክ አይቼ(ዝማሬ የአምልኮ አካል ከሆነ😁😁) በጣም ነው የሚያሳዝነው አንዳንዴ ሰዉ ወደ ራሱ መንገድ ይኳትነዋል አይገልጸውም.. የሆነ ግለሰብ አደረገ ሳይሆን አንድ አጥቢያ ውስጥ ያውም እሑድ የቅዳሴ ቀን..
የኢትዮጵያን ቤተ ክርስቲያን በጣም ከምወድላት ነገር ውስጥ አንዱ በጣም ኮንሰርቫቲቭ መሆኗ.. ያው የግብጽ ቤተ ክርስቲያንም የጴንጤ መዝሙርን ስሙ አትልም ግን በውጭ ያሉት ትንሽ ልቅቅ ያሉ ናቸው ስለዚህም የራሳቸው ችግር ነው.. ሲያሻቸው ፕሮቴስታንቶችን መናፍቅ አንልምም ይሉሃል ሎል
ለትንሽ ደቂቃ የሚቆይ ፖስት
@Apostolic_Answers
የኢትዮጵያን ቤተ ክርስቲያን በጣም ከምወድላት ነገር ውስጥ አንዱ በጣም ኮንሰርቫቲቭ መሆኗ.. ያው የግብጽ ቤተ ክርስቲያንም የጴንጤ መዝሙርን ስሙ አትልም ግን በውጭ ያሉት ትንሽ ልቅቅ ያሉ ናቸው ስለዚህም የራሳቸው ችግር ነው.. ሲያሻቸው ፕሮቴስታንቶችን መናፍቅ አንልምም ይሉሃል ሎል
ለትንሽ ደቂቃ የሚቆይ ፖስት
@Apostolic_Answers
Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች
ክርስቶስ ኢየሱስ ጠበቃችን ነው..??
ያው በመጽሐፍ ቅዱስ ወይም በቤተ ክርስቲያን መረዳት ካየነው.. ክርስቲያን ኃጢአት ከሠራ ከኃጢአት ለመላቀቅ ንስሐ መግባት አለበት እና ንስሐ ሲገባ ከኃጢአቱ የሚነጻው ደግሞ በክርስቶስ ሞት ነው.. ያኔ ከ2000 ዓመት በፊት በሰራው የማዳን ሥራ አሁንም ድረስ ደሙ የኃጢአታችን ማስተሰሪያ ከመሆኑ አንጻር ጠበቃ ተብሎ ሊጠራ ይችላል.. 1ዮሐ 2:1 ጀምሮ እንደተገለጸውም..
@Apostolic_Answers
ያው በመጽሐፍ ቅዱስ ወይም በቤተ ክርስቲያን መረዳት ካየነው.. ክርስቲያን ኃጢአት ከሠራ ከኃጢአት ለመላቀቅ ንስሐ መግባት አለበት እና ንስሐ ሲገባ ከኃጢአቱ የሚነጻው ደግሞ በክርስቶስ ሞት ነው.. ያኔ ከ2000 ዓመት በፊት በሰራው የማዳን ሥራ አሁንም ድረስ ደሙ የኃጢአታችን ማስተሰሪያ ከመሆኑ አንጻር ጠበቃ ተብሎ ሊጠራ ይችላል.. 1ዮሐ 2:1 ጀምሮ እንደተገለጸውም..
@Apostolic_Answers
Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች
የዚህን መዝሙር ታሪክ የሚነግረኝ..??
ምክንያቱም ልጅ እያለሁ ጀምሮ ማዘር ስትዘምረው እሰማ ነበር አሁን ደግሞ ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ሲዘምሩት ሰማሁ እና እንዴት ነው ይህ ነገር😁😁 እስቲ እናቶቻችሁን ጠይቁ😁😁
የነሱ ሊሆን ይችላል ያው ግን ባውቀው ብዬ ነው
ምክንያቱም ልጅ እያለሁ ጀምሮ ማዘር ስትዘምረው እሰማ ነበር አሁን ደግሞ ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ሲዘምሩት ሰማሁ እና እንዴት ነው ይህ ነገር😁😁 እስቲ እናቶቻችሁን ጠይቁ😁😁
የነሱ ሊሆን ይችላል ያው ግን ባውቀው ብዬ ነው
Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች
ኧረ በካቶሊኩ ዘንድ Vatican news አዲስ ዜና ይዞ ብቅ በሏል.. ነገርዬው ነገረ ማርያም ላይ ያጠነጥናል..
በፖፑም አፕሩቭ የተደረገው ኖት እንደሚገልጸው ከሆነ:
ቅድስት ድንግል “አብሮ ቤዛ/አዳኝ”(co-redemptrix የሚለው በብዙ ካቶሊኮች የሚታመነው መጠሪያዋ አስቸጋሪና አደናጋሪ መሆኑን ገልጸዋል.. እንዲሁም ደግሞ ማርያም “የጸጋ ሁሉ ወደ ሰዎች መፍሰሻ” (mediatrix of all graces) የሚለውንም እምነታቸውን በማንሳት ጸጋ ወደ ሰዎች የሚፈስሰው በማርያም በኩል ሳይሆን በእግዚአብሔር ልጅ በኢየሱስ በኩል ነው ብለዋል..
ተመስገን.. ነገረ ማርያምን ከመለጠጥ እንዲህ በአዋጅ መታቀብ ሲጀምሩ በጣም ደስ ይላል.. ጌታ ይርዳቸው..
በፖፑም አፕሩቭ የተደረገው ኖት እንደሚገልጸው ከሆነ:
ቅድስት ድንግል “አብሮ ቤዛ/አዳኝ”(co-redemptrix የሚለው በብዙ ካቶሊኮች የሚታመነው መጠሪያዋ አስቸጋሪና አደናጋሪ መሆኑን ገልጸዋል.. እንዲሁም ደግሞ ማርያም “የጸጋ ሁሉ ወደ ሰዎች መፍሰሻ” (mediatrix of all graces) የሚለውንም እምነታቸውን በማንሳት ጸጋ ወደ ሰዎች የሚፈስሰው በማርያም በኩል ሳይሆን በእግዚአብሔር ልጅ በኢየሱስ በኩል ነው ብለዋል..
ተመስገን.. ነገረ ማርያምን ከመለጠጥ እንዲህ በአዋጅ መታቀብ ሲጀምሩ በጣም ደስ ይላል.. ጌታ ይርዳቸው..
Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች
ቀጥታ ወደ አማርኛ ሲተረጎም:
ቫቲካን የክርስቶስን ብቸኛ አዳኝነት በማስረገጥ co-redemptrix እና “መካከለኛ” የሚለውን መጠሪያ ለማርያም ልንጠቀመው እንደማይገባ ገልጿል።
______________
የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ይህንን ስትል ዶግማ ላይ ተሳስቼ ኖሬ አሁን አስተካከልኩ እያለች አይደለም.. ይልቁንም በብዙዎች ዘንድ እኚህ መጠሪያዎች ጥቅም ላይ ይውሉ ስለነበር.. እና ደግሞ እነዚህን መጠሪያዎች ዶግማ የማድረግ ጥያቄም ስለነበር ቤተ ክርስቲያኒቱ ጭራሹኑ ባንጠቀማቸው አደናጋሪ ናቸው አለች ነው..
ያው ከዚህ ቀደም ዶግማ ይደረግ የሚል እንኳን ክርክር የነበረበትን ነገር ጭራሹኑ ማስወገዷ ነው ባለፈው ሃሪፍ ነው ያስባለን እንጂ ዶግማዋን አርማ አይደለም.. አንድ ፕሮቴስታንት ባልሆነ መልኩ ለመተቸት ሲሞክር አይቼ ነው..
የ6 ደቂቃ ፖስት
ቫቲካን የክርስቶስን ብቸኛ አዳኝነት በማስረገጥ co-redemptrix እና “መካከለኛ” የሚለውን መጠሪያ ለማርያም ልንጠቀመው እንደማይገባ ገልጿል።
______________
የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ይህንን ስትል ዶግማ ላይ ተሳስቼ ኖሬ አሁን አስተካከልኩ እያለች አይደለም.. ይልቁንም በብዙዎች ዘንድ እኚህ መጠሪያዎች ጥቅም ላይ ይውሉ ስለነበር.. እና ደግሞ እነዚህን መጠሪያዎች ዶግማ የማድረግ ጥያቄም ስለነበር ቤተ ክርስቲያኒቱ ጭራሹኑ ባንጠቀማቸው አደናጋሪ ናቸው አለች ነው..
ያው ከዚህ ቀደም ዶግማ ይደረግ የሚል እንኳን ክርክር የነበረበትን ነገር ጭራሹኑ ማስወገዷ ነው ባለፈው ሃሪፍ ነው ያስባለን እንጂ ዶግማዋን አርማ አይደለም.. አንድ ፕሮቴስታንት ባልሆነ መልኩ ለመተቸት ሲሞክር አይቼ ነው..
የ6 ደቂቃ ፖስት
Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች
ይቅርታ ልጠይቅ መሰለኝ..
በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ ከጥቂት አመታት በፊት በፕሮቴስታንት ተሐድሶዎች የተፈጠረው ነገር ብዛቱን ትናንት ለጉዳዩ ቅርብ ከነበሩ ሰዎች እየሰማሁ በጣም ነው የገረመኝ.. በብዙዎች ክርስቲያኖች ዘንድ አደገኛ የልብ ቁስለት ነው ያደረሰው.. እና አንዳንድ ሰዎች በቅንነት እኔን የሚቃወሙ ካሉ ያ ነገር ውስጣቸው ስላለ ነው.. ቁስላቸውን ነው የሚሰማቸው..
እና በቅንነት ከክፋት ውጪ ሆናችሁ የምትተቹኝ ወንድም እና እህቶቼ.. በአንድም በሌላም ላስከፋኋችሁ በጌታ ፊት ሆኜ ይቅርታ ጠይቃችኋለሁ.. እወዳችኋለሁ.. እኔም የቤተ ክርስቲያኔ ነገር ስለሚያንገበግበኝ ብቻ ነው ምፈጣጥነው😊😊 እና ይህንን ተረድታችሁ ይቅርታ አድርጉልኝ.. አይዟችሁ ደግሞ..
አክሊል
@Apostolic_Answers
በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ ከጥቂት አመታት በፊት በፕሮቴስታንት ተሐድሶዎች የተፈጠረው ነገር ብዛቱን ትናንት ለጉዳዩ ቅርብ ከነበሩ ሰዎች እየሰማሁ በጣም ነው የገረመኝ.. በብዙዎች ክርስቲያኖች ዘንድ አደገኛ የልብ ቁስለት ነው ያደረሰው.. እና አንዳንድ ሰዎች በቅንነት እኔን የሚቃወሙ ካሉ ያ ነገር ውስጣቸው ስላለ ነው.. ቁስላቸውን ነው የሚሰማቸው..
እና በቅንነት ከክፋት ውጪ ሆናችሁ የምትተቹኝ ወንድም እና እህቶቼ.. በአንድም በሌላም ላስከፋኋችሁ በጌታ ፊት ሆኜ ይቅርታ ጠይቃችኋለሁ.. እወዳችኋለሁ.. እኔም የቤተ ክርስቲያኔ ነገር ስለሚያንገበግበኝ ብቻ ነው ምፈጣጥነው😊😊 እና ይህንን ተረድታችሁ ይቅርታ አድርጉልኝ.. አይዟችሁ ደግሞ..
አክሊል
@Apostolic_Answers
Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
እኔ ራሱ ዛሬ ገና ነው ያስተዋልኩት..
ቤተ ክርስቲያናችን ይህንን ስእል ብታሻሽለውና ጸጉሩን ግንባሩ ድረስ ብትገጥምልን ደስ ይለኛል
ለ4 ደቂቃ የሚቆይ
ቤተ ክርስቲያናችን ይህንን ስእል ብታሻሽለውና ጸጉሩን ግንባሩ ድረስ ብትገጥምልን ደስ ይለኛል
ለ4 ደቂቃ የሚቆይ
Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ይሄ ጊዜ ትዝ ይላችኋል አይደል.. መሠረት ደፋር ስታሸንፍ ምስለ ፍቁር ወልዳን ካሜራ ፊት አውጥታ ለዓለም ሁሉ እመቤታችንን ስታሳይ..
ያኔ በዓለም አቀፍ ደረጃ ክርስቲያኖች ሁሉ እጅግ ደስ አላቸው.. ያው ጥንታውያን አብያተ ክርስቲያናት ካቶሊክን ጨምሮ ማለት ነው..
አሁን ደግሞ እኛ ሃገር የቲክቶክ አዋርድ ላይ አንዳንድ ልጆች ሲያሸንፉ የወላዲተ አምላክን ስም መጥራታቸው ለአንዳንዶች የሚጨንቅ ሆኗል እና ያሳዝናል..
ሰው አባቱን ወይም ወንድም እህቱን አለያም እናቱን ቢጠራ ምንም ችግር አይኖረውም.. እናቱን ማርያምን ግን ከጠራ ያበሳጫል.. እዛ መድረክ ላይ እኮ እየሰበኩ አይደለም እነዚህ ልጆች.. ያው ፍቅራቸውን እየገለጹ ነው እና ይግለጹ በጣም ደስ ይላል..
@Apostolic_Answers
ያኔ በዓለም አቀፍ ደረጃ ክርስቲያኖች ሁሉ እጅግ ደስ አላቸው.. ያው ጥንታውያን አብያተ ክርስቲያናት ካቶሊክን ጨምሮ ማለት ነው..
አሁን ደግሞ እኛ ሃገር የቲክቶክ አዋርድ ላይ አንዳንድ ልጆች ሲያሸንፉ የወላዲተ አምላክን ስም መጥራታቸው ለአንዳንዶች የሚጨንቅ ሆኗል እና ያሳዝናል..
ሰው አባቱን ወይም ወንድም እህቱን አለያም እናቱን ቢጠራ ምንም ችግር አይኖረውም.. እናቱን ማርያምን ግን ከጠራ ያበሳጫል.. እዛ መድረክ ላይ እኮ እየሰበኩ አይደለም እነዚህ ልጆች.. ያው ፍቅራቸውን እየገለጹ ነው እና ይግለጹ በጣም ደስ ይላል..
@Apostolic_Answers
Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ኧረ በጌታ ስም😁😁
ስግጥ ፍምስ ❌
ስግጥ ንግሥ ✅
ስግጥ ፍምስ ❌
ስግጥ ንግሥ ✅
Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች
ኢየሱስ አሁንም ድረስ በሰማይ አብን ይለምነዋል(ይጸልያል) እንዴ..??
በውስጥ የደረሰኝ ጥያቄ ነው..
ጌታችን በምድር ሳለ ጸልዩዋል ወደ አብ ማልዷል.. ግን ደግሞ ልክ እንዲሁ አሁንም በሰማይ የጸሎት እና ልመና ድርጊት እየተካሄደ ነው እና ምልጃ ምንለውም እሱን ነው የሚል ትምህርት በቤተ ክርስቲያን ደረጃ በየትም ቦታ አላውቅም.. ጌታ ኢየሱስ በምድር ላይ የሰራው ሥራ ለዘላለም ሕያው ነው.. ለዘላለም ሕያው የሆነው ደግሞ የማይለወጥ ክህነት ስላለውና በአብ ቀኝ አሁንም ድረስ ተቀምጦ ስለሚኖር ነው.. ስለዚህም ስለሁላችን ሞቶ የተነሳው ጌታ በአብ ቀኝ አለና በእርሱ የተሰራው ሥራ ሁሌም የሚያገለግል ነው..
ስለዚህም በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ውስጥ “ይጸልያል” የሚለውን ቃል የተጠቀሙ ሊቃውንት ቢገኝ እንኳን በምድር ላይ የሰራው ሥራ ሕያው መሆኑን ከማመልከት አንጻር ይሆናል እንጂ አሁንም የቀረ ጸሎት ያለ ይመስል እየደጋገመ እየጸለየ ይኖራል የሚለው ከክርስትና ራቅ ያለ መሰለኝ😁😁
ምንም ሆነ ምን ግን ከምን አንጻር እንደተጠቀሙት እናያለን እንጂ እንዲሁ ቃላት እየመዘዝን የራሳችንን አስተምህሮ ማለትም አሁንም ጌታ በአብ ፊት እየተማጸነ ነው የሚል ትምህርት መመስረት ከባድ ይመስለኛል..
- በፕሮቴስታንቶቹ እንኳን ለምሳሌ እነ ካልቪን የኢየሱስን ምልጃ ሲያስረዱ በመስቀል ላይ ሞቶ ከዚያም መነሳቱን እንጂ አሁን ላይ ይለምናል ማለት አይደለም እያሉ ነው..(commentary on romans 8:34)
- በካቶሊካውያን ዘንድም የምልጃን አሳብ ሲያብራሩ የጌታ መካከለኛነት እንደሆነና በመስቀሉ ሥራ የተከናወነ እንደሆነ ሲያስሰቀምጡ የቅዱሳንን ግን ጸሎት ልመና ብለው ይለዩታል(catholic encyclopedia, intercession(mediation)
ኢየሱስ በሰማይ ይለምናል የሚለው ቃል የቤተ ክርስቲያን ልምድም እንዳልሆነ ይናገራሉ(George haydock, comm. On romans)
- በግብጽም እነ አቡነ ሺኖዳ የጌታችንን አስታራቂነት ሲያብራሩ ከመስቀሉ ሥራ አንጻር ያደርጉትና ጸሎት ልመናን ግን ለይተው ለቅዱሳን ይሰጣሉ..(comparative theology, on intercession)
- የኛ ሃገር ሊቃውንትም ይማልዳል የሚለውን ሲያብራሩ በእለተ አርብ በመስቀል ላይ በሠራው ሥራ ለዘላለም ስለሚያስታርቅበት እንደሆነ ነው የሚያስቀምጡት(የሮሜም የዕብራውያንም አንድምታ ትርጓሜ)
@Apostolic_Answers
በውስጥ የደረሰኝ ጥያቄ ነው..
ጌታችን በምድር ሳለ ጸልዩዋል ወደ አብ ማልዷል.. ግን ደግሞ ልክ እንዲሁ አሁንም በሰማይ የጸሎት እና ልመና ድርጊት እየተካሄደ ነው እና ምልጃ ምንለውም እሱን ነው የሚል ትምህርት በቤተ ክርስቲያን ደረጃ በየትም ቦታ አላውቅም.. ጌታ ኢየሱስ በምድር ላይ የሰራው ሥራ ለዘላለም ሕያው ነው.. ለዘላለም ሕያው የሆነው ደግሞ የማይለወጥ ክህነት ስላለውና በአብ ቀኝ አሁንም ድረስ ተቀምጦ ስለሚኖር ነው.. ስለዚህም ስለሁላችን ሞቶ የተነሳው ጌታ በአብ ቀኝ አለና በእርሱ የተሰራው ሥራ ሁሌም የሚያገለግል ነው..
ስለዚህም በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ውስጥ “ይጸልያል” የሚለውን ቃል የተጠቀሙ ሊቃውንት ቢገኝ እንኳን በምድር ላይ የሰራው ሥራ ሕያው መሆኑን ከማመልከት አንጻር ይሆናል እንጂ አሁንም የቀረ ጸሎት ያለ ይመስል እየደጋገመ እየጸለየ ይኖራል የሚለው ከክርስትና ራቅ ያለ መሰለኝ😁😁
ምንም ሆነ ምን ግን ከምን አንጻር እንደተጠቀሙት እናያለን እንጂ እንዲሁ ቃላት እየመዘዝን የራሳችንን አስተምህሮ ማለትም አሁንም ጌታ በአብ ፊት እየተማጸነ ነው የሚል ትምህርት መመስረት ከባድ ይመስለኛል..
- በፕሮቴስታንቶቹ እንኳን ለምሳሌ እነ ካልቪን የኢየሱስን ምልጃ ሲያስረዱ በመስቀል ላይ ሞቶ ከዚያም መነሳቱን እንጂ አሁን ላይ ይለምናል ማለት አይደለም እያሉ ነው..(commentary on romans 8:34)
- በካቶሊካውያን ዘንድም የምልጃን አሳብ ሲያብራሩ የጌታ መካከለኛነት እንደሆነና በመስቀሉ ሥራ የተከናወነ እንደሆነ ሲያስሰቀምጡ የቅዱሳንን ግን ጸሎት ልመና ብለው ይለዩታል(catholic encyclopedia, intercession(mediation)
ኢየሱስ በሰማይ ይለምናል የሚለው ቃል የቤተ ክርስቲያን ልምድም እንዳልሆነ ይናገራሉ(George haydock, comm. On romans)
- በግብጽም እነ አቡነ ሺኖዳ የጌታችንን አስታራቂነት ሲያብራሩ ከመስቀሉ ሥራ አንጻር ያደርጉትና ጸሎት ልመናን ግን ለይተው ለቅዱሳን ይሰጣሉ..(comparative theology, on intercession)
- የኛ ሃገር ሊቃውንትም ይማልዳል የሚለውን ሲያብራሩ በእለተ አርብ በመስቀል ላይ በሠራው ሥራ ለዘላለም ስለሚያስታርቅበት እንደሆነ ነው የሚያስቀምጡት(የሮሜም የዕብራውያንም አንድምታ ትርጓሜ)
@Apostolic_Answers
Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች
ከብዙ ማመንታት በኋላ የተጻፈ ነው.. ያው አስቸጋሪ ነገሮችን እያስተዋልን ስለሆነ..
አንድ ወንድ በተለይ መንፈሳዊ ነገር ላይ በአደባባይ እየተሳተፈ.. ግን ደግሞ ለአንቺ በውስጥ ሲያወራሽ:- “ያው እኔ እንኳን እንደው ከጠቀመ በሚለው ላገልግል ብዬ እንጂ የራሴ ላይፍ ደግሞ አለኝ እና በዛ ላይፌ ደግሞ በጣም ደካማ ነኝ.. የተወሰነ እጠጣለሁ ምናምን..” ብሎ ጀምሮ በሆነ መልኩ ከአንቺ ጋር ለመውጣት መንገድ ካመቻቸ.. በወሬ ውስጥ sexual ነገርን እንድታስቢ ካደረገ.. ወይም ደግሞ መንፈሳዊ ሰው ነው ብለሽም ራስሽም አፕሮች አድርገሽው ግን እሱ ወደ መጠጥና ዝሙት ካሻገረሽ..
እመኚኝ ይህ ወንድም ዘማ ነው። እና በርካታ እህቶች ላይ ነው እንዲህ የሚሆነው ማለት ነው.. ያው አንቺም እንደዛውረከስ ያልሽ ከሆንሽ ሂጂበት.. የእግዚአብሔር ሴት ልጆች ግን እንዲህ ካለው የክርስቶስ ጠላት ራሳችሁን ጠብቁ.. ራሱንም ገድሎ እናንተንም ይገድላችኋልና.. ክርስቶስን እንዳትናፍቁት ተስፋችሁንም ጭምር ያጨልመዋልና..
በጣም እንደው ውስጤን ስለሚረብሸው የጻፍኩት ነው.. እኔ ደግሞ የሃገር ድክመቶች ያሉብኝ ሰው ስሆን እንዲህ መናገሬ ትእቢት እንዳይሆንብኝ ጌታ ይጠብቀኝ..
ለ3 ደቂቃ የሚቆይ
አንድ ወንድ በተለይ መንፈሳዊ ነገር ላይ በአደባባይ እየተሳተፈ.. ግን ደግሞ ለአንቺ በውስጥ ሲያወራሽ:- “ያው እኔ እንኳን እንደው ከጠቀመ በሚለው ላገልግል ብዬ እንጂ የራሴ ላይፍ ደግሞ አለኝ እና በዛ ላይፌ ደግሞ በጣም ደካማ ነኝ.. የተወሰነ እጠጣለሁ ምናምን..” ብሎ ጀምሮ በሆነ መልኩ ከአንቺ ጋር ለመውጣት መንገድ ካመቻቸ.. በወሬ ውስጥ sexual ነገርን እንድታስቢ ካደረገ.. ወይም ደግሞ መንፈሳዊ ሰው ነው ብለሽም ራስሽም አፕሮች አድርገሽው ግን እሱ ወደ መጠጥና ዝሙት ካሻገረሽ..
እመኚኝ ይህ ወንድም ዘማ ነው። እና በርካታ እህቶች ላይ ነው እንዲህ የሚሆነው ማለት ነው.. ያው አንቺም እንደዛው
በጣም እንደው ውስጤን ስለሚረብሸው የጻፍኩት ነው.. እኔ ደግሞ የሃገር ድክመቶች ያሉብኝ ሰው ስሆን እንዲህ መናገሬ ትእቢት እንዳይሆንብኝ ጌታ ይጠብቀኝ..
ለ3 ደቂቃ የሚቆይ
Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች
አንድ ሰው እንዲህ ሲል ሰማሁ..
“ጸሎት በግእዝ ሲሆን ይሰምራል ከአማርኛ ይልቅ.. ያው እንደ እውቀታችን በአማርኛ ስንጸልይም ቢሰማንም እንኳን ግን የአማርኛው የሰፈር ቃላት ይሆንብናል”
ኧረ አምላካችን በአማርኛ መሆኑ ብቻ ሳይሆን በአማርኛ ሆኖ እየተንተባተብን እንኳን ከልባችን ብንጸልይ ከግእዙ ባላነሰ መልኩ የሚቀበል ጌታ ነው.. በግእዝ ስለጸለይክ ብቻ ምንም የተለየ ነገር አትፈጥርም.. ከልብህ በንጽሕና ስትጸልይ ግን በየትኛው ቋንቋ ቢሆን ጆርውን ያዘነብልልሃል.. ስለዚህ ለጸሎት የሚያስፈልገው ልብ እንጂ ቋንቋ አይደለም
“ጸሎት በግእዝ ሲሆን ይሰምራል ከአማርኛ ይልቅ.. ያው እንደ እውቀታችን በአማርኛ ስንጸልይም ቢሰማንም እንኳን ግን የአማርኛው የሰፈር ቃላት ይሆንብናል”
ኧረ አምላካችን በአማርኛ መሆኑ ብቻ ሳይሆን በአማርኛ ሆኖ እየተንተባተብን እንኳን ከልባችን ብንጸልይ ከግእዙ ባላነሰ መልኩ የሚቀበል ጌታ ነው.. በግእዝ ስለጸለይክ ብቻ ምንም የተለየ ነገር አትፈጥርም.. ከልብህ በንጽሕና ስትጸልይ ግን በየትኛው ቋንቋ ቢሆን ጆርውን ያዘነብልልሃል.. ስለዚህ ለጸሎት የሚያስፈልገው ልብ እንጂ ቋንቋ አይደለም
Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የምርም እንዳለውም ልጅ ኖሮት ከሆነ አሳዛኝ ነው.. ሰው ዲያቆን ሆኖ ሳያገባ ልጅ ሊኖረው አይገባም ጸያፍ ነው..
ግን ደግሞ ሊኖረው አይችልም ማለት አይደለም በስህተት ወድቆ እንዲህ ያለ ነገር ሊፈጠር ይችል ይሆናል..
ግን ደግሞ ይህንን ነውሩንና እርኩሰቱን ለመደበቅ ግን “ዲያቆን እያለሁ ጨለማ ውስጥ ስለነበርኩ ነው” ማለት በጣም አደገኛ ነው..
ግን ደግሞ ሊኖረው አይችልም ማለት አይደለም በስህተት ወድቆ እንዲህ ያለ ነገር ሊፈጠር ይችል ይሆናል..
ግን ደግሞ ይህንን ነውሩንና እርኩሰቱን ለመደበቅ ግን “ዲያቆን እያለሁ ጨለማ ውስጥ ስለነበርኩ ነው” ማለት በጣም አደገኛ ነው..
Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች
አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ እንዳረፈ ሰማሁ እና ሰው ነንና መቼስ በጣም ያሳዝናል.. ጌታችን እንኳን አላዛር ሲያንቀላፋ አልቅሶ ነበር..
ያው በእርግጥ ወደ ጌታ ነው የሄደው.. ጌታ ምህረት እንደሚያደርግለትና ከእርሱ ጋር እንደሚያኖረውም አምናለሁ.. ስለዚህም እርሱ በዚህ ሰዓት ውስጥ በማይነገር ደስታ ውስጥ ነው..
አያችሁ የኔ ተወዳጆች በሕይወትም ብንኖር ብንሞትም ከጌታ ጋር ነን.. ይልቁን ደግሞ ስንሞት የበለጠ ወደ እርሱ እንሄዳለን.. ስለዚህም በጌታ ሆነን ስናንቀላፋ ለኛ ጥቅም ነው.. ጳውሎስ እንዲህ ይላል:
“ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ፥ ሞትም ጥቅም ነው።” [ፊል 1:21]
የኛ ተራም በፊታችን አለና ጌታ ኢየሱስን በሕይወታችን እናክብረው..
ኪሪዬ ኤሌይሶን - ጌታ ሆይ ማረን
ያው በእርግጥ ወደ ጌታ ነው የሄደው.. ጌታ ምህረት እንደሚያደርግለትና ከእርሱ ጋር እንደሚያኖረውም አምናለሁ.. ስለዚህም እርሱ በዚህ ሰዓት ውስጥ በማይነገር ደስታ ውስጥ ነው..
አያችሁ የኔ ተወዳጆች በሕይወትም ብንኖር ብንሞትም ከጌታ ጋር ነን.. ይልቁን ደግሞ ስንሞት የበለጠ ወደ እርሱ እንሄዳለን.. ስለዚህም በጌታ ሆነን ስናንቀላፋ ለኛ ጥቅም ነው.. ጳውሎስ እንዲህ ይላል:
“ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ፥ ሞትም ጥቅም ነው።” [ፊል 1:21]
የኛ ተራም በፊታችን አለና ጌታ ኢየሱስን በሕይወታችን እናክብረው..
ኪሪዬ ኤሌይሶን - ጌታ ሆይ ማረን
Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በመጽሐፈ ዚቅ በስህተት የገባ ነገር መኖሩን በመግለጽ አባታችን እንዲህ ይላሉ:-
ያው ስህተት ሲገኝ አባቶቻችንም እንዴት እንደሚናገሩበት ማወቅ ለምትፈልጉ ሰዎች ይሁን
ያው ስህተት ሲገኝ አባቶቻችንም እንዴት እንደሚናገሩበት ማወቅ ለምትፈልጉ ሰዎች ይሁን
Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች
አንድ ኦርቶዶክስ ከፕሮቴስታንት ጋር ሆኖ ሙስሊሞችን ሊከራከር ይገባልን..??
እሺ ጥቂት ሰዎች የጠቀየቁኝ ጥያቄ ስለሆነ ቀለል አድርጌ ግላዊ ምልከታዬን ላስቀምጥ..
እኔ ያው ሁሌም ቢሆን በራስ መሥራትን ነው ምመርጠው.. ግን ደግሞ እንደው አጋጣሚው ከተፈጠረም ይህ ነገር ሊከሰት የሚችለው ፕሮቴስታንቱ የኔን ቤተ ክርስቲያን የማይጠላና ባገኘው አጋጣሚ የማይሰድባት ከሆነ.. እንዲሁም የጌታ ቤተ ክርስቲያን መሆኗን ካመነ.. በአጠቃላይ በጣም ጥሩ ነገር ለቤተ ክርስቲያን ካየሁበት ብቻ..
ከዛ ውጪ ግን የክርስቶስ አካል የሆነችውን ቤተ ክርስቲያኔን ሲሳደብ የሚውል ከሆነ ግን በፍጹም አላደርገውም.. ክርስቶስና ቤተ ክርስቲያን(ንጉሡ እና መንግሥቲቱ) ይቀድማሉ
ለ3 ደቂቃ የሚቆይ
እሺ ጥቂት ሰዎች የጠቀየቁኝ ጥያቄ ስለሆነ ቀለል አድርጌ ግላዊ ምልከታዬን ላስቀምጥ..
እኔ ያው ሁሌም ቢሆን በራስ መሥራትን ነው ምመርጠው.. ግን ደግሞ እንደው አጋጣሚው ከተፈጠረም ይህ ነገር ሊከሰት የሚችለው ፕሮቴስታንቱ የኔን ቤተ ክርስቲያን የማይጠላና ባገኘው አጋጣሚ የማይሰድባት ከሆነ.. እንዲሁም የጌታ ቤተ ክርስቲያን መሆኗን ካመነ.. በአጠቃላይ በጣም ጥሩ ነገር ለቤተ ክርስቲያን ካየሁበት ብቻ..
ከዛ ውጪ ግን የክርስቶስ አካል የሆነችውን ቤተ ክርስቲያኔን ሲሳደብ የሚውል ከሆነ ግን በፍጹም አላደርገውም.. ክርስቶስና ቤተ ክርስቲያን(ንጉሡ እና መንግሥቲቱ) ይቀድማሉ
ለ3 ደቂቃ የሚቆይ
Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ሙስሊም ባሎች ሚስቶቻችሁን ከነዚህ ሰዎች ላይቭ አርቁ ፕሊስ..
ለምሳሌ የዚህ ሰውዬ ሚስት ከነዚህ ሰዎች ላይቭ ሰምታ ጥያቄ አብዝታ ልትፈታው ነው.. ልብ አርጉ እንግዲህ ያ ጀማ..
ለ4 ደቂቃ የሚቆይ ፖስት😁😁
ለምሳሌ የዚህ ሰውዬ ሚስት ከነዚህ ሰዎች ላይቭ ሰምታ ጥያቄ አብዝታ ልትፈታው ነው.. ልብ አርጉ እንግዲህ ያ ጀማ..
ለ4 ደቂቃ የሚቆይ ፖስት😁😁
Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች
"ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ" የሚለው የፕሮቴስታንቶች አሳብ አነሳሱ ያው ከቅዱሳን አንጻር አልነበረም.. እርግጥ ነው እርሱንም ሊያጠቃልል ቢችልም እንኳን ማለት ነው.. የመጀመሪያው የፕሮቴስታንቶች አሳብ እንዲህ ነው..
ሰው በኃጢአት ምክንያት ሞቷል ነጻ ፈቃዱንም አጥቷል.. ስለዚህም ሰው ለመዳን መፍቀድ እንኳን አይችልምና በፈቃዳችን ሳይሆን የምንድነው በእግዚአብሔር ቅድመ ውሳኔ መሠረት በጸጋው ብቻ በክርስቶስ ሥራ ነው.. ስለዚህም ከእኛ የሆነ ምንም ነገር የለምና ፈቃድ እና እምነትን ጨምሮ ማለት ነው.. ስለዚህም ክብሩን ሁሉ እግዚአብሔር ይውሰድ.. ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ ይሉናል።
እኔኮ የሚገርመኝ ነገር ፊት ለፊት ላይ ሲታይ ቃሉ ምናምን ውብ ነው "ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ" ሲባል.. ቀረብ ብላችሁ ስትፈትሹት ግን ብዙ ምንፍቅናዎችን አዝሎ ደግሞ ታገኙታላችሁ.. ለምሳሌ ብዙ ጴንጤዎችም ከላይ ያለውን ዓይነት የቅድመ ውሳኔ ትምህርት አይቀበሉም ግን ደግሞ "ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ" አመጣጡ ከዛ ነው።
መልካም የጌታ ቀን
ሰው በኃጢአት ምክንያት ሞቷል ነጻ ፈቃዱንም አጥቷል.. ስለዚህም ሰው ለመዳን መፍቀድ እንኳን አይችልምና በፈቃዳችን ሳይሆን የምንድነው በእግዚአብሔር ቅድመ ውሳኔ መሠረት በጸጋው ብቻ በክርስቶስ ሥራ ነው.. ስለዚህም ከእኛ የሆነ ምንም ነገር የለምና ፈቃድ እና እምነትን ጨምሮ ማለት ነው.. ስለዚህም ክብሩን ሁሉ እግዚአብሔር ይውሰድ.. ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ ይሉናል።
እኔኮ የሚገርመኝ ነገር ፊት ለፊት ላይ ሲታይ ቃሉ ምናምን ውብ ነው "ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ" ሲባል.. ቀረብ ብላችሁ ስትፈትሹት ግን ብዙ ምንፍቅናዎችን አዝሎ ደግሞ ታገኙታላችሁ.. ለምሳሌ ብዙ ጴንጤዎችም ከላይ ያለውን ዓይነት የቅድመ ውሳኔ ትምህርት አይቀበሉም ግን ደግሞ "ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ" አመጣጡ ከዛ ነው።
መልካም የጌታ ቀን
Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች
ብዙ ፕሮቴስታንቶች(እናቅባለን የሚሉትም) ጋር የሚታየው አስቸጋሪው ነገር እነርሱ ካሉበት ዲኖሚኔሽን ውጪ ያለውን ነገር ብዙም ስለማያውቁት የሆነ ነገር በተነገረ ቁጥር ያልተገባ ነገርን መመለስ ይጀምራሉ..
ከበፊት ጀምሮ እንደምታስታውሱት ሉተራን ምስጢራት ላይ ያላቸውን አቋም አንስተን ስናስረዳቸው ጭራሽ ሉተር ምስጢራትን ለድኅነት ነው ብሎ አያምንም ብለው መጥተው ሲከራከሩ ታስታውሳላችሁ.. አሁን ላይ ገብቷቸው አርፈው ተቀምጠዋል.. አሁን ደግሞ "ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ" የሚለው ትምህርት እና "ጸጋ ብቻ" የሚለው ትምህርት ምን ያህል እርስ በእርሱ የተያያዘ እንደሆነና "ጸጋ ብቻ" ከሚለው ትምህርት የተነሳ እንደሆነም አያውቁምና እንደለመዱት ለጊዜው ይቃወማሉ.. ከዚያም ላይቭ ገብተን በደንብ ስንሄድበት አርፈው ይቀመጣሉ ማለት ነው..
እኛ በድኅነታችን ውስጥ እኛም ክብር ይገባን አላልንም.. ታድያ ግን "ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ" የሚለው የፕሮቴስታንቱ እሳቤ ሲያዩት መልካም ቢመስልም ቀረብ ብላችሁ ስታዩት ግን ምንፍቅናን አዝሏል ነው.. ምንፍቅናውም "ጸጋ ብቻ" የሚለው የሐዳሲያኑ ትምህርት ነው።
ድኅነትን ሙሉ በሙሉ የተቀበልነው አዎ ከእግዚአብሔር ነው በእኛ ሥራ አይደለም.. ግን ደግሞ ቢያንስ ፈቅደን ነው የዳንነው.. ድኅነቱን ለመቀበል ቢያንስ ፈቅደን "እጃችንን ዘርግተናል"😁 በጸጋ ብቻ ትምህርት ግን active will(በመቀበል እንኳን ሊተባበር የሚችል ፈቃድ) የለህም.. ወዳጄ ውስጡ ያለው የስህተት ብዛት ትልቅ ነውና እንደው ብትተወው ብዙም ያላነበብክበትን ነገር።
ባይሆን እኛ እንደ አስፈላጊነቱ ላይቭ ላይ እንሄድበታለን😁😁 ለ10 ደቂቃ የሚቆይ ፖስት
ከበፊት ጀምሮ እንደምታስታውሱት ሉተራን ምስጢራት ላይ ያላቸውን አቋም አንስተን ስናስረዳቸው ጭራሽ ሉተር ምስጢራትን ለድኅነት ነው ብሎ አያምንም ብለው መጥተው ሲከራከሩ ታስታውሳላችሁ.. አሁን ላይ ገብቷቸው አርፈው ተቀምጠዋል.. አሁን ደግሞ "ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ" የሚለው ትምህርት እና "ጸጋ ብቻ" የሚለው ትምህርት ምን ያህል እርስ በእርሱ የተያያዘ እንደሆነና "ጸጋ ብቻ" ከሚለው ትምህርት የተነሳ እንደሆነም አያውቁምና እንደለመዱት ለጊዜው ይቃወማሉ.. ከዚያም ላይቭ ገብተን በደንብ ስንሄድበት አርፈው ይቀመጣሉ ማለት ነው..
እኛ በድኅነታችን ውስጥ እኛም ክብር ይገባን አላልንም.. ታድያ ግን "ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ" የሚለው የፕሮቴስታንቱ እሳቤ ሲያዩት መልካም ቢመስልም ቀረብ ብላችሁ ስታዩት ግን ምንፍቅናን አዝሏል ነው.. ምንፍቅናውም "ጸጋ ብቻ" የሚለው የሐዳሲያኑ ትምህርት ነው።
ድኅነትን ሙሉ በሙሉ የተቀበልነው አዎ ከእግዚአብሔር ነው በእኛ ሥራ አይደለም.. ግን ደግሞ ቢያንስ ፈቅደን ነው የዳንነው.. ድኅነቱን ለመቀበል ቢያንስ ፈቅደን "እጃችንን ዘርግተናል"😁 በጸጋ ብቻ ትምህርት ግን active will(በመቀበል እንኳን ሊተባበር የሚችል ፈቃድ) የለህም.. ወዳጄ ውስጡ ያለው የስህተት ብዛት ትልቅ ነውና እንደው ብትተወው ብዙም ያላነበብክበትን ነገር።
ባይሆን እኛ እንደ አስፈላጊነቱ ላይቭ ላይ እንሄድበታለን😁😁 ለ10 ደቂቃ የሚቆይ ፖስት
Forwarded from ኪዳን ዘኢየሱስ
ዶግማችን የቤተክርስቲያን አባቶች ትምህርት ይሁን!
ከሰሞኑ በቤተክርስቲያናችን በሰዉ ልብ ዘንድ የተሳለ አንድ ነገር አለ እርሱም ዶግማችን ከፕሮቴስታንቶች መለየት ማስመሰል ነው። ማለትም ወደ ፕሮቴስታንት የቀረበ የመሰለን ማንኛውም ትምህርት ዶግማ እስኪመስል ድረስ ማውገዝ እንዲሁም ከእነርሱ ትምህርት ለመራቅ ተብሎ አባታዊውን ትምህርት እስከ መካድ መድረስ።
ለምሳሌ የሰሞኑን ጳጳሳት ጉዳይ ብናይ "ማርያም ቤዛ አትባልም" ያሉትን ጳጳስ ከጫፍ እስከ ጫፍ ተቃውሞ ነው የተሰማው ምክንያቱም ቤዛ አትባልም የሚሉት ፕሮቴስታንቶች ናቸው። ነገር ግን በተቃራኒው "የምንቀበለው የማርያም ሥጋ ነው" ያሉትን ጳጳስ የተቃወሙ ቢኖሩም ተቃውሞው ግን አልበረታም ለምን "ፕሮቴስታንቶች የማርያምን ሥጋ ነው ምንቀበለው ስለማይሉ" እውነት ለመናገር ፕሮቴስታንቶች እንዲህ ያለ ትምህርት ቢኖራቸው ኖሮ ከጫፍ እስከ ጫፍ ተቃውሞ እንሰማ ነበር። ይገባኛል በቤተክርስቲያናችን ውስጥ ገብተን ፕሮቴስታንታዊ ትምህርት የሚያስተምሩ ተዋሕዶሶች ስለነበሩ የትኛውም ፕሮቴስታንታዊ የሚመስል ትምህርት ሲሆን ስጋት ይደቀንብናል ነገር ግን የአስተምህሮዋችን ማእከል የአባቶች ትምህርት እንጂ ፕሮቴስታንትን መቃወም ማድረግ የለብንም።
የክርስቶስ ምልጃ ጉዳይ ላይም ተመሳሳይ ነገር ነው የማየው ስለ ክርስቶስ ምልጃ ፕሮቴስታንቶች ስለሚያስተምሩ ከተሐድሶዎች ጋርም በዚህ ጉዳይ የክርክር ጠባሳ ስለነበር የትኛውም የክርስቶስን ምልጃ ያጎላ ትምህርት ስናይ ፕሮቴስታንታዊ ይመስለናል ነገር ግን የራሳችን የቤተክርስቲያን አባቶችም ሆኑ የአምልኮ መጻሕፍቶቻችን በክርስቶስ ምልጃ ትምህርት የተሞሉ መሆናችንን አንዘንጋ የክርስቶስ ምልጃ ትምህርት ኦርቶዶክሳዊ እንጂ ፕሮቴስታንታዊ አይደለም እንዳውም ከማንም ይልቅ ለእኛ የተገባ ነው አንድ ጊዜ በቀረበው መሥዋዕት በቁርባን አማካኝነት እንቀበለዋለንና ፕሮቴስታንቶች ግን ቁርባን የኃጢአት ይቅርታ የሚሰጥ የዕለተ አርቡ መሥዋዕት ነው ብለው ስለማያምኑ ለማስረዳት ይከብዳቸዋል።
እኔ ግን የመጨረሻ ነገር ልበላችሁ ለትምህርት ማንጸሪያዬ የቤተክርስቲያን አባቶች ናቸው እንጂ ፕሮቴስታንቶችን መቃወም አይደለም። ስለዚህ የቤተክርስቲያን አባቶች ያስተማሩትን በልበ ሙሉነት እኔም እናገረዋለሁ።
ከሰሞኑ በቤተክርስቲያናችን በሰዉ ልብ ዘንድ የተሳለ አንድ ነገር አለ እርሱም ዶግማችን ከፕሮቴስታንቶች መለየት ማስመሰል ነው። ማለትም ወደ ፕሮቴስታንት የቀረበ የመሰለን ማንኛውም ትምህርት ዶግማ እስኪመስል ድረስ ማውገዝ እንዲሁም ከእነርሱ ትምህርት ለመራቅ ተብሎ አባታዊውን ትምህርት እስከ መካድ መድረስ።
ለምሳሌ የሰሞኑን ጳጳሳት ጉዳይ ብናይ "ማርያም ቤዛ አትባልም" ያሉትን ጳጳስ ከጫፍ እስከ ጫፍ ተቃውሞ ነው የተሰማው ምክንያቱም ቤዛ አትባልም የሚሉት ፕሮቴስታንቶች ናቸው። ነገር ግን በተቃራኒው "የምንቀበለው የማርያም ሥጋ ነው" ያሉትን ጳጳስ የተቃወሙ ቢኖሩም ተቃውሞው ግን አልበረታም ለምን "ፕሮቴስታንቶች የማርያምን ሥጋ ነው ምንቀበለው ስለማይሉ" እውነት ለመናገር ፕሮቴስታንቶች እንዲህ ያለ ትምህርት ቢኖራቸው ኖሮ ከጫፍ እስከ ጫፍ ተቃውሞ እንሰማ ነበር። ይገባኛል በቤተክርስቲያናችን ውስጥ ገብተን ፕሮቴስታንታዊ ትምህርት የሚያስተምሩ ተዋሕዶሶች ስለነበሩ የትኛውም ፕሮቴስታንታዊ የሚመስል ትምህርት ሲሆን ስጋት ይደቀንብናል ነገር ግን የአስተምህሮዋችን ማእከል የአባቶች ትምህርት እንጂ ፕሮቴስታንትን መቃወም ማድረግ የለብንም።
የክርስቶስ ምልጃ ጉዳይ ላይም ተመሳሳይ ነገር ነው የማየው ስለ ክርስቶስ ምልጃ ፕሮቴስታንቶች ስለሚያስተምሩ ከተሐድሶዎች ጋርም በዚህ ጉዳይ የክርክር ጠባሳ ስለነበር የትኛውም የክርስቶስን ምልጃ ያጎላ ትምህርት ስናይ ፕሮቴስታንታዊ ይመስለናል ነገር ግን የራሳችን የቤተክርስቲያን አባቶችም ሆኑ የአምልኮ መጻሕፍቶቻችን በክርስቶስ ምልጃ ትምህርት የተሞሉ መሆናችንን አንዘንጋ የክርስቶስ ምልጃ ትምህርት ኦርቶዶክሳዊ እንጂ ፕሮቴስታንታዊ አይደለም እንዳውም ከማንም ይልቅ ለእኛ የተገባ ነው አንድ ጊዜ በቀረበው መሥዋዕት በቁርባን አማካኝነት እንቀበለዋለንና ፕሮቴስታንቶች ግን ቁርባን የኃጢአት ይቅርታ የሚሰጥ የዕለተ አርቡ መሥዋዕት ነው ብለው ስለማያምኑ ለማስረዳት ይከብዳቸዋል።
እኔ ግን የመጨረሻ ነገር ልበላችሁ ለትምህርት ማንጸሪያዬ የቤተክርስቲያን አባቶች ናቸው እንጂ ፕሮቴስታንቶችን መቃወም አይደለም። ስለዚህ የቤተክርስቲያን አባቶች ያስተማሩትን በልበ ሙሉነት እኔም እናገረዋለሁ።