Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ሙስሊም ባሎች ሚስቶቻችሁን ከነዚህ ሰዎች ላይቭ አርቁ ፕሊስ..
ለምሳሌ የዚህ ሰውዬ ሚስት ከነዚህ ሰዎች ላይቭ ሰምታ ጥያቄ አብዝታ ልትፈታው ነው.. ልብ አርጉ እንግዲህ ያ ጀማ..
ለ4 ደቂቃ የሚቆይ ፖስት😁😁
ለምሳሌ የዚህ ሰውዬ ሚስት ከነዚህ ሰዎች ላይቭ ሰምታ ጥያቄ አብዝታ ልትፈታው ነው.. ልብ አርጉ እንግዲህ ያ ጀማ..
ለ4 ደቂቃ የሚቆይ ፖስት😁😁
Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች
"ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ" የሚለው የፕሮቴስታንቶች አሳብ አነሳሱ ያው ከቅዱሳን አንጻር አልነበረም.. እርግጥ ነው እርሱንም ሊያጠቃልል ቢችልም እንኳን ማለት ነው.. የመጀመሪያው የፕሮቴስታንቶች አሳብ እንዲህ ነው..
ሰው በኃጢአት ምክንያት ሞቷል ነጻ ፈቃዱንም አጥቷል.. ስለዚህም ሰው ለመዳን መፍቀድ እንኳን አይችልምና በፈቃዳችን ሳይሆን የምንድነው በእግዚአብሔር ቅድመ ውሳኔ መሠረት በጸጋው ብቻ በክርስቶስ ሥራ ነው.. ስለዚህም ከእኛ የሆነ ምንም ነገር የለምና ፈቃድ እና እምነትን ጨምሮ ማለት ነው.. ስለዚህም ክብሩን ሁሉ እግዚአብሔር ይውሰድ.. ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ ይሉናል።
እኔኮ የሚገርመኝ ነገር ፊት ለፊት ላይ ሲታይ ቃሉ ምናምን ውብ ነው "ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ" ሲባል.. ቀረብ ብላችሁ ስትፈትሹት ግን ብዙ ምንፍቅናዎችን አዝሎ ደግሞ ታገኙታላችሁ.. ለምሳሌ ብዙ ጴንጤዎችም ከላይ ያለውን ዓይነት የቅድመ ውሳኔ ትምህርት አይቀበሉም ግን ደግሞ "ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ" አመጣጡ ከዛ ነው።
መልካም የጌታ ቀን
ሰው በኃጢአት ምክንያት ሞቷል ነጻ ፈቃዱንም አጥቷል.. ስለዚህም ሰው ለመዳን መፍቀድ እንኳን አይችልምና በፈቃዳችን ሳይሆን የምንድነው በእግዚአብሔር ቅድመ ውሳኔ መሠረት በጸጋው ብቻ በክርስቶስ ሥራ ነው.. ስለዚህም ከእኛ የሆነ ምንም ነገር የለምና ፈቃድ እና እምነትን ጨምሮ ማለት ነው.. ስለዚህም ክብሩን ሁሉ እግዚአብሔር ይውሰድ.. ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ ይሉናል።
እኔኮ የሚገርመኝ ነገር ፊት ለፊት ላይ ሲታይ ቃሉ ምናምን ውብ ነው "ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ" ሲባል.. ቀረብ ብላችሁ ስትፈትሹት ግን ብዙ ምንፍቅናዎችን አዝሎ ደግሞ ታገኙታላችሁ.. ለምሳሌ ብዙ ጴንጤዎችም ከላይ ያለውን ዓይነት የቅድመ ውሳኔ ትምህርት አይቀበሉም ግን ደግሞ "ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ" አመጣጡ ከዛ ነው።
መልካም የጌታ ቀን
Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች
ብዙ ፕሮቴስታንቶች(እናቅባለን የሚሉትም) ጋር የሚታየው አስቸጋሪው ነገር እነርሱ ካሉበት ዲኖሚኔሽን ውጪ ያለውን ነገር ብዙም ስለማያውቁት የሆነ ነገር በተነገረ ቁጥር ያልተገባ ነገርን መመለስ ይጀምራሉ..
ከበፊት ጀምሮ እንደምታስታውሱት ሉተራን ምስጢራት ላይ ያላቸውን አቋም አንስተን ስናስረዳቸው ጭራሽ ሉተር ምስጢራትን ለድኅነት ነው ብሎ አያምንም ብለው መጥተው ሲከራከሩ ታስታውሳላችሁ.. አሁን ላይ ገብቷቸው አርፈው ተቀምጠዋል.. አሁን ደግሞ "ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ" የሚለው ትምህርት እና "ጸጋ ብቻ" የሚለው ትምህርት ምን ያህል እርስ በእርሱ የተያያዘ እንደሆነና "ጸጋ ብቻ" ከሚለው ትምህርት የተነሳ እንደሆነም አያውቁምና እንደለመዱት ለጊዜው ይቃወማሉ.. ከዚያም ላይቭ ገብተን በደንብ ስንሄድበት አርፈው ይቀመጣሉ ማለት ነው..
እኛ በድኅነታችን ውስጥ እኛም ክብር ይገባን አላልንም.. ታድያ ግን "ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ" የሚለው የፕሮቴስታንቱ እሳቤ ሲያዩት መልካም ቢመስልም ቀረብ ብላችሁ ስታዩት ግን ምንፍቅናን አዝሏል ነው.. ምንፍቅናውም "ጸጋ ብቻ" የሚለው የሐዳሲያኑ ትምህርት ነው።
ድኅነትን ሙሉ በሙሉ የተቀበልነው አዎ ከእግዚአብሔር ነው በእኛ ሥራ አይደለም.. ግን ደግሞ ቢያንስ ፈቅደን ነው የዳንነው.. ድኅነቱን ለመቀበል ቢያንስ ፈቅደን "እጃችንን ዘርግተናል"😁 በጸጋ ብቻ ትምህርት ግን active will(በመቀበል እንኳን ሊተባበር የሚችል ፈቃድ) የለህም.. ወዳጄ ውስጡ ያለው የስህተት ብዛት ትልቅ ነውና እንደው ብትተወው ብዙም ያላነበብክበትን ነገር።
ባይሆን እኛ እንደ አስፈላጊነቱ ላይቭ ላይ እንሄድበታለን😁😁 ለ10 ደቂቃ የሚቆይ ፖስት
ከበፊት ጀምሮ እንደምታስታውሱት ሉተራን ምስጢራት ላይ ያላቸውን አቋም አንስተን ስናስረዳቸው ጭራሽ ሉተር ምስጢራትን ለድኅነት ነው ብሎ አያምንም ብለው መጥተው ሲከራከሩ ታስታውሳላችሁ.. አሁን ላይ ገብቷቸው አርፈው ተቀምጠዋል.. አሁን ደግሞ "ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ" የሚለው ትምህርት እና "ጸጋ ብቻ" የሚለው ትምህርት ምን ያህል እርስ በእርሱ የተያያዘ እንደሆነና "ጸጋ ብቻ" ከሚለው ትምህርት የተነሳ እንደሆነም አያውቁምና እንደለመዱት ለጊዜው ይቃወማሉ.. ከዚያም ላይቭ ገብተን በደንብ ስንሄድበት አርፈው ይቀመጣሉ ማለት ነው..
እኛ በድኅነታችን ውስጥ እኛም ክብር ይገባን አላልንም.. ታድያ ግን "ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ" የሚለው የፕሮቴስታንቱ እሳቤ ሲያዩት መልካም ቢመስልም ቀረብ ብላችሁ ስታዩት ግን ምንፍቅናን አዝሏል ነው.. ምንፍቅናውም "ጸጋ ብቻ" የሚለው የሐዳሲያኑ ትምህርት ነው።
ድኅነትን ሙሉ በሙሉ የተቀበልነው አዎ ከእግዚአብሔር ነው በእኛ ሥራ አይደለም.. ግን ደግሞ ቢያንስ ፈቅደን ነው የዳንነው.. ድኅነቱን ለመቀበል ቢያንስ ፈቅደን "እጃችንን ዘርግተናል"😁 በጸጋ ብቻ ትምህርት ግን active will(በመቀበል እንኳን ሊተባበር የሚችል ፈቃድ) የለህም.. ወዳጄ ውስጡ ያለው የስህተት ብዛት ትልቅ ነውና እንደው ብትተወው ብዙም ያላነበብክበትን ነገር።
ባይሆን እኛ እንደ አስፈላጊነቱ ላይቭ ላይ እንሄድበታለን😁😁 ለ10 ደቂቃ የሚቆይ ፖስት
Forwarded from ኪዳን ዘኢየሱስ
ዶግማችን የቤተክርስቲያን አባቶች ትምህርት ይሁን!
ከሰሞኑ በቤተክርስቲያናችን በሰዉ ልብ ዘንድ የተሳለ አንድ ነገር አለ እርሱም ዶግማችን ከፕሮቴስታንቶች መለየት ማስመሰል ነው። ማለትም ወደ ፕሮቴስታንት የቀረበ የመሰለን ማንኛውም ትምህርት ዶግማ እስኪመስል ድረስ ማውገዝ እንዲሁም ከእነርሱ ትምህርት ለመራቅ ተብሎ አባታዊውን ትምህርት እስከ መካድ መድረስ።
ለምሳሌ የሰሞኑን ጳጳሳት ጉዳይ ብናይ "ማርያም ቤዛ አትባልም" ያሉትን ጳጳስ ከጫፍ እስከ ጫፍ ተቃውሞ ነው የተሰማው ምክንያቱም ቤዛ አትባልም የሚሉት ፕሮቴስታንቶች ናቸው። ነገር ግን በተቃራኒው "የምንቀበለው የማርያም ሥጋ ነው" ያሉትን ጳጳስ የተቃወሙ ቢኖሩም ተቃውሞው ግን አልበረታም ለምን "ፕሮቴስታንቶች የማርያምን ሥጋ ነው ምንቀበለው ስለማይሉ" እውነት ለመናገር ፕሮቴስታንቶች እንዲህ ያለ ትምህርት ቢኖራቸው ኖሮ ከጫፍ እስከ ጫፍ ተቃውሞ እንሰማ ነበር። ይገባኛል በቤተክርስቲያናችን ውስጥ ገብተን ፕሮቴስታንታዊ ትምህርት የሚያስተምሩ ተዋሕዶሶች ስለነበሩ የትኛውም ፕሮቴስታንታዊ የሚመስል ትምህርት ሲሆን ስጋት ይደቀንብናል ነገር ግን የአስተምህሮዋችን ማእከል የአባቶች ትምህርት እንጂ ፕሮቴስታንትን መቃወም ማድረግ የለብንም።
የክርስቶስ ምልጃ ጉዳይ ላይም ተመሳሳይ ነገር ነው የማየው ስለ ክርስቶስ ምልጃ ፕሮቴስታንቶች ስለሚያስተምሩ ከተሐድሶዎች ጋርም በዚህ ጉዳይ የክርክር ጠባሳ ስለነበር የትኛውም የክርስቶስን ምልጃ ያጎላ ትምህርት ስናይ ፕሮቴስታንታዊ ይመስለናል ነገር ግን የራሳችን የቤተክርስቲያን አባቶችም ሆኑ የአምልኮ መጻሕፍቶቻችን በክርስቶስ ምልጃ ትምህርት የተሞሉ መሆናችንን አንዘንጋ የክርስቶስ ምልጃ ትምህርት ኦርቶዶክሳዊ እንጂ ፕሮቴስታንታዊ አይደለም እንዳውም ከማንም ይልቅ ለእኛ የተገባ ነው አንድ ጊዜ በቀረበው መሥዋዕት በቁርባን አማካኝነት እንቀበለዋለንና ፕሮቴስታንቶች ግን ቁርባን የኃጢአት ይቅርታ የሚሰጥ የዕለተ አርቡ መሥዋዕት ነው ብለው ስለማያምኑ ለማስረዳት ይከብዳቸዋል።
እኔ ግን የመጨረሻ ነገር ልበላችሁ ለትምህርት ማንጸሪያዬ የቤተክርስቲያን አባቶች ናቸው እንጂ ፕሮቴስታንቶችን መቃወም አይደለም። ስለዚህ የቤተክርስቲያን አባቶች ያስተማሩትን በልበ ሙሉነት እኔም እናገረዋለሁ።
ከሰሞኑ በቤተክርስቲያናችን በሰዉ ልብ ዘንድ የተሳለ አንድ ነገር አለ እርሱም ዶግማችን ከፕሮቴስታንቶች መለየት ማስመሰል ነው። ማለትም ወደ ፕሮቴስታንት የቀረበ የመሰለን ማንኛውም ትምህርት ዶግማ እስኪመስል ድረስ ማውገዝ እንዲሁም ከእነርሱ ትምህርት ለመራቅ ተብሎ አባታዊውን ትምህርት እስከ መካድ መድረስ።
ለምሳሌ የሰሞኑን ጳጳሳት ጉዳይ ብናይ "ማርያም ቤዛ አትባልም" ያሉትን ጳጳስ ከጫፍ እስከ ጫፍ ተቃውሞ ነው የተሰማው ምክንያቱም ቤዛ አትባልም የሚሉት ፕሮቴስታንቶች ናቸው። ነገር ግን በተቃራኒው "የምንቀበለው የማርያም ሥጋ ነው" ያሉትን ጳጳስ የተቃወሙ ቢኖሩም ተቃውሞው ግን አልበረታም ለምን "ፕሮቴስታንቶች የማርያምን ሥጋ ነው ምንቀበለው ስለማይሉ" እውነት ለመናገር ፕሮቴስታንቶች እንዲህ ያለ ትምህርት ቢኖራቸው ኖሮ ከጫፍ እስከ ጫፍ ተቃውሞ እንሰማ ነበር። ይገባኛል በቤተክርስቲያናችን ውስጥ ገብተን ፕሮቴስታንታዊ ትምህርት የሚያስተምሩ ተዋሕዶሶች ስለነበሩ የትኛውም ፕሮቴስታንታዊ የሚመስል ትምህርት ሲሆን ስጋት ይደቀንብናል ነገር ግን የአስተምህሮዋችን ማእከል የአባቶች ትምህርት እንጂ ፕሮቴስታንትን መቃወም ማድረግ የለብንም።
የክርስቶስ ምልጃ ጉዳይ ላይም ተመሳሳይ ነገር ነው የማየው ስለ ክርስቶስ ምልጃ ፕሮቴስታንቶች ስለሚያስተምሩ ከተሐድሶዎች ጋርም በዚህ ጉዳይ የክርክር ጠባሳ ስለነበር የትኛውም የክርስቶስን ምልጃ ያጎላ ትምህርት ስናይ ፕሮቴስታንታዊ ይመስለናል ነገር ግን የራሳችን የቤተክርስቲያን አባቶችም ሆኑ የአምልኮ መጻሕፍቶቻችን በክርስቶስ ምልጃ ትምህርት የተሞሉ መሆናችንን አንዘንጋ የክርስቶስ ምልጃ ትምህርት ኦርቶዶክሳዊ እንጂ ፕሮቴስታንታዊ አይደለም እንዳውም ከማንም ይልቅ ለእኛ የተገባ ነው አንድ ጊዜ በቀረበው መሥዋዕት በቁርባን አማካኝነት እንቀበለዋለንና ፕሮቴስታንቶች ግን ቁርባን የኃጢአት ይቅርታ የሚሰጥ የዕለተ አርቡ መሥዋዕት ነው ብለው ስለማያምኑ ለማስረዳት ይከብዳቸዋል።
እኔ ግን የመጨረሻ ነገር ልበላችሁ ለትምህርት ማንጸሪያዬ የቤተክርስቲያን አባቶች ናቸው እንጂ ፕሮቴስታንቶችን መቃወም አይደለም። ስለዚህ የቤተክርስቲያን አባቶች ያስተማሩትን በልበ ሙሉነት እኔም እናገረዋለሁ።
Forwarded from ኪዳን ዘኢየሱስ
በአብ ቀኝ ያለ ጠበቃ
ብዙ ሰው ኢየሱስ በመስቀል ላይ ለኃጢአታችን ማስተሠርያ ከሆነ በኋላ በአብ ቀኝ ለፍርድ የተቀመጠ ዳኛ ኃጢአት ስንሠራ ለምን ሠራችሁ ብሎ የሚቆጣ ፈራጅ አድርገን እንስለዋለን ስለዚህም ኢየሱስ ተቆጪ አምላክ ስለሆነ ርኅርኅተ ህሊና በሆነችው በእመቤታችን በኩል እናገኘዋለን እሱ ፈራጅ እርሷ ግን ሩኅሩኅ አድርጎ መሳል አለ።
ነገር ግን አንድ ነገር አስታውሱ ኢየሱስ በመስቀል ላይ ባለ ፍቅሩ አሁንም በአብ ቀኝ አለ ፤ በመስቀል ላይ ለኃጢአታችን ማስተሠርያ እንደሆነው አሁንሞ በአብ ቀኝ ለኃጢአታችን ማስተሠርያ ነው ለኃጢአታችን ብቻ አይደለም ለዓለም ሁሉ ኃጢአት እንጂ። ኢየሱስ በአብ ቀኝ የተቀመጠው ኃጢአት በሠራን ቁጥር ለምን ብሎ የሚቆጣን ፈራጅ ሳይሆን አንዴ ባቀረበው ምልጃ የሚያስታርቀን አስታራቂ ነው በገዛ በደሙ ወደ ሰማያት ገብቷልና! ነገር ግን የኃጢአታችን ጠበቃ በሰማያት አለ ብለን ኃጢአትን የመሥራት ነጻነት የምናገኝ አይደለም ይልቅስ በአብ ቀኝ ያለውን ጌታችንን ለመምሰል በቅድስና ሕይወት እንመላለሳለን እንጂ ደካሞች ነንና ብንወድቅም በደሙ እንነጻለን።
በእመቤታችን በኩል ወደ ጌታ መቅረብ መልካም ነው ነገር ግን ጌታን ተቆጪ አደርጎ በመሳል አይደለም "በእርሱም ዘንድ ባለ እምነታችን በኩል በመታመን ድፍረትና መግባት በእርሱ አለንና። (ኤፌ 3:12)
በመስቀሉ ላይ በታላቅ መቃተት ምልጃን በማቅረብ የወደደን ጌታ አሁንም በዚሁ ፍቅሩ በአብ ቀኝ አለ ስለዚህም ስለእኛ ይማልድልናል ፤ ከአቤል ደም ይልቅ የሚጮህ ደም ❤️
@KidanZeIyesus
ብዙ ሰው ኢየሱስ በመስቀል ላይ ለኃጢአታችን ማስተሠርያ ከሆነ በኋላ በአብ ቀኝ ለፍርድ የተቀመጠ ዳኛ ኃጢአት ስንሠራ ለምን ሠራችሁ ብሎ የሚቆጣ ፈራጅ አድርገን እንስለዋለን ስለዚህም ኢየሱስ ተቆጪ አምላክ ስለሆነ ርኅርኅተ ህሊና በሆነችው በእመቤታችን በኩል እናገኘዋለን እሱ ፈራጅ እርሷ ግን ሩኅሩኅ አድርጎ መሳል አለ።
ነገር ግን አንድ ነገር አስታውሱ ኢየሱስ በመስቀል ላይ ባለ ፍቅሩ አሁንም በአብ ቀኝ አለ ፤ በመስቀል ላይ ለኃጢአታችን ማስተሠርያ እንደሆነው አሁንሞ በአብ ቀኝ ለኃጢአታችን ማስተሠርያ ነው ለኃጢአታችን ብቻ አይደለም ለዓለም ሁሉ ኃጢአት እንጂ። ኢየሱስ በአብ ቀኝ የተቀመጠው ኃጢአት በሠራን ቁጥር ለምን ብሎ የሚቆጣን ፈራጅ ሳይሆን አንዴ ባቀረበው ምልጃ የሚያስታርቀን አስታራቂ ነው በገዛ በደሙ ወደ ሰማያት ገብቷልና! ነገር ግን የኃጢአታችን ጠበቃ በሰማያት አለ ብለን ኃጢአትን የመሥራት ነጻነት የምናገኝ አይደለም ይልቅስ በአብ ቀኝ ያለውን ጌታችንን ለመምሰል በቅድስና ሕይወት እንመላለሳለን እንጂ ደካሞች ነንና ብንወድቅም በደሙ እንነጻለን።
በእመቤታችን በኩል ወደ ጌታ መቅረብ መልካም ነው ነገር ግን ጌታን ተቆጪ አደርጎ በመሳል አይደለም "በእርሱም ዘንድ ባለ እምነታችን በኩል በመታመን ድፍረትና መግባት በእርሱ አለንና። (ኤፌ 3:12)
በመስቀሉ ላይ በታላቅ መቃተት ምልጃን በማቅረብ የወደደን ጌታ አሁንም በዚሁ ፍቅሩ በአብ ቀኝ አለ ስለዚህም ስለእኛ ይማልድልናል ፤ ከአቤል ደም ይልቅ የሚጮህ ደም ❤️
@KidanZeIyesus
Forwarded from ኪዳን ዘኢየሱስ
በቤታችን ያለን anti-intellectualism አካሔድ ግድ ማጥራት አለብን ወገን። ማኅበረ ቅዱሳን ላይ መጽሐፍ ቅዱስ 81 ወይስ 66 በሚል ርእስ የተለቀቀ ቪዲዮ እያየሁ ተሳቅቄ ልሞት።
1. መጽሐፍ ቅዱስ 81 አድርገው የወሰኑልን በ3ተኛው ክፍለ ዘመን የነበሩ ሠለስቱ ምእት ናቸው ይላል። እኛ ግን የተገኘውን ነገር ሁሉ ያለ ጥናት ሠለስቱ ምእት ላይ ለምን እንደምናሳብብ ይገርመኛል። አንደኛ ሠለስቱ ምእት በ3ተኛው ሳይሆን በ4ተኛው ክፍለ ዘመን ነበሩ (ይህ እንኳን understandable ስህተት ነው 325 ዓ.ም ሲባል ብዙ ሰው 3ተኛው ክፍለ ዘመን ይመስለዋል) ሌላው የሚያሳቅቀው ነገር ግን 318ቱ ሊቃውንት በኒቅያ ጉባኤ የመጻሕፍትን ቁጥር የወሰኑበት ምንም አይነት ሒደት አለመኖሩ ነው። የመጻሕፍትን ቁጥር የወሰኑ ጉባኤያት ላይ ሠለስቱ ምእት ተሳትፈው አያውቁም ይልቅስ ከኒቅያ ጉባኤ በኋላ የተደረጉት የለዶቅያ ፣ የሂፖ ፣ የቅርጣግናና የሮም ጉባኤያት ናቸው የመጻሕፍትን ቁጥር የወሰኑት ነገር ግን እነዚህ ጉባኤያት 81 የመጻሕፍት ቁጥር አልወሰኑም ይልቅስ 73 መጻሕፍትን የወሰነ ጉባኤ አለ።
2. የዮሐንስ ራዕይ መጽሐፍ ጠፍቶ ነበር ነበር ከዛ ዮሐንስ አፈወርቅ በጸሎት ተገልጦለት ዮሐንስ አፈረወርቅ ነው የመጨረሻውን "በዚህ ትንቢት መጽሐፍ የጨመረ ወይም የቀነሰ" የሚለውን አረፍተ ነገር የጻፈው ይለናል። ይህም በምንም አይነት የታሪክ ጥናት ላይ ያልተመሠረተ መላ ምት ብቻ ነው።
3. 81 መጽሐፍ ከየት መጣ የሚለውን ሲያስረዳ የዮሐንስ ወንጌል 2፡20 ላይ "ስለዚህ አይሁድ። ይህ ቤተ መቅደስ ከአርባ ስድስት ዓመት ጀምሮ ይሠራ ነበር፥ አንተስ በሦስት ቀን ታነሣዋለህን? አሉት።" የሚለውን ጥቅሶ 46 የሚለው ቁጥር 46ቱን የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ያሳያል ስለዚህ እዚህ ጋር ኢየሱስ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት 46 መሆናቸውን እየነገረን ነው ይላል። እዚህ ጋር ይገባኛል allegory or metaphor እየተጠቀምን አስተምህሯችንን ልናሳይ እንችላለን ነገር ግን allegory እንደ ማስረጃ አይቀርብም ሲጀመርም ያንን connection የሠራው ሰው መጀመሪያውኑ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት 46 መሆናቸውን ካመነ በኋላ ነው እንጂ ለማመን አይደለምና።
4. 81 መጻሕፍትን ለማሳየት የቃኤልን ሚስት ጥቅሶ ሚስቱ ማን እንደ ሆነች የሚነግረን መጽሐፈ ኩፋሌ ነው ስለዚህ 81 ትክክል ነው ይላል። ይህ ደግሞ በጣም የሚያሳቅቅ አካሔድ ነው commentary ራሱ አያስፈልገውም ነገር ግን የቃኤልን ሚስት ማን እንደሆነች ለማወቅ ቢያስፈልግ እንኳን የቃኤል ሚስት ማን እንደሆነች የሚነግረን መጽሐፍ ሁሉ መጽሐፍ ቅዱስ ሊሆን ነው ማለት ነው? እንደዛ ከሆነ የአይሁድ ሥራዎች መካከል ሴዴር ሃዶሮት የተባለው መጽሐፍ የቃኤል ሚስት ካልማና እንደምትባል ይነግረናል ለምን መጽሐፍ ቅዱስ አይሆንም ታድያ? እንዲሁም በዚህ ሎጂክ ትክክል ቢሆን ራሱ መጽሐፈ ኩፋሌን ትክክል ያደርገዋል እንጂ 81 መጻሕፍትን አያሳይም።
5. ሌሎችም እንዲሁ አንድ አንድ መጻሕፍትን የሚያሳዩ ከመጽሐፍ ቅዱ ተጠቅሰዋል ለጊዜው እነርሱን ልተዋቸውና የመጨረሻው ሃሳብ ላይ ላተኩር "81ዱን መጽሐፍ ባልቀበል በነፍስ ያስጠይቃል ወይ?" የሚለውን ጥያቄ ሲመልስ ያስጠይቃል እንጂ በሐዋርያት መሠረትነት ላይ ታንጻችኋል ይላል ስለዚህ የሐዋርያትን አስተምህሮ ያልተቀበለ ጌታ አልተቀበለም ማለት ነው በማለት ይመልሳል። Interviewወሯ የቁጥሩን ጉዳይ ነው ብላ clear ለማድረግ ብትሞክርም መልሶ አዎ ቁጥሩም የሐዋርያት አስተምህሮ ነው በማለት ይመልሳል። ይህኛው ደግሞ ከሁሉም አደገኛ ሃሳብ ነው የመጀመሪያ "81" የሚለውን የመጻሕፍት ቁጥር ከሐዋርያት አስተምህሮ (Deposit of Faith) ውስጥ አስገብቶታል ይህ ደግሞ መሠረት አልባ ነው deposit of faith ውስጥ ለመግባት መጀመሪያ በሁል ጊዜ ፣ በሁሉም ቦታ ፣ በሁሉም አባቶች የሚታመን መሆኑን ማሳየት ግድ ይላል ነገር ግን እንደማያሟላ ግልጽ ነው ለምሳሌ 81 የመጻሕፍት ቁጥር ከሐዋርያት ዘመን ጀምሮ ተቀባይነት እንደነበረው ማሳየት ይቻላል? ይቻላል ከተባለ burden of proof አለበት ነገር ግን ሙሉ ትምህርቱ ላይ ማሳየት አልቻለም ፣ ሁለተኛ በሁሉ ቦታ የሚታመን መሆኑን ማሳየት ያስፈልጋል ይህ ደግሞ ወዲያው ይፈርሳል ከኢትዮጵያና ከኤርትራ ውጪ አይታመንምና ፣ ሦስተኛ ደግሞ በሁሉም አባቶች የሚታመን መሆኑን ማሳየት ያስፈልጋል ነገር ግን ይህንንም እንደማያሟላ ለማሳየት ብዙ መልፋት አያስፈልግም። ደግሞ የዚህኛው አቋም ትልቁ ችግር የመጻሕፍት ቁጥር 81 መሆናቸውን ማመን የመዳን ጉዳይ አድርጎታል ስለዚህ ከኢትዮያና ከኤርትራ ውጪ ያሉ አማኞች በነፍሳቸው ይጠየቁበታል ማለት ነው።
የዚህ ትችት ዓላማ ለምናምናቸው አስተምህሮዎች የተሻሉና በታሪክ ጥናት ላይ የተመሠረቱ ሙግቶችን እንድናመጣ ነው።
1. መጽሐፍ ቅዱስ 81 አድርገው የወሰኑልን በ3ተኛው ክፍለ ዘመን የነበሩ ሠለስቱ ምእት ናቸው ይላል። እኛ ግን የተገኘውን ነገር ሁሉ ያለ ጥናት ሠለስቱ ምእት ላይ ለምን እንደምናሳብብ ይገርመኛል። አንደኛ ሠለስቱ ምእት በ3ተኛው ሳይሆን በ4ተኛው ክፍለ ዘመን ነበሩ (ይህ እንኳን understandable ስህተት ነው 325 ዓ.ም ሲባል ብዙ ሰው 3ተኛው ክፍለ ዘመን ይመስለዋል) ሌላው የሚያሳቅቀው ነገር ግን 318ቱ ሊቃውንት በኒቅያ ጉባኤ የመጻሕፍትን ቁጥር የወሰኑበት ምንም አይነት ሒደት አለመኖሩ ነው። የመጻሕፍትን ቁጥር የወሰኑ ጉባኤያት ላይ ሠለስቱ ምእት ተሳትፈው አያውቁም ይልቅስ ከኒቅያ ጉባኤ በኋላ የተደረጉት የለዶቅያ ፣ የሂፖ ፣ የቅርጣግናና የሮም ጉባኤያት ናቸው የመጻሕፍትን ቁጥር የወሰኑት ነገር ግን እነዚህ ጉባኤያት 81 የመጻሕፍት ቁጥር አልወሰኑም ይልቅስ 73 መጻሕፍትን የወሰነ ጉባኤ አለ።
2. የዮሐንስ ራዕይ መጽሐፍ ጠፍቶ ነበር ነበር ከዛ ዮሐንስ አፈወርቅ በጸሎት ተገልጦለት ዮሐንስ አፈረወርቅ ነው የመጨረሻውን "በዚህ ትንቢት መጽሐፍ የጨመረ ወይም የቀነሰ" የሚለውን አረፍተ ነገር የጻፈው ይለናል። ይህም በምንም አይነት የታሪክ ጥናት ላይ ያልተመሠረተ መላ ምት ብቻ ነው።
3. 81 መጽሐፍ ከየት መጣ የሚለውን ሲያስረዳ የዮሐንስ ወንጌል 2፡20 ላይ "ስለዚህ አይሁድ። ይህ ቤተ መቅደስ ከአርባ ስድስት ዓመት ጀምሮ ይሠራ ነበር፥ አንተስ በሦስት ቀን ታነሣዋለህን? አሉት።" የሚለውን ጥቅሶ 46 የሚለው ቁጥር 46ቱን የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ያሳያል ስለዚህ እዚህ ጋር ኢየሱስ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት 46 መሆናቸውን እየነገረን ነው ይላል። እዚህ ጋር ይገባኛል allegory or metaphor እየተጠቀምን አስተምህሯችንን ልናሳይ እንችላለን ነገር ግን allegory እንደ ማስረጃ አይቀርብም ሲጀመርም ያንን connection የሠራው ሰው መጀመሪያውኑ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት 46 መሆናቸውን ካመነ በኋላ ነው እንጂ ለማመን አይደለምና።
4. 81 መጻሕፍትን ለማሳየት የቃኤልን ሚስት ጥቅሶ ሚስቱ ማን እንደ ሆነች የሚነግረን መጽሐፈ ኩፋሌ ነው ስለዚህ 81 ትክክል ነው ይላል። ይህ ደግሞ በጣም የሚያሳቅቅ አካሔድ ነው commentary ራሱ አያስፈልገውም ነገር ግን የቃኤልን ሚስት ማን እንደሆነች ለማወቅ ቢያስፈልግ እንኳን የቃኤል ሚስት ማን እንደሆነች የሚነግረን መጽሐፍ ሁሉ መጽሐፍ ቅዱስ ሊሆን ነው ማለት ነው? እንደዛ ከሆነ የአይሁድ ሥራዎች መካከል ሴዴር ሃዶሮት የተባለው መጽሐፍ የቃኤል ሚስት ካልማና እንደምትባል ይነግረናል ለምን መጽሐፍ ቅዱስ አይሆንም ታድያ? እንዲሁም በዚህ ሎጂክ ትክክል ቢሆን ራሱ መጽሐፈ ኩፋሌን ትክክል ያደርገዋል እንጂ 81 መጻሕፍትን አያሳይም።
5. ሌሎችም እንዲሁ አንድ አንድ መጻሕፍትን የሚያሳዩ ከመጽሐፍ ቅዱ ተጠቅሰዋል ለጊዜው እነርሱን ልተዋቸውና የመጨረሻው ሃሳብ ላይ ላተኩር "81ዱን መጽሐፍ ባልቀበል በነፍስ ያስጠይቃል ወይ?" የሚለውን ጥያቄ ሲመልስ ያስጠይቃል እንጂ በሐዋርያት መሠረትነት ላይ ታንጻችኋል ይላል ስለዚህ የሐዋርያትን አስተምህሮ ያልተቀበለ ጌታ አልተቀበለም ማለት ነው በማለት ይመልሳል። Interviewወሯ የቁጥሩን ጉዳይ ነው ብላ clear ለማድረግ ብትሞክርም መልሶ አዎ ቁጥሩም የሐዋርያት አስተምህሮ ነው በማለት ይመልሳል። ይህኛው ደግሞ ከሁሉም አደገኛ ሃሳብ ነው የመጀመሪያ "81" የሚለውን የመጻሕፍት ቁጥር ከሐዋርያት አስተምህሮ (Deposit of Faith) ውስጥ አስገብቶታል ይህ ደግሞ መሠረት አልባ ነው deposit of faith ውስጥ ለመግባት መጀመሪያ በሁል ጊዜ ፣ በሁሉም ቦታ ፣ በሁሉም አባቶች የሚታመን መሆኑን ማሳየት ግድ ይላል ነገር ግን እንደማያሟላ ግልጽ ነው ለምሳሌ 81 የመጻሕፍት ቁጥር ከሐዋርያት ዘመን ጀምሮ ተቀባይነት እንደነበረው ማሳየት ይቻላል? ይቻላል ከተባለ burden of proof አለበት ነገር ግን ሙሉ ትምህርቱ ላይ ማሳየት አልቻለም ፣ ሁለተኛ በሁሉ ቦታ የሚታመን መሆኑን ማሳየት ያስፈልጋል ይህ ደግሞ ወዲያው ይፈርሳል ከኢትዮጵያና ከኤርትራ ውጪ አይታመንምና ፣ ሦስተኛ ደግሞ በሁሉም አባቶች የሚታመን መሆኑን ማሳየት ያስፈልጋል ነገር ግን ይህንንም እንደማያሟላ ለማሳየት ብዙ መልፋት አያስፈልግም። ደግሞ የዚህኛው አቋም ትልቁ ችግር የመጻሕፍት ቁጥር 81 መሆናቸውን ማመን የመዳን ጉዳይ አድርጎታል ስለዚህ ከኢትዮያና ከኤርትራ ውጪ ያሉ አማኞች በነፍሳቸው ይጠየቁበታል ማለት ነው።
የዚህ ትችት ዓላማ ለምናምናቸው አስተምህሮዎች የተሻሉና በታሪክ ጥናት ላይ የተመሠረቱ ሙግቶችን እንድናመጣ ነው።
Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች
አስበኸዋል አንድ ሰው የደሃን ገንዘብ እየበዘበዘ አልያም በዝሙት ኃጢአት ውስጥ እየኖረ ግን ደግሞ ግጥሙ ጤናማ የሆነ ዘፈንን ኃጢአት ነው ሲል..??
እውነቱን ለመናገር እኔ ዘፈን አዳማጭ አይደለሁም.. የሚያዳምጡ ክርስቲያኖችም እንደው ቀስ በቀስም ቢሆን እየተዉት ቢሄዱ ብዬ የማስብ ሰው ነኝ.. ታድያ ግን ዘፈን ባለመስማቱ እንደሚመጻደቅ ሰው ሰነፍ ያለም አይመስለኝም በስመአብ.. ከዛ ደግሞ ጭራሽ የሚሰሙትንም ሊኮንን ይወዳል እንጂ..
ብዙ የተወደዱ ፕሮቴስታንቶች አሉ ግን ደግሞ በዛው ልክ የፈሪሳውያኑ አበዛዛቸው😁😁 በውጩ ዓለም እኮ አይከለከልም በፕሮቴስታንቱም.. ጭራሽ ማርቲን ሉተር የእግዚአብሔር ሥጦታ ነው ብሎ ነው የሚያምነው ዘፈንን..
ለ10 ደቂቃ የሚቆይ
እውነቱን ለመናገር እኔ ዘፈን አዳማጭ አይደለሁም.. የሚያዳምጡ ክርስቲያኖችም እንደው ቀስ በቀስም ቢሆን እየተዉት ቢሄዱ ብዬ የማስብ ሰው ነኝ.. ታድያ ግን ዘፈን ባለመስማቱ እንደሚመጻደቅ ሰው ሰነፍ ያለም አይመስለኝም በስመአብ.. ከዛ ደግሞ ጭራሽ የሚሰሙትንም ሊኮንን ይወዳል እንጂ..
ብዙ የተወደዱ ፕሮቴስታንቶች አሉ ግን ደግሞ በዛው ልክ የፈሪሳውያኑ አበዛዛቸው😁😁 በውጩ ዓለም እኮ አይከለከልም በፕሮቴስታንቱም.. ጭራሽ ማርቲን ሉተር የእግዚአብሔር ሥጦታ ነው ብሎ ነው የሚያምነው ዘፈንን..
ለ10 ደቂቃ የሚቆይ
Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች Chat
አይ የፈሪሳውያን ጠባይ ያለባቸው ሰዎች አሉ.. ቀላሉን ነገር እንደ ከባድ ኃጢአት አድርገው ያጮሁታል.. እነርሱ ግብ ምሰሶውን ተሸክመውታል.. እና ይህ ፈሪሳዊነቱ ያስጠላል..
በውጩም ዓለማት በኦርቶዶክስም ጭምር ዘፈን ከግጥሙ አንጻር የሚታይ ነገር ነው.. ግን ደግሞ ወደ መዝሙር ነው ማዘንበል ያለብን ነው.. በዓለም ፍቅር ተነድፈን እንዳንኖር
በውጩም ዓለማት በኦርቶዶክስም ጭምር ዘፈን ከግጥሙ አንጻር የሚታይ ነገር ነው.. ግን ደግሞ ወደ መዝሙር ነው ማዘንበል ያለብን ነው.. በዓለም ፍቅር ተነድፈን እንዳንኖር
Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች Chat
ዘፈን ኖርማል ነው ብለን ሳይሆን አንተ ስታነበው እንደዛ አንብበኸው ነው ሙሌ.. እስቲ መነጽሯን አውልቀህ ሞክራት ሎል
አይ ግን ያው ጤናማ ግጥም ያለው ዘፈን በራሱ ኃጢአት አይደለም..ግን ደግሞ የዓለምን ፍቅር በውስጥ ሊያሳድር ስለሚችል መዝሙር ነው መስማት ያለብን.. ዓለምን መውደድ ከእግዚአብሔር ጋር ጥል ነውና
አይ ግን ያው ጤናማ ግጥም ያለው ዘፈን በራሱ ኃጢአት አይደለም..ግን ደግሞ የዓለምን ፍቅር በውስጥ ሊያሳድር ስለሚችል መዝሙር ነው መስማት ያለብን.. ዓለምን መውደድ ከእግዚአብሔር ጋር ጥል ነውና
Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች
አንድ ፕሮቴስታንት ወንድም እንዲህ ሲል ይተቻል..
[ ክርስቲያኖች ቤተ ክርስቲያን ቅጥር ውስጥ ዘፈን አትሰሙም.. ከዚያ ስትወጡ ግን የምትሰሙ ከሆነ እንግዲያውስ ለእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ የሆናችሁት በትርፍ ሰዓታችሁ ነው(ቤተ ክርስቲያን ስትሄዱ ብቻ) ]
ይሄ ወንድም የምር በተገኘበት መሸለም አለበት.. እንዲህ ያለ ብሩህ እና ታላቅ የማሰላሰል ብቃት ያለው አእምሮን ይዞ በቲክቶክ ብቻ መገደብ የለበትም.. ዓለም ላይ ላሉ ብዙ ችግሮች መፍትሄ ማምጣት የሚችል ዓይነት ሰው እንደሆነ እርግጠኛ ነኝ..
እናንተ ደግሞ “ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሙቪ አናይም ስንወጣ ግን እናያለን..” እንዳትሉ ቆይ😁😁
[ ክርስቲያኖች ቤተ ክርስቲያን ቅጥር ውስጥ ዘፈን አትሰሙም.. ከዚያ ስትወጡ ግን የምትሰሙ ከሆነ እንግዲያውስ ለእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ የሆናችሁት በትርፍ ሰዓታችሁ ነው(ቤተ ክርስቲያን ስትሄዱ ብቻ) ]
ይሄ ወንድም የምር በተገኘበት መሸለም አለበት.. እንዲህ ያለ ብሩህ እና ታላቅ የማሰላሰል ብቃት ያለው አእምሮን ይዞ በቲክቶክ ብቻ መገደብ የለበትም.. ዓለም ላይ ላሉ ብዙ ችግሮች መፍትሄ ማምጣት የሚችል ዓይነት ሰው እንደሆነ እርግጠኛ ነኝ..
Forwarded from ኪዳን ዘኢየሱስ
ዛሬ የምር በጣም አሳዛኝ ነገር ነው የሰማሁት ለነገሩ ዛሬ ብቻ አይደለም ብዙ ጊዜ በውስጥ የሚመጡልኝ መልእክቶች በክርስትና በጣም እንደሚቀረን ነው እየተረዳሁ ያለሁት ፤ ክርስትናን ሳይሆን እየኖርን ያለነው ይሁዲነትን ነው ያስብላል አንዳንዴ።
ለምሳሌ ከሰማሁት ልንገራቹ አንዲት ሴት ገና teenager እያለች ትደፈራለች በኋላ ስታድግ በቤተክርስቲያን ውስጥ በተክሊል ማግባት አትችዪም ትባላለች ፤ እንዲሁም ዲያቆን ድንግል ስለሆነ ማግባት ያለበት ከአንድ ዲያቆን ጋር ቢዋደዱ እንኳን መጋባት አትችሉም ይባላሉ።
Really? አሁን ክርስቶስ ቢወርድ ኖሮ ፈሪሳዊያንን እንደ ወቀሰ አይወቅሰንም? ቆይ ተክሊል ድንግልናን እስከ ትዳር ለጠበቁ ሽልማት ነው አልተባለም እንዴ ታድያ የተደፈረች ሴት ምን አጥፍታ ሽልማቷ ይቀርባታል? ቆይ ድንግልናን የምንመለከተው ከሥጋ አንጻር ብቻ ነው እንዴ? እንደሱ ከሆነማ ብዙ ሴቶች በተፈጥሮም ሆነ በከባድ ሥራ የማይኖራቸው አለ እነርሱስ ሊከለከሉ ነው?
በአንዲት ሴት ላይ እኮ መደፈር ከባድ የሆነ አካላዊም ሆነ ስነ ልቦናዊ ጉዳት ነው የሚያደርሰው ፤ አንድ አንድ ሴቶች ጭራሽ ወንድ የተባለ ፍጡርን የሚጠሉ አሉ ፤ ራሳቸውን እንደ ረከሱ ያያሉ ፣ እንዲሁም long lasting trauma ነው የሚከተላቸው ፣ ጭራሽ የእኛ ማኅበረሰብ ደግሞ የራሳቸው ጥፋት እንደሆነ አድርገው ነው ጣታቸውን ወደ ተጠቂዎቹ ሴቶች የሚጠቁሙት።
ታድያ ቤተክርስቲያን በዚህ ጊዜ ማረፊያ መሆን ሲገፋት ጭራሽ ቤተክርስቲያንም ስታገል ምኑን ከማኅበረሰቡ ተለየች? ምኑን የክርስቶስ ልብ ኖራት? አስቡት ያለ ፈቃድሽ አንድ አረመኔ ጨካኝ ወንድ ስለ ተጫወተብሽ ረክሰሻል ተክሊል አይገባሽም ስትባል? ጭራሽ እኮ ዲያቆን ክህነቱ ንጹሕ ነው ታረክሺዋለሽ ካገባሽ ነው የተባለችው። I don't even have the words to describe my anger ብቻ ቤተክርስቲያናችን በጣም የተማሩ ንስሐ አባቶች እንደሚያስፈልጓት ነው የተረዳሁት በዚህ ታሪክ ብቻ ሳይሆን በብዙ ታሪኮች ፤ በተለይ ሴቶች እኅቶቻችን ላይ የሚደርሰው ግፍ ከባድ ነው። ጌታ ይታደገን ብቻ ምን ይባላል።
የሚጠፋ እንደዚህ አይነት ነገር ምናልባት ስለማልጽፍ
ለምሳሌ ከሰማሁት ልንገራቹ አንዲት ሴት ገና teenager እያለች ትደፈራለች በኋላ ስታድግ በቤተክርስቲያን ውስጥ በተክሊል ማግባት አትችዪም ትባላለች ፤ እንዲሁም ዲያቆን ድንግል ስለሆነ ማግባት ያለበት ከአንድ ዲያቆን ጋር ቢዋደዱ እንኳን መጋባት አትችሉም ይባላሉ።
Really? አሁን ክርስቶስ ቢወርድ ኖሮ ፈሪሳዊያንን እንደ ወቀሰ አይወቅሰንም? ቆይ ተክሊል ድንግልናን እስከ ትዳር ለጠበቁ ሽልማት ነው አልተባለም እንዴ ታድያ የተደፈረች ሴት ምን አጥፍታ ሽልማቷ ይቀርባታል? ቆይ ድንግልናን የምንመለከተው ከሥጋ አንጻር ብቻ ነው እንዴ? እንደሱ ከሆነማ ብዙ ሴቶች በተፈጥሮም ሆነ በከባድ ሥራ የማይኖራቸው አለ እነርሱስ ሊከለከሉ ነው?
በአንዲት ሴት ላይ እኮ መደፈር ከባድ የሆነ አካላዊም ሆነ ስነ ልቦናዊ ጉዳት ነው የሚያደርሰው ፤ አንድ አንድ ሴቶች ጭራሽ ወንድ የተባለ ፍጡርን የሚጠሉ አሉ ፤ ራሳቸውን እንደ ረከሱ ያያሉ ፣ እንዲሁም long lasting trauma ነው የሚከተላቸው ፣ ጭራሽ የእኛ ማኅበረሰብ ደግሞ የራሳቸው ጥፋት እንደሆነ አድርገው ነው ጣታቸውን ወደ ተጠቂዎቹ ሴቶች የሚጠቁሙት።
ታድያ ቤተክርስቲያን በዚህ ጊዜ ማረፊያ መሆን ሲገፋት ጭራሽ ቤተክርስቲያንም ስታገል ምኑን ከማኅበረሰቡ ተለየች? ምኑን የክርስቶስ ልብ ኖራት? አስቡት ያለ ፈቃድሽ አንድ አረመኔ ጨካኝ ወንድ ስለ ተጫወተብሽ ረክሰሻል ተክሊል አይገባሽም ስትባል? ጭራሽ እኮ ዲያቆን ክህነቱ ንጹሕ ነው ታረክሺዋለሽ ካገባሽ ነው የተባለችው። I don't even have the words to describe my anger ብቻ ቤተክርስቲያናችን በጣም የተማሩ ንስሐ አባቶች እንደሚያስፈልጓት ነው የተረዳሁት በዚህ ታሪክ ብቻ ሳይሆን በብዙ ታሪኮች ፤ በተለይ ሴቶች እኅቶቻችን ላይ የሚደርሰው ግፍ ከባድ ነው። ጌታ ይታደገን ብቻ ምን ይባላል።
የሚጠፋ እንደዚህ አይነት ነገር ምናልባት ስለማልጽፍ
Forwarded from ደቂቀ አትናቴዎስ አማርኛ
ትንሽ እንጨዋወት መሰለኝ 😁
ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ በእርሱ ዘመን የነበሩ ክርስቲያኖች ትንሹም ፣ ትልቁም ከባድ ነገረ መለኮታዊ ርዕሶችን ባገኙት ቦታ ሲወያዩ ተመልክቶ :- “ሥነ መለኮት ለሁሉም አይሆንም ስለዚህ በብዙ ልንጠነቀቅ እና ራሳችንን ልንጠብቅ ይገባል።” በማለት ገሰጻቸው።
Meanwhile የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምዕመናን በ 21 ኛው ክፍለ ዘመን የሚወያዩባቸው ርዕሶች :- “ቡና መጣጣት ኃጢአት ነው ወይስ አይደለም ? የቴዲ አፍሮን ዘፈን መስማት ኃጢአት ነውን ? አሳ ጾም አለው ወይስ የለውም ?”😭😭
ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ እንደው ምን ሊለን የሚችል ይመስላችኋል ?
ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ በእርሱ ዘመን የነበሩ ክርስቲያኖች ትንሹም ፣ ትልቁም ከባድ ነገረ መለኮታዊ ርዕሶችን ባገኙት ቦታ ሲወያዩ ተመልክቶ :- “ሥነ መለኮት ለሁሉም አይሆንም ስለዚህ በብዙ ልንጠነቀቅ እና ራሳችንን ልንጠብቅ ይገባል።” በማለት ገሰጻቸው።
Meanwhile የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምዕመናን በ 21 ኛው ክፍለ ዘመን የሚወያዩባቸው ርዕሶች :- “ቡና መጣጣት ኃጢአት ነው ወይስ አይደለም ? የቴዲ አፍሮን ዘፈን መስማት ኃጢአት ነውን ? አሳ ጾም አለው ወይስ የለውም ?”😭😭
Forwarded from ኪዳን ዘኢየሱስ
መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ በቂ ነውን?
አንድ ሰው ለመዳን የሚያስፈልጉትን እውቀቶች ከመጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ማግኘት ይችላልን? ማለትም ኹሉም እውቀቶች በሙሉ ከመጽሐፍ ቅዱስ ይገኛሉ ለማለት ሳይኾን ለመዳን የሚያስፈልጉ መሠረታዊ ዶግማዊ እውቀቶች ግልጽ በኾነ መንገድ (explicitly) ወይም ግልጽ ባልኾነ መንገድ (implicitly) ከመጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ማግኘት ይቻላል?
አይቻልም ብላችሁ የምትከራከሩ አንድ ወጥመድ ውስጥ ትገባላችሁ እርሱም ለመዳን የሚያስፈልጉ እውቀቶች በመጽሐፍ ቅዱስ ማግኘት እንደሚቻል መጽሐፍ ቅዱስም ኾነ የጥንት ቤተክርስቲያን አባቶች ጽፈዋል የቤተክርስቲያን አባቶችማ ከዚህም ገፍተው ስለ ዶግማዊ ነገር መጽሐፍ ቅዱስ ጠቅሰን ካላስተማርናችሁ አትቀበሉን ሲሉ ጽፈዋል እስቲ ጥቂት ምሳሌ እንመልከት:
John 20 አማ - ዮሐንስ
30: ኢየሱስም በዚህ መጽሐፍ ያልተጻፈ ሌላ ብዙ ምልክት በደቀ መዛሙርቱ ፊት አደረገ፤
31: ነገር ግን ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ታምኑ ዘንድ፥ አምናችሁም በስሙ ሕይወት ይሆንላችሁ ዘንድ ይህ ተጽፎአል። (ኹሉ ነገር አልተጻፈም ለእምነትና ለሕይወት በቂ የኾኑት ነገሮች ግን ተጽፈዋል)
2 Timothy 3 አማ - 2ኛ ጢሞቴዎስ
15: ከሕፃንነትህም ጀምረህ ክርስቶስ ኢየሱስን በማመን፥ መዳን የሚገኝበትን ጥበብ ሊሰጡህ የሚችሉትን ቅዱሳን መጻሕፍትን አውቀሃል።
16-17: የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል።
Gregory of Nyssa
Irenaeus of Lyons
Athanasius of Alexandria
እነዚህን ካየን ይብቃንና እነዚህ ማስረጃዎች የሚያረጋግጡልን ለመዳን የሚያስፈልጉ ዶግማዎች በሙሉ ከመጽሐፍ ቅዱስ ማግኘት እንደምንችል ነው። ይህ ማለት ታድያ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ በቂ ነውን? የሚለውን ጥያቄ ስንመለከት "በቂ" የሚለው ቃል ምን ማለት ነው የሚለውን መገምገም አለብን። እኛ መጽሐፍ ቅዱስ ለመዳን የሚኾኑ እውቀቶችን በሙሉ ይዟል ነገር ግን እነዚህን እውቀቶች በጽሑፍ ደረጃ ነው እንጂ የያዘው ለእነዚህ እውቀቶች contextኡን የያዘው የቤተክርስቲያን ትውፊት ነው እንላለን (The Church is the active agent of infallibility )፤ ይህን Material sufficiency of Scripture ብለን ልንጠራው እንችላለን። ዶግማዎቻችን እንዳለ የሚወጡት ከመጽሐፍ ቅዱስ ነው ለእዚህ መጽሐፍ ግን infallible በኾነ መንገድ ትርጓሜ የምትሰጠው ቤተክርስቲያን ናት። በአጭሩ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ቢያንስ implicitly እንኳን የሌለ ዶግማ የለንም።
ይህን በምሳሌ ለመረዳት መጽሐፍ ቅዱስ አንድ ሕንፃ የሚሠራበት blue print ነው ፣ ሕንጻው ደግሞ የቤተክርስቲያን ዶግማዋ ነው blue printኡ ላይ የሌለ ነገር አይሠራም ነገር ግን blue printኡ ብቻውን ሕንፃ አይኾንም context የሚሠጠው የቤተክርስቲያን ትውፊት ያስፈልጋል።
በመጨረሻም ይህ ማለት መጽሐፍ ቅዱስ ላይ የማይገኙ ትውፊቶች የለንም ማለት አይደለም ይልቅስ ዶግማ የኾኑ ትውፊቶች መጽሐፍ ቅዱስ ላይ የማይገኙ የሉንም ማለት ነው።
@KidanZeIyesus
አንድ ሰው ለመዳን የሚያስፈልጉትን እውቀቶች ከመጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ማግኘት ይችላልን? ማለትም ኹሉም እውቀቶች በሙሉ ከመጽሐፍ ቅዱስ ይገኛሉ ለማለት ሳይኾን ለመዳን የሚያስፈልጉ መሠረታዊ ዶግማዊ እውቀቶች ግልጽ በኾነ መንገድ (explicitly) ወይም ግልጽ ባልኾነ መንገድ (implicitly) ከመጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ማግኘት ይቻላል?
አይቻልም ብላችሁ የምትከራከሩ አንድ ወጥመድ ውስጥ ትገባላችሁ እርሱም ለመዳን የሚያስፈልጉ እውቀቶች በመጽሐፍ ቅዱስ ማግኘት እንደሚቻል መጽሐፍ ቅዱስም ኾነ የጥንት ቤተክርስቲያን አባቶች ጽፈዋል የቤተክርስቲያን አባቶችማ ከዚህም ገፍተው ስለ ዶግማዊ ነገር መጽሐፍ ቅዱስ ጠቅሰን ካላስተማርናችሁ አትቀበሉን ሲሉ ጽፈዋል እስቲ ጥቂት ምሳሌ እንመልከት:
John 20 አማ - ዮሐንስ
30: ኢየሱስም በዚህ መጽሐፍ ያልተጻፈ ሌላ ብዙ ምልክት በደቀ መዛሙርቱ ፊት አደረገ፤
31: ነገር ግን ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ታምኑ ዘንድ፥ አምናችሁም በስሙ ሕይወት ይሆንላችሁ ዘንድ ይህ ተጽፎአል። (ኹሉ ነገር አልተጻፈም ለእምነትና ለሕይወት በቂ የኾኑት ነገሮች ግን ተጽፈዋል)
2 Timothy 3 አማ - 2ኛ ጢሞቴዎስ
15: ከሕፃንነትህም ጀምረህ ክርስቶስ ኢየሱስን በማመን፥ መዳን የሚገኝበትን ጥበብ ሊሰጡህ የሚችሉትን ቅዱሳን መጻሕፍትን አውቀሃል።
16-17: የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል።
Gregory of Nyssa
"What then is our reply? We do not think that it is right to make their prevailing custom the law and rule of sound doctrine. For if custom is to avail for proof of soundness, we too, surely, may advance our prevailing custom; and if they reject this, we are surely not bound to follow theirs. Let the inspired Scripture, then, be our umpire, and the vote of truth will surely be given to those whose dogmas are found to agree with the Divine words." (Dogmatic Treatises, Book 12. On the Trinity, To Eustathius.)
“Let the inspired Scriptures then be our umpire, and the vote of truth will be given to those whose dogmas are found to agree with the Divine words.” (On the Holy Trinity, NPNF, p. 327)
Irenaeus of Lyons
We have learned from none others the plan of our salvation, than from those through whom the Gospel has come down to us, which they did at one time proclaim in public, and, at a later period, by the will of God, handed down to us in the Scriptures, to be the ground and pillar of our faith. (Against Heresies, 3.1.1)
Athanasius of Alexandria
These are fountains of salvation, that they who thirst may be satisfied with the living words they contain. In these alone is proclaimed the doctrine of godliness. Let no man add to these, neither let him take ought from these. For concerning these the Lord put to shame the Sadducees, and said, ‘Ye do err, not knowing the Scriptures.’ And He reproved the Jews, saying, ‘Search the Scriptures, for these are they that testify of Me.’ (Festal Letter 39, 6–7)
“Vainly then do they run about with the pretext that they have demanded Councils for the faith’s sake; for divine Scripture is sufficient above all things.” ( Letter, De Synodis, Par. 6; 296)
እነዚህን ካየን ይብቃንና እነዚህ ማስረጃዎች የሚያረጋግጡልን ለመዳን የሚያስፈልጉ ዶግማዎች በሙሉ ከመጽሐፍ ቅዱስ ማግኘት እንደምንችል ነው። ይህ ማለት ታድያ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ በቂ ነውን? የሚለውን ጥያቄ ስንመለከት "በቂ" የሚለው ቃል ምን ማለት ነው የሚለውን መገምገም አለብን። እኛ መጽሐፍ ቅዱስ ለመዳን የሚኾኑ እውቀቶችን በሙሉ ይዟል ነገር ግን እነዚህን እውቀቶች በጽሑፍ ደረጃ ነው እንጂ የያዘው ለእነዚህ እውቀቶች contextኡን የያዘው የቤተክርስቲያን ትውፊት ነው እንላለን (The Church is the active agent of infallibility )፤ ይህን Material sufficiency of Scripture ብለን ልንጠራው እንችላለን። ዶግማዎቻችን እንዳለ የሚወጡት ከመጽሐፍ ቅዱስ ነው ለእዚህ መጽሐፍ ግን infallible በኾነ መንገድ ትርጓሜ የምትሰጠው ቤተክርስቲያን ናት። በአጭሩ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ቢያንስ implicitly እንኳን የሌለ ዶግማ የለንም።
ይህን በምሳሌ ለመረዳት መጽሐፍ ቅዱስ አንድ ሕንፃ የሚሠራበት blue print ነው ፣ ሕንጻው ደግሞ የቤተክርስቲያን ዶግማዋ ነው blue printኡ ላይ የሌለ ነገር አይሠራም ነገር ግን blue printኡ ብቻውን ሕንፃ አይኾንም context የሚሠጠው የቤተክርስቲያን ትውፊት ያስፈልጋል።
በመጨረሻም ይህ ማለት መጽሐፍ ቅዱስ ላይ የማይገኙ ትውፊቶች የለንም ማለት አይደለም ይልቅስ ዶግማ የኾኑ ትውፊቶች መጽሐፍ ቅዱስ ላይ የማይገኙ የሉንም ማለት ነው።
@KidanZeIyesus
Forwarded from ኪዳን ዘኢየሱስ
ኢየሱስ ይወዳችኋል
ብዙ ጊዜ ዕቅበተ እምነት ላይ ብቻ ስናተኩር የክርስትናን ዋና መሠረትን እንዘነጋለን። ዕቅበተ እምነት በጣም አስፈላጊ ነገር ቢኾንም እኛ ሰዎች ግን በአመክንዮ የታጠርን ብቻ አይደለንም አንዳንድ ጊዜ ሰው "ክርስትና ለምን እውነት እንደኾነ 10 አሳማኝ ምክንያቶችን" የሚል ሙግት ላይፈልግ ይችላል ይልቅስ የፈለግነውን ተዋስኦ ብናቀርብ የምንናገረው ነገር ወደ ልቡ ውስጥ ካልገባ ደረቅ እውነት ብቻ ይኾንበታል።
ሐዋርያት ወደ ዓለም ዳርቻ የተላኩት ወንጌልን ሊሰብኩ ነው εὐαγγέλιον - የምስራች ማለት ነው። እግዚአብሔር አንድያ ልጁን አሳልፎ እስኪሰጥ ዓለምን እንዲሁ ወዷል ፤ ወልደ እግዚአብሔር ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስም ኃጢአታችሁን በመስቀል ላይ ተሸክሞ እንዲሁ በጸጋው ድናችኋል እያሉ የምስራቹን መልካም ዜና ወደ ዓለም እየሰበኩ አሰራጩ። በእርግጥ ከእነርሱ ስነ አመክንዮን እየተጠቀሙ የተጠበቀው መሢሕ በእውነትም ኢየሱስ እንደኾነ የክርስትናን እውነታ መጽሐፍ እየጠቀሱ ሞግተዋል ይህም ዐቃቤ እምነት ያደርጋቸዋል። ነገር ግን ዐቃቤ እምነት ብቻ አልነበሩም የምስራቹ ወንጌል ሰባኪያን ናቸው እንጂ።
አሁን ላይ ከኦርቶዶክሳዊያን ወገን ጥሩ የዕቅበተ እምነት ሥራዎች እየተሠሩ ነው በዚህም እንደሰታለን። ነገር ግን ከፕሮቴስታንት አንድ መማር ያለብን ነገር አለ የወንጌል ሥርጭት። ወንጌል ዕቅበተ እምነት ብቻ አይደለም ለተጨነቁት መድኃኒት ላጡት ይኸው መድኃኒት ብሎ መስበክ ነው ፤ ደስታ ለራቃቸው ኹል ጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ እያሉ ማስደሰት ነው ፤ ፍቅር ለራቃቸውም ኢየሱስ ይወዳችኋል ስለ ኃጢአታችሁ ሞቶላችኋል እያሉ ማጽናናት ነው።
በእርግጥም ፍቅር የኾነው ኢየሱስ ይወደናል ስለዚህ በፍቅሩ እንኑር ፍቅሩንም ለኹሉም እናጋራ ፤ ደቀ መዛሙርቱ መኾናችን የሚታወቀው በምናቀርባቸው ሙግቶችና ባለን እውቀት ደረጃ ሳይኾን ከፍቅራችን የተነሣ ነውና!
ኢየሱስ ይወዳችኋል!
ብዙ ጊዜ ዕቅበተ እምነት ላይ ብቻ ስናተኩር የክርስትናን ዋና መሠረትን እንዘነጋለን። ዕቅበተ እምነት በጣም አስፈላጊ ነገር ቢኾንም እኛ ሰዎች ግን በአመክንዮ የታጠርን ብቻ አይደለንም አንዳንድ ጊዜ ሰው "ክርስትና ለምን እውነት እንደኾነ 10 አሳማኝ ምክንያቶችን" የሚል ሙግት ላይፈልግ ይችላል ይልቅስ የፈለግነውን ተዋስኦ ብናቀርብ የምንናገረው ነገር ወደ ልቡ ውስጥ ካልገባ ደረቅ እውነት ብቻ ይኾንበታል።
ሐዋርያት ወደ ዓለም ዳርቻ የተላኩት ወንጌልን ሊሰብኩ ነው εὐαγγέλιον - የምስራች ማለት ነው። እግዚአብሔር አንድያ ልጁን አሳልፎ እስኪሰጥ ዓለምን እንዲሁ ወዷል ፤ ወልደ እግዚአብሔር ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስም ኃጢአታችሁን በመስቀል ላይ ተሸክሞ እንዲሁ በጸጋው ድናችኋል እያሉ የምስራቹን መልካም ዜና ወደ ዓለም እየሰበኩ አሰራጩ። በእርግጥ ከእነርሱ ስነ አመክንዮን እየተጠቀሙ የተጠበቀው መሢሕ በእውነትም ኢየሱስ እንደኾነ የክርስትናን እውነታ መጽሐፍ እየጠቀሱ ሞግተዋል ይህም ዐቃቤ እምነት ያደርጋቸዋል። ነገር ግን ዐቃቤ እምነት ብቻ አልነበሩም የምስራቹ ወንጌል ሰባኪያን ናቸው እንጂ።
አሁን ላይ ከኦርቶዶክሳዊያን ወገን ጥሩ የዕቅበተ እምነት ሥራዎች እየተሠሩ ነው በዚህም እንደሰታለን። ነገር ግን ከፕሮቴስታንት አንድ መማር ያለብን ነገር አለ የወንጌል ሥርጭት። ወንጌል ዕቅበተ እምነት ብቻ አይደለም ለተጨነቁት መድኃኒት ላጡት ይኸው መድኃኒት ብሎ መስበክ ነው ፤ ደስታ ለራቃቸው ኹል ጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ እያሉ ማስደሰት ነው ፤ ፍቅር ለራቃቸውም ኢየሱስ ይወዳችኋል ስለ ኃጢአታችሁ ሞቶላችኋል እያሉ ማጽናናት ነው።
በእርግጥም ፍቅር የኾነው ኢየሱስ ይወደናል ስለዚህ በፍቅሩ እንኑር ፍቅሩንም ለኹሉም እናጋራ ፤ ደቀ መዛሙርቱ መኾናችን የሚታወቀው በምናቀርባቸው ሙግቶችና ባለን እውቀት ደረጃ ሳይኾን ከፍቅራችን የተነሣ ነውና!
Forwarded from ኪዳን ዘኢየሱስ
ታቦትና መሠውያ
መምህር ዘበነ ከ5 ቀን በፊት በሠራው Video ላይ እንድ ነገር መናገር ፈለኩ። ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከመቅናት የተነሣ ታቦትና ጽላት ያለን ከዓለም እኛ ብቻ ነን ሌሎቹ ኦርቶዶክሳውያን ያላቸው Altar (መሠውያ) ወይም Lord's Table (ጠረጴዛ) ብቻ ነው። እኛ ግን ከመሠውያ በተጨማሪ አሠርቱ ትእዛዛት የተጻፈበት ጽላት እንዲሁም የብሉይ ኪዳን የቃልኪዳኑ ታቦት አለን። መሠውያ የምንለውም ሥጋውና ደሙ የሚሠዋበት ሳይኾን ድርገት ሲወርድ ለምእመናን የሚቀርበበት ነው ይለናል።
ይህ ግን የኢትዮጵያን ቤተክርስቲያን ፍጹም ኦሪታዊት የሚያስመስል አደገኛ ትምህርት ነው። ቤተክርስቲያን አሠርቱ ትእዛዛት የተጻፈበት ጽላትም ኾነ የብሉዩ የቃልኪዳን ታቦት የላትም። ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ አንድ ላይ አዲስ ቤተክርስቲያን እንዴት እንደሚከብር ሲናገር አሠርቱ ትአዛዛት ስለተጻፈበት ጽላትም አያነሳም እንዲሁም ጽላቱ ስለሚቀመጥበት የቃልኪዳን ታቦት አላነሳም ይልቅስ "የመሠውያውን ታቦት በዘይት ያክብሩት ... በመሠዊያው ላይም ይቀድሱ ... ወደ መሠዊያው ቦታ ይስገዱ" እያለ ታቦት እና መሠዊያ የሚባሉትን ቃላት በተለዋዋጭ የክርስቶስ ሥጋና ደም ስለሚሠዋበት ቅድስት ጠረጴዛ ይናገራል ነገር ግን ድርገት ሲወርድ ሥጋወ ደሙ የሚቀርበበትን ንዋይ አንድም ቦታ መሠዊያ አይለውም ፣ ጠረጴዛም አይለውም። ይህ የጌታ ሥጋና ደም የሚቀርበበት ታቦተ ምሥዋዕ ደግሞ የሚገኘው በኢትዮጵያ ብቻ ሳይኾን የክርስቶስ ሥጋና ደም እውነተኛ መሥዋዕት ነው ተብሎ በሚያምኑ አብያተ ክርስቲያናት በሙሉ ነው።
ይህ የኢትዮጵያን ቤተክርስቲያን ከዓለም ልዩ ለማድረግ ተብሎ ኦሪታዊት ለማስመሰል የሚደረገው ሙከራ መቆም አለበት።
መምህር ዘበነ ከ5 ቀን በፊት በሠራው Video ላይ እንድ ነገር መናገር ፈለኩ። ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከመቅናት የተነሣ ታቦትና ጽላት ያለን ከዓለም እኛ ብቻ ነን ሌሎቹ ኦርቶዶክሳውያን ያላቸው Altar (መሠውያ) ወይም Lord's Table (ጠረጴዛ) ብቻ ነው። እኛ ግን ከመሠውያ በተጨማሪ አሠርቱ ትእዛዛት የተጻፈበት ጽላት እንዲሁም የብሉይ ኪዳን የቃልኪዳኑ ታቦት አለን። መሠውያ የምንለውም ሥጋውና ደሙ የሚሠዋበት ሳይኾን ድርገት ሲወርድ ለምእመናን የሚቀርበበት ነው ይለናል።
ይህ ግን የኢትዮጵያን ቤተክርስቲያን ፍጹም ኦሪታዊት የሚያስመስል አደገኛ ትምህርት ነው። ቤተክርስቲያን አሠርቱ ትእዛዛት የተጻፈበት ጽላትም ኾነ የብሉዩ የቃልኪዳን ታቦት የላትም። ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ አንድ ላይ አዲስ ቤተክርስቲያን እንዴት እንደሚከብር ሲናገር አሠርቱ ትአዛዛት ስለተጻፈበት ጽላትም አያነሳም እንዲሁም ጽላቱ ስለሚቀመጥበት የቃልኪዳን ታቦት አላነሳም ይልቅስ "የመሠውያውን ታቦት በዘይት ያክብሩት ... በመሠዊያው ላይም ይቀድሱ ... ወደ መሠዊያው ቦታ ይስገዱ" እያለ ታቦት እና መሠዊያ የሚባሉትን ቃላት በተለዋዋጭ የክርስቶስ ሥጋና ደም ስለሚሠዋበት ቅድስት ጠረጴዛ ይናገራል ነገር ግን ድርገት ሲወርድ ሥጋወ ደሙ የሚቀርበበትን ንዋይ አንድም ቦታ መሠዊያ አይለውም ፣ ጠረጴዛም አይለውም። ይህ የጌታ ሥጋና ደም የሚቀርበበት ታቦተ ምሥዋዕ ደግሞ የሚገኘው በኢትዮጵያ ብቻ ሳይኾን የክርስቶስ ሥጋና ደም እውነተኛ መሥዋዕት ነው ተብሎ በሚያምኑ አብያተ ክርስቲያናት በሙሉ ነው።
ይህ የኢትዮጵያን ቤተክርስቲያን ከዓለም ልዩ ለማድረግ ተብሎ ኦሪታዊት ለማስመሰል የሚደረገው ሙከራ መቆም አለበት።
Forwarded from ኪዳን ዘኢየሱስ
ስለእኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው
ኢየሱስ ክርስቶስ ስለእኛ ይማልዳል ስንል የክርስቶስ ምልጃ አንድ ጊዜ ቀርቦ ለኹልጊዜ ይሠራል ማለታችን ነው። ቅዳሴ አትናቴዎስ ቁጥር 144 ላይ " ወልድ ሆይ እንደ ታመመ ሰው አሰምተህ ተናገር ኤልማስ ላማ ሰበቅታኒ በል። በአፋቸውም ውስጥ እያለ አባ አባቴ ሆይ ሥጋዬን የበሉትን ደሜን የጠጡትን ማራቸውም ይቅር በላቸው በል" እያለ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሳለ በታላቅ መቃተት ያቀረበው ምልጃ ዛሬም በሥጋውና ደሙ ገና በአፋችን ሳለ እንደሚሠራልን ያስገነዝበናል። የክርስቶስ ምልጃ ፍጹም ነው እንደ ብሉይ ኪዳን ሊቃነ ካህናት በየዓመቱ መደጋገም አይጠበቅበትም አንድ ጊዜ ባቀረበው ምልጃ ዘለዓለም ሊያድነን ይችላል "ስለ እነርሱም ሊማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራል" እንዲል ቅዱስ ጳውሎስ።
እንዲህ ያለ ከፍ ያለ የታመነ ሊቀ ካህናት በሰማይ አለን ለኃጢአታችን ሥርየት አንድ ጊዜ ባፈሰሰው ደም ዛሬም ይምረናል "ሊቀ ካህናት ዘይቀውም ሎሙ ለቅዱሳን በደብተራ ስምእ እንተ እግዚአብሔር ተከላ ውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ-እግዚአብሔር በተከላት ምሥክር ድንኳን ውስጥ ለቅዱሳን የሚቆምላቸው ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው" እንዲል አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ። አንድ ጊዜ ወደ ቅድስተ ቅዱሳን በደሙ ገብቷል እኛም የክርስቶስን ደም አንድ ጊዜ በማቅረብ ተቀድሰናል እስከ ሕይወት ፍጻሜያችንም እንቀደሳለን ምልጃው ድግግሞሽ የማይስፈልገው አንድ ጊዜ ለዘለዓለም የቀረበ ፍጹም ነውና!
በአብ ዘንድ የታመነ ጠበቃ አለን ለኃጢአታችን ብቻ ሳይኾን ለዓለም ኹሉ ኃጢአት ሥርየት አንድ ጊዜ የቀረበ አስታራቂ በአብ ቀኝ አለን ልያውም በድካማችን የሚያግዘን ፈተናችንን ኹሉ የተፈተነ ሊራራልን የሚችል ሊቀ ካህናት በሥራው ኹሉ የታመነ ነው ወደ እርሱ እንቅረብ ከኃጢአታችን ኹሉ በቅዱስ ደሙ ያነጻናልና!
ኢየሱስ ክርስቶስ ስለእኛ ይማልዳል ስንል የክርስቶስ ምልጃ አንድ ጊዜ ቀርቦ ለኹልጊዜ ይሠራል ማለታችን ነው። ቅዳሴ አትናቴዎስ ቁጥር 144 ላይ " ወልድ ሆይ እንደ ታመመ ሰው አሰምተህ ተናገር ኤልማስ ላማ ሰበቅታኒ በል። በአፋቸውም ውስጥ እያለ አባ አባቴ ሆይ ሥጋዬን የበሉትን ደሜን የጠጡትን ማራቸውም ይቅር በላቸው በል" እያለ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሳለ በታላቅ መቃተት ያቀረበው ምልጃ ዛሬም በሥጋውና ደሙ ገና በአፋችን ሳለ እንደሚሠራልን ያስገነዝበናል። የክርስቶስ ምልጃ ፍጹም ነው እንደ ብሉይ ኪዳን ሊቃነ ካህናት በየዓመቱ መደጋገም አይጠበቅበትም አንድ ጊዜ ባቀረበው ምልጃ ዘለዓለም ሊያድነን ይችላል "ስለ እነርሱም ሊማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራል" እንዲል ቅዱስ ጳውሎስ።
እንዲህ ያለ ከፍ ያለ የታመነ ሊቀ ካህናት በሰማይ አለን ለኃጢአታችን ሥርየት አንድ ጊዜ ባፈሰሰው ደም ዛሬም ይምረናል "ሊቀ ካህናት ዘይቀውም ሎሙ ለቅዱሳን በደብተራ ስምእ እንተ እግዚአብሔር ተከላ ውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ-እግዚአብሔር በተከላት ምሥክር ድንኳን ውስጥ ለቅዱሳን የሚቆምላቸው ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው" እንዲል አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ። አንድ ጊዜ ወደ ቅድስተ ቅዱሳን በደሙ ገብቷል እኛም የክርስቶስን ደም አንድ ጊዜ በማቅረብ ተቀድሰናል እስከ ሕይወት ፍጻሜያችንም እንቀደሳለን ምልጃው ድግግሞሽ የማይስፈልገው አንድ ጊዜ ለዘለዓለም የቀረበ ፍጹም ነውና!
በአብ ዘንድ የታመነ ጠበቃ አለን ለኃጢአታችን ብቻ ሳይኾን ለዓለም ኹሉ ኃጢአት ሥርየት አንድ ጊዜ የቀረበ አስታራቂ በአብ ቀኝ አለን ልያውም በድካማችን የሚያግዘን ፈተናችንን ኹሉ የተፈተነ ሊራራልን የሚችል ሊቀ ካህናት በሥራው ኹሉ የታመነ ነው ወደ እርሱ እንቅረብ ከኃጢአታችን ኹሉ በቅዱስ ደሙ ያነጻናልና!
Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች
አንድ ወንድም አንዲት እህት ላይ በዩትዩብ ሄደባት አሉ😁😁 ጀለስ እኮ ያኔ ከእኔ ጋር በተያያዘ ሚዲያው ላይ ውዝግብ በተነሳበት ወቅትም ምንም በማያውቀው ነገር ትንሽ ተናግሮኝ ነበር.. እና በዛው የተወሰኑ ሰዎችን አምጥቶ ቪዲዮ ሲሰራ ነበር እና ተሳስቼም ከሆነ ጌታ ይቅር ይበለኝ ግን በቃ እሱ ኮንተንት ነው የሚያደርግህ😁😁 ያው ግን ሰው ነኝና ተሳስቼ ተረድቼውም ሊሆን ይችላል
ስለ ቅድስና ከተወራ ግን እኛ ሁላችን አምላክ ያለን ሕዝቦች ነን.. ያውም ኢየሱስን የመሰለ ጌታ ነው ንጉሳችን.. ስለዚህም አምላክ እንደሌለው ሰው እንዲሁ ልንኖር አይገባም.. ይሄ የማንንም ልብ ስለማላውቅ ማንንም ስህተት ወይም ትክክል ለማለት አልደፍርም.. አንድ የማውቀው ነገር ግን አምላክ እንደሌላቸው ሕዝቦች አንኖርም
ስለ ቅድስና ከተወራ ግን እኛ ሁላችን አምላክ ያለን ሕዝቦች ነን.. ያውም ኢየሱስን የመሰለ ጌታ ነው ንጉሳችን.. ስለዚህም አምላክ እንደሌለው ሰው እንዲሁ ልንኖር አይገባም.. ይሄ የማንንም ልብ ስለማላውቅ ማንንም ስህተት ወይም ትክክል ለማለት አልደፍርም.. አንድ የማውቀው ነገር ግን አምላክ እንደሌላቸው ሕዝቦች አንኖርም
Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች
ኧረ አንዱ ወዳጄ ምን ቢለኝ.. ለአንድ መምህር ስለ እኔ አጋጣሚ ሆኖ አንስቶባቸው ምን ቢሉት..?? “ያ በሡሪ ቁረቡ የሚለው ልጅ”😭😭
ኧረ መምህርዬ እኔ እንደዛ አላልኩም ይሄ ከኔ ይራቅ😭😭 እኔ ያልኩት ውጭ ላይ ባለ ሕይወቷ ቀለል ያለ ሱሪ ብትለብስም ከቁርባን ግን አትቅሪ ነው.. ለምሳሌ ስፖርት ስትሰራም በቀሚስ አይሆን መቼስ አይደል.. ብቻ ግን ያው ውጭ ባለው ሕይወቷ ነው.. የዛን ቀንማ ፏ ብላ በቀሚስ ነው እንጂ.. ከቻለች ነጭ ቀሚስ ከሌላትም ያው ያለውን😁😁
ኧረ መምህርዬ እኔ እንደዛ አላልኩም ይሄ ከኔ ይራቅ😭😭 እኔ ያልኩት ውጭ ላይ ባለ ሕይወቷ ቀለል ያለ ሱሪ ብትለብስም ከቁርባን ግን አትቅሪ ነው.. ለምሳሌ ስፖርት ስትሰራም በቀሚስ አይሆን መቼስ አይደል.. ብቻ ግን ያው ውጭ ባለው ሕይወቷ ነው.. የዛን ቀንማ ፏ ብላ በቀሚስ ነው እንጂ.. ከቻለች ነጭ ቀሚስ ከሌላትም ያው ያለውን😁😁
❤1
Forwarded from ሐዋርያዊ መልሶች