Afar Communication Bureau
791 subscribers
3.97K photos
232 videos
39 files
908 links
Rakaakayak Doolat Angaarawih Biiro
Download Telegram
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የትናንትና በአንድ ጀምበር ከ800 ሚሊዮን በላይ ችግኞች፤ በ26 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ማሳካት ታሪካዊ ፅናት እና የጋራ ድል ነው! ምስጋና ለሁሉም።- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

#አረንጓዴዐሻራ #GreenLegacy
መንግሥት ሌብነትን እና ሕገወጥነትን ለመከላከል ጠንካራ እርምጃ እየወሰደ ነው ፡፡

ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም

የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

በኢትዮጵያ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሱ እና የሀገር ሀብት በሚመዘብሩ አካላት ላይ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ መሆኑን አስታወቀ።

የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወይዘሮ እናትዓለም መለሰ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ፈጣን ልማትና ዕድገት እንድታረጋግጥ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፣ በዚህም ሰፋፊና አስደናቂ ሀገራዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡ በዚህ ሂደት ግን ይህ ውጤት ጉዞው አልጋ በአልጋ እንዳልነበር አመላክተዋል ። ከተለያዩ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች ባሻገር፣ ሕገ-ወጥነት እና የሙስና ተግባራት የልማቱ ዋነኛ ፈተና ሆነው መቆየታቸውንም ክብርት ሚኒስትሯ አብራርተዋል።

እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ፣ የሕገ-ወጥነት ችግር በአንድ ወገን ብቻ የሚፈጸም ሳይሆን በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸው ከውስጥም ከውጪም ያሉ ኃይሎች በተደራጀ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበር፡፡ በንግዱ ማኅበረሰብ፣ በልማት ድርጅቶች፣ በመንግሥት መዋቅር፣ በግለሰቦች እና በተገልጋዮች ጭምር በተደራጀ መንገድ በስፋት የሚታይ ነው።

እነዚህ አካላት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከቁጥጥር ውጭ ለማድረግ በፋይናንስ እና በንግድ ሥርዐቱ ውስጥ ሰርገው በመግባት የኢኮኖሚ አሻጥር ሲፈጽሙ ቆይተዋል" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ድርጊቱ ሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ እንድታጣ፣ የዋጋ ንረትና ኮንትሮባንድ እንዲባባስ እንዲሁም በፍጆታ እቃዎች ላይ ሰው ሠራሽ እጥረት እንዲፈጠር ማድረጉን አስታውቀዋል። ይህንን የተደራጀ አሻጥር ለመግታት መንግሥት እና የሚመለከታቸው የሕግ አካላት ባከናወኑት ሰፊ ኦፕሬሽን አሻጥሩን ማክሸፍ መቻሉ ተገልጿል።

በሌላ በኩል በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት እንዲሁም የሕዝብ ተቋማት ውስጥ የተሰገሰጉ ሌቦችን በማጽዳት ረገድ መንግሥት ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ያስታወቁት ወ/ሮ እናትዓለም በሕዝብ ሀብት ላይ ምዝበራ የፈጸሙ እና ተቋማዊ አሻጥር በሠሩ አመራሮች እና ሌሎች የጥቅም ትስስሮችና ድርጅቶች ላይ የማያዳግም እርምጃ መወሰዱንም አስታውቀዋል። በተለይም በሚከተሉት ቁልፍ ዘርፎች ላይ በተፈጸሙ ወንጀሎች ሰፊ ማጣራት ተደርጎ ተጠያቂነት ሰፍኗል ሲሉ ገልጸዋል፡

በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ የልማት ዘርፎች ውስጥ የተፈጸሙ ዋና ዋና የሙስና እና አሻጥር ወንጀሎችን ለማረም በተወሰዱት ሰፊ ኦፕሬሽኖች እና ሕግ የማስከበር እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ማሻሻያውን ለማደናቀፍ በማሰብ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በማከማቸት እጥረት እንዲፈጠርና ዋጋ እንዲንር ሲያደርጉ የነበሩ 13 አቅራቢ ድርጅቶች ባለቤቶች ላይ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፤ ሕገ-ወጥ ተግባር ሲፈጽሙ በነበሩ ከ7 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶችና መጋዘኖች ላይ የማሸግ እርምጃ ተወስዷል።

በፋይናንስ ተቋማት እና የገንዘብ ዝውውር፡ በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በሐዋላ እና በጥቁር ገበያ ተሳታፊ የሆኑ 169 ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገር ዜጎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተደራጀ መንገድ ከንግድ ባንክ ደንበኞች አካውንት ላይ በማጭበርበር ገንዘብ የወሰዱ 36 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው የባንክ ሒሳባቸው እንዲታገድ ተደርጓል።
ለሕገ-ወጥ ዝውውር ሽፋን ይሰጡ የነበሩ 7 የክሪፕቶ ካረንሲ መተግበሪያዎች በሀገር ውስጥ እንዳይሠሩ ሙሉ በሙሉ ታግደዋል፤ ምርት ልከው የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ያላደረጉ 29 ላኪ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይም የህግ ተጠያቂነት ሰፍኗል።

በቤቲንግ እና ፊንቴክ ቢዝነሶች፡ የደንበኞችን መረጃ በመደበቅ መንግሥትን ግብር ያጭበረበሩ፣ ገቢያቸውን የሰወሩ እና ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር በፈጸሙ 38 የቤቲንግ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወስዶ ባለቤቶቻቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ የእነዚህ ሕገ-ወጥ ተቋማት የባንክ ሒሳብ ታግዷል፤

በማዕድን ዘርፍ ሕገ-ወጥ ዝውውር፡ የወርቅ ምርትን ከገበያ ውጭ በኮንትሮባንድ በማስወጣት ወንጀል የተሳተፉ የመንግሥት ኃላፊዎችን፣ የፀጥታ መዋቅር አመራሮችን፣ አምራቾችን እና የውጭ ዜጎችን ጨምሮ 183 ግለሰቦች በሕግ ተጠያቂ ተደርገዋል። በወንጀሉ የተሳተፉ የውጭ ሀገር ዜጎች ከሀገር እንዲወጡ ተደርገዋል፤ ሕገ-ወጥ ወርቅ፣ የወርቅ ሚዛንና ማቅለጫ፣ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች፣ እንዲሁም የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።

ከነዳጅ አቅርቦት እና ሎጂስቲክስ አንጻር፡ በሕገ-ወጥ መንገድ የሽፋን ደብዳቤዎችን በማዘጋጀት፣ ነዳጅ በመደበቅ እና አየር በአየር በመሸጥ ወንጀል የተሳተፉ 38 የመንግሥት አመራሮች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተጨማሪም በሀገር አቀፍ ደረጃ በሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድ ላይ የተሰማሩ ከ650 በላይ ግለሰቦች፣ ማደያዎች እና አቅራቢ ኩባንያዎች ላይ የህግ እርምጃ ተወስዷል።

በአፈር ማዳበሪያ ግዢ አሻጥር፡ በተቋሙ የጥቅም ትስስር በመፍጠር ጥራት የጎደለውና ጊዜው ያለፈበት የአፈር ማዳበሪያ ግዢ እንዲፈጸም በማድረግ ሆን ብለው ችግር በፈጠሩ የግብርና ሚኒስቴር አመራሮች ላይ የወንጀል ተጠያቂነት እርምጃ ተወስዷል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP)፡ ተገቢው መመሪያ በሌለበት ሁኔታ ከ36 የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ጋር ሕገ-ወጥ የኃይል ሽያጭ ውል የፈጸሙ 4 ከፍተኛ አመራሮች ላይ እርምጃ ተወስዷል። የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት የፈጸሙ ድርጅቶች እና ግለሰቦችም እንዲሁ በሕግ እንዲጠየቁ ተደርጓል።

በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የሰዎች ዝውውር የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሲስተምን በማዛባት እና ጉቦ በመቀበል ወንጀል የተሳተፉ 8 ከፍተኛ አመራሮችና ሠራተኞች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል። እንዲሁም በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የተሰማሩ 44 ደላሎች እና አዘዋዋሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር ሲውሉ፣ ሕገ-ወጥ ፈቃድ የነበራቸው ተቋማት ሙሉ በሙሉ ታሽገዋል።

በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ፡ የግብር ውሳኔዎችን በመቀነስ፣ ሐሰተኛ ደረሰኞች በማወራረድ፣ እና በሲስተም መረጃ በማጥፋት የመንግሥት ገቢን ባሳጡ አካላት ላይ ኦፕሬሽን ተካሂዷል። በራሳቸው፣ በዘመድ እና በሹፌሮቻቸው አካውንት በመጠቀም የጥቅም ትስስር የፈጠሩ 109 ተጠርጣሪዎች ተለይተው ከእነዚህ መካከል 91 ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
መንግሥት የልማት እንቅፋት የሆኑትን ሙስና እና ሌብነት እንደማንኛውም ፈተና በጽናት እየተጋፈጣቸው መሆኑን ሚኒስትሯ አረጋግጠዋል።

መንግሥት ሌብነትን ለማጥፋት ዘመናዊ አሠራሮችን በመዘርጋት እና በዲሲፕሊን የታነጸ አመራር ለመገንባት ቁርጠኛ ነው" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ሕዝቡ በስፋት የሚያነሣቸውን "ሌብነትን አስቁሙልን" ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመረዉ ጠንካራ እርምጃ ውጤታማ እንዲሆኑ ማኅበረሰቡ ሙስናን በማጋለጥ፣ ሕጋዊ መብቱን በመደለያ ባለመጠየቅ እና ከሕገወጦች ጋር ባለመተባበር ከመንግሥት ጎን በመቆም ሀገርን ከሕገወጥነትና ሙስና የመከላከል ታሪካዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የተሰጠ መግለጫ
1👍1
"ኢትዮጵያን ከወጣቶቿ ነጥሎ ማየት አይቻልም!"

ኢትዮጵያን ከወጣቶቿ ነጥሎ ማየት እንደማይቻል የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ የወጣቶች አብላጫ ዕድሜ ስብጥር ለሀገር ብልጽግና መረጋገጥና መጽናት ታላቅ ዕድል መሆኑን አሳሰቡ።

የኢትዮጵያ ወጣት መልካም ዓላማን አንግቦ የሚንቀሳቀስ፣ የለውጥ ዋነኛ ሞተርና የሉዓላዊነት ጽኑ ማገር መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

ወጣቱ ትውልድ የሀገሩን ታሪክ በአዲስ ብዕርና ብራና እየጻፈ እንደሚገኝ ጠቁመው፣ ሀገራችንን የኋሊት ጠፍንገው የያዟትን አጓጉል ልማዶች፣ አላስፈላጊ ንትርኮች፣ ጭቅጭቅ እና ግጭቶች በመራቅ አሁን ያለው ወጣት በልማት ላይ አተኩሮ ድህነትን እንደተጠየፈ ገልጸዋል።

የመደመር መንግሥትም የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትና የአመራርነት ሚና ለማጠናከር በትኩረትና በቁርጠኝነት እየሰራ እንደሚገኝ አስታውሰዋል።

በመጨረሻም ሀገራዊ ርዕይን ዕውን ለማድረግ ሁሉም በንቃት እንዲተጋና በፍቅር እንዲመላለስ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት ጥሪ አቅርበዋል።
“በክልሉ እየተካሄደ ያለው የአረንጓዴ አሻራ እንቅስቃሴ ለአካባቢው ስነ-ምህዳር ጥበቃ ብቻ ሳይሆን ለማህበረሰቡ የጎላ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያስገኘና የወጣቶችን ተሳትፎ በማሳደግ በኩል አዎንታዊ አስተዋጽኦ ያበረከተ ነው።”

አቶ ኡመር ኑር

የአፋር ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የመሬት ቢሮ ኃላፊ
"ዛሬ የምንተክላቸው ችግኞች ነገ በብዙ ጥቅም የሚሰጡ ናቸው።"

አቶ መሐመድ አሊ ቢኢዶ
የአፋር ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ
4👏1
ስለ #አረንጓዴዐሻራ መርሃግብር ማወቅ ያለብዎት 10 እውነታዎች፦ 🌱

ለለመለመች ኢትዮጵያ ተስፋን መትከላችንን እንቀጥል! 🇪🇹

#PMOEthiopia #አረንጓዴዐሻራ
👏1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
"በዚህ ሀገራዊ ምክክር የሚከስር የለም፤ ኢትዮጵያ ግን ታሸንፋለች" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Afar Communication Bureau
Photo
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉዞ በወፍ በረር

ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም

ኢትዮጵያዊያን ለበርካታ ዘመናት የሃሳብ ልዩነቶቻንን በውይይት ከመፍታት ይልቅ የኃይል አማራጮችን ስንጠቀም ከርመናል። እነዚህ አማራጮች በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የተፈጠሩ አለመግባባቶችን በማባባስና ግጭቶችን በማፋፋም ከፍተኛ ሰብአዊ እና ኢኮኖሚያዊ ኪሳራ እንዳስከተሉ የታሪክ መዛግብት እማኝ ናቸው።

የሃይል አማራጭ ያስከተለውን ዘመን ተሻጋሪ ኪሳራ የተረዳው የዚህ ዘመን ትውልድ በሀገራችን ኢትዮጵያ ዘመናትን የተሻገሩ ችግሮች መፍትሔ እንደሚያስፈልጋቸው በማመን የሀገራዊ ምክክር ሃሳብን ቀስ በቀስ በማጎልበት ወደ ተግባር ምዕራፍ አድርሶታል፡፡ ትውልዱ ከሀሳብም ወደ ተቋም አሸጋግሮታል፡፡

👉ከሃሳብ ወደ ተቋም

በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር እንዲካሄድ ፍላጎት የመጣው ከአንድ ወገን ብቻ አልነበረም። የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማህበራት፣ የሀገር ሽማግሌዎች መማክርት እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በሀገሪቱ ውስጥ የሚስተዋሉትን ያለመግባባት አዙሪቶች በምክክር የሚፈቱበት መድረክ እንዲመቻች ለበርካታ ጊዜያት ሲወተውቱ ቆይተዋል። ከዚህ ባሻገር እነዚህ አካላት በሌሎች ሀገራት ከተካሄዱ የሀገራዊ ምክክር ተሞክሮዎች ትምህርት በመውሰድ፣ ምክክር ወደ መግባባት ሊያደርስ የሚችል አዋጭ መንገድ እንደሆነ በመገንዘብ መንግስት እርምጃ እንዲወስድ አበረታተዋል፤ ጠይቀውማል፡፡

ይህ ሂደት በተለይም በታህሳስ ወር 2014 ዓ.ም በሀገሪቱ የምክክርን መሰረት በመጣል ረገድ አንድ እርምጃ ተራመደ፡፡ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአዋጅ ቁጥር 1265/2014 የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንን በማቋቋም የሀገራዊ ምክክር ሂደቱን እንዲመራና እንዲያስተባብር ኃላፊነት ሰጠው።

የኮሚሽኑ አመሰራረት በራሱ የሕዝብ ተሳትፎን ባማከለ መልኩ የተቃኘ ነበር፡፡ ከሕዝብ በቀረበው ጥቆማ መሠረት 632 ዕጩዎች ለኮሚሽነርነት ተጠቁመው፣ 42ቱ በዕጩነት ከተመረጡ በኋላ፣ በመጨረሻም 11 ኮሚሽነሮች ተመርጠው ተቋሙን እንዲመሩ ቃለ መሐላ ፈጸሙ።

👉የሂደቱን መሠረት መጣል

የኮሚሽኑ የመጀመሪያ ተግባር በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን በአንድ አዳራሽ ውስጥ መሰብሰብ አልነበረም፡፡ ይልቁንም የምክክር ሂደቱ ትርጉም ያለው እንዲሆን መደላድል መፍጠር ነበር፡፡ በመሆኑም ኮሚሽኑ በመጀመሪያ ሥራው እጅግ መሰረታዊ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያሉ የአለመግባባት መንስኤዎችን ለመለየት፣ እነማን መሳተፍ እንዳለባቸው ለመወሰን እና ኢትዮጵያውያን ለምክክር የሚሆኑ ጉዳዮችን በማዋጣት ረገድ እንዴት አስተዋፅኦ ማበርከት እንደሚችሉ የሚያስችል ሥነ-ዘዴ አዘጋጀ፡፡ በሂደቱ በወረዳ ደረጃ ከሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ጀምሮ እስከ ፖለቲካና የሃሳብ መሪዎች፣ የመንግስት ተቋማት፣ ማህበራት እና በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን በማካተት የሰፊ ባለድርሻ አካላት ስብስብን ለየ፡፡

በክልሎች/ ከተማ አስተዳደሮች የተካሄደው የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ከፖለቲካ እና ከተቋማት ወሰን የተሻገረ እንዲሆን ተደርጎ የተቃኘ ነበር፡፡ የአርሶ/አርብቶ አደር ተወካዮች፣ የንግዱ ማህበረሰብ፣ ሴቶች፣ ወጣቶች፣ እድሮች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ የመንግስት ሰራተኞች፣ መምህራን፣ በባህል እና በሙያቸው ምክንያት የተገለሉ እንዲሁም ተፈናቃዮች በክልል እና በከተማ አስተዳደር ደረጃ በተካሄዱ ሂደቶች ተሳታፊዎች ሆነዋል፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የመንግስት ተወካዮች፣ ተቋማት እና ታዋቂ ግለሰቦችም እንደ ቁልፍ ባለድርሻ አካላት ተሳታፊዎች ሆነዋል፡፡

በፌዴራል ደረጃ 38 የባለድርሻ አካላት ቡድኖች በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደቱ የነቃ ተሳትፎ አድርገዋል፡፡ በዚህ ሂደት በተለይም የሃይማኖት ተቋማትን፣ የዲሞክራሲ ተቋማትን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችን፣ የሲቪል ማህበራትን፣ የመንግስት አካላትን፣ ሀገር አቀፍ ማህበራትን፣ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችን እና የሚዲያ ተቋማትን የወከሉ ወኪሎች ተሳታፊዎች ሆነዋል፡፡

በሌላ በኩል ኮሚሽኑ በአፍሪካ፣ ሰሜን አሜሪካ፣ መካከለኛው ምስራቅ እና አውሮፓ ከሚገኙ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን አጀንዳ አሰባስቧል፡፡

👉ሀገራዊ አጀንዳ መቅረፅ

የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራው እንደተጠናቀቀ ኮሚሽኑ የሰበሰባቸውን አጀንዳዎች መቅረፅ እና ለምክክር ሂደቱ የማዘጋጀት ሥራ አከናወነ፡፡ ይህንን ተከትሎ ረቂቅ አጀንዳዎች ለሃይማኖት ተቋማት፣ ለሲቪክ ማህበራት፣ ለፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ለመንግስት አካላት፣ ለምሁራን እና ለሌሎች ባለድርሻ አካላት ግብዓት እንዲሰጡባቸው ቀርበው ሁሉም አካላት የበኩላቸው አበርክተዋል፡፡ ይህ ሂደት የተቀረፁ የምክክር አጀንዳዎችን ለማጥራት ብቻ ሳይሆን፣ ባለድርሻ አካላት ሃሳቦቻቸው በሂደቱ ውስጥ መንፀባረቃቸውን በማረጋገጥ ወደ ሀገራዊ መግባባት ሊያደርሱ የሚችሉ ርዕሰ ጉዳዮችን በመቅረፅ ረገድ አስተዋፅኦ እንዲያደርጉ ዕድል ሰጥቷል፡፡

👉ኢትዮጵያዊያንን ወደ ምክክር መድረክ ማሰባሰብ

ከየወረዳው ከሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎች፣ ከክልል እና ከተማ አስተዳደሮች ባለድርሻ አካላት፣ ከፌዴራል ባለድርሻ አካላት እና ከዲያስፖራው የተውጣጡ 4000 ኢትዮጵያዊያን ተሳታፊዎች በአንድ ላይ ለመመካከር ተሰባሰቡ፡፡ እነዚህ ተሳታፊዎች ኮሚሽኑ ቀደም ሲል አጀንዳዎችን ካሰባሰበባቸው አካላት እና ባለድርሻ አካላት የተመረጡ ወይም የተወከሉ ሲሆኑ ይህም በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለውን ውክልና ከቀደሙት የምክክር ሂደቶች ጋር በአግባቡ ያጣመረ ነበር፡፡

የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ዓላማ ኢትዮጵያውያን እጅግ መሰረታዊ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮቻቸው ላይ የሚመካከሩበት፣ የተሻለ መግባባትን የሚያጎለብቱበት፣ የጋራ መግባባት የሚደረስባቸውን አቅጣጫዎች የሚለዩበትን መድረክ መፍጠር ነበር፡፡ በጥቅሉ ሂደቱ ምክክርን የአለመግባባቶች መፍቻ የማዕዘን ድንጋይ የማድረግ ጥረት ነበር፡፡

👉ምክክርን ማዕከል ያደረጉ ሃሳቦች

የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ የተጀመረ ሲሆን ሂደቱ 4,000 ተመካካሪዎችን ከሁሉም የሀገራችን እና የዓለማችን ክፍሎች ማሰባሰብ ችሏል።

በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ምክክር የሚደረግባቸው ስምንት ሀገራዊ አጀንዳዎች የተለዩ ሲሆን እያንዳንዱ 500 አባላት ያሉት ተመካካሪ ቡድን በአንድ አጀንዳ ላይ ሲመካከር ሰንብቷል፡፡

ጉባኤው የተመራበት ሥነ-ዘዴም ተመካካሪዎች የመናገር፣ የመደማመጥ እና የመግባቢያ ነጥቦችን የመለየት ዕድል እንዲኖራቸው በሚያስችል መልኩ ነበር። ከዚህ ባሻገር የምክክር ሂደቱ 10 አባላት ባሏቸው ትንንሽ ቡድኖች ተጀምሮ፣ 50 አባላት ወዳሏቸው ንዑሳን ቡድኖች፣ በመቀጠልም 250 አባላት ወዳሏቸው ስልታዊ ቡድኖች አድጓል።

በምክክር ሂደቱ የቀረቡ ምክረ-ሀሳቦች ከላይ በተጠቀሱት መንገዶች ምክክር ተደርጎባቸው ከተጣሩ በኋላ የተጠቃለሉ ምክረ-ሃሳቦች 500 አባላት ባሉት የአጀንዳ ተመካካሪ ቡድን ቀርበው ፀድቀዋል። እያንዳንዱ ተመካካሪ ቡድን በመጨረሻም በተለያዩ አጀንዳዎች መካከል የቀረቡ ምክረ-ሃሳቦችን ማጣጣም (cross-validation) ለማካሄድ 15 ተወካዮችን መርጧል፡፡ በዚህ መሰረት በአጠቃላይ 120 የሚሆኑ የምክረ-ሃሳብ አቀናጆች ተመርጠው ሥራቸውን በአግባቡ አከናውነዋል፡፡ በሂደቱ ምክረ-ሃሳቦችን የማጣጣም ዋነኛ ዓላማም በተለያዩ ተመካካሪ ቡድኖች ውስጥ የተነሱ ምክረ-ሃሳቦች እርስ በእርስ እንዳይጣረሱ እና አላስፈላጊ ድግግሞሽ እንዳይኖር በማሰብ ነበር፡፡
Afar Communication Bureau
Photo
ይህ ጉባኤ ስኬታማ ይሆን ዘንድ በተለያዩ ዘርፎች ሙያዊ እገዛ ያደረጉ ባለሙያዎች መኖራቸው ሊዘነጋ አይገባም። 80 የባለሙያዎች ቡድን ለተሳታፊዎች በአጀንዳዎቹ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ሰጥቷል፤ ይህም ተሳታፊዎች መረጃን ማዕከል ያደረገ ምክክር እንዲያደርጉ ትልቅ ሚና ተጫውቷል፡፡

ከዚያ በተጨማሪ 160 የሚጠጉ አመካካሪዎች የምክክሩን ሂደት የመሩ ሲሆን፣ 158 ቃለ-ጉባኤ አዘጋጆች (rapporteurs) በእያንዳንዱ የምክክር ሂደት ውስጥ የነበሩ ምክረ-ሃሳቦችን በመሰነድ ለሂደቱ መሳካት ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርገዋል።

👉ከመግባባት ያለፈ ሀገራዊ ምክክር

የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ፋይዳ ምክረ-ሃሳቦችን በመግባባት ማዘጋጀት ብቻ አልነበረም። ከዚያ በተጨማሪ የተለያየ ልምድ፣ ፍላጎት እና የፖለቲካ አቋም ያላቸው ሰዎች እርስ በእርስ በቀጥታ የሚነጋገሩበትን መድረክ መፍጠርም ጭምር ነበር፡፡

ይህ መድረክ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ባህል ውስጥ ትልቅ ሽግግርን ያመለክታል፦ የሂደቱ ግብ "ማን አሸነፈ፣ ማን ተሸነፈ?" ከሚለው ኋላ ቀር እሳቤ ይልቅ ወደ "በምን ላይ መስማማት እንችላለን? ምን አይነት ልዩነቶችን ማስተናገድ ይቻላል? እና በአንድነት ምን አይነት የጋራ ተስፋ መገንባት እንችላለን?" ወደሚለው ጥያቄ መሸጋገር ነው፡፡

👉የመዝጊያ ሥነ-ሥርዓት

ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም በተካሄደው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው የመዝጊያ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴን ጨምሮ ጥሪ የተደረጋላቸው የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገራት የክብር እንግዶች ተገኝተው የተለያዩ መልዕክቶችን አስተላልፈዋል፡፡ በመድረኩ ላይ ፕሬዚዳንት ታዬ እንደተናገሩት ሀገራዊ ምክክሩ አንድነትን የሚያጠናክር ትልቅ የታሪክ ምዕራፍ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡

በሌላ በኩል በክብር እንግድነት የተገኙት የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ፣ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተወጣጡ ወኪሎች እርስ በእርስ ለመግባባት ያሳዩትን ተነሳሽነት አድንቀው ይህም ዜጎች በጋራ ጉዳዮቻቸው ላይ ለመነጋገር ፈቃደኛ ሲሆኑ የበለጠ ፍሬያማ እንደሚሆን አውስተዋል፡፡

የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ምክክር የሀገሪቱን ፈተናዎች ለመፍታት የሚያስችል አቅም ያለው መንገድ መሆኑን ጠቁመው ኢትዮጵያ በምክክር ልትፈታው የማትችለው ምንም ዓይነት ፈተና እንደሌለ አፅዕኖት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡ አክለውም በኃይል አማራጭ አሸናፊ የሚሆን አካል እንደማይኖር ገልፀው ምክክር ሁሉንም አሸናፊ እንደሚያደርግ ጠቁመዋል።

ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሂሩት ገብረሥላሴ በበኩላቸው የሀገራዊ ምክክሩ መጠናቀቅ በኢትዮጵያ የፖለቲካ እና የማህበራዊ ጉዞ ውስጥ ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል። ምክትል ዋና ኮሚሽነሯ አክለውም ሀገራዊ ምክክሩ ኢትዮጵያውያን ለረጅም ጊዜ የቆዩ ቅሬታዎችን፣ የፖለቲካ ልዩነቶችን እና የታሪክ ክፍፍሎችን ከግጭት ይልቅ በምክክር እንዲፈቱ ዕድል የፈጠረ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

👉የነገው መንገዳችን

የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ከአንድ ወቅት ክስተት ባላፈ የሚሻገሩ ታላላቅ ግቦች አሉት፡፡ በዚህ ሂደት የሚጠበቁ ውጤቶች መሰረታዊ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መግባባትን መፍጠር፣ ሀገራዊ አንድነትን እና ማህበራዊ ትስስርን ማጠናከር፣ የመፍትሔ ሃሳቦች የሕዝብ ባለቤትነት እንዲኖራቸው ማድረግ፣ በተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች መካከል እምነትን መገንባት እና ለዘላቂ ሰላም፣ ለዲሞክራሲያዊ አስተዳደር እና ለሀገር ግንባታ መሠረት መጣልን ያካትታሉ፡፡

የሀገራዊ ምክክር ጉዞ ረጅም ነበር። ተቋም መፍጠርን፣ ሥነ-ዘዴን ማዘጋጀትን፣ ባለድርሻ አካላትን መለየትን፣ አጀንዳ ማሰባሰብን፣ የሕዝብ ተሳትፎን ማጎልበት፣ ውክልናን ማረጋገጥ፣ አጀንዳን መቅረፅን እና በሀገር አቀፍ ደረጃ የምክክር ጉባኤ ማካሄድን ጠይቋል፡፡

በሀገራችን ኢትዮጵያ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በአንድነት መቀመጥ፣ መደማመጥ እና የጋራ መግባባትን መፈለግ በራሱ ትልቅ እርምጃ ነው።

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የኢትዮጵያ ልጆች ሀገራዊ ችግሮችን በምክክር መፍታት እንደሚችሉ ያስመሰከሩበት መድረክ!

በምክክር ሁሉም አሸናፊ ነው!
Afar Communication Bureau
Photo
ቃል ሐሳብን ይቀርጻል፤ ሐሳብ ደግሞ ዓለምን ይለውጣል። ንግግሮች የጊዜን ወሰን ሰብረው፣ ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚሻገሩ የሕዝቦች የማንነት ማኅተምና የዘመን ምስክር ናቸው። በመሪዎች መነጽር ሲታይ ቃል ቀላል ድምፅ ሳይሆን፣ ታሪክን የሚወስን፣ ማኅበረሰብን የሚቀይር እና ሀገርን የሚገነባ የኃይል ምንጭ ነው። በመሪዎች ቃል ውስጥ ህዝብ የሀገርን ተስፋና የመሪዎቹን ርዕይ እንዲቃኝ ያስችላል።

በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አዘጋጅነት የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር) ከ2017 እስከ 2018 ዓ.ም ያደረጓቸውን ንግግሮች እና ያስተላለፏቸውን መልዕክቶች ዳግም «ከመስከረም እስከ መስከረም» በተሰኘው መጽሐፍ 8ተኛ ቅጽ በይፋ ለአንባቢያን ቀርቧል።
እርስዎም በመጽሐፉ ዘልቀው ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተለያየ አቅጣጫ ሀገር ለማቅናት የተጓዟቸውን የዓመት ጉዞ በተለያዩ ጊዜያት ባደረጓቸው ቁልፍ ንግግሮች እና ያስተላለፏቸውን አቅጣጫ ጠቋሚ መልዕክቶች ይቃኙ።

ሙሉ መጽሐፉን ለማግኘት ይህን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ:-https://share.google/uTjPqcMG1OFDWj7Xq

Words shape thought, and thought transforms the world. Speeches transcend the boundaries of time, serving as an enduring seal of a people's identity and a testament to an era, passed down from generation to generation. Viewed through the lens of leadership, a word is never merely a fleeting sound, it is a source of power that defines history, reshapes society, and builds a nation, allowing the public to discern a nation's hope and its leaders' vision through their executive rhetoric.

Prepared by the Office of the Prime Minister of Ethiopia, the speeches and messages delivered by His Excellency Prime Minister Abiy Ahmed (PhD) from 2017 to 2018 E.C. have been officially released to readers in the 8th volume of the book entitled “Meskerem to Meskerem.” Delve into this volume to explore His Excellency the Prime Minister’s year long journey and multifaceted efforts to reconstruct and uplift the nation through his key speeches and strategic directives delivered over time.

↓ Discover the full journey, access the book here ↓

Link: https://share.google/uTjPqcMG1OFDWj7Xq

#PMOEthiopia
1