✅ኩረጃ ምንድን ነው? (
በድጋሜ የተለጠፈ)✅ከዚህ ቀደም
ቢቢሲ በሰራው አንድ ዘገባም ተማሪዎች ለኩረጃ ይመቻቸው ዘንድ ከጎበዝ ተማሪዎች ጋር በማመሳሰል ስማቸውን በፍርድ ቤት አስለውጠዋል።
✅ኩረጃ በአንድ የፈተና ክፍል ውስጥ ብቻ የሚካሄድ ሳይሆን በዕለት ተዕለት ትምህርት ስርዓት ውስጥ የሚዳብር መሆኑን ጨምረው ያስረዳሉ።
✅የራስ ያልሆነን ስራ እንደራስ አድርጎ ማቅረብ፣ ትክክለኛ ምክንያት ባለመስጠት መምህሩን ማሳሳት እና የማይገባውን ውጤት ለማግኘት የሚደረግ ጥረት፣ ያልተገባ ውጤት ለማግኘት መምህርን ማታለል በአጠቃላይ ኩረጃ ነው ይላሉ ወንድይፍራው (ዶ/ር)።
✅ጓደኛ እንዲኮርጅ መርዳት፣ በግል የተሰጠ ምዘናን ወይንም የቤት ሥራ በቡድን መስራት ሁሉ በኩረጃ ስር እንደሚጠቃለሉ ጨምረው ይገልጻሉ።
✅በትምህርት ቤት ሕይወታቸው ቢያንስ አንድ ጊዜ በኩረጃ ላይ የተሳተፉ ግለሰቦች በርካታ መሆናቸውን በተለያዩ አገራት የተሰሩ ጥናቶች ያሳያሉ።
✅ተማሪዎች የሚኮርጁት ለፈተናው ወይንም ደግሞ ምዘናው በቂ የስነልቦና ዝግጅት ሳይኖራቸው ሲቀር መሆኑን ይናገራሉ።
✅ተማሪዎች በተገቢው መጠን ራሳቸውን ካለመዘጋጀት ውጪ፣ ትምህርትን በአግባቡ አለመከታተል፣ ኩረጃ አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሌለው ግንዛቤ መያዝ ወደ ኩረጃ የሚገፉ ሌሎች ምክንያቶች ናቸው ይላሉ።
✅ከዚህም በተጨማሪ ወንድይፍራው (ዶ/ር) እንደሚሉት የወላጆች 'ልጆቼ ተምረው፣ ሕይወቴን ይለውጡኛል' የሚለው ገለጻ ልጆች ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ያሳርፋል።ይህ ቤተሰብ የሚያደርገው ጫና ተማሪዎችን ለማበረታታት የተደረገ ነገር ቢሆንም ለኩረጃ እንደሚገፋም ያስረዳሉ።
✅በራሱ ጥረት ወላጆቹ ወዳሰቡለት ስኬት መድረስ ያልቻለ ተማሪም የወላጆቹን ጫና ለመሸሽ ጎበዝ የሚባሉ ተማሪዎችን በመደገፍ ጥሩ ውጤት ለማስመዝገብ ይሞክራል በማለት ሃሳባቸውን ያጠናክራሉ። ኩረጃ ከክፍል ክፍል ሲኬድ እያደገ የሚሄድ ብቻ ሳይሆን፣ በሕይወት ውስጥ ዘላቂ የሆነ ተጽዕኖ እንዳለውም ጨምረው ገልፀዋል።
✅"ጥናቶች እንደሚያመለክቱት በትምህርት ዓለም የነበረን የኩረጃ ሕይወት ወደ ሥራ ዓለም ስንገባም ያንኑ የመተግበር እድሉ ከፍተኛ እንደሆነ እና ተያያዥነት እንዳለው ነው፤ አንድ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ በኩረጃ ታግዞ ወደ ከፍተኛ ተቋም ሲገባ፣ እዚያም በኩረጃ ታግዞ ቢመረቅ በስራው ዓለም መደለያ ለመቀበል አያቅማማም።"
✅ተማሪዎች በጓደኞቻቸው ዘንድ ሰነፍ ሆኖ ላለመታየት፣ በውጤት አንሶ ላለመገኘት፣ ወደ ኩረጃ እንደሚገቡም አክለው ተናግረዋል።ተማሪዎቹ ወደ መፈተኛ ክፍል ከመግባታቸው በፊት፣ ለኩረጃ ሲዘጋጁ ኔትወርክ ፈጥረው፣ የመጀመሪያው እቅድ ባይሳካ በሚል ሁለት እና ሶስት እቅዶችን ነድፈው መሆኑንም ጠቅሰዋል።
✅ከዚህ በተጨማሪ የነደፉት ስልት በፈተና የመጀመሪያ ቀን ካልሰራ፣ ለቀጣዩ ፈተና ቀን ሌላ ስልት ነድፈው እንደሚመጡም ይናገራሉ።ከዚህ የሞባይል ቴክኖሎጂን ተጠቅመው በሚያደርጉት ኩረጃም ከትምህርት ቤት ውጪ ያሉ ግለሰቦችን እንደሚያካትቱ ጨምረው ያስረዳሉ።
✅አንዳንድ ትምህርት ቤቶች በቀጥታም ባይሆን በተዘዋዋሪ ተማሪዎችቻቸውን የመደገፍ ነገር ማስተዋላቸውን የሚናገሩት ወንድይፍራው (ዶ/ር) ፣ በትምህርት ቤቶች መካከል ያለው ውድድር ለዚህ አስተዋጽኦ ማድረጉን ይጠቅሳሉ።
✅ለፈተና ስርቆት እና ኩረጃ መስፋፋት እገዛ የሚያደርገው ቴክኖሎጂ ብቻ ሳይሆን የመምህራን እና የትምህርት ቤቱ አስተዳደሮች ቁርጠኛ አለመሆን ጭምር መሆኑንም አክለው ገልፀዋል።
✅በኩረጃ ሲሳተፉ የተገኙ ተማሪዎች ላይ የሚወሰዱ እርምጃዎች ምን ያህል ፈጣን እና አስተማሪ ናቸው? ሲሉ የሚጠይቁት ምሁሩ፣ የተወሰደ እርምጃ ቢኖር እንኳ ለተማሪዎች በፍጥነት አለመንገር ለኩረጃ መስፋፋት አስተዋጽኦ ያደርጋል ሲሉ ሃሳባቸውን ያጠናክራሉ።
✅ኩረጃን ማስቀረት ይቻላል?⭐️ኩረጃን ማጥፋት ሳይሆን መቀነስ ይቻላል የሚሉት ወንድይፍራው (ዶ/ር) ከመጀመሪያ ደረጃ ጀምሮ ተማሪዎች ስለታማኝነት እየተማሩ መምጣት እንዳለባቸው ይመክራሉ።
⭐️ታዳጊዎች ከታች ክፍል ጀምሮ መኮረጅ አስፀያፊ መሆኑን እየነገሩ ማሳደግ በኋላ በከፍተኛ ትምህርት ተቋምም ሆነ በሁለተኛ ደረጃ ላይ በስነምግባር የታነፀ ትውልድ እንዲኖር ይረዳል።
⭐️ከሥርዓተ ትምህርት አንጻርም ስለኩረጃ፣ ስለታማኝነት በየትምህርት ዓይነቶቹ ላይ ማካተት እንደሚያስፈልግ ያስረዳሉ።
⭐️መምህራንም ቢሆኑ ኃላፊነት ተሰምቷቸው በትክክል ተማሪዎቻቸውን መመዘን የሚያስችል ፈተና ማዘጋጀት ይጠበቅባቸዋል ሲሉ ይመክራሉ።
⭐️ፈተና በሚሰጥበት ክፍል ውስጥም ቢሆን መምህሩ በአግባቡ መፈተን መቻሉ ኩረጃን ለመቀነስ የራሱ አስተዋጽኦ አለው ሲሉ ያስቀምጣሉ።
⭐️የትምህርት አስተዳደሮችም ቢሆኑ ለተማሪዎች በሚያወጧቸው መመሪያዎችን እና መተዳደሪያ ደንቦችን በአመቱ መጀመሪያ ላይ ለተማሪዎቹ በሚገባ ማስተዋወቅ እንደሚያስፍልጋቸው ይገልጻሉ።
⭐️የወጡ መመሪያና ደንቦችን ተከትሎም ለሚፈፀሙ ጥፋቶች የተቀመጡ ተገቢ ቅጣቶችን ሳይዘገዩ ተፈጻሚ ማድረግ ወሳኝ መሆኑን ያብራራሉ።
⭐️ተማሪው ያጠፋውን ጥፋትን እና ቅጣቱን ለማገናኘት እንዲችል፣ ሲኮርጅ እንደተያዘ ወድያውኑ እርምጃ መውሰድ ለትምህርት ቤቱ ተማሪዎችም ወዲያውኑ ማሳወቅ እንደሚገባ ይናገራሉ።
በምንጭነት
✅BBC Amharic
⭐️ ሀገር አቀፍና ከተማ አቀፍ ፈተናዎች የሚሰጡበት ቀን እየቀረበ ነውና በቀሪ አጭር ቀናት ጠንክረን እናጥና !!
⛔️ኩረጃን በጋራ
እንከላከል❌📣በቀጣይ በተከታታይ ለፈተና ዝግጅት የሚጠቅሙ መረጃዎችንና ሞዴል ፈተናዎች እንለቃለን ቻናሉን ለሌሎች ያጋሩ
🤝👏👏መልካም ጥናት✅🔠🔠🔠🅰️ 🔤🔤🔤ቻናላችን ይህ ነው👇👇👇👇👇👇❤️❤️❤️❤️❤️https://t.me/dam76