ኮተቤ የመ/ደ/ት/ቤት የተማሪዎች ጥያቄ ማስተላለፊያ
290 subscribers
2.14K photos
81 videos
584 files
100 links
learning Room
Download Telegram
Forwarded from Alem Abebe
በቀን 1/8/2018 በክላሰተር ደረጃ በእንግሊዘኛና በሂሳብ ት/ት በተደረገ ጥያቃና መልስ ውድድር በ6ኛ ክፍል1ኛና3ኛ በ8ኛ ክፍል 2ኛ በት/ቤት ደረጃ 1ኛ በመውጣት አጠናቀናል
Forwarded from Yeka Education
ኩረጃ ምንድን ነው?
(በድጋሜ የተለጠፈ)

ከዚህ ቀደም ቢቢሲ በሰራው አንድ ዘገባም  ተማሪዎች ለኩረጃ ይመቻቸው ዘንድ ከጎበዝ ተማሪዎች ጋር በማመሳሰል ስማቸውን በፍርድ ቤት አስለውጠዋል።

ኩረጃ በአንድ የፈተና ክፍል ውስጥ ብቻ የሚካሄድ ሳይሆን በዕለት ተዕለት ትምህርት ስርዓት ውስጥ የሚዳብር መሆኑን ጨምረው ያስረዳሉ።

የራስ ያልሆነን ስራ እንደራስ አድርጎ ማቅረብ፣ ትክክለኛ ምክንያት ባለመስጠት መምህሩን ማሳሳት እና የማይገባውን ውጤት ለማግኘት የሚደረግ ጥረት፣ ያልተገባ ውጤት ለማግኘት መምህርን ማታለል በአጠቃላይ ኩረጃ ነው ይላሉ ወንድይፍራው (ዶ/ር)።

ጓደኛ እንዲኮርጅ መርዳት፣ በግል የተሰጠ ምዘናን ወይንም የቤት ሥራ በቡድን መስራት ሁሉ በኩረጃ ስር እንደሚጠቃለሉ ጨምረው ይገልጻሉ።

በትምህርት ቤት ሕይወታቸው ቢያንስ አንድ ጊዜ በኩረጃ ላይ የተሳተፉ ግለሰቦች በርካታ መሆናቸውን በተለያዩ አገራት የተሰሩ ጥናቶች ያሳያሉ።

ተማሪዎች የሚኮርጁት ለፈተናው ወይንም ደግሞ ምዘናው በቂ የስነልቦና ዝግጅት ሳይኖራቸው ሲቀር መሆኑን ይናገራሉ።

ተማሪዎች በተገቢው መጠን ራሳቸውን ካለመዘጋጀት ውጪ፣ ትምህርትን በአግባቡ አለመከታተል፣ ኩረጃ አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሌለው ግንዛቤ መያዝ ወደ ኩረጃ የሚገፉ ሌሎች ምክንያቶች ናቸው ይላሉ።

ከዚህም በተጨማሪ ወንድይፍራው (ዶ/ር) እንደሚሉት የወላጆች 'ልጆቼ ተምረው፣ ሕይወቴን ይለውጡኛል' የሚለው ገለጻ ልጆች ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ያሳርፋል።ይህ ቤተሰብ የሚያደርገው ጫና ተማሪዎችን ለማበረታታት የተደረገ ነገር ቢሆንም ለኩረጃ እንደሚገፋም ያስረዳሉ።

በራሱ ጥረት ወላጆቹ ወዳሰቡለት ስኬት መድረስ ያልቻለ ተማሪም የወላጆቹን ጫና ለመሸሽ ጎበዝ የሚባሉ ተማሪዎችን በመደገፍ ጥሩ ውጤት ለማስመዝገብ ይሞክራል በማለት ሃሳባቸውን ያጠናክራሉ። ኩረጃ ከክፍል ክፍል ሲኬድ እያደገ የሚሄድ ብቻ ሳይሆን፣ በሕይወት ውስጥ ዘላቂ የሆነ ተጽዕኖ እንዳለውም ጨምረው ገልፀዋል።

"ጥናቶች እንደሚያመለክቱት በትምህርት ዓለም የነበረን የኩረጃ ሕይወት ወደ ሥራ ዓለም ስንገባም ያንኑ የመተግበር እድሉ ከፍተኛ እንደሆነ እና ተያያዥነት እንዳለው ነው፤ አንድ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ በኩረጃ ታግዞ ወደ ከፍተኛ ተቋም ሲገባ፣ እዚያም በኩረጃ ታግዞ ቢመረቅ በስራው ዓለም መደለያ ለመቀበል አያቅማማም።"

ተማሪዎች በጓደኞቻቸው ዘንድ ሰነፍ ሆኖ ላለመታየት፣ በውጤት አንሶ ላለመገኘት፣ ወደ ኩረጃ እንደሚገቡም አክለው ተናግረዋል።ተማሪዎቹ ወደ መፈተኛ ክፍል ከመግባታቸው በፊት፣ ለኩረጃ ሲዘጋጁ ኔትወርክ ፈጥረው፣ የመጀመሪያው እቅድ ባይሳካ በሚል ሁለት እና ሶስት እቅዶችን ነድፈው መሆኑንም ጠቅሰዋል።

ከዚህ በተጨማሪ የነደፉት ስልት በፈተና የመጀመሪያ ቀን ካልሰራ፣ ለቀጣዩ ፈተና ቀን ሌላ ስልት ነድፈው እንደሚመጡም ይናገራሉ።ከዚህ የሞባይል ቴክኖሎጂን ተጠቅመው በሚያደርጉት ኩረጃም ከትምህርት ቤት ውጪ ያሉ ግለሰቦችን እንደሚያካትቱ ጨምረው ያስረዳሉ።

አንዳንድ ትምህርት ቤቶች በቀጥታም ባይሆን በተዘዋዋሪ ተማሪዎችቻቸውን የመደገፍ ነገር ማስተዋላቸውን የሚናገሩት ወንድይፍራው (ዶ/ር) ፣ በትምህርት ቤቶች መካከል ያለው ውድድር ለዚህ አስተዋጽኦ ማድረጉን ይጠቅሳሉ።

ለፈተና ስርቆት እና ኩረጃ መስፋፋት እገዛ የሚያደርገው ቴክኖሎጂ ብቻ ሳይሆን የመምህራን እና የትምህርት ቤቱ አስተዳደሮች ቁርጠኛ አለመሆን ጭምር መሆኑንም አክለው ገልፀዋል።

በኩረጃ ሲሳተፉ የተገኙ ተማሪዎች ላይ የሚወሰዱ እርምጃዎች ምን ያህል ፈጣን እና አስተማሪ ናቸው? ሲሉ የሚጠይቁት ምሁሩ፣ የተወሰደ እርምጃ ቢኖር እንኳ ለተማሪዎች በፍጥነት አለመንገር ለኩረጃ መስፋፋት አስተዋጽኦ ያደርጋል ሲሉ ሃሳባቸውን ያጠናክራሉ።

ኩረጃን ማስቀረት ይቻላል?

⭐️ኩረጃን ማጥፋት ሳይሆን መቀነስ ይቻላል የሚሉት ወንድይፍራው (ዶ/ር) ከመጀመሪያ ደረጃ ጀምሮ ተማሪዎች ስለታማኝነት እየተማሩ መምጣት እንዳለባቸው ይመክራሉ።

⭐️ታዳጊዎች ከታች ክፍል ጀምሮ መኮረጅ አስፀያፊ መሆኑን እየነገሩ ማሳደግ በኋላ በከፍተኛ ትምህርት ተቋምም ሆነ በሁለተኛ ደረጃ ላይ በስነምግባር የታነፀ ትውልድ እንዲኖር ይረዳል።

⭐️ከሥርዓተ ትምህርት አንጻርም ስለኩረጃ፣ ስለታማኝነት በየትምህርት ዓይነቶቹ ላይ ማካተት እንደሚያስፈልግ ያስረዳሉ።

⭐️መምህራንም ቢሆኑ ኃላፊነት ተሰምቷቸው በትክክል ተማሪዎቻቸውን መመዘን የሚያስችል ፈተና ማዘጋጀት ይጠበቅባቸዋል ሲሉ ይመክራሉ።

⭐️ፈተና በሚሰጥበት ክፍል ውስጥም ቢሆን መምህሩ በአግባቡ መፈተን መቻሉ ኩረጃን ለመቀነስ የራሱ አስተዋጽኦ አለው ሲሉ ያስቀምጣሉ።

⭐️የትምህርት አስተዳደሮችም ቢሆኑ ለተማሪዎች በሚያወጧቸው መመሪያዎችን እና መተዳደሪያ ደንቦችን በአመቱ መጀመሪያ ላይ ለተማሪዎቹ በሚገባ ማስተዋወቅ እንደሚያስፍልጋቸው ይገልጻሉ።

⭐️የወጡ መመሪያና ደንቦችን ተከትሎም ለሚፈፀሙ ጥፋቶች የተቀመጡ ተገቢ ቅጣቶችን ሳይዘገዩ ተፈጻሚ ማድረግ ወሳኝ መሆኑን ያብራራሉ።

⭐️ተማሪው ያጠፋውን ጥፋትን እና ቅጣቱን ለማገናኘት እንዲችል፣ ሲኮርጅ እንደተያዘ ወድያውኑ እርምጃ መውሰድ ለትምህርት ቤቱ ተማሪዎችም ወዲያውኑ ማሳወቅ እንደሚገባ ይናገራሉ።

በምንጭነት BBC Amharic

⭐️ ሀገር አቀፍና ከተማ አቀፍ ፈተናዎች የሚሰጡበት ቀን እየቀረበ ነውና በቀሪ አጭር ቀናት  ጠንክረን እናጥና !!

⛔️ኩረጃን በጋራ
እንከላከል


📣በቀጣይ በተከታታይ ለፈተና ዝግጅት የሚጠቅሙ መረጃዎችንና ሞዴል ፈተናዎች እንለቃለን ቻናሉን ለሌሎች ያጋሩ🤝👏👏

መልካም  ጥናት

🔠🔠🔠🅰️ 

🔤🔤🔤

ቻናላችን ይህ ነው
👇👇👇👇👇👇
❤️❤️❤️❤️❤️
https://t.me/dam76
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Forwarded from Yeka Education
🔠🔠🔠

✔️በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተናዎች የሚሰጡበት ጊዜ ይፋ ሆናል፡፡  
 
(ግንቦት 13/2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን ከተማ አቀፍ የ6ኛ ክፍል የአንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና እና የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና  የሚሰጥበት ጊዜ ይፋ ሆናል፡፡
 
📌በዚህ መሰረትም ከተማ አቀፍ የ6ኛ ክፍል የአንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና ሰኔ 8 ፣ 9 እና 10/2018 ዓ.ም

እንዲሁም የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና  ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሚሰጥ ይሆናል፡፡
 
📌ከሰኔ 8 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም በሚሰጠው በዚህ ከተማ አቀፍ ፈተና በ6ኛ ከፍል 84,882 ተማሪዎች 199  የመፈተኛ ጣቢያዎች  እንዲሁም በ8ኛ ከፍል 86,808 ተማሪዎች 201 የመፈተኛ ጣቢያዎች  ፈተናዉን ለመውሰድ ተመዝግበዋል፡፡
 
 መልካም  ፈተና

🔠🔠🔠🅰️ 
🔤🔤🔤🔤 

🔠🔠🔠
🔤🔤🔤

ቻናላችን ይህ ነው
👇👇👇👇👇👇
❤️❤️❤️❤️❤️
https://t.me/dam76
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Forwarded from Adugnaw Bamlaku
✔️ይነበብ
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Forwarded from Yeka Education (Adugnaw Bamlaku)
የፈተና ጊዜ ሲቃረብ ሁላችንም በመጠኑ መጨነቅ እና ከወትሮው ከፍ ባለ መጠን ውጥረት ውስጥ መግባታችን የተለመደ ነገር ነው

📌 ይህም ጤናማ ፍርሀት ለፈተና እንድንተጋ ስለሚረዳን በተሻለ ለመዘጋጀት እንዲሁም ጥሩ ትኩረት ለማድረግ ያስችለናል።

✔️ ሆኖም ግን ይህ ጭንቀት ወይም ቴንሽን መጠነኛ ካልሆነ ወደ መደናገር እና ከፍተኛ ለሆነ ውጥረት ይዳርገናል ። በዚህም የተነሳ ፈተናችንን በጥሩ እንዳናስኬድ እና ተገቢውን ትኩረት እንዳንሰጥ ያደረፈርገናል ። 

✔️ከዚህም ሀሳብ ጋር በተያያዘ ለዚህ አይነቱ #ጭንቀት እና ውጥረት ውስጥ #እንድንገባ አስተዋጽኦ ከሚያደርጉ #ምክንያቶች ውስጥ #ጥቂቶቹ:

➡️ አሉታዊ ሀሳቦች ወደ አዕምሮ በመምጣት ሀሳባችን በሙሉ ስለ ፈተናው አስከፊነት እና ስለውጤት መበላሸት አብዝተን ስናስብ ።

➡️ በቂ እና ምክንያታዊ ያልሆነ ግመታ እና ድምዳሜ አጠቃሎ ስለፈተናው ማሰብ ።

➡️ የውጫዊ ተፅእኖ እንደ ቤተሰብ ፣ መምህራን እና ጓደኛ የሚመጡ ጫናዎች አስተሳሰባችን ላይ ይህ መሆን አለበት ወይም መሆን የለበትም የሚል አቋም መያዝ ስህተትን እንዳንቀበል እና መሳሳትን እንድንፈራ ስለሚያረግ በፈተና መዳረሻ ከፍተኛ ለሆነ ውጥረት ይዳርገናል ።

➡️ሙሉ ሀሳብን ወደ ፈተናው ይዘት እና ሁኔታ ከማተኮር ይልቅ ወደ ውጤት እና ነጥብ ብቻ ላይ ማተኮር እና ማስላት።  እነዚህ ዋና ዋናዎቹ በፈተና ወቅት ውጥረትን እና ጭንቀትን የሚያስከትሉ ምክንያቶች ናቸው።

ስለዚህ ተፈታኞች የተወሰነ ዘዴን በመጠቀም ይህን አይነቱን ከፍተኛ ውጥረት መቆጣጠር የምትችሉበትን መንገድ አንድ በአንድ እንመልከት፤

⭐️  ከፈተና በፊት ማድረግ የሚገባን ዜዴዎች፤ -

➡️ ፈተና ሲመጣ መጠነኛ ውጥረት እና ጭንቀት ተፈጥሮአዊ እና ሁሉም ተፈታኝ ተማሪ እንደሚያጋጥመው መረዳት።

➡️ ለፈተና ስንዘጋጅ አዎንታዊ እና በጎ ሀሳቦችን ማሰብ፡፡ ይህ ማለት ስለፈተናው ክብደት እና አስከፊነት ከማሰብ በተቃራኒው በአይነ ህሊና (visualization) ዘና ብለን ስንፈተን እና ፈተናውን በተገቢ መንገድ ስንፈተን በአእምሮችን መሳል ።

ከዚህ ጋር በተያያዘ ከዚህ ቀደም በክፍል ውስጥ በብቃት የሰራናቸውን ፈተናዎች እና የገኘነውን ጥሩ ውጤቶች ማሰብ።  እናም ምን አይነት ፈተና ሊመጣ ይችላል ብለን አብዝተን አለመጨነቅ ይልቅ የሚመጣው ፈተና ከዚህ በፊት ከተማርነው የተለየ አለመሆኑን መረዳት እና መጪውም ፈተና በተመሳሳይ እንደምንሰራው ማሰብ።

➡️ፈተና ማለት ከዚህ ቀደም ከተማርነው ነገር የተረዳነውን እና የቀሰምነውን እውቀት የምንለካበት መመዘኛ እንጂ የኛ የህይወት ምዕራፍ ማብቂያ ወይም አጠቃላይ ችሎታችንን የሚያመላክት አይደለም ።

ምክንያቱም ከላይ እንደ ምክንያት ለተቀመጡት ነጥቦች ከዚህ ሀሳብ በተያያዘ አንድ ተማሪ በፈተና ጥሩ ውጤት ባያገኝ እና ቢሳሳት ቀድሞውኑ ወደ ጭንቅላቱ የሚመጣው አለማወቁ ዋጋ እንደሚያስከፍለው እና ቤተሰቦቹም ሆነ መምህራን እንደ ሰነፍ እና ዋጋ እንደሌለው ስለሚገመት ስህተትን አስተካክሎ ለቀጣይ ለማሻሻል እና ለመማር መሰናክል ይፈጥራል።

ስለዚህ ማወቅ ያለብን አንድ ነገር ቢኖር መሳሳትን አለመፍራት እና ሁሌም ለማወቅ እና ራስን ለማሻሻል ዝግጅ መሆንን ነው ። እንዲሁም አሁን የምንፈተነው ፈተና እንዳሰብነው እንኳን ውጤቱ ባያስደስት ለቀጣይ ማስተካከል እና ማሻሻል እንደሚቻል ማመን።

➡️ከጓደኞቻችን ጋር ያጠናነውን ነገር በጋራ ሆነን መጠያየቅ እና እርስ በርስ ያወቅነውን ነገር መለዋወጥ፡፡ ይህ ዘዴ ይበልጥ የማስታወስ ብቃታችንን እንደሚጨምር እና የተጠያየቅነው ነገር እንዳይረሳን ያረጋል ።

📌ከዚህም በተጨማሪ የተሳሳትነውን ነገር ድጋሚ እንድንከልስ እና እርማት እንድናረግ ያግዘናል።

➡️ የፈተና ቀን ሲቃረብ እንደ ወትሮው ዘና ማለት እና በቂ እረፍትና በቂ እንቅልፍ  መተኛት ። ይህም ጭንቀትን ይቀንስልናል፣ እንዲሁም ተረጋግተን ያጠናነውን ነገር አስበን እንድንሰራ ይረዳናል።

✔️ ፈተና ከጀመርን በኋላ መድረግ የሚገቡን ነገሮች (ፈተና ላይ እያለን)፤

➡️ ወደ ፈተና ከመሄዳችን ቀደም ብለን ለፈተና የሚረዱንን መሳሪያዎች እና የመፈተኛ ቁሶችን ማዘጋጀት። 

➡️አብዝተን ፈተናን እና የምናመጣውን ነጥብ ስሌት አለመገመት ።

➡️ ፈተና ስንጨርስ የተሳሳትነውን ጥያቄ አብዝቶ ማሰብ እና ሌላ ተማሪ መጠየቅ ጭንቀት ውስጥ ስለሚከተን ከዚህ ይልቅ ቤት ሄደን እረፍት ማድረግ እና ለቀጣይ ፈተና መዘጋጀት ።

በፈተና ጊዜ ድንገተኛ ጭንቀት እና ድንጋጤ ከገጠመን ወዲያው የምንሰራውን ገታ አድርገን በጥልቀት አየር በአፍንጫችን ስበን ወደ ሳንባ እያስገባን መልሰን ማስወጣት ይህንንም እስክንረጋጋ መደጋገም ።
 
➡️ ፈተና በምንሰራ ጊዜ ግራ ያጋባንን እና እርግጠኛ ያልሆንበትን ጥያቄ በይለፍ ማቆየት እና ወደ ቀጣዩ ጥያቄ መሄድ ይህም ጊዜያችንን በአግባቡ እንድንጠቀም ይረዳናል። ነገር ግን ምልክት አድርገን ማለፍ፤  •

✔️በተመሳሳይ እርግጠኛ ያልሆልንበትን መልስ ላይ ተደናግጠን መሰረዝ እና መደለዝን መቀነስ

ይህም ስንደነግጥ እና ስንጨነቅ የምናውቀውን መልስ ትተን ወደ ሌላ መልስ እንድሰጥ ስለሚያረግ መሰረዝና መደለዝን መቀነስ ።

ፈተናውን ወደ ማገባደድ ስንደርስ በይለፍ ያስቀመጥናቸውን ግራ ያጋቡንን ጥያቄዎች ጥቂት አስበንበት መልስ መስጠት ፤ ካልሆነም ደግሞ ብልሀት ተጠቅመን የግመታ መልስ ሰጥተን ወደ ቀጣዩ ጥያቄ መሄድ ።

📌በተደጋጋሚ ሰአትን አለመመልከት ወይም ሰአት በቃን አልበቃን እያልን አለመጨነቅ።

ይልቅ በጣም ሳንንቀራፈፍ ተረጋግተን ፈተናውን  መስራት እና ፈተናውን ከጨረስን በኋላ ተመልሰን የሰራነውን ጥያቄ አጠቃላይ ማየት ያስፈልጋል።           

⭐️የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ከ10ቀናት ያልበለጡ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1 ወር ያነሱ ቀናት ይቀሩታል!

#️⃣Share

⭐️ ለሁሉም ተፈታኞች
መልካም የጥናትና የፈተና ጊዜ!
⭐️

🔠🔠🔠🔠

🔠🔠🔠

Our Channel
⬇️⬇️⬇️
https://t.me/dam76
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Forwarded from Adugnaw Bamlaku
✔️ለ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተፈተኞች የትምህርት አይነትና ኮድ
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM