የአዳማ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት
1.11K subscribers
1.77K photos
24 videos
22 files
227 links
ይሄ የቴሌግራም ገፅ በምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተክህነተ በሰ/ት/ቤቶች አንድነት የተከፈተ ሲሆን በዚህ ቻናል መንፈሳዊ ትምህርቶችን፣ ዜና ቤተክርስቲያንና ወቅታዊ ጉዳይ የምንዘግብበት ነው። እርሶም ለኦርትዶክሳውያን ሁሉ ቻናሉን በማጋራት ለቅድስት ቤተክርስቲያን ድምጽ ይሁኑ።
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን!
Download Telegram
የመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተክህነት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት  ከማኅበረ ቅዱሳን አዳማ ማዕከል እና ማኅበራት ጥምርት ጋር በመተባባር  ተግዳሮትን መቋቋምና  ዕድሎችን መጠቀም በምል ርዕስ ሥልጠና  ለአጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች ሥራ አመራር እና ሥራ አስፈጻሚ እንድሁም የማኅበረ ቅዱሳን አባላት ፤ግቢ ጉባኤያት  እና የማኅበራት ተወካዮች በማሳተፍ ሥልጠና አሰጠ፡፡
ደብረ ዘይት (እኩለ ጾም)

"ከክብሩ ውበት ከጽዮን እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል። አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም፤ እሳት በፊት ይነዳል።" መዝ 49(50)፡2-3

መልካም ዕለተ ሰንበት!
የበረከት ጾም ያድርግልን።

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!

(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
የናዝሬት ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ገዳምና ካቴድራል ፈለገ ጥበብ ሰ/ት/ቤት የሥራ አመራር ልዑካን ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥር ከሚገኙ ከሦስት ሰ/ት/ቤቶችን ጋር የልምድ ልውውጥ መርሐግብር አካሔደ፡፡ የልምድ ልውውጥ መርሐግብሩ ዋና ዓላማው የተሻለ አፈጻጸም ካላቸው አቻ ሰ/ት/ቤቶች ጋር የአፈጻጸም ተሞክሮ መውሰድና ልምድ በመቅሰም የሰ/ት/ቤቱን አገልግሎቱን ማጠናከር ነው፡፡ የሰ/ት/ቤቱ የሥራ አመራር ልዑካንም ከመናገሻ ገነት ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰ/ት/ቤት፣ የመንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ  ኆኅተ መንግሥተ ሰማይ ሰ/ት/ቤት እና የመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ  ውልደ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ጋር በሰ/ት/ቤቶቹ የማኅበራዊ አገልግሎት በተለይም በነድያን አገልግሎት፣ በሥርዓተ ትምህርት አተገባበርና በመዋቅራዊ አደረጃጀት ዙሪያ ልምድ የተወሰደ ሲሆን በተጨማሪነትም ሌሎች ልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይም ልምድ ለመውሰድ ተችሏል።

👉👉 መረጃው ከሰ/ት/ቤቱ ጽ/ቤት👈👈
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
በሰንበት ት/ቤቶችማደራጀ መምሪያ የሰንበት ት/ቤቶች  አንድነት የተዘጋጀ 64 የሰንበት ት/ቤቶች የሥርዓተ ትምህርት መማሪያ መጻሕፍት ታትመው በስርጭት ላይ ልውሉ ነው።

መረጃው👇👇👇👇👇👇👇👇
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት👈👈👈
👍2
የሰንበት ትምህርት ቤቶች የመማርያ መጻሕፍት ሥርጭት                                                                                            *****

በኢት
ዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ ዕድሜን መሠረት ያደረገ ወጥ የሆነ ሥርዓተ ትምህርት አዘጋጅቶ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት በትግበራ ላይ ይገኛል።

ለሥርዓተ ትምህርት ትግበራውም ለረጅም ጊዜያት በቤተክርስቲያን ሊቃውንትና መምህራን እንዲሁ በሥርዓተ ትምህርት ባለሙያዎች ሲደከምበት የኖረውን የሥርዓተ ትምህርት መማርያ መጻሕፍት በባለፈው ዓመት ከ1ኛ-4ኛ ክፍል 23 የመማሪያ መጻሕፍት በማሳተም በሥርጭት ላይ ማዋሉ ይታወቃል።

በዘንድሮውም ዓመት ደግሞ በአምላካችን ቅዱስ ፈቃድ

👉 ከ1-4ኛ ክፍል 23 የኦሮምኛ ትርጉም የመማርያ መጻሕፍት በአራት ጥራዝ

👉 ከ5ኛ እስከ 7ኛ ክፍል በ3 ጥራዝ የተዘጋጁ 18 መጻሕፍት በአጠቃላይ 41 መጻሕፍት  ተዘጋጅተው ለኅትመትና ለሥርጭት በቅተዋል።  

ለሕዝበ ክርስቲያንም በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን፡


(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
🙏2
በምሥራቅ ሸዋ ሀ/ስብከት በመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ  (አዳማ ) ወረዳ ቤተ ክህነት ስር በሚገኙ ሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርቱን እያስተማሩ ከሚገኙ መምህራን ጋር  በትምህርት አተገባበሩ ዙርያ  በቀን 20/07/2017 ዓ.ም ውይይት እና ስልጠና ተከናወነ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የመንበረ ጵጵስና ሰ/ት/ቤቶች አንድነት በ2014 ዓ.ም በ2 ሰ/ት/ቤቶች ብቻ የተጀመረውን የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ በማጠናከር  በአሁኑ ሰዓት በከተማው በሚገኙ 26 ሰ/ት/ቤቶች እየተገበረ የሚገኝ ሲሆን ፤ ባለፉት 3 ዓመታት ለሥርዓት ት/ቱ ባለ ድርሻ አካላት ብዙ ስልጠናዎች  ሰጥቷል።የዛሬው ሰልጠና በዋናነት “የማስተማር  ሥነ -ዘዴ” ላይ ያተኮረ ሲሆን ፤ ስልጠናው  ከመንበረ ፓትርያርክ  የጠቅላይ ቤተ ክህነት  ሰ/ት/ቤቶች አንድነት በመጡት መ/ር ያረጋል ተሰጥቷል። በስልጠናው የሰ/ት/ቤት አባላት ፣ሰባኪያነ ወንጌል እና  የአብነት መምህራን የተሳተፋ ሲሆን ከስልጠናው በተጨማሪ መምህራን በማስተማር ሒደቱ ያጋጠሟቸውን ችግሮች ላይ ሰፊ ውይይት ተደረጓል።   
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።             የመንበረ ጵጵስናው ሰ/ት/ቤቶች አንድነት
👍3🙏2
ከ8ኛ እስከ 12ኛ ክፍል የሰንበት ት/ቤቶች መማሪያ መጸሐፍት የአርትዖ ሥራ መርሐ ግብር ተካሔደ።
የመንበረ ፓትሪያሪክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የሚዘጋጀው የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መማሪያ መጻሕፍት ከ1-7ኛ ክፍል በአማርኛ እንዲሁም 1ኛ እስከ 4ኛ ክፍል ደግሞ በኦሮምኛ ቋንቋ አዘጋጅቶ ለኅትመት እና ሥርጭት ማብቃቱ ይታወቃል።  አሁን ደግሞ ከ8-12ኛ ክፍል ያሉትን የመማሪያ መጸሐፍት አዘጋጅቶ ለማጠናቀቅ ባሳለፍነው ሳምንት ከመጋቢት 19 እስከ 21 ለ3 ተከታታይ ቀናት በጌቴሰማኔ ቤተ ደናግል ጠባባት የሴቶች ገዳም  የ8ኛ እና የ9ኛ ክፍል መጸሐፍትን የአርትኦት ሥራ ማካሔዱን በመንበረ ፓትሪያሪክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሓላፊ የሆኑት መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወ/ትንሣኤ ገልጸዋል። በዚህ የአርትኦት ሥራ የሊቃውንት ጉባኤ ምክትል ሐላፊ መጋቤ ምሥጢር ፍሬ ስብሐት ዱባለን ጨምሮ መምሪያው ሊቃውን ፣ የነገረ መለኮት ምሁራን ፣  የሰንበት ት/ቤቶች መምህራን እና የሥርዓተ ትምህርት ባለሞያዎች ተሳትፈዋል።
የመምሪያው ሐላፊ  እንደገለጹት የአርትኦት ሥራውን አርታኢያኑ በ3 ምድብ ተከፋፍለው የሠሩት ሲሆን  በእያንዳንዱ ምድብ ከ3-4 መጸሐፍት አርትኦት እንደተደረጉ እንዲሁም በአርትዖ ሥራው ላይ በየቡድኑ ቀርበው የነበሩ አሻሚ ጉዳዮች ላይ ሁሉም የአርትዖ ኮሚቴ ዓባላት ባሉበት በአንድነት ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸው መፍትሔ እንደተሰጣቸው ተናግረዋል።
በአርትኦት ሥራው ተሳታፊ የነበሩት ዓባላትም ቆይታቸው የተሳካ የአርትዖ ሥራውም ውጤታማ እንደነበር ገልጸዋል። በመጨረሻም በዚህ የአርትኦት ሥራ ላይ ጊዜያቸውን ሰጥተው ለተሳተፉ የአርትኦት ኮሚቴ አባላት በሙሉ የመምሪያ ሓላፊ መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወ/ትንሣኤ ምስጋናን አቅርበዋል።
👍1