የና/ደ/መ/መድኃኔዓለም ገዳምና ካቴድራል ፈለገ ጥበብ ሰ/ት/ቤት ከገዳሙና ከካቴድራሉ ሰበካ ጉባኤ በመተባባር ለገዳሙና ካቴድራሉ ማኅበረ ካህናት የሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫና የውይይት መርሐግብር አካሔድዋል፡፡ ሥልጠናው የተሰጠው ከጠቅላይ ቤተክህነት ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ዓለም አቀፍ የሰ/ት/ቤቶች አንድንት አገልጋይ በየሆኑት ቀሲስ አለማየሁ ሲሆን ከሥልጠናው በተጨማሪ ከማኅበራት ካህናት በተሰኑ ጥያቄዎች ላይ በቂ ማብራሪያና ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ ጳውሎስ መርሐግብሩን በጸሎት በማስጀመር የሥልጠናውን ዓላማውን በመግለጸ መርሐግብሩን ያስጀመሩ ሲሆን ማኅበረ ካህናቱም በሥርዓተ ትምህርቱ ተግበራ ላይ ከማስተማረ ጀምሮ በንሰሐ ልጆቻቸው በኩል ሰፊ የቅስቃሳና ሥርዓተ ትምህርቱን የማስተዋወቅ ሥራ እንዲሰሩ መመሪያ አስተላልፈዋል፡፡ በመጨረሻም መሰል ሥልጠናዎች ጠቀሜታቸው የጎላ በመሆኑ እንዲሚቀጥሉም አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡
👍5
የአንተ ሥራ
የአንተ ሥራ የአንተ ሥራ
የአንተ ሥራ ለዓለም ይወራ /2/
በዮሐንስ ወንጌል በምዕራፍ አምስት
መጻጉዕ ተብሎ ተኝቶ ባዐራት
ዘመን ያስቆጠረ ሠላሳ ስምንት
ተነሳ ተባለ አገኘ ምህረት
ሰውነቱ ደቆ እጅግ የታመመ /2/
በሱ ድንቅ ስራ አልጋ ተሸከመ /2/
ወገን ያልነበረው ወድቆ የተረሳ /2/
ምሕረት አገኘና በድንገት ተነሳ /2/
ያዳነው ኢየሱስ መሆኑን ሲናገር
ያልተፈቀደውን ይሄው ሰንበት ሲሽር
አየነው ሰማነው አያሻም ምስክር
ብለው ተነሱበት በጠማማ ምክር
ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ ወልደቂርቆስ
የአንተ ሥራ የአንተ ሥራ
የአንተ ሥራ ለዓለም ይወራ /2/
አዝ
በዮሐንስ ወንጌል በምዕራፍ አምስት
መጻጉዕ ተብሎ ተኝቶ ባዐራት
ዘመን ያስቆጠረ ሠላሳ ስምንት
ተነሳ ተባለ አገኘ ምህረት
አዝ
ሰውነቱ ደቆ እጅግ የታመመ /2/
በሱ ድንቅ ስራ አልጋ ተሸከመ /2/
አዝ
ወገን ያልነበረው ወድቆ የተረሳ /2/
ምሕረት አገኘና በድንገት ተነሳ /2/
አዝ
ያዳነው ኢየሱስ መሆኑን ሲናገር
ያልተፈቀደውን ይሄው ሰንበት ሲሽር
አየነው ሰማነው አያሻም ምስክር
ብለው ተነሱበት በጠማማ ምክር
ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ ወልደቂርቆስ
የመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተክህነት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ከማኅበረ ቅዱሳን አዳማ ማዕከል እና ማኅበራት ጥምርት ጋር በመተባባር ተግዳሮትን መቋቋምና ዕድሎችን መጠቀም በምል ርዕስ ሥልጠና ለአጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች ሥራ አመራር እና ሥራ አስፈጻሚ እንድሁም የማኅበረ ቅዱሳን አባላት ፤ግቢ ጉባኤያት እና የማኅበራት ተወካዮች በማሳተፍ ሥልጠና አሰጠ፡፡
ደብረ ዘይት (እኩለ ጾም)
"ከክብሩ ውበት ከጽዮን እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል። አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም፤ እሳት በፊት ይነዳል።" መዝ 49(50)፡2-3
መልካም ዕለተ ሰንበት!
የበረከት ጾም ያድርግልን።
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
"ከክብሩ ውበት ከጽዮን እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል። አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም፤ እሳት በፊት ይነዳል።" መዝ 49(50)፡2-3
መልካም ዕለተ ሰንበት!
የበረከት ጾም ያድርግልን።
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
የናዝሬት ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ገዳምና ካቴድራል ፈለገ ጥበብ ሰ/ት/ቤት የሥራ አመራር ልዑካን ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥር ከሚገኙ ከሦስት ሰ/ት/ቤቶችን ጋር የልምድ ልውውጥ መርሐግብር አካሔደ፡፡ የልምድ ልውውጥ መርሐግብሩ ዋና ዓላማው የተሻለ አፈጻጸም ካላቸው አቻ ሰ/ት/ቤቶች ጋር የአፈጻጸም ተሞክሮ መውሰድና ልምድ በመቅሰም የሰ/ት/ቤቱን አገልግሎቱን ማጠናከር ነው፡፡ የሰ/ት/ቤቱ የሥራ አመራር ልዑካንም ከመናገሻ ገነት ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰ/ት/ቤት፣ የመንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ ኆኅተ መንግሥተ ሰማይ ሰ/ት/ቤት እና የመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ውልደ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ጋር በሰ/ት/ቤቶቹ የማኅበራዊ አገልግሎት በተለይም በነድያን አገልግሎት፣ በሥርዓተ ትምህርት አተገባበርና በመዋቅራዊ አደረጃጀት ዙሪያ ልምድ የተወሰደ ሲሆን በተጨማሪነትም ሌሎች ልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይም ልምድ ለመውሰድ ተችሏል።
👉👉 መረጃው ከሰ/ት/ቤቱ ጽ/ቤት👈👈
👉👉 መረጃው ከሰ/ት/ቤቱ ጽ/ቤት👈👈
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
በሰንበት ት/ቤቶችማደራጀ መምሪያ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የተዘጋጀ 64 የሰንበት ት/ቤቶች የሥርዓተ ትምህርት መማሪያ መጻሕፍት ታትመው በስርጭት ላይ ልውሉ ነው።
መረጃው👇👇👇👇👇👇👇👇
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት👈👈👈
መረጃው👇👇👇👇👇👇👇👇
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት👈👈👈
👍2
የሰንበት ትምህርት ቤቶች የመማርያ መጻሕፍት ሥርጭት *****
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ ዕድሜን መሠረት ያደረገ ወጥ የሆነ ሥርዓተ ትምህርት አዘጋጅቶ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት በትግበራ ላይ ይገኛል።
ለሥርዓተ ትምህርት ትግበራውም ለረጅም ጊዜያት በቤተክርስቲያን ሊቃውንትና መምህራን እንዲሁ በሥርዓተ ትምህርት ባለሙያዎች ሲደከምበት የኖረውን የሥርዓተ ትምህርት መማርያ መጻሕፍት በባለፈው ዓመት ከ1ኛ-4ኛ ክፍል 23 የመማሪያ መጻሕፍት በማሳተም በሥርጭት ላይ ማዋሉ ይታወቃል።
በዘንድሮውም ዓመት ደግሞ በአምላካችን ቅዱስ ፈቃድ
👉 ከ1-4ኛ ክፍል 23 የኦሮምኛ ትርጉም የመማርያ መጻሕፍት በአራት ጥራዝ
👉 ከ5ኛ እስከ 7ኛ ክፍል በ3 ጥራዝ የተዘጋጁ 18 መጻሕፍት በአጠቃላይ 41 መጻሕፍት ተዘጋጅተው ለኅትመትና ለሥርጭት በቅተዋል።
ለሕዝበ ክርስቲያንም በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን፡
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ ዕድሜን መሠረት ያደረገ ወጥ የሆነ ሥርዓተ ትምህርት አዘጋጅቶ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት በትግበራ ላይ ይገኛል።
ለሥርዓተ ትምህርት ትግበራውም ለረጅም ጊዜያት በቤተክርስቲያን ሊቃውንትና መምህራን እንዲሁ በሥርዓተ ትምህርት ባለሙያዎች ሲደከምበት የኖረውን የሥርዓተ ትምህርት መማርያ መጻሕፍት በባለፈው ዓመት ከ1ኛ-4ኛ ክፍል 23 የመማሪያ መጻሕፍት በማሳተም በሥርጭት ላይ ማዋሉ ይታወቃል።
በዘንድሮውም ዓመት ደግሞ በአምላካችን ቅዱስ ፈቃድ
👉 ከ1-4ኛ ክፍል 23 የኦሮምኛ ትርጉም የመማርያ መጻሕፍት በአራት ጥራዝ
👉 ከ5ኛ እስከ 7ኛ ክፍል በ3 ጥራዝ የተዘጋጁ 18 መጻሕፍት በአጠቃላይ 41 መጻሕፍት ተዘጋጅተው ለኅትመትና ለሥርጭት በቅተዋል።
ለሕዝበ ክርስቲያንም በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን፡
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
🙏2
በምሥራቅ ሸዋ ሀ/ስብከት በመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ (አዳማ ) ወረዳ ቤተ ክህነት ስር በሚገኙ ሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርቱን እያስተማሩ ከሚገኙ መምህራን ጋር በትምህርት አተገባበሩ ዙርያ በቀን 20/07/2017 ዓ.ም ውይይት እና ስልጠና ተከናወነ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የመንበረ ጵጵስና ሰ/ት/ቤቶች አንድነት በ2014 ዓ.ም በ2 ሰ/ት/ቤቶች ብቻ የተጀመረውን የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ በማጠናከር በአሁኑ ሰዓት በከተማው በሚገኙ 26 ሰ/ት/ቤቶች እየተገበረ የሚገኝ ሲሆን ፤ ባለፉት 3 ዓመታት ለሥርዓት ት/ቱ ባለ ድርሻ አካላት ብዙ ስልጠናዎች ሰጥቷል።የዛሬው ሰልጠና በዋናነት “የማስተማር ሥነ -ዘዴ” ላይ ያተኮረ ሲሆን ፤ ስልጠናው ከመንበረ ፓትርያርክ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት በመጡት መ/ር ያረጋል ተሰጥቷል። በስልጠናው የሰ/ት/ቤት አባላት ፣ሰባኪያነ ወንጌል እና የአብነት መምህራን የተሳተፋ ሲሆን ከስልጠናው በተጨማሪ መምህራን በማስተማር ሒደቱ ያጋጠሟቸውን ችግሮች ላይ ሰፊ ውይይት ተደረጓል።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። የመንበረ ጵጵስናው ሰ/ት/ቤቶች አንድነት
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የመንበረ ጵጵስና ሰ/ት/ቤቶች አንድነት በ2014 ዓ.ም በ2 ሰ/ት/ቤቶች ብቻ የተጀመረውን የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ በማጠናከር በአሁኑ ሰዓት በከተማው በሚገኙ 26 ሰ/ት/ቤቶች እየተገበረ የሚገኝ ሲሆን ፤ ባለፉት 3 ዓመታት ለሥርዓት ት/ቱ ባለ ድርሻ አካላት ብዙ ስልጠናዎች ሰጥቷል።የዛሬው ሰልጠና በዋናነት “የማስተማር ሥነ -ዘዴ” ላይ ያተኮረ ሲሆን ፤ ስልጠናው ከመንበረ ፓትርያርክ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት በመጡት መ/ር ያረጋል ተሰጥቷል። በስልጠናው የሰ/ት/ቤት አባላት ፣ሰባኪያነ ወንጌል እና የአብነት መምህራን የተሳተፋ ሲሆን ከስልጠናው በተጨማሪ መምህራን በማስተማር ሒደቱ ያጋጠሟቸውን ችግሮች ላይ ሰፊ ውይይት ተደረጓል።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። የመንበረ ጵጵስናው ሰ/ት/ቤቶች አንድነት
👍3🙏2