በመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረደ ቤተክህነት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የተዘጋጀው የአንደኛ መንፈቀ ዓመት ማጠቃለያ ፈተና ከ1ኛ _ 5ኛ ክፍል በሁሉም አጥቢያ የተሰጠው በሰላም ተጠናቋል። የረዳን እግዚአብሔር ስሙ የተመሰገነ ይሁን
ሰንበት ቅድስት
ሰንበት ቅድስት ዕለተ ዕረፍት
የደስታ ቀን ናት ዕለተ ትፍሥሕት
የሰማይ መላእክት እግዚአብሔርን አይተው
ያመሰገኑባት ሥሉስ ቅዱስ ብለው
አዝ
በዕለተ ሰንበት ከሰማይ ወረደ
በድንግል ማኅፀን ሥጋን ተዋሐደ
ሰንበትን ቀደሳት ከዕለታት ለይቶ
ሞትን አሸንፎ ከመቃብር ወጥቶ
ኑ እናክብራት ኑ እንቀድሳት
የበዓላት በኩር ሰንበት ቅድስት ናት/2/
አዝ
ጌታ በሰንበት ነው ሥልጣኑን ያሳየ
ሰይጣንን ከሰው ልብ በቃሉ የለየ
ጎባጣ ያቀና ድውይ የፈወሰ
የስውራንን ዐይን ብርሃን የመለሰ
ኑ እናክብራት ኑ እንቀድሳት
የበዓላት በኩር ሰንበት ቅድስት ናት/2/
አዝ
ኑ በቅዳሴ በማኅሌት እናክብር
ጌታችን ሲመጣ እንዳይዘጋብን በር
የሰንበት ጌታዋ በሰንበት ይመጣል
ቅድስቷን ከተማ ለጻድቃን ያወርሳል
ኑ እናክብራት ኑ እንቀድሳት
የበዓላት በኩር ሰንበት ቅድስት ናት/2/
አዝ
ዛሬ ለምስጋና ለቁርባን መጥተናል
ለሚመጣው ሕይወት እርሱ ያዘጋጀናል
ዛሬ የሰማነው የወንጌሉ ቃል ነው
ለዘላለም ሕይወት ለክብር የሚያበቃው
ኑ እናክብራት ኑ እንቀድሳት
የበዓላት በኩር ሰንበት ቅድስት ናት/2/
ዘማሪት ሲስተር ሕይወት ተፈሪ
ሰንበት ቅድስት ዕለተ ዕረፍት
የደስታ ቀን ናት ዕለተ ትፍሥሕት
የሰማይ መላእክት እግዚአብሔርን አይተው
ያመሰገኑባት ሥሉስ ቅዱስ ብለው
አዝ
በዕለተ ሰንበት ከሰማይ ወረደ
በድንግል ማኅፀን ሥጋን ተዋሐደ
ሰንበትን ቀደሳት ከዕለታት ለይቶ
ሞትን አሸንፎ ከመቃብር ወጥቶ
ኑ እናክብራት ኑ እንቀድሳት
የበዓላት በኩር ሰንበት ቅድስት ናት/2/
አዝ
ጌታ በሰንበት ነው ሥልጣኑን ያሳየ
ሰይጣንን ከሰው ልብ በቃሉ የለየ
ጎባጣ ያቀና ድውይ የፈወሰ
የስውራንን ዐይን ብርሃን የመለሰ
ኑ እናክብራት ኑ እንቀድሳት
የበዓላት በኩር ሰንበት ቅድስት ናት/2/
አዝ
ኑ በቅዳሴ በማኅሌት እናክብር
ጌታችን ሲመጣ እንዳይዘጋብን በር
የሰንበት ጌታዋ በሰንበት ይመጣል
ቅድስቷን ከተማ ለጻድቃን ያወርሳል
ኑ እናክብራት ኑ እንቀድሳት
የበዓላት በኩር ሰንበት ቅድስት ናት/2/
አዝ
ዛሬ ለምስጋና ለቁርባን መጥተናል
ለሚመጣው ሕይወት እርሱ ያዘጋጀናል
ዛሬ የሰማነው የወንጌሉ ቃል ነው
ለዘላለም ሕይወት ለክብር የሚያበቃው
ኑ እናክብራት ኑ እንቀድሳት
የበዓላት በኩር ሰንበት ቅድስት ናት/2/
ዘማሪት ሲስተር ሕይወት ተፈሪ
በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የመንብረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተክህነት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የ2017 ዓ.ም አንደኛ መንፈቅ ዓመት ማጠቃለያ ምዘና አሰጠ፡፡
የመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተክህነት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት በወረደ ሥር ላሉ 26 አጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች ለይ በሀገረ አቀፍ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በወጠ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት በ23/06/2017 ከ1ኛ -5ኛ ክፍል እና በ30/06/2017 ዓ.ም ከ6ኛ - 9ኛ ክፍል ያሉ አዲሱን የሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት እየተገበሩ ላሉ አጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ላይ ምዘና አሰጥቷል፡፡
የመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተክህነት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት በወረደ ሥር ላሉ 26 አጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች ለይ በሀገረ አቀፍ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በወጠ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት በ23/06/2017 ከ1ኛ -5ኛ ክፍል እና በ30/06/2017 ዓ.ም ከ6ኛ - 9ኛ ክፍል ያሉ አዲሱን የሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት እየተገበሩ ላሉ አጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ላይ ምዘና አሰጥቷል፡፡
❤2👍1