ነፍሴ ሆይ
ነፍሴ ሆይ /3/ እግዚአብሔርን ባርኪ
አጥንቶቼም ሁሉ /3/ የተቀደሰ ስሙን
በደስታ ዘምሪ በአዲስ ምስጋና
ጸጥታ እና ሰላም አድሎሻልና
መሠንቆውን አንሺ ቅኔ ተቀኚለት
ለውጦሻልና በደስታ ዘይት
ሀሴትን አድርጊ ነፍሴ በእግዚአብሔር
ይሰጥሻልና በክብር ላይ ክብር
ደሴቶች ሲያወሩ በደስታ መንፈስ
እየተወያዩ ስለ ሥሉስ ቅዱስ
ሰማያት ሲያወሩ ጽድቅን ሲወያዩ
ሲጠራው አድምጪ ቀላዩን ቀላዩ
ደመናው ጭጋጉ በዙሪያው ከበውት
ቅኔ ያቀርባሉ ለፍጥረታት አባት
መብረቅም ይሰማል ሰማዩን ሰንጥቆ
ምስጋናውን ሊያቀርብ ጊዜውን ጠብቆ
በፊቱ ይነዳል እሳትም በግርማ
ምድር ተናወጠች ነጎድጓዱን ሰምታ
ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ
ነፍሴ ሆይ /3/ እግዚአብሔርን ባርኪ
አጥንቶቼም ሁሉ /3/ የተቀደሰ ስሙን
በደስታ ዘምሪ በአዲስ ምስጋና
ጸጥታ እና ሰላም አድሎሻልና
መሠንቆውን አንሺ ቅኔ ተቀኚለት
ለውጦሻልና በደስታ ዘይት
አዝ
ሀሴትን አድርጊ ነፍሴ በእግዚአብሔር
ይሰጥሻልና በክብር ላይ ክብር
ደሴቶች ሲያወሩ በደስታ መንፈስ
እየተወያዩ ስለ ሥሉስ ቅዱስ
አዝ
ሰማያት ሲያወሩ ጽድቅን ሲወያዩ
ሲጠራው አድምጪ ቀላዩን ቀላዩ
ደመናው ጭጋጉ በዙሪያው ከበውት
ቅኔ ያቀርባሉ ለፍጥረታት አባት
አዝ
መብረቅም ይሰማል ሰማዩን ሰንጥቆ
ምስጋናውን ሊያቀርብ ጊዜውን ጠብቆ
በፊቱ ይነዳል እሳትም በግርማ
ምድር ተናወጠች ነጎድጓዱን ሰምታ
ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ
የ2017 ዓ.ም የአንጀኛ ዓመት የመንፈቀ ትምህርት ማጠቃለያ ፈተና የቅድመ ዝግጅት ሥራ መጠናቀቁ ተገለጸ፡፡
*******
የካቲት 20 ቀን 2017 ዓ.ም
ሐመረ ተዋሕዶ ሚዲያ /Hamere Tewahedo Media
Adama, Ethiopia
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተ ክህነት ሥር የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አንደኛ መንፈቀ ዓመት ማጠቃለያ ፈተና በወረዳው በሚገኙ ካቴድራል አድባራትና ገዳማት ለመስጠት የቅድመ ዝግጅት ሥራ መጠናቀቁን ገለጸ፡፡
በሥርዓተ ትምህርቱ መሠረት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ ከ6960 በላይ ( ከስድስት ሺህ ዘጠኝ መቶ ስልሳ ተማሪዎች በሃያ ስድስቱም አብያተ ክርስቲያናት የሀገር አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ባወጣው የጊዜ ሠሌዳ መሠረት ሲሆን:-
👉 ከ1ኛ-5ኛ ክፍል የካቲት 23 ቀን 2017 ዓ.ም
- ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት
ከ6ኛ-9ኛ ክፍል የካቲት 30 ቀን/ 2017 ዓ.ም
- ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት
በአፋን ኦሮሞ እና በአማረኛ እንደሚሰጥ የመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተ ክህነት የሰንበት ት/አንድነት ጽ/ቤት ለሚዲያችን ገልጿል።
#ኢትዮጵያ #ኦርቶዶክስ #ተዋሕዶ #ቤተክርስቲያን #ሰንበት #ትምህርት #ቤት #አዳማ
*******
የካቲት 20 ቀን 2017 ዓ.ም
ሐመረ ተዋሕዶ ሚዲያ /Hamere Tewahedo Media
Adama, Ethiopia
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተ ክህነት ሥር የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አንደኛ መንፈቀ ዓመት ማጠቃለያ ፈተና በወረዳው በሚገኙ ካቴድራል አድባራትና ገዳማት ለመስጠት የቅድመ ዝግጅት ሥራ መጠናቀቁን ገለጸ፡፡
በሥርዓተ ትምህርቱ መሠረት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ ከ6960 በላይ ( ከስድስት ሺህ ዘጠኝ መቶ ስልሳ ተማሪዎች በሃያ ስድስቱም አብያተ ክርስቲያናት የሀገር አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ባወጣው የጊዜ ሠሌዳ መሠረት ሲሆን:-
👉 ከ1ኛ-5ኛ ክፍል የካቲት 23 ቀን 2017 ዓ.ም
- ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት
ከ6ኛ-9ኛ ክፍል የካቲት 30 ቀን/ 2017 ዓ.ም
- ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት
በአፋን ኦሮሞ እና በአማረኛ እንደሚሰጥ የመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተ ክህነት የሰንበት ት/አንድነት ጽ/ቤት ለሚዲያችን ገልጿል።
#ኢትዮጵያ #ኦርቶዶክስ #ተዋሕዶ #ቤተክርስቲያን #ሰንበት #ትምህርት #ቤት #አዳማ
👍5
በመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረደ ቤተክህነት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የተዘጋጀው የአንደኛ መንፈቀ ዓመት ማጠቃለያ ፈተና ከ1ኛ _ 5ኛ ክፍል በሁሉም አጥቢያ የተሰጠው በሰላም ተጠናቋል። የረዳን እግዚአብሔር ስሙ የተመሰገነ ይሁን
ሰንበት ቅድስት
ሰንበት ቅድስት ዕለተ ዕረፍት
የደስታ ቀን ናት ዕለተ ትፍሥሕት
የሰማይ መላእክት እግዚአብሔርን አይተው
ያመሰገኑባት ሥሉስ ቅዱስ ብለው
አዝ
በዕለተ ሰንበት ከሰማይ ወረደ
በድንግል ማኅፀን ሥጋን ተዋሐደ
ሰንበትን ቀደሳት ከዕለታት ለይቶ
ሞትን አሸንፎ ከመቃብር ወጥቶ
ኑ እናክብራት ኑ እንቀድሳት
የበዓላት በኩር ሰንበት ቅድስት ናት/2/
አዝ
ጌታ በሰንበት ነው ሥልጣኑን ያሳየ
ሰይጣንን ከሰው ልብ በቃሉ የለየ
ጎባጣ ያቀና ድውይ የፈወሰ
የስውራንን ዐይን ብርሃን የመለሰ
ኑ እናክብራት ኑ እንቀድሳት
የበዓላት በኩር ሰንበት ቅድስት ናት/2/
አዝ
ኑ በቅዳሴ በማኅሌት እናክብር
ጌታችን ሲመጣ እንዳይዘጋብን በር
የሰንበት ጌታዋ በሰንበት ይመጣል
ቅድስቷን ከተማ ለጻድቃን ያወርሳል
ኑ እናክብራት ኑ እንቀድሳት
የበዓላት በኩር ሰንበት ቅድስት ናት/2/
አዝ
ዛሬ ለምስጋና ለቁርባን መጥተናል
ለሚመጣው ሕይወት እርሱ ያዘጋጀናል
ዛሬ የሰማነው የወንጌሉ ቃል ነው
ለዘላለም ሕይወት ለክብር የሚያበቃው
ኑ እናክብራት ኑ እንቀድሳት
የበዓላት በኩር ሰንበት ቅድስት ናት/2/
ዘማሪት ሲስተር ሕይወት ተፈሪ
ሰንበት ቅድስት ዕለተ ዕረፍት
የደስታ ቀን ናት ዕለተ ትፍሥሕት
የሰማይ መላእክት እግዚአብሔርን አይተው
ያመሰገኑባት ሥሉስ ቅዱስ ብለው
አዝ
በዕለተ ሰንበት ከሰማይ ወረደ
በድንግል ማኅፀን ሥጋን ተዋሐደ
ሰንበትን ቀደሳት ከዕለታት ለይቶ
ሞትን አሸንፎ ከመቃብር ወጥቶ
ኑ እናክብራት ኑ እንቀድሳት
የበዓላት በኩር ሰንበት ቅድስት ናት/2/
አዝ
ጌታ በሰንበት ነው ሥልጣኑን ያሳየ
ሰይጣንን ከሰው ልብ በቃሉ የለየ
ጎባጣ ያቀና ድውይ የፈወሰ
የስውራንን ዐይን ብርሃን የመለሰ
ኑ እናክብራት ኑ እንቀድሳት
የበዓላት በኩር ሰንበት ቅድስት ናት/2/
አዝ
ኑ በቅዳሴ በማኅሌት እናክብር
ጌታችን ሲመጣ እንዳይዘጋብን በር
የሰንበት ጌታዋ በሰንበት ይመጣል
ቅድስቷን ከተማ ለጻድቃን ያወርሳል
ኑ እናክብራት ኑ እንቀድሳት
የበዓላት በኩር ሰንበት ቅድስት ናት/2/
አዝ
ዛሬ ለምስጋና ለቁርባን መጥተናል
ለሚመጣው ሕይወት እርሱ ያዘጋጀናል
ዛሬ የሰማነው የወንጌሉ ቃል ነው
ለዘላለም ሕይወት ለክብር የሚያበቃው
ኑ እናክብራት ኑ እንቀድሳት
የበዓላት በኩር ሰንበት ቅድስት ናት/2/
ዘማሪት ሲስተር ሕይወት ተፈሪ