የአዳማ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት
1.11K subscribers
1.76K photos
24 videos
22 files
227 links
ይሄ የቴሌግራም ገፅ በምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተክህነተ በሰ/ት/ቤቶች አንድነት የተከፈተ ሲሆን በዚህ ቻናል መንፈሳዊ ትምህርቶችን፣ ዜና ቤተክርስቲያንና ወቅታዊ ጉዳይ የምንዘግብበት ነው። እርሶም ለኦርትዶክሳውያን ሁሉ ቻናሉን በማጋራት ለቅድስት ቤተክርስቲያን ድምጽ ይሁኑ።
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን!
Download Telegram
"ጾምን የምንጾመው  ዲያብሎስንና ግብረ ኃጢአትን ለማሸነፍ  ነው::" ቅዱስነታቸው

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የ2017 ዓ.ም የዐቢይ ጾምን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ !

የካቲት 15 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ /አዲስ አበባ)

ቅዱስነታቸው በመልእክታቸው መነሻ <<ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፈለገ ዮርዳኖስ ከተጠመቀ በኋላ ሳይውል ሳያድር ወዲያውኑ ወደ በረኻ በመሄድ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾመ፡፡>> በማለት የጌታችንና አምላካችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመጾሙን ጥንተ ነገር አውስተዋል።

ቅዱስነታቸው በአርባ ቀናት ውስጥ የጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በዲያቢሎስ መፈተንና ድል መንሳትም አብራርተው  ሲያወሱ <<በዚህ ጊዜ የጌታችን መልስ “ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ ኣይኖርም” የሚል ነበረ፤
ጌታችን በዚህ አባባሉ የዲያብሎስን ክፉ ሐሳብ የሚንድ እንጂ የእሱ ታዛዥ አለመሆኑን ኣሳየ፤ ዲያብሎስ በዚህ ሳያበቃ በትዕቢት በፍቅረ ንዋይና በባዕድ አምልኮ ሊጥለው ደጋግሞ ሙከራ አደረገ፤ ግን አልተሳካለትም፤>> ብለዋል።

ቅዱስነታቸው የመጾማችንን ምክንያት ሲያጠይቁ <<...የዲያብሎስን ፈተናዎች እንዴት በድል ማለፍ እንደምንችል ጌታችን በተግባር ኣሳይቶናል፤ ጌታችን ዲያብሎስን ያሸነበፈበት ስልት በመንፈስ ልዕልና እንጂ በዱላም፣ በካባድ መሳሪያም ኣይደለም፤ አለመሆኑንም የድርጊቱ ሂደት በግልጽ ያመለክታል፤ እንግዲያውስ እኛም ዲያብሎስን የምናሸንፈው በዚህ የመንፈስ  ልዕልና ነው ማለት ነው::... ስለሆነም ጾምን የምንጾመው በዚህ ስልት ዲያብሎስንና ግብረ ኃጢአትን ለማሸነፍ  ነው::
ከዚህ አኳያ ዲያብሎስን ለማሸነፍ መጾም ግድ ስለሆነ ጌታችን በከፈተልንና ባሳየን መንገድ እንጾማለን>> ብለዋል።

ስንጾምም <<የምንጾመው መልካም ኅሊና ኖሮን ለእግዚአብሔር ለመታዘዝና ለመገዛት፣ ከዚያም ከቃሉ በተነገረን መሠረት የተራቡትን ልንመግብ፣ የተራቈቱትን ልናለብስ፣ የተጣሉትን ልናስታርቅ፣ ፍትሕ ያጡትን ፍትሕ እንዲያገኙ ልናደርግ፣ ለንኡሳን የሕብረተ ሰብ ክፍሎች የተለየ ትኵረት ልንሰጥ፤ እኩልና ፍትሓዊ የሀብት ክፍፍል በሰው ልጆች መካከል ልናረጋግጥ፣ ሰብኣዊ ክብር እንዳይነካ ጦርነት፣ ጥላቻ፣ አደገኛ የቃላት ውርወራና መነቃቀፍ እንዲቀር ልናደርግ ነው፤>> በማለት አጽንዖት ሰጥተው አባታዊ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ጾም የሥጋ ምኞትን የምታጠፋ የነፍስን ቁስል የምታደርቅ  ለጎልማሶችም ጸጥታንና እርጋታን የምታስተምር ደገኛ ሥርዓት ነች፡፡
👍2
ዘወረደ
ዘወረደ ማለት "ከላይ የመጣ፣ የወረደ'' ማለት ነው።  ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን "ዘወረደ እምላዕሉ አይሁድ ሰቀሉ ወሚመ ኢያእመሩ እግዚአ ኩሉ ዘየሐዩ፤ አዳምን ለማዳን ከሰማይ የወረደውን አምላክ አይሁድ ሰቀሉት፤ የሰማይ ሥልጣን ያለው የሁሉ ጌታ እንደሆነም ምንም አላወቁም"  እያለች በሰንበት ዋዜማ ዜማውን መሐትው (መግቢያ) አድርጋ የሳምንቱን ዜማ በማስተጋባት የጌታችንን ከሰማይ መውረድ ታመሠጥርበታለች፤ ታመሰግንበታለች። (ጾመ ድጓ፥ ዘዘወረደ ዋዜማ)
ይህን ሳምንት በልዕልና በዘለዓለማዊ ቅድስና እና በማትመረመር ጥበብ ራሱን ሰውሮ የሚኖር አምላክ በገሃድ  ለሰው ልጅ የተገለጠበትን፣ ዘለዓለማዊ አምላክ ሰውን ከተደበቀበት  ለመፈለግ ብሎ ''ኦ አዳም አይቴ ሀሎከ- አዳም ሆይ ወዴት ነህ" እያለ በማያልቅ የፍቅር ድምፅ ፍለጋ ወደ ዱር (ወደ ዓለም) የገባበትን ሳምንት የምንዘክርበት ነው። አምላካችን እግዚአብሔር የሰውን ልጅ ምን ያህል በበዛ ፍቅሩ እንደሚፈልገው፣ ከፍ ላለ ዓላማውም እንዳጨው ያሳየበት፣ ከሁሉም ደግሞ በሕሊና ሊታሰብ የማይችለውን የሰማይ አኗኗሩን ትቶ በሚታይ የአዳም ሥጋ የተገለጠበት፣ መጋረጃው እሳት፣ ዙፋኑ እሳት፣ ልብሱ እሳት የሆነው አምላክ በሚበሰብስ ሥጋ የተገለጠበት፣ በጨርቅ፣ ያንን የሚያስደነግጥ መለኮታዊ ክብሩን ስለ ሰው ልጅ መዳን ተጨንቆ በሕፃን አምሳል ተገልጦ በበረት የተገኘበትን ሳምንት እናስብበታለን።
🙏3
ነፍሴ ሆይ

ነፍሴ ሆይ /3/ እግዚአብሔርን ባርኪ
አጥንቶቼም ሁሉ /3/ የተቀደሰ ስሙን

በደስታ ዘምሪ በአዲስ ምስጋና
ጸጥታ እና ሰላም አድሎሻልና
መሠንቆውን አንሺ ቅኔ ተቀኚለት
ለውጦሻልና በደስታ ዘይት
አዝ

ሀሴትን አድርጊ ነፍሴ በእግዚአብሔር
ይሰጥሻልና በክብር ላይ ክብር
ደሴቶች ሲያወሩ በደስታ መንፈስ
እየተወያዩ ስለ ሥሉስ ቅዱስ
አዝ

ሰማያት ሲያወሩ ጽድቅን ሲወያዩ
ሲጠራው አድምጪ ቀላዩን ቀላዩ
ደመናው ጭጋጉ በዙሪያው ከበውት
ቅኔ ያቀርባሉ ለፍጥረታት አባት
አዝ

መብረቅም ይሰማል ሰማዩን ሰንጥቆ
ምስጋናውን ሊያቀርብ ጊዜውን ጠብቆ
በፊቱ ይነዳል እሳትም በግርማ
ምድር ተናወጠች ነጎድጓዱን ሰምታ

ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ
የ2017 ዓ.ም የአንጀኛ ዓመት የመንፈቀ ትምህርት ማጠቃለያ ፈተና የቅድመ ዝግጅት ሥራ መጠናቀቁ ተገለጸ፡፡
*******

የካቲት 20 ቀን 2017 ዓ.ም
ሐመረ ተዋሕዶ ሚዲያ /Hamere Tewahedo Media
Adama, Ethiopia

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተ ክህነት ሥር የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አንደኛ መንፈቀ ዓመት ማጠቃለያ ፈተና በወረዳው በሚገኙ ካቴድራል አድባራትና ገዳማት ለመስጠት የቅድመ ዝግጅት ሥራ መጠናቀቁን ገለጸ፡፡

በሥርዓተ ትምህርቱ መሠረት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ ከ6960 በላይ ( ከስድስት ሺህ ዘጠኝ መቶ ስልሳ ተማሪዎች በሃያ ስድስቱም አብያተ ክርስቲያናት የሀገር አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ባወጣው የጊዜ ሠሌዳ መሠረት ሲሆን:-

👉 ከ1ኛ-5ኛ ክፍል የካቲት 23 ቀን 2017 ዓ.ም
- ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት
ከ6ኛ-9ኛ ክፍል የካቲት 30 ቀን/ 2017 ዓ.ም
- ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት

በአፋን ኦሮሞ እና በአማረኛ እንደሚሰጥ የመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተ ክህነት የሰንበት ት/አንድነት ጽ/ቤት ለሚዲያችን ገልጿል።

#ኢትዮጵያ #ኦርቶዶክስ #ተዋሕዶ #ቤተክርስቲያን #ሰንበት #ትምህርት #ቤት #አዳማ
👍5
እንኳን ለአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

"በአንተ ጠላቶቻችንን እንወጋቸዋለን፥ በስምህም በላያችን የቆሙትን እናዋርዳቸዋለን።
በቀስቴ የምታመን አይደለሁምና፥ ሰይፌም አያድነኝምና፤ አንተ ግን ከጠላቶቻችን አዳንኸን፥
የሚጠሉንንም አሳፈርሃቸው።" መዝ 43(44) ፡ 5 - 7

መልካም በዓል!

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!

(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
በመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረደ ቤተክህነት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የተዘጋጀው የአንደኛ መንፈቀ ዓመት ማጠቃለያ ፈተና ከ1ኛ _ 5ኛ ክፍል በሁሉም አጥቢያ የተሰጠው በሰላም ተጠናቋል። የረዳን እግዚአብሔር ስሙ የተመሰገነ ይሁን
የና/ደ/ቤቴል ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ዓምደ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት አንደኛው መንፈቀ ዓመት ማጠቃለያ ፈተና
👍3