የአዳማ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት
1.11K subscribers
1.76K photos
24 videos
22 files
227 links
ይሄ የቴሌግራም ገፅ በምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተክህነተ በሰ/ት/ቤቶች አንድነት የተከፈተ ሲሆን በዚህ ቻናል መንፈሳዊ ትምህርቶችን፣ ዜና ቤተክርስቲያንና ወቅታዊ ጉዳይ የምንዘግብበት ነው። እርሶም ለኦርትዶክሳውያን ሁሉ ቻናሉን በማጋራት ለቅድስት ቤተክርስቲያን ድምጽ ይሁኑ።
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን!
Download Telegram
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
በኢትዮጵያ ኦርዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የመንበረ ጵጵስና ወረዳ ቤተ ክህነት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት የ2017 ዓ/ም አንደኛ መንፈቅ ዓመት ማጠቃለይ ፈተና በሃያ አምስት (25) አጥቢያ ሰ/ት/ቤት ከስድስት ሺ ስምንት መቶ ዘጠና ሶስት(6893) በላይ ሥርዓተ ትምህርቱን ሲማሩ የነበሩ ተማሪዎችን ለማስፈተን ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡ፈተና የሚሰጠው በሀገር አቀፍ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ሲሆን ቀድሞ ከአጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች የትምህርት አፈጻጸም እና ስልጠና ክፍሎች ጋር የፈተና ዝግጅትና እና አሰጣት ዙሪያ ውይይት አድርጓል፡፡ በዚህም መሠረት በሁሉም አጥቢያ ሰ/ት/ቤት ከ1ኛ ክፍል እስከ 5ኛ ክፍል  የካቲት 23/2017 ዓ/ም ከጠዋት 4፡00 ጀምሮ የሚሰጥ ሲሆን ከ6ኛ ክፍል እስከ 9ኛ ክፍል የካቲት 30/2017 ዓ/ም ከጠዋት 4:00 ጀምሮ የሚሰጥ ይሆናል፡፡
ሥርዓተ ትምህርቱ በሁለት ቋንቋ እየተሰጠ ሲሆን በአማርኛ ቋንቋ፡-
1ኛ ክፍል……….1532 
2ኛ ክፍክ…………884
3ኛ ክፍል………..560
4ኛ ክፍል………..792
5ኛ ክፍል………..346
6ኛ ክፍል…………455
7ኛ ክፍል…………942
8ኛ ክፍል………….611
9ኛ ክፍል………….403
በአጠቃላይ 6525 ሲሆን እንዲሁም በአፋን ኦሮሞ ቋንቋ፡-
1ኛ ክፍል………112
2ኛ ክፍል………..46
6ኛ ክፍል………..19
7ኛ ክፍል………191
የሚፈተኑ ሲሆን በአጠቃላይ 368 ተማሪዎች በአፋን ኦሮሞ ቋንቋ ይፈተናሉ፡፡
ስለሆነም የቤተክርስቲያን አስተዳዳሪዎች፣ካህናት አባቶች፣ሰባኪያን ወንጌል መምህራኖች እና የተማሪ ወላጅ ቤተሰቦች ይህንን የፈተናው መርሐ ግብር በተሳካ ሁኔታ እንዲሰጥ ከሰ/ት/ቤቱ ጎን በመሆን እንድታግዙ ስንል ሰ/ት/ቤት አንድነቱ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
👍62🤔1
👍5
🎤🎤🎤መልካም ዜና ❤️❤️❤️❤️
የሥርዓተ ትምህርት መመሪያ መጽሐፍት 🔔🔹 ከ 1ኛ_4ኛ ክፍል በኦሮምኛ ቋንቋ
🔷🔷ከ5ኛ _7ኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ ሕትመቱ ተጠናቋል ።
👍3
🎤🙏❤️ Oduu Gammachisaa🌷❤️🙏
Kitaabni Sirna Barnoota Barattoota Dilbataa kan kutaa
1ffaa_4ffaa Afaan Oromoon
Kutaa 5ffaa_7ffaa Afaan Amaariffaan qophaa'ee maxxansi isaa dhumee jira.
የግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት  የአገልጋይ እጦት እንደገጠመው ተገለጸ።

የመንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት የሚገኙ አባላት የልማት ተነሺዎች መሆናቸው አገልግሎቱን እንዳሰተጓጎለውም ተጠቁሟል። 

አቶ ዘውዱ ከተማ የሰንበት ትምህርት ቤቱ ሰብሳቢ ከማኀበረ ቅዱሳን የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር ባደረጉት ቆይታ በአካባቢው የሚኖር ሰውና ምእመን በመቀነሱ ሳምንታዊ ፕሮግራሞችን ወደ ወርሀዊ የመቀየር፣ሕጻናት ባሉበት ሆነው እንዲማሩ ዕድሉን እንዲያገኙ የማመቻቸት እና የኦላይን ትምህርቶችን ለመስጠት ሥራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ 

የሰንበት ትምህርት ቤቱ አባላቱ በኢኮኖሚያዊ፣በማኅበራዊ ጉዳዮች በተለይም በሃይማኖታዊ አንጻር ቃለ እግዚአብሔር እንዳይሰሙ ጫና እንደደረሰባቸው የሰንበት ትምህርት ቤቱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ዘነበ ክፍሉ ተናግረዋል።

በአገልጋይ እጦት ምክንያት አንዳንድ ክፍሎች መታጣፋቸውን የሰንበት ትምህርት ቤቱ አባል የሆኑት መቅደላዊት ተሾመ የተናገሩ ሲሆን ያሉትም ጥቂት አባላቶች ክፍሎችን ደርበው እንዲያገለግሉ እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

በዚህም ችግሩን ለማቃለል በገዳሙ ውስጥ የሚገኙ አባቶችን በመጠቀም የሰንበት ትምህርት ቤት አባላቱ እንዲመጡ ቅስቀሳ የማካሄድ እና በወር አንድ ጊዜ ጉባኤ በማዘጋጀት እንዲሳተፉ እየተደረገ መሆኑን አባሏ አንስተዋል፡፡

ዘገባው የማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት ነው።
😢4👍2
"ጾምን የምንጾመው  ዲያብሎስንና ግብረ ኃጢአትን ለማሸነፍ  ነው::" ቅዱስነታቸው

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የ2017 ዓ.ም የዐቢይ ጾምን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ !

የካቲት 15 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ /አዲስ አበባ)

ቅዱስነታቸው በመልእክታቸው መነሻ <<ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፈለገ ዮርዳኖስ ከተጠመቀ በኋላ ሳይውል ሳያድር ወዲያውኑ ወደ በረኻ በመሄድ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾመ፡፡>> በማለት የጌታችንና አምላካችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመጾሙን ጥንተ ነገር አውስተዋል።

ቅዱስነታቸው በአርባ ቀናት ውስጥ የጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በዲያቢሎስ መፈተንና ድል መንሳትም አብራርተው  ሲያወሱ <<በዚህ ጊዜ የጌታችን መልስ “ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ ኣይኖርም” የሚል ነበረ፤
ጌታችን በዚህ አባባሉ የዲያብሎስን ክፉ ሐሳብ የሚንድ እንጂ የእሱ ታዛዥ አለመሆኑን ኣሳየ፤ ዲያብሎስ በዚህ ሳያበቃ በትዕቢት በፍቅረ ንዋይና በባዕድ አምልኮ ሊጥለው ደጋግሞ ሙከራ አደረገ፤ ግን አልተሳካለትም፤>> ብለዋል።

ቅዱስነታቸው የመጾማችንን ምክንያት ሲያጠይቁ <<...የዲያብሎስን ፈተናዎች እንዴት በድል ማለፍ እንደምንችል ጌታችን በተግባር ኣሳይቶናል፤ ጌታችን ዲያብሎስን ያሸነበፈበት ስልት በመንፈስ ልዕልና እንጂ በዱላም፣ በካባድ መሳሪያም ኣይደለም፤ አለመሆኑንም የድርጊቱ ሂደት በግልጽ ያመለክታል፤ እንግዲያውስ እኛም ዲያብሎስን የምናሸንፈው በዚህ የመንፈስ  ልዕልና ነው ማለት ነው::... ስለሆነም ጾምን የምንጾመው በዚህ ስልት ዲያብሎስንና ግብረ ኃጢአትን ለማሸነፍ  ነው::
ከዚህ አኳያ ዲያብሎስን ለማሸነፍ መጾም ግድ ስለሆነ ጌታችን በከፈተልንና ባሳየን መንገድ እንጾማለን>> ብለዋል።

ስንጾምም <<የምንጾመው መልካም ኅሊና ኖሮን ለእግዚአብሔር ለመታዘዝና ለመገዛት፣ ከዚያም ከቃሉ በተነገረን መሠረት የተራቡትን ልንመግብ፣ የተራቈቱትን ልናለብስ፣ የተጣሉትን ልናስታርቅ፣ ፍትሕ ያጡትን ፍትሕ እንዲያገኙ ልናደርግ፣ ለንኡሳን የሕብረተ ሰብ ክፍሎች የተለየ ትኵረት ልንሰጥ፤ እኩልና ፍትሓዊ የሀብት ክፍፍል በሰው ልጆች መካከል ልናረጋግጥ፣ ሰብኣዊ ክብር እንዳይነካ ጦርነት፣ ጥላቻ፣ አደገኛ የቃላት ውርወራና መነቃቀፍ እንዲቀር ልናደርግ ነው፤>> በማለት አጽንዖት ሰጥተው አባታዊ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ጾም የሥጋ ምኞትን የምታጠፋ የነፍስን ቁስል የምታደርቅ  ለጎልማሶችም ጸጥታንና እርጋታን የምታስተምር ደገኛ ሥርዓት ነች፡፡