የአዳማ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት
1.12K subscribers
1.76K photos
24 videos
22 files
227 links
ይሄ የቴሌግራም ገፅ በምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተክህነተ በሰ/ት/ቤቶች አንድነት የተከፈተ ሲሆን በዚህ ቻናል መንፈሳዊ ትምህርቶችን፣ ዜና ቤተክርስቲያንና ወቅታዊ ጉዳይ የምንዘግብበት ነው። እርሶም ለኦርትዶክሳውያን ሁሉ ቻናሉን በማጋራት ለቅድስት ቤተክርስቲያን ድምጽ ይሁኑ።
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን!
Download Telegram
ብፁዕ አባታችን አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምና ሥራ አመራር መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ኃላፊ የቅዱስ ሲኖዶስ ቋሚ አባል እንዲሁም  የኢትዮጵያ ሃይማኖቶች ተቋማት የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሰብሳቢ ለአዳማ ናዝሬት ደብረ ሰላም ካቴድራል የፈለገ ሰላም ዘመላዕክት ሰንበት ትምህርት ቤት የሚገነባውን ህንፃ የመሰረት ድንጋይ ጥለዋል።
👍1
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
በኢትዮጵያ ኦርዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የመንበረ ጵጵስና ወረዳ ቤተ ክህነት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት የ2017 ዓ/ም አንደኛ መንፈቅ ዓመት ማጠቃለይ ፈተና በሃያ አምስት (25) አጥቢያ ሰ/ት/ቤት ከስድስት ሺ ስምንት መቶ ዘጠና ሶስት(6893) በላይ ሥርዓተ ትምህርቱን ሲማሩ የነበሩ ተማሪዎችን ለማስፈተን ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡ፈተና የሚሰጠው በሀገር አቀፍ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ሲሆን ቀድሞ ከአጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች የትምህርት አፈጻጸም እና ስልጠና ክፍሎች ጋር የፈተና ዝግጅትና እና አሰጣት ዙሪያ ውይይት አድርጓል፡፡ በዚህም መሠረት በሁሉም አጥቢያ ሰ/ት/ቤት ከ1ኛ ክፍል እስከ 5ኛ ክፍል  የካቲት 23/2017 ዓ/ም ከጠዋት 4፡00 ጀምሮ የሚሰጥ ሲሆን ከ6ኛ ክፍል እስከ 9ኛ ክፍል የካቲት 30/2017 ዓ/ም ከጠዋት 4:00 ጀምሮ የሚሰጥ ይሆናል፡፡
ሥርዓተ ትምህርቱ በሁለት ቋንቋ እየተሰጠ ሲሆን በአማርኛ ቋንቋ፡-
1ኛ ክፍል……….1532 
2ኛ ክፍክ…………884
3ኛ ክፍል………..560
4ኛ ክፍል………..792
5ኛ ክፍል………..346
6ኛ ክፍል…………455
7ኛ ክፍል…………942
8ኛ ክፍል………….611
9ኛ ክፍል………….403
በአጠቃላይ 6525 ሲሆን እንዲሁም በአፋን ኦሮሞ ቋንቋ፡-
1ኛ ክፍል………112
2ኛ ክፍል………..46
6ኛ ክፍል………..19
7ኛ ክፍል………191
የሚፈተኑ ሲሆን በአጠቃላይ 368 ተማሪዎች በአፋን ኦሮሞ ቋንቋ ይፈተናሉ፡፡
ስለሆነም የቤተክርስቲያን አስተዳዳሪዎች፣ካህናት አባቶች፣ሰባኪያን ወንጌል መምህራኖች እና የተማሪ ወላጅ ቤተሰቦች ይህንን የፈተናው መርሐ ግብር በተሳካ ሁኔታ እንዲሰጥ ከሰ/ት/ቤቱ ጎን በመሆን እንድታግዙ ስንል ሰ/ት/ቤት አንድነቱ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
👍62🤔1
👍5
🎤🎤🎤መልካም ዜና ❤️❤️❤️❤️
የሥርዓተ ትምህርት መመሪያ መጽሐፍት 🔔🔹 ከ 1ኛ_4ኛ ክፍል በኦሮምኛ ቋንቋ
🔷🔷ከ5ኛ _7ኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ ሕትመቱ ተጠናቋል ።
👍3
🎤🙏❤️ Oduu Gammachisaa🌷❤️🙏
Kitaabni Sirna Barnoota Barattoota Dilbataa kan kutaa
1ffaa_4ffaa Afaan Oromoon
Kutaa 5ffaa_7ffaa Afaan Amaariffaan qophaa'ee maxxansi isaa dhumee jira.
የግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት  የአገልጋይ እጦት እንደገጠመው ተገለጸ።

የመንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት የሚገኙ አባላት የልማት ተነሺዎች መሆናቸው አገልግሎቱን እንዳሰተጓጎለውም ተጠቁሟል። 

አቶ ዘውዱ ከተማ የሰንበት ትምህርት ቤቱ ሰብሳቢ ከማኀበረ ቅዱሳን የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር ባደረጉት ቆይታ በአካባቢው የሚኖር ሰውና ምእመን በመቀነሱ ሳምንታዊ ፕሮግራሞችን ወደ ወርሀዊ የመቀየር፣ሕጻናት ባሉበት ሆነው እንዲማሩ ዕድሉን እንዲያገኙ የማመቻቸት እና የኦላይን ትምህርቶችን ለመስጠት ሥራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ 

የሰንበት ትምህርት ቤቱ አባላቱ በኢኮኖሚያዊ፣በማኅበራዊ ጉዳዮች በተለይም በሃይማኖታዊ አንጻር ቃለ እግዚአብሔር እንዳይሰሙ ጫና እንደደረሰባቸው የሰንበት ትምህርት ቤቱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ዘነበ ክፍሉ ተናግረዋል።

በአገልጋይ እጦት ምክንያት አንዳንድ ክፍሎች መታጣፋቸውን የሰንበት ትምህርት ቤቱ አባል የሆኑት መቅደላዊት ተሾመ የተናገሩ ሲሆን ያሉትም ጥቂት አባላቶች ክፍሎችን ደርበው እንዲያገለግሉ እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

በዚህም ችግሩን ለማቃለል በገዳሙ ውስጥ የሚገኙ አባቶችን በመጠቀም የሰንበት ትምህርት ቤት አባላቱ እንዲመጡ ቅስቀሳ የማካሄድ እና በወር አንድ ጊዜ ጉባኤ በማዘጋጀት እንዲሳተፉ እየተደረገ መሆኑን አባሏ አንስተዋል፡፡

ዘገባው የማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት ነው።
😢4👍2