በአዳማ ቦኩ ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የፈለገ ምህረት ሰንበት ትምህርት ቤት የነዳያን ምገባ መርሃግብር አከናወነ፦ ሰንበት ትምህርት ቤቱ በየአመቱ የዳግማትንሳኤ ዕለት እንደሚያደርገው ዘንድሮም ከበጎ አድራጊ ክርስቲያኖች ሰብስቦ በአጥቢያው ያሉ ነዳያንን፣ በከርቸሌ የሚገኙ እስረኞችን፣ በአርቱ አርሴማ የሚገኙ ፀበልተኞችን እና ሌሎችንም የተቸገሩ የታመሙ ወገኖችን ምግብ በማዘጋጀት መግቧል። ይሄ መልካም ስራ ለሚቀጥሉት አመታትም የሚቀጥል ይሆናል የዓመት ሰው ይበለን። አሜን
በአዳማ ናዝሬት ደብረ ታቦር ምስራቀ ፀሀይ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤተክርስቲያን የፈለገ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት የነዳያን ምገባ መርሃግብር አከናወነ፦ ሰንበት ትምህርት ቤቱ በየአመቱ የትንሳኤ ዕለት እንደሚያደርገው ዘንድሮም ከበጎ አድራጊ ክርስቲያኖች ሰብስቦ በአጥቢያው ያሉ ነዳያንን፣ እስረኞችን፣ በግቢው የሚገኙ ፀበልተኞችን እና ሌሎችንም የተቸገሩ የታመሙ ወገኖችን የምገባ መርሃግብር አዘጋጅቷል።
በናዝሬት ደብረ መድሃኒት መድሃኒዓለም ገዳም እና ካቴድራል የፈለገ ጥበብ ሰንበት ትምህርት ቤት የነዳያን ምገባ መርሃግብር አከናወነ፦ ሰንበት ትምህርት ቤቱ በየአመቱ የትንሳኤ ዕለት እንደሚያደርገው ዘንድሮም በአጥቢያው ያሉ ነዳያንን እና ሌሎችንም የተቸገሩ የታመሙ ወገኖችን ምግብ በማዘጋጀት የምገባ እና የትምህርት መርሃ ግብር አከናውኗል።