Unity Park-አንድነት ፓርክ
563 subscribers
164 photos
1 video
20 links
አንድነት ፓርክ በ 2012 ተቋቋመ ፡፡ ፓርኩ የሚገኘው በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ በሚገኘው ታላቁ ቤተመንግስት ውስጥ ሲሆን ከመቶ ምዕተ ዓመት በላይ የመንግሥት መቀመጫ ሆኖ ቆይቷል፡፡
Download Telegram
Congratulations to all Ethiopians in all corners of the country for finalizing a successful #GreenLegacy season this year with 6.7bil seedlings planted, surpassing our set target.
ኢትዮጵያዊነት የኢትዮጵያውያን የመተሣሠሪያ ማንነት ነው። ብዝኃ ባህል፣ ብዝኃ ቋንቋ፣ ብዝሃ እምነት፣ ብዝኃ አመለካከት ያለንን ኢትዮጵያውያን አንድ አድርጎ ለአንድ ሀገራዊ ዓላማ የሚያቆመን ዕሴት - ኢትዮጵያዊነት ነው። 1/2
ለኢትዮጵያዊነታችን ብዝኃነታችን ማገሩ፣ ጀግንነታችን አጥሩ፣ አንድነታችን ዓምዱ፣ ነጻነታችን መንገዱ ነው ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር። 2/2
እንኳን ለ1496 ኛው የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
#dr.abiy ahmed
"ታሪካችንን ሳያውቁ የሚገጥሙንን ታሪካችንን ዐውቀን እንጠብቃቸዋለን። ለወዳጃችን ወተት፣ ለጠላታችን ዕሬት መስጠት እንችልበታለን። ከቶም ኢትዮጵያ የሚለው ስም ከማሸነፍ እንጂ ከመሸነፍ ጋራ ተጠርቶ አያውቅም።"

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በወሎ ግንባር በነበረ ውጊያ ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ ኃይሎች ተሳትፈዋል አሉ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት ለከፍተኛ የመንግሥት አመራሮች በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ነው።

" በወሎ ግንባር በነበረው ውጊያ ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ ኃይሎች ከአሸባሪው ቡድን ጋር ተሳትፈዋል" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጦርነቱ የተሳተፉት እንነዚህ አካላት ኢትዮጵያውያን ያልሆኑና የኢትዮጵያውያን ዝርያ የሌላቸው #ነጮች እና #ጥቁሮች ናቸው ብለዋል ፤ በጦርነቱ ላይ ተሳትፈውም መስዋትነት መክፈላቸውን ገልፀዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የገጠመችው ጦርነት ከአንድ ወገን ጋር ብቻ እንዳልሆነ በመረዳት ህዝቡ ዋጋ ለመክፈል ያለውን ፍቅር በተግባር ሊገልጽ እንደሚገባ አሳስበዋል ሲል ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።
“ኢትዮጵያ” የሚለውን የነጻነት ስም የማስጠበቅ የታሪክ አደራ አለብን!
Unity Park-አንድነት ፓርክ
Video
Video : የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ወደ ግንባር ዘምተው ሰራዊቱን እንደሚመሩ በይፋ ካሳወቁ በኃላ ዛሬ በቴሌቪዥን መስኮት ለህዝብ ታይተዋል።

እየመሩት ያለው ሰራዊት ከፍተኛ ድል እያስመዘገበ መሆኑን አሳውቀዋል።

ጠ/ሚኒስትሩ ለሚዲያ በሰጡት አጭር መግለጫ ካሳጊታ መያዙን ዛሬ ደግሞ ጭፍራ እንዲሁም ቡርቃ እንደሚያዙ ገልፀዋል። "ነገምይቀጥላል ትላልቅ ድሎች አሉ " ብለዋል።

ዶክተር ዐቢይ አህመድ ፥ "የምንፈልገው እኛ ሞተን የምትቆም ኢትዮጵያን ማየት ነው" ያሉ ሲሆን " የኢትዮጵያ ነጻነት አስኪረጋገጥ ወደ ኋላ ማለት የለም " ብለዋል።

አክለውም ፥ " በአሁኑ ሰዓት የኢትዮጵያ ሰራዊት ሞራል ከፍተኛ ነው ፤ ጠላት ከእኛ ጋር ለመፎካከር የሚያስችል ቁመና የለውም " ሲሉ ተናግረዋል።
Happy Saturday 🌄