ጦሳ ሚዲያ (Tossa Media)
304 subscribers
689 photos
14 videos
6 files
1.04K links
ፈጣን እና ወቅታዊ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገራት መረጃዎችን ለማግኘት ይከተሉን
Download Telegram
ትራምፕ የኢራን ስልጣኔ ዛሬ ምሽት መጥፊያው ነው ሲሉ አስፈራሩ

ይህ እንዳይሆን ሀገሪቱ ስምምነት መድረስ እንዳለባት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት በማኅበራዊ ገጻቸው ባሰራጩት የዛቻ መልዕክት ጠቁመዋል፡፡ ስፑትኒክ
#ሰበር_ዜና: የኢራን አብዮታዊ ዘብ (IRGC) ባለሁለት ተኳሽ መካከለኛ ርቀት ባሊስቲክ ሚሳኤሎችን አሰማራ!

የኢራን አብዮታዊ ዘብ ኃይል (IRGC) በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ጠንካራ ነዳጅ (Solid-fuel) የሚጠቀሙ መካከለኛ ርቀት ባሊስቲክ ሚሳኤሎችን ባለሁለት ተኳሽ መድረኮች (dual-launcher platforms) በወቅታዊው ግጭት ውስጥ ጥቅም ላይ ማዋሉን የወጡ ሪፖርቶች አመልክተዋል።

ሥርዓቱ በርካታ ሚሳኤሎችን በፈጣን ተከታታይነት ለመተኮስ የሚያስችል ሲሆን፣ የመምታት ፍጥነትን እና በውጊያ ወቅት የመትረፍ ዕድልን (survivability) በእጅጉ እንደሚያሳድግ ይታመናል። ጥቃቱ ስለተሰነዘረባቸው ግቦች እና ስላደረሱት የጉዳት መጠን ዝርዝር መረጃ እስካሁን አልተገኘም።
🌍የእለተ ማክሰኞ ምሽት አጫጭር መረጃዎች

🇺🇸🇮🇷ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሆርሙዝ የባህር ዳርቻ ሙሉ በሙሉ እንዲከፈት በሰጡት ቀነ ገደብ መሰረት “ዛሬ ምሽት ሙሉ የኢራን ስልጣኔ ይሞታል” ሲሉ ተናገሩ

🇮🇷🇺🇸የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ኮርፖሬሽን ከቀጠናው ውጭ የአፀፋ ምላሽ እንደሚሰጥ እና ዩናይትድ ስቴትስ "ቀይ መስመሮችን" ካለፈች እንዲሁን የሲቪል ተቋማትን ካጠቃች አሜሪካ እና አጋሮቿ "ለበርካታ አመታት" ዘይት እና ጋዝ እንደሚጡ ዛተ።

🇮🇷  የኢራኑ ፕሬዝዳንት ማሱድ ፔዜሽኪያን እንዳስታወቁት ከ14 ሚሊዮን በላይ ጀግኖች ኢራናውያን ሀገራቸዉን ለመከላከል ሕይወታቸውን ለመሰዋት ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል። ግጭቱ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ በኢራን ቢያንስ 2,076 ሰዎች ሲገደሉ 26,500 ቆስለዋል።

🇮🇱 ሂዝቦላህ በእስራኤል ከተሞች እና ጦር ሰራዊት ላይ አዳዲስ ጥቃቶችን መክፈቱን አስታወቀ፡፡የሊባኖስ ታጣቂ ቡድን ሂዝቦላ ተዋጊዎች በሰሜን እስራኤል በሽሎሚ እና በሜናኬም ጥቃት ፈጽሟል፡፡


🇺🇸🇮🇮🇷  አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን አልቦርዝ ግዛት ላይ በፈጸሙት ጥቃት ከተገደሉት 18 ሰዎች  መካከል ሁለት ህጻናት ናቸዉ፡፡ከመንግስት ጋር የተቆራኘዉ የፋርስ የዜና ወኪል እንደዘገበው የአልቦርዝ ግዛት ምክትል አስተዳዳሪ መሞታቸውን በመግለጽ ሌሎች 24 ሰዎች ቆስለዋል ብሏል።


🇮🇱🇮🇷  የእስራኤል ጦር በደቡብ ምዕራብ ኢራን በሺራዝ የሚገኘውን የፔትሮ ኬሚካል ተቋምን መምታቱን አስታወቀ። ጦሩበመግለጫው "ናይትሪክ አሲድ ለኢራን የሽብር አገዛዝ የጦር ኃይሎች የተመረተበትን የፔትሮኬሚካል ተቋም መምታቱን" ገልጿል።


🇵🇰🇺🇸🇮🇷 በፓኪስታን የኢራን አምባሳደር ነሬዛ አሚሪ ሞጋዳም አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ የሚያደርጉትን ጦርነት ለማስቆም "ወሳኝ፣ ሚስጥራዊነት ያለው" ደረጃ ላይ እየቀረበ ነው ሲሉ ተናገሩ፡፡

🇸🇦🇮🇷🇧🇭  ሳዑዲ አረቢያ ባለፉት ጥቂት ሰዓታት ውስጥ በሀገሪቱ ላይ የተተኮሱ 18 ሰው አልባ አውሮፕላኖችን ማዉደሙን የመከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ። በሌላ በኩል ኢራን የአሜሪካ ባህር ሃይል መርከቦችን የያዘውን ምስራቃዊ ግዛቴን ለመምታት ዝታለች ስትል ሳውዲ አረቢያ ከባህሬን ጋር የሚያገናኛትን ብቸኛዉን የኪንግ ፋህድ ካውዝ  መንገድ ዘግታለች።


🇺🇸🇮🇷 የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሆርሙዝ የባህር ዳርቻ እስከ ማክሰኞ የቀኑ መጨረሻ ድረስ ሙሉ በሙሉ ካልተከፈተ በጥቂት ሰዓታት ውስጥ የኢራን የኃይል ማመንጫዎች እና ድልድዮች “ሙሉ በሙሉ እንደሚፈርሱ” አስጠንቅቀዋል ።

🇧🇭🇮🇷 የባህሬን መከላከያ ሃይል ዕዝ የአየር መከላከያ ስርአቱ ግጭቱ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ከኢራን የተወነጨፉ 188 ሚሳኤሎችን እና 477 ሰው አልባ አውሮፕላኖችን በመጥለፍ ማውደሙን አስታውቋል።

🇮🇷  የኢራን የባህል ቅርስ ሚኒስትር ለዩኔስኮ ዋና ዳይሬክተር የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እስራኤልን የኢራንን የባቡር መስመር ለማጥቃት የምታደርሰውን ስጋት እንዲያወግዝ በመጠየቅ ደብዳቤ ልከዋል ሲል የኢራን የዜና ወኪል ዘግቧል።

🇮🇷 በአምስተርዳም ዩኒቨርሲቲ የአለም አቀፍ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ረዳት ፕሮፌሰር ማሪኬ ደ ሁን በኢራን የሲቪል መሠረተ ልማት ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶች የጦር ወንጀሎች ሊሆኑ እንደሚችሉ ለአልጀዚራ ተናግረዋል።
2👍1
ሰበር 🔥

አሜሪካ እና ኢራን የ2 ሳምንት የተኩስ አቁም ስምምነት አድርገዋል ። የሆርሙዝ ሰርጥም ሙሉ ለሙሉ ይከፈታል ።
🌍የእለተ እሮብ አጫጭር መረጃዎች

🇮🇱🇱🇧 የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የተኩስ አቁም ሊባኖስን እንደማይጨምር ገለፀ። የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ እንዳሉት እስራኤል በኢራን ላይ የምታደርገውን ጥቃት ለሁለት ሳምንታት ለማቆም ተስማምታለች፤ ይህ ስምምነት ግን ሊባኖስን እንደማይጨምር አክለዋል።

🇮🇷🇺🇸 የተኩስ አቁም መደረሱን ተከትሎ ጊዜ መግዛት ይፈልጋሉ ሲሉ አንዳንድ ኢራናውያን ስለ አሜሪካ ዓላማ ተጠራጣሪ መሆናቸውን ተናገሩ።

🇮🇷🇴🇲🇵🇰ኢራን እና ኦማን በፓኪስታን ሸምጋይነት ለሁለት ሳምንት በሚዘልቀው የተኩስ አቁም ስምምነት አካል በሆነው በሆርሙዝ ባህር ላይ በሚያልፉ መርከቦች ላይ ክፍያ መሰብሰብ ይችላሉ።

🇱🇧🇮🇱 በሊባኖስ በእስራኤል እና በኢራን በሚደገፈው ሂዝቦላህ መካከል ከአንድ ወር በላይ በዘለቀው ጦርነት የሞቱት ሰዎች ቁጥር 1,530 ደረሰ። ከሟቾቹ መካከል 102 ሴቶች እና 130 ህፃናት ናቸው።

🇦🇺🇺🇸🇮🇷የአውስትራሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኔዝ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፔኒ ዎንግ አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ ለሚያካሂደው ጦርነት መፍትሄ ለመስጠት ለሁለት ሳምንታት የደረሱትን የእርቅ ስምምነት በደስታ እንደሚቀበሉ ተናገሩ።

🇺🇸🇮🇶 የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ አሜሪካዊቷ ጋዜጠኛ ሼሊ ኪትልሰን በኢራቅ ታግታ ከቆየች ከበርካታ ቀናት በኋላ መፈታቷን ተናግረዋል። የኢራቅ ታጣቂ ቡድን ካታይብ ሂዝቦላህ ኪትልሰን በፍጥነት ኢራቅን ለቃ እንድትወጣ በሚል ቅድመ ሁኔታ እንደሚፈታ አስቀድሞ መናገሩ ይታወሳል።

🇺🇸 ትራምፕ ከአንዳንድ ሪፐብሊካኖች ድጋፍ አጥተዋል።የኢራንን ስልጣኔ እንደሚያፈርሱ ትራምፕ ከዛቱ በኃላ በሪፐብሊካን ፓርቲ ውስጥ የረዥም ጊዜ አጋሮቻቸው ድጋፍ ነፍገዋል።ከነዚህ መካከል የጆርጂያ ኮንግረስ አባል ኦስቲን ስኮት ፣የቴክሳስ ሪፐብሊካን ናትናኤል ሞራን፣የቀድሞ የኮንግረሱ አባል የሆነችው ማርጆሪ ቴይለር ግሪን እና የብሔራዊ የፀረ-ሽብርተኝነት ማዕከል የቀድሞ ዳይሬክተር ጆ ኬንት ተጠቃሽ ናቸው።
👍2
ኢራን በድጋሚ የሆርሙዝ ሰርጥን ዘጋች።

እስራኤል በሊባኖስ ላይ የምትፈፅመውን ጥቃት ባለማቆሟ ነው ሰርጡ የተዘጋው ተብሏል።

በስምምነቱ መሰረት የሆርሙዝ ሰርጥ ከነገ ሀሙስ ወይም አርብ ጀምሮ ክፍት እንደሚሆን ተመላክቷል።

ይሁን እንጂ አንዳንድ ሀገራት አሁንም ስጋታቸውን እየገለፁ ይገኛሉ።

ከስምምነቱ በኋላ ሁለት ነዳጅ የጫኑ መርከቦች ብቻ ማለፋቸው ተገልጿል።  #dailystar
🌍የእለት ሁሙስ አጫጭር መረጃዎች

🇬🇧🇬🇧🇱🇧ፈረንሳይ እና እንግሊዝ ባወጡት መግለጫ እስራኤል በሊባኖስ ላይ የምትፈጽመዉ ጥቃት ተቀባይነት የለዉም ሲሉ ተናገሩ፡፡የዩናይትድ ኪንግደም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢቬት ኩፐር እስራኤል በሊባኖስ ላይ ያደረሰችውን ጥቃት “ፍፁም ስህተት ነው” ብለዋል። የፈረንሳይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዣን ኖኤል ባሮት ጥቃቱ “ተቀባይነት የለውም” ሲሉ ተናግረዋል፡፡

🇪🇸🇮🇷  ስፔን በኢራን ዋና ከተማ ቴህራን ኤምባሲዋን እንደገና እንደምትከፍት የሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አስታወቁ። ጆሴ ማኑኤል አልባረስ እንደተናገሩት እስራኤል “የተኩስ አቁምን” እና “ዓለም አቀፍ ህግን እየጣሰች ነዉ” ሲል ከሰዋል።


🇮🇱🇱🇧 የእስራኤል ጦር በቤይሩት በፈጸመዉ የአየር ጥቃት የሂዝቦላህ ዋና ፀሃፊ ናኢም ቃሴም የግል ረዳት አሊ ዩሱፍ ሃርሺን መግደሉን አስታወቀ፡፡ ጦሩ በሰጡት መግለጫ ሃርሺ ለካሴም “የቅርብ አጋር እና የግል አማካሪ” እንደነበረ ገልጿል። የእስራኤል ወታደራዊ ኃይል በሊታኒ ወንዝ ላይ ሁለት "ቁልፍ ማቋረጫዎችን" እንዲሁም በደቡባዊ ሊባኖስ የሂዝቦላ መሠረተ ልማት ላይ ጥቃት ማድረሱን አስታዉቋል።

🇮🇱  የእስራኤል የዲያስፖራ ጉዳዮች ሚኒስትር እና የገዢው ሊኩድ ፓርቲ አባል አሚቻይ ቺክሊ ከኢራን ጋር የተኩስ አቁም ስምምነት መደረሱ “ስህተት ነው” ሲሉ ተናገሩ፡፡"በዚህ ጊዜ ወደ ተኩስ አቁም መሄድ ስህተት ነበር ብዬ አስባለሁ፤ እንደ እነዚህ ያሉ ሀገራት ልክ እንደ ጃፓን ኢምፓየር፣ ናዚ ጀርመን ማንበርከክ ያስፈልጋል" ሲሉ ለእስራኤሉ 103 ኤፍኤም ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡ የተኩስ አቁም ስምምነቱ የሚዘልቅበት እድል 50 በመቶ ነው ሲሉ ተደምጠዋል፡፡

🇮🇹🇮🇷🇺🇸 የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተደረሰውን የተኩስ አቁም ስምምነት የሚጥስ ማንኛውንም አካል በፅኑ እናወግዛለን ብለዋል፡፡ጣሊያን እና የአውሮፓ ህብረት፣ በሆርሙዝ ባህር ውስጥ "የመርከቦች ነፃነት" መመለስ አስፈላጊ እንደሆነ ያምናሉ ብለዋል፡፡

🇨🇳  ቻይና በተቻለ ፍጥነት በመካከለኛው ምስራቅ አካባቢ መረጋጋት ለማምጣት በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተኩስ አቁም ማዕቀፍ ላይ የሚደራደሩትን ወገኖች ጠይቃለች።የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ የሆነችዉ ማኦ ኒንግ ለመገናኛ ብዙሃን እንደተናገረችዉ ቤጂንግ ሁኔታውን ለማቃለል እና ጦርነቱን ሙሉ በሙሉ ለማስቆም የምታደርገዉን ጥረት ትቀጥላለች ሲሉ ገልጸዋል።

🇱🇧 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ “በሊባኖስ ዙሪያ እስራኤል በፈፀመችውን ግዙፍ ጥቃት ህጻናትን ጨምሮ 254 ከነዚህ መካከል አብዛኛዎቹ ሲቪሎች የተገደሉበት ወታደራዊ እርምጃ” አውግዘዋል።

🇺🇸 የዩናይትድ ስቴትስ አጋሮች በትራምፕ እውነተኛ የጦርነቱ አላማዎች ላይ ተጠራጣሪ መሆናቸዉ ተነገረ፡፡ የትራምፕ ተለዋዋጭ የጦርነት ግቦች እና አደገኛ ንግግሮች በኢራን ላይ ለመተባበር ፈቃደኞች ሊሆኑ የሚችሉትን በርካታ የአሜሪካ አጋሮችን ገፍቷቸዋል ሲሉ በለንደን የሚገኘው የቻተም ሀውስ የጥናት ቡድን ባልደረባ ሳናም ቫኪል ተናግረዋል ።

🇮🇱 የእስራኤል ጤና ሚኒስቴር እንዳስታወቀው ዩናይትድ ስቴትስ እና እስራኤል በኢራን ላይ ጦርነት ከከፈቲ ወዲህ በአጠቃላይ 7,451 እስራኤላዉያን ቆስለዋል እና ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል ።

🇺🇸🇮🇷  ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቴህራን ጋር የተኩስ አቁም ስምምነት “ሙሉ በሙሉ እስኪፈፀም ድረስ” ሁሉም የአሜሪካ መርከቦች ፣ አውሮፕላኖች እና ወታደራዊ ሰራተኞች በኢራን ዙሪያ ባሉበት ይቆያሉ ሲሉ ተናገሩ።

🇦🇺🇱🇧 የአውስትራሊያው ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኔዝ በዩናይትድ ስቴትስ እና በኢራን መካከል የተኩስ አቁም ስምምነት "በሊባኖስ ላይ መተግበር አለበት" ሲሉ ተናገሩ፡፡ የእስራኤል ጥቃት በመላዉ ሊባኖስ ረቡዕ እለት ብቻ ቢያንስ 254 ሰዎችን መግደሉን ተከትሎ በመላዉ ዓለም ቁጣን ቀስቅሷል፡፡
🌍አጫጭር መረጃዎች

🇮🇷🇺🇸የኢራን ታጣቂ ኃይል ዩናይትድ ስቴትስ "በአለም አቀፍ የውሃ መስመር ላይ መርከቦች እንዳይዘዋወሩ እገዳ መጣል ህገ-ወጥ ድርጊት እና የባህር ላይ ወንበዴነት ነው" ሲል አወገዘ።

🇨🇳🇮🇷ቻይና በሆርሙዝ የባህር ዳርቻ ላይ የባህር ኃይል እገዳን ትረምፕ ለመጣል የወሰዱት እርምጃ እንደሚያሰጋት በማንሳት ሁሉም አካል እንዲረጋጋ አሳሰበች። ቁልፍ የውሃ መንገዱን ደህንነቱ የተጠበቀ፣ የተረጋጋ እና ያልተደናቀፈ ማድረግ የአለም አቀፉን ማህበረሰብ የጋራ ጥቅም እንደሚያስከብር የገለፁት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጉኦ ጂያኩን ቻይና የሃይል ደህንነትን እና አቅርቦትን ለመጠበቅ ከሁሉም አካላት ጋር ለመስራት ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል።

🇱🇧🇮🇱በደቡባዊ ሊባኖስ ውስጥ በምትገኘው ቢንት ጀበይ ከተማ ላይ እስራኤል የአየር ጥቃት የፈፀመች ሲሆን በደቡባዊ ሊባኖስ ውስጥ በምትገኘው አባቢያ ከተማ ላይ አስቀድማ የድሮን ጥቃት ፈፅማለች።


🇱🇧🇮🇱የሊባኖስ ታጣቂ ቡድን ሄዝቦላህ በሽሎሚ ሰፈር ውስጥ የእስራኤል ወታደሮችን ኢላማ ያደረገ ጥቃት መፈፀሙን አስታወቀ። ቡድኑ " የእስራኤል-አሜሪካውያን ወረራ በአገራችን እና በህዝባችን ላይ እየደረሰ ያለው ጥቃት እስኪቆም ድረስ ጥቃቱ ይቀጥላል” ሲል አክሏል።

🇮🇱🇱🇧ከድሮን የወጣ ፍርስራሽ በእስራኤል ፋብሪካ ላይ ጉዳት አደረሰ። የእስራኤሉ ቻናል 12 ብሮድካስቲንግ እንደዘገበው አንድ የሰው አልባ አውሮፕን ሲጠለፍ በተከሰተው ፍርስራሽ በዳልተን ኢንዱስትሪያል ፓርክ ውስጥ በሚገኙ መጋዘኖች ላይ ጉዳት አድርሷል። ይህው ስፍራ በሰሜናዊ እስራኤል ገሊላ አካባቢ ነው። በሰው ህይወት ላይ ስለደረሰ ጉዳት እስካሁን የተገለጸ ነገር የለም።

🇮🇷ኢራን በቴህራን፣ ታብሪዝ እና ማሽሃድ ከየሞች መካከል ያለውን የባቡር መስመር ወደነበረበት መለሰች። የኢራን የዜና ወኪል እንደዘገበው ተበላሽቶ የነበረው የባቡት መስመር ከአራት እስከ አምስት ቀናት ከቆዩ በኋላ አገልግሎቱ ዳግም ጀምሯል።

🇮🇱🇱🇧እስራኤል ረቡዕ ኤፕሪል 8 ብቻ በመላው ሊባኖስ ከ350 በላይ ሰዎችን መግደሏ ተረጋገጠ። በሊባኖስ ጦርነቱ ከተጀመረ ወዲህ ቢያንስ 2055 ሰዎች ተገድለዋል።

🇺🇸የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ በሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃልኪዳን ኔቶ ላይ ፈሰስ የምታደርገው ወጪ በከባድ ምርመራ ላይ ይቆያል ሲሉ ተናገሩ። ትራምፕ ኔቶ በኢራን ላይ የሚያደርጉትን ጦርነት ለመደገፍ ባለመቻሉ ቅር እንዳሰኛቸው በድጋሚ ገልፀዋል።
🌍አጫጭር መረጃዎች

🇱🇧🇮🇱 የሊባኖስ ታጣቂ ቡድን በእስራኤል ወታደራዊ ቦታዎች ላይ ተከታታይ ጥቃቶችን መፈጸሙን አስታወቀ፡፡ሂዝቦላህ እንደገለፀው ተዋጊዎቹ በባይያዳ ከተማ አዲስ የተቋቋሙትን የእስራኤል የጦር ሰፈር ቦታዎችን በሮኬት መትቷል።

🇱🇧🇮🇱  የሊባኖስ ብሄራዊ የዜና አገልግሎት እንደዘገበው እስራኤል በምዕራብ ቤካ ሳህማር ላይ በፈጸመችዌ የአየር ጥቃት ከአንድ ቤተሰብ ሦስት ሰዎች ተገድለዋል።በተከታታይ የአየር ላይ ጥቃት በከተማዋ ከ10 በላይ ቤቶች ወድመዋል።

🇺🇸🇨🇳  አሜሪካ የኢራን ወደቦችን መከልከሏ አደገኛ እና ኃላፊነት የጎደለው ነው ስትል ቻይና ተናገረች።የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጉዎ ጂያኩን እንዳሉት ዩናይትድ ስቴትስ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎችን ጨምራለች እና የታለመ የማገጃ እርምጃ ወስዳለች ፣ ይህም ውጥረቱን ከማባባስ እና ቀድሞውንም ደካማ የሆነውን የተኩስ አቁም ስምምነት ክፉኛ ይጎዳል ብለዋል፡፡

🇮🇷  ኢራን በጦርነቱ ላይ በሰራችዉ የመጀመሪያ ግምት 270 ቢሊዮን ዶላር ኪሳራ እንደረሰባት አስታዉቃለች፡፡፣ የኢራን መንግስት ቃል አቀባይ ፋተሜህ ሞሃጄራኒ  አሃዛዊ ግምቱ የመጀመሪያ ቢሆንም የመጨረሻው ወጪ ከፍተኛ ሊሆን እንደሚችል መናገራቸዉን የኢራን ታስኒም የዜና ወኪል ገልጿል።

🇮🇷  የኢራን የነዳጅ ሚኒስትር ሞህሰን ፓክኔጃድ ጦርነቱ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ለኢራን የነዳጅ ሽያጭ "አመቺ" ሆኗል ሲሉ ተናገሩ፡፡ለፋርስ የዜና ወኪል በሰጡት አስተያየት  ከተገኘዉ ሀብቱ የተወሰነው በጦርነቱ የተጎዳውን ኢንዱስትሪ መልሶ ለመገንባት ጥቅም ላይ መዋል አለበት ብለዋል።ሚኒስትሩ ባለፈው ወር የኢራን ድፍድፍ ነዳጅ ዘይት የመሸጫ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል ሲሉ አክለዋል።

🇱🇧🇮🇱  የእስራኤል ጦር በደቡባዊ ሊባኖስ በተካሄደው ጦርነት አንድ ወታደሩ ሲገደልበት ሌሎች 3 ቆስለዋል ብሏል፡፡

🇱🇧🇮🇱  የሊባኖስ ጤና ሚኒስቴር ከመጋቢት ወር አንስቶ በእስራኤል ጥቃቶች ከ 2,000 በላይ ሰዎች ሲገደሉ ከ 6,000 በላይ ሰዎች ቆስለዋል ብሏል።ይህንኑ ተከትሎ የቃጠሎ ጉዳት ባለባቸው ታካሚዎች የጤና ተቋማት ከፍተኛ መጨናነቅ አስከትሏል፡፡

🇮🇷  ኢራን በሆርሙዝ ሰርጥ ውስጥ ደህንነት ‘ለሁሉም ወይም ለማንም መሆን የለበትም’ ስትል አስታወቀች፡፡

🇺🇸🇮🇷🇵🇰 የዩናይትድ ስቴትስ-ኢራን ድርድር ለማደስ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች የቀጠሉ ሲሆን ፓኪስታን በዚህ ሳምንት በኢስላማባድ ሁለተኛ ዙር ድርድር ለማዘጋጀት ጥሪ አቅርባለች፡፡

🇺🇸  የዩናይትድ ስቴትስ የኢነርጂ ፀሐፊ ክሪስ ራይት “በሆርሙዝ ባህር ውስጥ ትርጉም ያለው የመርከብ ትራፊክ እንቅስቃሰሴ እስክናገኝ ድረስ” የነዳጅ ዘይት ዋጋ እየጨመረ ሊሄድ ይችላል ሲሉ ተናገሩ፡፡
1
የእስራኤል ወታደሮች የአየሱስ ክርስቶስን ሐውልት አውድመዋል።

በርካታ ክርስቲያኖች በሚኖሪባት ሊባኖስ ላይ ወረራዋን የቀጠለቺው እስራኤል ወታሮቿ በደረሱባቸው የደቡብ ሊባኖስ አካባቢዎች መስጅድና ቤተክርስቲያን እያወደሙ ይገኛሉ።

እናም በዛሬው እለት በደቡባዊ ሊባኖስ የሚገኘውን የኢየሱስ ክርስቶስ ሀውልት አውድመውታል።
#ሰበር_ዜና‼️
የብሪክስ አባል ሀገራት በቅርቡ ህንድ ላይ በሚካሄደው የ2026 የመሪዎች ጉባኤ ላይ አዲሱን የ“BRICS PAY” የዲጂታል የግብይት ስርዓት ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ሊያደርጉ መሆኑ ተገለጸ።
የብሪክስ ህብረት፡ በብሎክቼይን ላይ የተመሰረተውን የ“BRICS PAY” የዲጂታል የግብይት ስርዓት ህንድ ውስጥ በሚካሄደው የ2026 የመሪዎች ጉባኤ ላይ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ ማቀዱን በይፋ አስታውቋል።
ይህ እርምጃ የህብረቱ አባል ሀገራት በቀጥታ በየራሳቸው ገንዘብ እንዲገበያዩ ያስችላቸዋል ተብሏል።
ዕቅዱ በተሳካ ሁኔታ ተግባራዊ ከተደረገ በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ላይ ከፍተኛ ለውጥ የሚያመጣ ሲሆን፡ ዶላርን ከገበያ ለማውጣት የሚደረገውን ጥረት ያፋጥናል ተብሏል።
🌍አጫጭር መረጃዎች

🇮🇷🇮🇱 በኢራን ውስጥ ለሞሳድ በመሰለል ወንጀል ጥፋተኛ የተባሉ ሁለት ሰዎች ተገደሉ።የኢራኑ ታስኒም የዜና ወኪል እንደዘገበው ከእስራኤል የስለላ ድርጅት ሞሳድ ጋር የተገናኘ የአውታረ መረብ አባል በመሆን የተከሰሱ ሁለት ሰዎች ሰኞ ማለዳ ላይ ተገድለዋል።

🇮🇷  ኢራን 95 በመቶ የኤርፖርት መሠረተ ልማቷ እንዳልተጎዳ የፋርስ የዜና ወኪል ዘግቧል፡፡የአየር መንገዱ ማኅበር ፀሐፊን በመጥቀስ ፋርስ ቢበዛ ወደ 20 የሚጠጉ የሀገሪቱ አውሮፕላኖች ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል ብሏል።ኢራን የአየር ክልሏን ለንግድ በረራዎች ለመክፈት በዝግጅት ላይ ትገኛለች፡፡

🇫🇷🇱🇧🇮🇱  ታዋቂው የፈረንሣይ-ሊባኖስ ጥምር ዜግነት ያለዉ አርቲስት አሊ ቼሪ በቤይሩት ቤተሰቡ መኖሪያ ቤት ላይ በደረሰው ጥቃት ወላጆቹን ለገደለዉ ጥቃት በእስራኤል ላይ የጦር ወንጀል ክስ አቀረበ፡

🇺🇸🇮🇷  ኢራን ከአሜሪካ ጋር ተጨማሪ ውይይት ለማድረግ እቅድ የላትም ሲል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ አክሎም የተኩስ አቁም ስምምነቱን ከትግበራው ጀምሮ በአሜሪካ በኩል ተጥሷል፣ ይህንንም ለፓኪስታን አስታራቂ ቡድን አሳውቀናል ብሏል።

🇺🇸🇮🇷 አሜሪካውያን ኢራንን የመውቀስ ጨዋታ እየተጫወቱ ነው ሲሉ የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ተናገሩ፡፡አዎንታዊ ሚና ከመጫወት ይልቅ ነገሩን እያበላሹ ነዉ፤ አሜሪካውያን እውነቱን እንዲናገሩ መጠበቅ አንችልም፤ ሁልጊዜ እኛን እየከሰሱን ነው ሲሉ አክለዋል፡፡

🇨🇳  የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ የኢራን ባንዲራ የያዘችው ቱስካ መርከብ መያዙን ተከትሎ በኢራን እና በአሜሪካ መካከል የሰላም ድርድር እንዲቀጥል ጠይቀዋል።ጉዎ ጂያኩን እንደተናገሩት ቻይና መርከቧን በአሜሪካ ኃይሎች በኃይል መጥለፍ ላይ የተሰማትን ስጋት ገልጻለች፡፡

🇮🇱🇮🇷  እስራኤል ለኢራን ሲሰልሉ የነበሩ ሁለት ተጠርጣሪ ሰላዮችን አሰረች።የእስራኤል ቻናል 12 እንደዘገበዉ ተጠርጣሪዎቹ የአስራ ዘጠኝ ዓመቱ ሳጊ ሃይክ እና የ21 ዓመቱ አሳፍ ሼትሪት ሲሆኑ ከነስ ጽዮና ከተማ የመጡ ናቸው።

🇮🇱🇵🇸በጋዛ ላይ እስራኤል ጦርነት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ቢያንስ 1,151 ፍልስጤማውያን በዌስት ባንክ ሲገደሉ ከ11,885 በላይ ሰዎች ደግሞ ቆስለዋል።በዚሁ ወቅት ከ23,000 በላይ ፍልስጤማውያን ታስረዋል።


🇺🇸🇮🇷  ትራምፕ የኢራን መርከብ ተያዘች ካሉ በኋላ የነዳጅ ዋጋ ጨምሯል።ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዩናይትድ ስቴትስ የኢራን ባንዲራ የያዘች የጭነት መርከብ ተይዛለች ካሉ በኋላ ሰኞ እለት የአለም የነዳጅ ዋጋ ጨምሯል።የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ በዓለም አቀፍ ገበያ 4.74 በመቶ ጨምሮ 94.66 ዶላር ሲደርስ በዌስት ቴክሳስ ኢንርሚዲየት ገበያ ደግሞ 5.6 በመቶ ጭማሪ በማሳየት ወደ 88.55 ዶላር ከፍ ብሏል።

🇮🇱🇱🇧 እስራኤል በሊባኖስ ላይ ህጋዊ ወረራ ለማድረግ ከሂዝቦላህ ጋር የተኩስ አቁም ስምምነቱን እየተጠቀመች ሊሆን እንደሚችል ተነገረ፡፡መቀመጫቸውን በእስራኤል ያደረጉት የፖለቲካ ተንታኝ አቤድ አቡ ሽሃዴህ ምናልባት እስራኤል ከሂዝቦላህ ጋር የጀመረችውን የተኩስ አቁም የሊባኖስን ይዞታ ወደራሷ በመጠቅለል ህጋዊ ለማድረግ እየተጠቀመች ነው ብለዋል።
ሰበር_ዜና: ፕሬዝዳንት ትራምፕ የኒውክሌር ኮዶችን እንዳይጠቀሙ በከፍተኛ የጦር መኮንን መታገዳቸው ተገለጸ!

በዋይት ሀውስ በተካሄደ ስብሰባ ላይ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሀገሪቱን የኒውክሌር ኮዶች ለመጠቀም ባደረጉት ሙከራ፣ ከአንድ ከፍተኛ የጦር መኮንን ጠንካራ ተቃውሞ እንደገጠማቸው ተዘገበ።

እንደ የዜና ምንጮች ዘገባ፣ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሀገሪቱ የጦር አዛዥ አማካኝነት የኒውክሌር ኮዶችን እንዳያገኙ እገዳ ተጥሎባቸዋል። የቀድሞው የሲአይኤ (CIA) ተንታኝ ላሪ ጆንሰን "Judging Freedom" በተሰኘው የዩቲዩብ መርሃ-ግብር ላይ እንደገለጹት፤ ፕሬዝዳንቱ ቅዳሜ ዕለት በተካሄደ ድንገተኛ ስብሰባ ላይ ኮዶቹን ለማግኘት ጥረት አድርገው ነበር።

ጆንሰን በወቅቱ የነበረውን ሁኔታ ሲያብራሩ፦

"ከዋይት ሀውስ የወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣ ትራምፕ የኒውክሌር ኮዶቹን ለመጠቀም በፈለጉበት ወቅት ጀነራል ዳን ኬን በቆራጥነት በመነሳት 'አይሆንም' የሚል ምላሽ ሰጥተዋል። ጀነራሉ እንደ ጦር ኃይሉ መሪነታቸው ያላቸውን ልዩ ሥልጣን ተጠቅመው ኮዶቹን የከለከሉ ሲሆን፣ ድርጊቱም ከፍተኛ ውዝግብ አስከትሏል" ብለዋል።

ምንም እንኳን የቀረቡት ክሶች በገለልተኛ ወገን ያልተረጋገጡ ቢሆንም፣ ፕሬዝዳንቱ ኮዶቹን ለማግኘት የፈለጉበት ምክንያትም በግልጽ የታወቀ ነገር የለም።

ከዚህ ጋር ተያይዞ፣ በኢራን ውስጥ ይካሄድ በነበረ ወሳኝ የነፍስ አድን ዘመቻ ወቅት ፕሬዝዳንት ትራምፕ በወታደራዊ አማካሪዎቻቸው አማካኝነት መቆጣጠሪያ ክፍል (Situation Room) መታገዳቸው ተመልክቷል። ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ፕሬዝዳንቱ ያላቸው ግ*ልፍተኛ ባህሪ እና ውሳኔ የመስጠት ወጥነት ማጣት ዘመቻውን አደጋ ላይ ሊጥል ይችላል የሚል ስጋት እንደነበራቸው ተዘግቧል።

በተጨማሪም፣ በኢራን ኃይሎች የዩኤስ አውሮፕላን መመታቱን ተከትሎ ፕሬዝዳንቱ በ1979ኙ የኢራን ታጋቾች ቀውስ ትውስታ በመታወክ፣ በዋይት ሀውስ ምዕራባዊ ክንፍ ውስጥ በሥራ ባልደረቦቻቸው ላይ ከፍተኛ ጩኸት ሲያሰሙ እንደነበር በዘገባው ተካቷል።

ምንጭ: The Mirror
🔶እስራኤል ግብረሰዶማዊነትን ተቀበለች!

እስራኤል ግብረ ሰዶማዊነትን በይፋ በመቀበል በመካከለኛው ምስራቅ ታሪክ ለመጀመሪያው ጊዜ የግብረሰዶማውያንን ቀን በሚቀጥለው ሰኔ ወር ልታካሂድ ነው፡፡

የእስራኤል ቱዴይ ዘገባ መሰረት፣ ‹‹የኩራት ምድር›› የሚል ስያሜ የተሰጠው ይህ ኢ ምግባራዊ በዓል የሚከበረው በመጽሀፍ ቅዱስ በተጠቀሱት ሰዶም እና ገሞራህ ከተሞች ነው፡፡ ይህ ክበረ በአል በእስራኤል የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ዋና አዘጋጅነት የተሰናዳ መሆኑን ዘገባው ጠቅሷል፡፡
የኢራን አዲስ ማስጠንቀቂያ‼️
የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ቃልአቀባይ 'በኢራን ላይ የሚደረግ ማንኛውንም አዲስ ጥቃት ለመጋፈጥ ዝግጁ መሆኑን እና እንደገና ጦርነት የሚነሳ ከሆነ “በጠላት ቀሪ ንብረቶች ላይ ከባድ ድብደባ እንደሚፈጽም' ተናግረዋል።
ከባለፈው ጦርነት የባሰ አስከፊ ውድመት እናደርሳለን፣ለአሜሪካ የሚተባበሩ የአረብ ሀገራት ነዳጅ እንዳያመርቱ እናደርጋለን፣ አይተው የማያውቁትን ጥቃት እናከናንባቸዋለን "ብለዋል። ትራምፕ ዛሬ የሚያበቃውን የተኩስ አቁም ስምምነት በኢራን ጥያቄ መሰረት አራዝሚያለሁ ያሉ ሲሆን ኢራን ግን የተኩስ አቁም ስምምነቱ እንዲራዘም ለአሜሪካ ምንም አይነት ጥያቄ እንዳላቀረበች ገልፃለች።
የዓለምን ስጋት የጨመረው የቻይናው "DF-5C" ሚሳይል!
************************
ቤጂንግ መላውን ዓለም መድረስ የሚችልና የጠላትን መከላከያ ሰብሮ የሚገባ እጅግ ዘመናዊ የኒውክሌር ሚሳይሏን ለዓለም አሳይታለች።

ቻይና በቅርቡ ባካሄደቻቸው ታላላቅ ወታደራዊ ትርኢቶች ላይ የዓለምን ወታደራዊ ሚዛን ሊቀይር ይችላል የተባለለትን DF-5C የተሰኘ አህጉር አቋራጭ ሚሳይል በይፋ አሳይታለች።

ይህ ሚሳይል የቻይና የረጅም ርቀት የኒውክሌር መከላከያ አቅም ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን የሚያረጋግጥ ሲሆን በርካታ አስገራሚ ቴክኒካዊ ብቃቶችንም አካትቷል።
ይህ ሚሳይል እስከ 20,000 ኪሎ ሜትር የመጓዝ ተወዳዳሪ የሌለው አቅም ያለው ሲሆን ይህም ከቻይና ተነስቶ ማንኛውንም የዓለም ክፍል በቀጥታ ለመምታት ያስችለዋል።

ከርቀቱ በተጨማሪ በአንድ ጊዜ እስከ 10 የሚደርሱ የኒውክሌር አረሮችን ተሸክሞ የመምዘግዘግ ብቃት ያለው ሲሆን እነዚህም አረሮች ወደ ጠላት ምድር ሲቃረቡ ተለይተው የተለያዩ ኢላማዎችን በተመሳሳይ ሰዓት ማውደም ይችላሉ።

ከፍተኛ ፍጥነቱና ከመደበኛ አረሮች ጋር የሚላኩት አሳሳች መረጃዎች የጠላትን የሚሳይል መከላከያ ጋሻ ሰብሮ ለመግባት ምቹ ያደርጉታል። የቤጂንግ ባለሥልጣናት ይህንን ቴክኖሎጂ ይፋ ያደረጉት የሀገሪቱን ሉዓላዊነት ለማስከበርና የጥቃት መከላከያ አቅማቸውን ለማሳየት መሆኑን ቢገልጹም በታላላቅ ሀገራት መካከል ያለውን የጦር መሣሪያ ፉክክር ይበልጥ ሊያፋፍመው እንደሚችል ወታደራዊ ተንታኞች ስጋታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ።
ቻይና ለትራምፕ እጅግ ከባድ እና የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጠች! ነገሩ ከረረ! 🚨
***************************
​ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ "በሆርሙዝ የባህር ሰርጥ ላይ ያደረግነውን ማዕቀብ (Blockade) አናነሳም፤ ህግ የሚጥሱ መርከቦችንም ማገታችንን እንቀጥላለን!" ካሉ በኋላ፣ አሜሪካ ከቻይና ወደ ኢራን ሲጓዝ የነበረን የጭነት መርከብ በቁጥጥር ስር ማዋሏ ቻይናን ክፉኛ አስቆጥቷል! 😡🇨🇳
​የቻይና መንግስት የሰጠው አስደንጋጭ ማስጠንቀቂያ፦
🗣 "አሜሪካ ከቻይና ወደ ኢራን ሲጓዝ የነበረን የሲቪል ጭነት መርከብ ህገ-ወጥ በሆነ መንገድ ማገቷን በሚገባ ታዝበናል። አንድ ነገር በግልፅ እናስቀምጥ፤ አሜሪካ በአለም መድረክ ላይ የፈለገችውን ነገር ልታደርግ ትችላለች። ነገር ግን ከቻይና የሚነሱ ወይም ወደ ቻይና የሚመለሱ መርከቦችን ማጥቃት፣ ማሰር ወይም ማንገላታት በቻይና መንግስት እና ህዝብ ዘንድ በፍጹም ዝም ተብሎ አይታለፍም! 🚢🚫
​ይህ አይነቱ ድርጊት በቻይና ሉዓላዊነት፣ ንግድ እና ብሄራዊ ጥቅም ላይ የተሰነዘረ ቀጥተኛ ጥቃት ተደርጎ ይወሰዳል 💥
⚠️ ይህ ለአሜሪካ የመጀመሪያ እና የመጨረሻ ማስጠንቀቂያችን ነው! የተሳሳተ ስሌት ውስጥ አትግቡ (Do not miscalculate)፤ በእሳትም አትጫወቱ! 🔥
​ቻይና ህጋዊ መብቷን እና ጥቅሟን ለማስጠበቅ ማንኛውንም አስፈላጊ እርምጃ ሁሉ ትወስዳለች። ከዚህ በኋላ ለሚፈጠሩ ማናቸውም ቀውሶች እና ትንኮሳዎች አሜሪካ ሙሉ ኃላፊነቱን ትወስዳለች!" በማለት ቻይና ዛቻዋን አጠናክራለች።
​ይህ የቻይና እና የአሜሪካ እሰጥ አገባ ጉዳዩን ከኢራን አልፎ አለምን ወደ ከፋ ጦርነት እንዳያስገባት በብዙዎች ዘንድ ተሰግቷል! 👀🌍 አሜሪካስ ምን ምላሽ ትሰጥ ይሆን?
በቡርኪና ፋሶ 🇧🇫፣ ፕረዚዳንት ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ የቅኝ ግዛት እስር ቤቶችን አስወግዶ በእርሻ ልማት ፣ የግብርና ክህሎት ማሳደግያ ማእከል እንዲሆኑ አድርጓል።

ዓለም ትልልቅ እስር ቤቶችን ሲገነባ፣ ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ የቅኝ ግዛት እስር ቤቶችን በእርሻ ልማትና በግብርና በሰው ኃይል ልማት ተክቷቸዋል ።

በትራኦሬ የእስር ቤት ማሻሻያ ፕሮግራሙ በእርሻዎች ላይ ለሚሰሩ እስረኞች  በአመት የ3 ወር የእስራት ግዜ እንዲቀንስላቸው ይደረግላቸዋል።

አሁን ላይ የግብርና እርሻዎች  እስረኞች ወሳኝ የእርሻ ቴክኒኮችን የሚማሩበት፣ ለብሔራዊ ኢኮኖሚ በቀጥታ የሚያበረክቱበት እና የዓላማ ስሜት የሚያዳብሩበት ቦታዋች ናቸው።

ይህ ቅኝ ገዥዎች የተውት ስርዓት አይደለም። ይህ አፍሪካ ለራሷ የምታስብበት መንገ
ድ ነው!
---
🔶ትራምፕ ግብዣ ላይ ተኩስ_ተከፈተ

የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ለኋይት ሃውስ ቋሚ ዘጋቢዎች ባዘጋጁት የእራት ግብዣ ስነስርአት ላይ ተኩስ ተከፍቷል።

ትላንት ምሽት በዋሽንግተን ሂልተን ለኋይት ሀውስ ቋሚ ዘጋቢ የሚዲያ ባለሙያዎች በተዘጋጀ የእራት ግብዣ ላይ ፕሬዝዳንቱን ጨምሮ ባለቤታቸው ሜላኒያ ትራምፕ፣ ምክትል ፕሬዝደንት  ጄ.ዲ. ቫንስና ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናት የታደሙ ሲሆን ተኩስ እንደተከፈተ በፍጥነት በደህንነት አባላት ሽፋን ተሰጥቶአቸው ከስፍራው ተወስደዋል።

ተኩስ የከፈተው ግለሰብ ፕሬዝደንቱ በሚገኙበት 50 ያርድ ርቀት ገደማ ወደ መድረኩ እየሮጠ እንደነበር የተጠቆመ ሲሆን፣ በተኩሱ አንድ የደህንነት አባል በቅርብ ርቀት በጥይት ቢመታም ባደረገው የጥይት መከላከያ ጃኬት ከሞት መትረፍ መቻሉ ተገልፆአል።

ፕሬዝደንቱ ተኩሱን የከፈተው ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉን ይፋ አድርገው በተፈጠረው የተኩስ ልውውጥ  ጥቃት ተሰንዝሮበት ሕይወቱ የተረፈውን የደህንነት ባልደረባ አግኝተው ማናገራቸውንና በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝም ነው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የጠቆሙት።

================