الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም
22.5K subscribers
359 photos
17 videos
7 files
913 links
﴿وَمِنْ آيَاتِهِ أَنْ خَلَقَ لَكُم مِّنْ أَنفُسِكُمْ أَزْوَاجًا لِّتَسْكُنُوا إِلَيْهَا وَجَعَلَ بَيْنَكُم مَّوَدَّةً وَرَحْمَةً﴾

ለማንኛዉም አስተያየት☞☞ @Tidarbaislam_bot
ለይ ያድርሱን

ለጥያቄ ☞☞ t.me/Hayatbintkedir
Download Telegram
#ወንዶች
ሚስቶቻቹ ለናንተ እንደሚዋቡት ሁሉ እናንተም ልትዋቡላቸው ይገባል።
እሷን በኒሳዕ ሳሙና ታጠቢ እያልክ አንተ በአጃክስ/ላርጎ እንድትታጠብ ማን ፈቀደልክ?!

#እስኪ #ስሚ #እህቴ......

መንገድ ከጀመረ በተውሒድ ጎዳና
በነብያት መንገድ በሩሱሉ ፋና

በሽሪአ ልጓም መኖር ከጀመረ
የተውሒድ ቀለበት አጥብቆ ካሰረ

የእለት ተግባሩ ካረገ በሱና
ለዲኑ ታታሪ ማይበገር ጀግና

አኽላቁ ካማረሽ እንዲሁም ምግባሩ
ምርጫሽ ይሁን እሱ።
ምን አለሽ ከዘሩ!!❗️

            ቴሌግራማችን

╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ-
╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
አሰላሙ አለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካትሁ
አስደሳች ዜና በወንድማችን ሀሰን አህመድ
 
ጋብቻ  በኢስላም  
      ጣፋጩ  የህይወት  መንገድ በሚል ርዕስ አዲስ መፅሐፍ ለእህት ወንድሞቹ ለህዝበ ሙስሊሙ አበረከተ !!

መፅሐፉ ስለ ጋብቻ ምንነት ፣ስለ ጋብቻ አስፈላጊነትና  አንገብጋቢነት ፣ ስለ ትዳር በቂ የሆነ  ግንዛቤ   እንድንይዝ  የሚረዳን መፅሐፍ ነዉ ።


እንዲሁም መፅሀፉ ሰላም የሰፈነበትን፣እዝነትና ፍቅር የበዛበትን ፣ጣፋጭና ደስተኛ የትዳር ህይወት ለመመስረትና ለመምራት እንዲሁም ኢስላማዊ ቤተሰብ ለመገንባት ትልቅ አስተዋጽኦ ያደርጋል ።

መፅሃፉን ለማግኝት በዚህ አድራሻችን ያናግሩን👇
📞09_56_57_69_02/ 0956566902 ☜

📞ደዉለዉ ይዘዙን።
#ሼር_በማድረግም_ያስተላልፉ
☞ሴት ልጅ ከምታጌጥባቸው ጌጦች ሁሉ የተሻለው #ሃያእ_ነው
ሴቶች ሁሉ በተፈጥሯቸው ውቦች ናቸው።
#ሃያዕ ከነርሱ የተገፈፈ ጊዜ ግን የእውነት ፉንጋዎች❗️ ይሆናሉ።

አላህ ሆይ ለሙስሊም እህቶቻችን ሃያዕን አላብስልን አሚን።🤲
            ቴሌግራማችን

╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ-
╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
◾️:::::::::የማይነጋ ለሊት:::::::::◾️

መከራ በዝቶብኝ በሲቃ ሳነባ
ከጎኔ ሰው በዝቶ አንጀት የሚያባባ

እንደ ክረምት ዝናብ የዶፍ እንባ ካይኔ
ጭንቀቴ በርትቶ እንዳዘንኩኝ ያኔ

ልቤ ተሰብሮብኝ አይዞህ ባይ አጥቼ
ከተራራው ጫፍ ላይ ብቻዬን ወጥቼ

ማንም እንዳያየኝ ብቻዬን ብደበቅ
ማሰብም አቁሜ ከሰው ሁሉ ስርቅ

❗️ በጣም ተማርሬ

ከፈጣሪ ጋራ ክርክር ገጥሜ
ምነው የኔ ብቻ ጠፋብኝ አለሜ

ብዬ ስናገረው መች አስከፋኝ እሱ
የሚያሙህ ቢበዙ ስምህን እያነሱ

ችግርህ ቢበዛ ገዝፎ እንካን ቢቆለል
መያዣው ጠፍቶብህ ሀሳብህ ቢዋልል

ጠንከር በል እና ጥሩ ነገር አልም
የማይነጋ ለሊት የማያልፍ ቀን የለም።

            ቴሌግራማችን

╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ-
╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
"❗️ሊነጋ ሲል ይጨልማል
           ጨልሞ አይቀር ዳግም ይነጋል
         ተስፋ አትቁረጥ ሁሉም ያልፋል!"

      ነገን ለማየት የዛሬውን ጭለማ መታገስ
                           አለብክ!

                     ቴሌግራማችን

╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ-
╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
በስስስ ኮመንት ቀንሱ ምነው እህቶች እንደው ስራ የሌለን ይመስል አንድት ግሩፕ ክፍት ካገኘን ግርርርር ብለን ኮመን ህ!

እስኪ መሰተርን ከወንዶች እንማር ሴት ነበረች መሰተር ያለባት ሴቶች ግን በየኮመንቱ ስር ሲጫጭሩ የሚውሉት በቃ ጉዳዩ ተመቻቹህ እዚያ ዱዓ አድርጋቹህ ዝም በሉ ምነው ግን ስንት ስትር ሴቶች አንድ ኮመንት ስር የማትገኘ ባለችበት በናንተ ምክናየት አብራ ሴቶች ትባላለች

በተለይ በተለይ የወንዶች ቻናል ላይ የሚረባም የማይረባም ፁሁፍ ይፃፍ በቃ ክክክ ሀሀሀ ከዚያ ደግሞ በኮመንት ዱዓ ማድረግ ሹ ሀዳ ?

የሴቶች ቻናል ላይ ግን ጥያቄ እንኳን ቢለቀቅ አትሳተፉም ምን ጉድ ነው በረቢ



እስኪ እህቶች እንደው ለአላህ ብላቹህ ጉዳዩ አስፈላጊ ካልሆነ ዱዓም ይሁን ሙገሳ እባካቹህ እዚያው በውስጣቹህ አድርጉት እንደው በአላህ ይሁንባቹህ በያገኛቹህበት አትፃፉ

እስኪ የወንዶች ኮመንት አንድ አይገኘም
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#አደራ_አደራ_የምለው_ነገር_ቢኖር _በፅናት_ጉዳይ_ነው። ❗️

በተለይ በዚህ የሚገለባበጥ በበዛበት ወቅት የፅናት ጉዳይ እጅግ አንገብጋቢ ነው❗️!! በዚህን ጊዜ
#በሐቅ ላይ #በኢኽላስ መፅናት የተሰጠው ሰው አላህ ከሚሰጡ ነገሮች ትልቁን ስጦታ ሰጥቶታልና አላህን ሊያመሰግንና ፅናቱን አላህ እንዲያዞትርለት አላህን ሊለምን ይገበዋል!!።

ታላቁ ዓሊም ሙሀመድ ቢን ሷሊህ አል-ዑሰይሚን (ረሂመሁላህ) እንዲህ አሉ:-
“የሰው ልጅ ነፍሱ ከሰውነቱ እስከቆየች ድረስ ለፊትና የተጋለጠች ናት። በመሆኑም እራሴንም እናንተንም የምመክረው ዘውትር አላህን ፅናት እንዲሰጠን በመለመን ላይ ነው። ልትፈሩ ይገባል!፣ ምክንያቱም ከእግራቹ ስር የሚያዳልጡ ነገሮች አሉ። የላቀው አላህ ፅናቱን ካልሰጣችሁ ጥፋት ላይ ልትወድቁ ትችላላቹ።
አላህ ለመልክተኛው ﷺ የተናገረውን ስሙ:-

وَلَوْلَا أَن ثَبَّتْنَاكَ لَقَدْ كِدتَّ تَرْكَنُ إِلَيْهِمْ شَيْئًا قَلِيلًا

«ባላረጋንህም ኖሮ ወደነሱ ጥቂትን (ዝንባሌ) ልትዘነበል በእርግጥ በተቃረብክ ነበር፡፡» አል-ኢስራእ 74

ይህ የተባለው ለመልእክተኛው ﷺ ከሆነ የኛ ጉዳይስ እንዴት ይሆን?፣ እኛ በኢማናችንም በየቂናችንም ደካሞች ነን፣ ብዥታዎችና ስሜቶች ይቀጣጩናል። እኛ ከባድ የሆነ አደጋ ላይ ነን፣ የላቀውን አላህን ልባችንን ከቅኑ እንዳያዘነብልብን፣ በሐቅ ላይ ፅናት እንዲሰጠን ልንጠይቀው ይገባል፣ ይህ ነው የማስተዋል (የአዕምሮ) ባለ ቤቶች ዱዓ ማለት።

رَبَّنَا لَا تُزِغْ قُلُوبَنَا بَعْدَ إِذْ هَدَيْتَنَا وَهَبْ لَنَا مِن لَّدُنكَ رَحْمَةً ۚ إِنَّكَ أَنتَ الْوَهَّابُ

«እነሱም ይላሉ፡- "ጌታችን ሆይ! ቅኑን መንገድ ከመራሀን በኋላ ልቦቻችንን አታዘምብልብን፡፡ ከአንተ ዘንድ የሆነን ችሮታም ለኛ ስጠን፡፡ አንተ በጣም ለጋስ ነህና፡፡» ኣል-ዒምራን 8
[ሸርህ አልሙምቲዕ 5/388]

            ቴሌግራማችን

╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ-
╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
=>ከሀሰት ፍቅር ከጥላት ምክር ከውሸት
ትዳር ከመጥፎ ጓደኝ አላህ ይጠብቀን!

            ቴሌግራማችን

╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ-
╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
💥ሸይኽ ኢብኑ ዑሰይሚን አሏህ ይዘንላቸውና፦
((አንዲት ሴት ባሏን በሁለተኛ ሚስቱ ጥሎሽ መርዳት አለባት።))
فتاوى الحرم المكة١٤١٤
الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም
💥ሸይኽ ኢብኑ ዑሰይሚን አሏህ ይዘንላቸውና፦ ((አንዲት ሴት ባሏን በሁለተኛ ሚስቱ ጥሎሽ መርዳት አለባት።)) فتاوى الحرم المكة١٤١٤
👉እህቶች ባሎቻቹን ዳሩ የኔ ብቻ አትበሉ ሃቁን ከተወጣ 4 ያድርጋቹ  እንጂ አንቺም ሷሊሃ ጓደኛን ታገኚያለሽ።
እስከመቼ የኔ ብቻ????
ረሱል ስንት ሚስት ነበር ያገቡት ??
እና ያንቺ ባል ከረሱል በልጦ ነው ሌላ አያገባም የምትዩው በሀቁ የምተወጂው ከሆነ 2/3 ሲጨምር አትቆጪው እንዲጨምር ገፋፊው። ስንቶች ናቸው የሱና አንበሳ አጥተው ሳያገቡ የቀሩት በእርግጥ ሁሉ ነገር በአሏህ እጅ ነው ሰህ። ወላኪን አንቺም ሰበብያውን ማድረስ አለብሽ ላንቺ የወደድሽውን ለእህትሽም ውደጂ/ተመኚላት።
ኢንተቢሂ👈ሁሉም የዘራውን ነው ሚያጭደው። የዘራሽው ኸይር ከሆነ ኸይርን ታፍሻለሽ። በተቃራኒው ከሆነ ግን ዋ ፀፀቴ ነው መጨረሻሽ።


📌እናማ ስለ ሁለተኛ ሚስት ሲነሳ ራስሽን አይመምሽ እንደውም ድል ባለ ሰርግ ነው የምድረው ብለሽ ነፍሲያን+ሸይጧንን ራሳቸውን አሳምሚያቸው።
ሁለተኛ ላይ የሚያገባትንም እህትሽን አትዝለፊያት፣አትበዲያት  ያንቺንስ መጨረሻ በምን አወቅሽ?  መድረሻሽ ምን ላይ እንደሚቋጭ አታውቂምና ተጠንቀቂ ያ ኢኽቲል ጓሊያህ።


📌ሁለተኛ ሚስቶችም ሶስተኛ ሲጨምር አታጉረምርሙ ሶስተኞች ደግሞ አራተኛ ሲጨምር ፌንት አትስሩ ከአንደኛዋ ተማሩ።
ወንድሞች ደግሞ ምንም አይነት ዒልም ሳይኖራቹ ስለ ሁለተኛ ሚስት ሲወራ ሱብሃነክ እጃቹን እስኪያማቹ አትፃፉ እስኪ ስለሌላውም ርዕስ ተመካከሩ       ሁሌ ትዳር   ትዳር 👈  ያውም ላጤዎች   በሃሳብ አትዋኙ።
ኸይር አስቡና ወደ ተግባር ሂዱ በየግሩፑ ያሰባቹትን አታውሩ።     እናንተም ማላ ያዕኒን አታውሩ ሴቶች ብቻ አይደሉም የሚመከሩት።
💥ስሚኝ እህቴ የሚያምር ፀባይ ካለሽ ከማንም በላይ ቆንጆ ነሽ። አትገላለጪ!!
💥ዚና ሲቀል ኒካህ ይከብዳል!!!
አሏህ ይጠብቀን
☀️እህቴ ሆይ እስቲ አንዴ ከሂወትሽ ትንሽን ደቂቃ ቀንሰሽ እህህ ብለሽ ስሚኝ ምናልባት ይጠቅምሽ ይሆናል...

قال الرسول ﷺ: "الحياء شعبة من الإيمان"
💫 ነቢዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም እንዲህ ይላሉ :- "ሀያዕ ( ማፈር ) ከኢማን ቅርንጫፎች ውስጥ ነው "

💫 ውዷ እህቴ ሀያዕ ማድረግ ለሴት ልጅ  ክብር ነው እንደውም ውበቷም ጭምር ነው ።

💫 አንዳንድ እህቶች አሉ አለባበሳቸው፣ አረማመዳቸው፣ አነጋገራቸው ሀታ ካፊሮች የሚሻሏዋቸው አላህን እንፍራ ዛሬ እንደዚ እንድትመፃደቂ እንደዚ እንድትሆኚ የሚያደርጉሽ ነገሮች ሁሉ ያልፋሉ ይጠፋሉ ግና ለሚያልፍ ነገር ለሚጠፋ ነገር ብለን የነገው አኼራችንን የንገው የዘላለማዊ ሂወታችንን አናበላሻት ...

💫 ውዷ እህቴ ዛሬ ባንቺ ንግግር፣ ባንቺ አረማመድ፣ ባንቺ አወራር ተማርከው የሚያሞግሱሽ እና የሚያደንቁሽ ነገ ከእሳት ነገ ከቀብር ጭንቀት አያድኑሽም ካንቺ ቅጣት ቅንጣትን አይጋሩልሽም ሁሉም ነፍሴ ነፍሴ ነው ሚለው ስለዚህ ዛሬ ስሜትሽን ነፍስያሽን አሸንፈሽ ለነገው ሀገርሽ ብትለፊ መልካም ነው።

💫 ወላሂ ይደንቁኛል እነዚያ ኒቃብን ለብሰው፣ ጅልባብን ለብሳ ንግግሯን፣ ሳቋን፣ ከሩቅ የምትሰሟት ያረህማን ቢያንስ ለለበስነው ልብስ ክብር ይኑረን የሰው ልጅ ያው ሰው ነው ምንም አያመጣም ነገር ግን አላህን እንፍራ የለበስነው ልብስ አይደለም ኒቃብ፣ እና ጅልባብ ሀታ ጭንቅላትሽ ግማሽ ላይ ጣል ምታደርጊያት እስከርብ አንቺን  ከመሸፈኑ ባሻገር ኢስላም የሚል ትልቅ ባንዲራን ነው ይዘሽ ምትጓዢው ባንቺ አንዲት ስህተት ጥርሳችው የወለቀለትን፣ ደማቸው የፈሰሰለትን፣ እርቧችው ሆዳቸው ላይ ዲንጋይ ያሰሩለትን የኛ ነቢይ አለይሂሙ ሰላቱ ወሰላም  ይዘውት የመጡትን ዲን ሰሀቦች አጥንታቸውን ከስክሰው ለኛ ያስረከቡትን ዲን ባንቺ ስህተት ታሰድቢዋለሽ ቢላህ አለይኩም እህቶቼ ሁሉም ነገር ያልፋል ይሄዳል ምንም ማንም ሚቀር የለም አላህ ሱብሀነሁ ወተዐላ ሲቀር ስለዚህ ለሚያልፍ ነገር የማያልፍን ድርጊት አትስሪ ይቅርብሽ ዲንሽን አጥብቀሽ ያዢ ዲንሽ ነው ላንቺ የሚሆንሽ ስሜትሽ ነፍሲያሽን አትከተዪ።

💥 አፍወን አረዘምኩት አሁን ላይ የምናየው የምንሰማው ቢፃፍ ቢፃፍ አያልቅም አላህ ሁላችንንም ከመጥፎ ነገር ይጠብቀን ።
الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም
☀️እህቴ ሆይ እስቲ አንዴ ከሂወትሽ ትንሽን ደቂቃ ቀንሰሽ እህህ ብለሽ ስሚኝ ምናልባት ይጠቅምሽ ይሆናል... قال الرسول ﷺ: "الحياء شعبة من الإيمان" 💫 ነቢዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም እንዲህ ይላሉ :- "ሀያዕ ( ማፈር ) ከኢማን ቅርንጫፎች ውስጥ ነው " 💫 ውዷ እህቴ ሀያዕ ማድረግ ለሴት ልጅ  ክብር ነው እንደውም ውበቷም ጭምር ነው ። 💫 አንዳንድ እህቶች አሉ አለባበሳቸው፣…
#የቀጠለ
☀️በርካታ እህቶች ሒጃብ ከማድረጋቸው ጋር አንዳንድ ሒጃብ ካደረገች ሴት የማይጠበቁ ነገሮችን ሲያደርጉም ይስተዋላል ለምሳሌ፥መንገድ ላይ ሲሄዱና ታክሲ ውስጥ ሆነው ጮክ ብሎ ማውራት፣ መሳቅና መቀለድ፣ ያለ በቂ ምክንያት መንገድ ዳር ላይ በሚያጠራጥር መልኩ ከወንድ ጋር መቆም (ዘመድ/መሕረም እንኳ ቢሆን ይህ ተገቢ አይደለም)፣ ጅልባብ ላይ፤ ሻሽ (ሒጃብ) መጠቅለል፣ጃኬት መደረብ፣ ሲራመዱ ጅልባብን ወደ ላይ ሰብስቦ በመያዝ እግር/ባት እንዲታይ ማድረግ፣ ዘመዴ ነው የአጎት የአክስት ልጅ ነው ወዘተ እያሉ ለሱ ፊትን መግለጥና ተጠጋግቶ መቀመጥ፣ ካፌና ምግብ ቤት መመላለስ ማብዛትና እዛ ውስጥም አደብ የጣሰ አካሄድን መሄድ ወዘተ አንዳንድ እህቶች ጋ የሚታዩ ስህተቶች ናቸውና

እህቴ ሆይ፥ የሒጃብን አላማ እወቂ ዲንና ክብርሽንም ጠብቂ! ሒጃብ አድርገሽ የኢስላምን አደብ ባለመጠበቅሽ ምክንያት ኢስላምን አታሰድቢ
#ይቀጥላል...
📌ሴቶች መህራቹን ከፍ አታድርጉ ።
ሞዴልሽ እነ ሃፍሷ ፋጢማህ ሊሆኑ ይገባል!
الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም
#የቀጠለ ☀️በርካታ እህቶች ሒጃብ ከማድረጋቸው ጋር አንዳንድ ሒጃብ ካደረገች ሴት የማይጠበቁ ነገሮችን ሲያደርጉም ይስተዋላል ለምሳሌ፥መንገድ ላይ ሲሄዱና ታክሲ ውስጥ ሆነው ጮክ ብሎ ማውራት፣ መሳቅና መቀለድ፣ ያለ በቂ ምክንያት መንገድ ዳር ላይ በሚያጠራጥር መልኩ ከወንድ ጋር መቆም (ዘመድ/መሕረም እንኳ ቢሆን ይህ ተገቢ አይደለም)፣ ጅልባብ ላይ፤ ሻሽ (ሒጃብ) መጠቅለል፣ጃኬት መደረብ፣ ሲራመዱ ጅልባብን…
☀️ታክሲ/ትራንስፖርት ላይ በተወሰነ መልኩ ከወንድ ጋር መገናኘት (መቀራረብ) ሁኔታዎች የሚያስገድዱት ነገር ሊሆን ይችላል ይሁንና በተቻለሽ ያክል ከወንድ አጠገብ ላለመቀመጥ እንዲሁም ስትገቢ ከወንድ ጋር ላለመላፋት ሞክሪ።ነገር ግን! በምንም ሁኔታ ላይ ታክሲ እየጠበቅሽም ይሁን እየተጓዛሽ በሁለት ባዕድ ወንዶች መሃል አትሁኚ! (አትቁሚ/አትቀመጪ)! እጅግ በጣም የሚያሳዝነው አልፎ አልፎ ሙስሊም ሴት ከባጃጅ ሾፌር ጋር ጋቢና ቁጭ ብላ ሰውነቷን ከሰውነቱ ጋር አጣብቃ ስትሄድ ይታያል!!
فالله المستعان!
"እህት ሆይ፥ አላህን ፍሪ! ከእንዲህ ዓይነቱ ድርጊት ዲንና ኢማን ባያግድሽ ዓቅል/ህሊናሽ ሊከለክልሽ ይገባል!
💥((ሐያዕ የሌለው ኢማን የለውም))
#ይቀጥላል
            ቴሌግራማችን

╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ-
╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም
☀️ታክሲ/ትራንስፖርት ላይ በተወሰነ መልኩ ከወንድ ጋር መገናኘት (መቀራረብ) ሁኔታዎች የሚያስገድዱት ነገር ሊሆን ይችላል ይሁንና በተቻለሽ ያክል ከወንድ አጠገብ ላለመቀመጥ እንዲሁም ስትገቢ ከወንድ ጋር ላለመላፋት ሞክሪ።ነገር ግን! በምንም ሁኔታ ላይ ታክሲ እየጠበቅሽም ይሁን እየተጓዛሽ በሁለት ባዕድ ወንዶች መሃል አትሁኚ! (አትቁሚ/አትቀመጪ)! እጅግ በጣም የሚያሳዝነው አልፎ አልፎ ሙስሊም ሴት ከባጃጅ…
☀️በርካታ ወጣቶች (ሁለቱም ጾታዎች) ትዳር ሲያስቡና ጉዳዩን ሲጀምሩ ከእጮኛቸው ጋር የሚሄዱት አካሄድ በጣም ያሚያስፈራና አላህን የሚያስቆጣ የዲን አደብን የጣሰ የሚሆንበት ሁኔታ በሰፊው እየታየና እየተሰማ ነው። ለምሳሌ፥ ኒካሕ ሳይታሰር በፊት ስልክ መደዋወልና መጻጻፍን ማብዛት፣ ምሳ መገባበዝ/ አብሮ ሻይ ቡና ማለት፣ መጀመሪያ ተያይተው ጨርሰው ሳለ በተለያዩ ምክንያቶችና አጋጣሚዎች በተደጋጋሚ መተያየት ወዘተ ትልቅ ስህተትና ትዳሩ በወንጀል በመጀመሩ ምክንያትም  የወደፊት ህይወት ስኬት እንዲያጣ ሊያደርግ የሚችል ከመሆኑ አንጻር ለዲናችሁና ለራሳችሁ ህይወትም ስትሉ አካሄዳችሁን አስተካክሉ!
ይህ በእንዲህ እንዳለም እንዲህ ዓይነቱ አካሄድ ከኒካሕ በፊት የሐራም ግንኙነት ላይ እንዲወድቁ የሚያደርግ ከመሆኑም አንጻር እጅጉን ልትጠነቀቁትና የጠላታችንን የሸይጣንን በር ልትዘጋጋ ይገባናል
#የመጨረሻውን_በቀጣይ_ክፍል....
           
ቴሌግራማችን

╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ-
╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam