ከ427 በላይ ቻይናውያን ያለቁበት የኮሮና ቫይረስ እጅግ አሳሳቢ ሆኗል
**************
የብዙ ቻይናውይን ህይወት በመቅጠፍ ላይ የሚገኘው የኮሮና ቫይረስ ዛሬ ደግሞ ኤዢያ ታይምስ ይዞት በወጣው መረጃ መሰረት የሟቾች ቁጥር ከ427 በላይ መሻገሩ ተነግሯል፡፡ ከችግሩ አሳሳቢነት አንፃር ብዙ ጎረቤት ሃገሮች ከቻይና ጋር የሚያዋስናቸውን ድንበር ለመዝጋት የተገደዱ ሲሆን፤ ሌሎች ሃገራትም ወደቻይና የሚደረጉ ማንኛውም በረራዎችን ለማቆም እንደተገደዱ ተገልጿል፡፡
በሃገረ ቻይና እንዲሁ ቫይረሱ ለመጀመሪያ ጊዜ በተስፋፋባቸው ግዛቶች ምንም አይነት የመግባትና የመውጣት አንቅስቃሴ እንዳይደረግ ቢታገድም የስርጭቱ መጠን ከሚታሰበው ባላይ አሳሳቢ አየሆነ እንደመጣ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በተለይም ቫይረሱ በሁቤይ ግዛት ከምተገኘው ዉሃን ከተባለቸው ከተማ ለመጀመሪያ ጊዜ ከተነሳ በኋላ አሁን ላይ 20,661 የሚሆኑ ቻይናውያን ቫይረሱ እንዳለባቸው መታወቁ እና በአለም አቀፍ ደረጃም በ24 ሃገራት ውስጥ መስፋፋቱ አደጋው ከፍተኛ አንዲሆን አስችሏል፡፡
ቫይረሱ በሃገራቸው በሚኖሩ ዜጎች ላይ መታያቱን ያረጋገጡት የጂ 7 ሃገራትም (ካናዳ፣ ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ ጣልያን፣ ጃፓን፣ እንግሊዝ እና አሜሪካ) በችግሩ ላይ በትብብር በመስራት ምላሽ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን የጀርመን የጤና ሚኒስቴር ጄንስ ፋህን በትላንትናው ዕለት ተናግረዋል፡፡
የኮሮና ቫይረስ አስካሁን ድረስ ምንም አይነት ፈዋሽ መድኃኒት ወይም ክትባት ያልተገኘለት ሲሆን በዋናነት የመተንፈሻ አካላትን በማጥቃት ሰዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለሞት የሚዳርግ በሽታ ነው፡፡ የኮሮና ቫይረስ እንደአውሮፓውያኑ በ2003 በቻይና ከተከሰተው “ሳርስ” በሽታ ጋር የመተንፈሻ አካልን በማጥቃት በኩል ተመሳሳይ ቢመስልም፤ የስርጭት መጠኑ እና የሚያደርሰው ጉዳት ግን እጅግ ከፍተኛ መሆኑ የሚለየው ጉዳይ ነው፡፡
Asia Times
**************
የብዙ ቻይናውይን ህይወት በመቅጠፍ ላይ የሚገኘው የኮሮና ቫይረስ ዛሬ ደግሞ ኤዢያ ታይምስ ይዞት በወጣው መረጃ መሰረት የሟቾች ቁጥር ከ427 በላይ መሻገሩ ተነግሯል፡፡ ከችግሩ አሳሳቢነት አንፃር ብዙ ጎረቤት ሃገሮች ከቻይና ጋር የሚያዋስናቸውን ድንበር ለመዝጋት የተገደዱ ሲሆን፤ ሌሎች ሃገራትም ወደቻይና የሚደረጉ ማንኛውም በረራዎችን ለማቆም እንደተገደዱ ተገልጿል፡፡
በሃገረ ቻይና እንዲሁ ቫይረሱ ለመጀመሪያ ጊዜ በተስፋፋባቸው ግዛቶች ምንም አይነት የመግባትና የመውጣት አንቅስቃሴ እንዳይደረግ ቢታገድም የስርጭቱ መጠን ከሚታሰበው ባላይ አሳሳቢ አየሆነ እንደመጣ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በተለይም ቫይረሱ በሁቤይ ግዛት ከምተገኘው ዉሃን ከተባለቸው ከተማ ለመጀመሪያ ጊዜ ከተነሳ በኋላ አሁን ላይ 20,661 የሚሆኑ ቻይናውያን ቫይረሱ እንዳለባቸው መታወቁ እና በአለም አቀፍ ደረጃም በ24 ሃገራት ውስጥ መስፋፋቱ አደጋው ከፍተኛ አንዲሆን አስችሏል፡፡
ቫይረሱ በሃገራቸው በሚኖሩ ዜጎች ላይ መታያቱን ያረጋገጡት የጂ 7 ሃገራትም (ካናዳ፣ ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ ጣልያን፣ ጃፓን፣ እንግሊዝ እና አሜሪካ) በችግሩ ላይ በትብብር በመስራት ምላሽ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን የጀርመን የጤና ሚኒስቴር ጄንስ ፋህን በትላንትናው ዕለት ተናግረዋል፡፡
የኮሮና ቫይረስ አስካሁን ድረስ ምንም አይነት ፈዋሽ መድኃኒት ወይም ክትባት ያልተገኘለት ሲሆን በዋናነት የመተንፈሻ አካላትን በማጥቃት ሰዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለሞት የሚዳርግ በሽታ ነው፡፡ የኮሮና ቫይረስ እንደአውሮፓውያኑ በ2003 በቻይና ከተከሰተው “ሳርስ” በሽታ ጋር የመተንፈሻ አካልን በማጥቃት በኩል ተመሳሳይ ቢመስልም፤ የስርጭት መጠኑ እና የሚያደርሰው ጉዳት ግን እጅግ ከፍተኛ መሆኑ የሚለየው ጉዳይ ነው፡፡
Asia Times
ቨርቹዋል ሪያሊቲ ሰዎችን የመታደግ ስራውን ቀጥሏል
****************
ምናባዊ ምስለ-እውነታ ወይም ቨርቹዋል ሪያሊቲ ያለ ምንም ጭስ፣ ያለ ምንም ውሀ እንዲሁም ያለ ምንም ብክነትና ቆሻሻ በውስጡ በያዛቸው አስደናቂ ቴክኖሎጂዎች በመታገዝ ብቻ የእሳት አደጋ ሰራተኞችን ማሰልጠን ስለመቻሉ እየተነገረ ይገኛል፡፡ የቨርቹዋል ሪያሊቲ የእሳት አደጋ ሰራተኞች በስልጠና ወቅት በብዛት ተጋላጭ የሚሆኑበትን አደገኛ ሁኔታዎችን አስመስሎ በመፍጠር የእሳት አደጋ መከላከል አገልግሎት ስልጠናን ማዘመን እንዳስቻለ ተገልጿል፡፡
እንደሚታወቀው አውስትራሊያ ባለፉት አስርት አመታት ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በአስከፊ እሳት አደጋ መጎዳቷ የሚታወስ ሲሆን፤ በአደጋውም ከ2.3 ሚሊዮን ሄክታር በላይ በቃጠሎ እንደወደመ እና ወደ ግማሽ ቢሊዮች የሚጠጉ እንስሳት ላይም ጉዳት እንደደረሰ የሚታወቅ ነው፡፡ ሳይንቲስቶችም የአየር ንብረት ለውጡን ለጉዳቱ መባባስ በምክንያትነት ያስቀመጡ ሲሆን፤ በካሊፎርኒያም ተመሳሳይ ተፅዕኖዎችን እንደተመለከቱ ገልፀዋል፡፡
ታዲያ እነዚህን የመሰሉ የእሳት አደጋዎች በብዛት እየተፈጠሩ ከመሆናቸው ጋር ተያይዞ የእሳት አደጋ ሰራተኞች ችግሩን ለመቋቋም ወደሚያስችላቸው አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ፊታቸውን እያዞሩ ይገኛሉ፡፡ በተለይም በአውስትራሊያ እና አሜሪካ የሚገኙ አንዳንድ የእሳት አደጋ ዲፓርመንቶች የእሳት አደጋ ባለሙያዎችን ለማሰልጠን የቨርቹዋል ሪያሊቲ (ምናባዊ ምስለ-እውነታ) ቴክኖሎጂን መጠቀም ጀምረዋል፡፡
አውስትራሊያ ላይ መቀመጫውን ያደረገው ፍሌም ሲስተምስ የተባለው ኩባንያ ለእሳት አደጋ ሰራተኞች ይህን የምናባዊ ምስለ-እውነታ ማሰልጠኛ ቴክኖሎጂ ያበለፀገ ሲሆን ሰልጣኞች የጆሮ ማዳመጫና የቪ.አር መነፅር በማድረግ ብቻ በእውኑ አለም ሳይገኙ እንዲሰለጥኑ በማድረግ የእውነተኛ-የህይወት ሁኔታዎች ውስጥ ጠልቀው እንዲገቡ እና ይበልጥ ዝግጁ እንዲሆኑ መደረጉን ተነግሯል፡፡
ቴክኖሎጂው ምናባዊ ጭስ፣ እሳት፣ ውሀ እንዲሁም የእሳት ማጥፊያ ፎም በተለያዩ ሁኔታዎች እንደ ቤት ቃጠሎ፣ የአውሮፕላን ቃጠሎ ወይም የዱር ቃጠሎ ምስለ-መልክ ይፈጥራል፤ ሰልጣኞችም የእያንዳንዱን ሁኔታ የሙቀት መጠን አስመስሎ የሚፈጥር ሙቀትን የሚያመነጭ ልብስ እንዲለብሱ በማድረግ እንዲሁም የእሳቱን ቅርበት እና አቅጣጫ በመወሰን ግለሰቡ ላይ በምን ያህል መጠን ተፅዕኖ እንደሚኖረው በሚወስን ሶፍትዌር ቁጥጥር ይደረግበታል፡፡
የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቴክኖሎጂን በእሳት አደጋ ስልጠና ላይ መጠቀም አካባቢያዊ ተፅዕኖዎችን የሚቀንስ ሲሆን ከዚህ በፊት የተለመደው የስልጠና አሰጣጥ ከሚቃጠሉ ንጥረ ነገሮች ጭስንና ሌሎች በካዮችን ወደ አየር እንዲለቀቁ የሚያደርግ፣ ለስልጠናው ሲባል ብቻ መጠኑ ብዙ የሆነ ውሀን የሚጠይቅና ይህም በብዛት ድርቅ ለሚያጠቃቸው አካባቢዎች በራሱ ችግር የሚፈጥረውን ሁኔታ እንደሚያስቀር ታምኖበታል፡፡ እንዲሁም በስልጠና ወቅት የሚጠቀሙት የእሳት ማጥፊያ ኬሚካል ፎምም በእሳት አደጋ ሰራተኞች ላይ የጎንዮሽ የጤና ጉዳት ከማስከተሉ ባሻገር የኬሚካሉ ፍሳሽ ለአፈርና ውሀ መበከል አይነተኛ አስተዋፅዖ ከማድረጉ አንፃር፤ አዲሱ የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቴክኖሎጂ አየርን የሚበክሉትን እነዚህን ኬሚካል ፎሞች እና ጭስን መጠቀም ሳያስፈልገው፣ ውሀንም መጠቀም ሳይጠይቅ ለእሳት አደጋ ሰራተኞች በተሻለ ሁኔታ ስልጠና እንዲያገኙ ማስቻሉ በዘገባው ተገልጿል፡፡
ምንጭ፡ ሲ.ኤን.ኤን
****************
ምናባዊ ምስለ-እውነታ ወይም ቨርቹዋል ሪያሊቲ ያለ ምንም ጭስ፣ ያለ ምንም ውሀ እንዲሁም ያለ ምንም ብክነትና ቆሻሻ በውስጡ በያዛቸው አስደናቂ ቴክኖሎጂዎች በመታገዝ ብቻ የእሳት አደጋ ሰራተኞችን ማሰልጠን ስለመቻሉ እየተነገረ ይገኛል፡፡ የቨርቹዋል ሪያሊቲ የእሳት አደጋ ሰራተኞች በስልጠና ወቅት በብዛት ተጋላጭ የሚሆኑበትን አደገኛ ሁኔታዎችን አስመስሎ በመፍጠር የእሳት አደጋ መከላከል አገልግሎት ስልጠናን ማዘመን እንዳስቻለ ተገልጿል፡፡
እንደሚታወቀው አውስትራሊያ ባለፉት አስርት አመታት ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በአስከፊ እሳት አደጋ መጎዳቷ የሚታወስ ሲሆን፤ በአደጋውም ከ2.3 ሚሊዮን ሄክታር በላይ በቃጠሎ እንደወደመ እና ወደ ግማሽ ቢሊዮች የሚጠጉ እንስሳት ላይም ጉዳት እንደደረሰ የሚታወቅ ነው፡፡ ሳይንቲስቶችም የአየር ንብረት ለውጡን ለጉዳቱ መባባስ በምክንያትነት ያስቀመጡ ሲሆን፤ በካሊፎርኒያም ተመሳሳይ ተፅዕኖዎችን እንደተመለከቱ ገልፀዋል፡፡
ታዲያ እነዚህን የመሰሉ የእሳት አደጋዎች በብዛት እየተፈጠሩ ከመሆናቸው ጋር ተያይዞ የእሳት አደጋ ሰራተኞች ችግሩን ለመቋቋም ወደሚያስችላቸው አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ፊታቸውን እያዞሩ ይገኛሉ፡፡ በተለይም በአውስትራሊያ እና አሜሪካ የሚገኙ አንዳንድ የእሳት አደጋ ዲፓርመንቶች የእሳት አደጋ ባለሙያዎችን ለማሰልጠን የቨርቹዋል ሪያሊቲ (ምናባዊ ምስለ-እውነታ) ቴክኖሎጂን መጠቀም ጀምረዋል፡፡
አውስትራሊያ ላይ መቀመጫውን ያደረገው ፍሌም ሲስተምስ የተባለው ኩባንያ ለእሳት አደጋ ሰራተኞች ይህን የምናባዊ ምስለ-እውነታ ማሰልጠኛ ቴክኖሎጂ ያበለፀገ ሲሆን ሰልጣኞች የጆሮ ማዳመጫና የቪ.አር መነፅር በማድረግ ብቻ በእውኑ አለም ሳይገኙ እንዲሰለጥኑ በማድረግ የእውነተኛ-የህይወት ሁኔታዎች ውስጥ ጠልቀው እንዲገቡ እና ይበልጥ ዝግጁ እንዲሆኑ መደረጉን ተነግሯል፡፡
ቴክኖሎጂው ምናባዊ ጭስ፣ እሳት፣ ውሀ እንዲሁም የእሳት ማጥፊያ ፎም በተለያዩ ሁኔታዎች እንደ ቤት ቃጠሎ፣ የአውሮፕላን ቃጠሎ ወይም የዱር ቃጠሎ ምስለ-መልክ ይፈጥራል፤ ሰልጣኞችም የእያንዳንዱን ሁኔታ የሙቀት መጠን አስመስሎ የሚፈጥር ሙቀትን የሚያመነጭ ልብስ እንዲለብሱ በማድረግ እንዲሁም የእሳቱን ቅርበት እና አቅጣጫ በመወሰን ግለሰቡ ላይ በምን ያህል መጠን ተፅዕኖ እንደሚኖረው በሚወስን ሶፍትዌር ቁጥጥር ይደረግበታል፡፡
የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቴክኖሎጂን በእሳት አደጋ ስልጠና ላይ መጠቀም አካባቢያዊ ተፅዕኖዎችን የሚቀንስ ሲሆን ከዚህ በፊት የተለመደው የስልጠና አሰጣጥ ከሚቃጠሉ ንጥረ ነገሮች ጭስንና ሌሎች በካዮችን ወደ አየር እንዲለቀቁ የሚያደርግ፣ ለስልጠናው ሲባል ብቻ መጠኑ ብዙ የሆነ ውሀን የሚጠይቅና ይህም በብዛት ድርቅ ለሚያጠቃቸው አካባቢዎች በራሱ ችግር የሚፈጥረውን ሁኔታ እንደሚያስቀር ታምኖበታል፡፡ እንዲሁም በስልጠና ወቅት የሚጠቀሙት የእሳት ማጥፊያ ኬሚካል ፎምም በእሳት አደጋ ሰራተኞች ላይ የጎንዮሽ የጤና ጉዳት ከማስከተሉ ባሻገር የኬሚካሉ ፍሳሽ ለአፈርና ውሀ መበከል አይነተኛ አስተዋፅዖ ከማድረጉ አንፃር፤ አዲሱ የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቴክኖሎጂ አየርን የሚበክሉትን እነዚህን ኬሚካል ፎሞች እና ጭስን መጠቀም ሳያስፈልገው፣ ውሀንም መጠቀም ሳይጠይቅ ለእሳት አደጋ ሰራተኞች በተሻለ ሁኔታ ስልጠና እንዲያገኙ ማስቻሉ በዘገባው ተገልጿል፡፡
ምንጭ፡ ሲ.ኤን.ኤን
ከተወለደ 30 ሰዓት ብቻ የሆነው ህፃን በኮሮና ቫይረስ ተጠቅቷል
#########################
በቻይና አዲስ የተወለደ ህፃን ባልታሰበ ሁኔታ የቫይረሱ ተጠቂ መሆኑ እያነጋገረ ይገኛል፡፡ በየካቲት ሁለት ቫይረሱ በተስፋፋበት ዉሃን ከተማ ወስጥ በሚገኝ በአንድ ሆስፒታል የተወለደው ይህ ህፃን በ30 ሰዓቱ በቫይረሱ መጠቃቱ እጅግ ድንጋጤን እንደፈጠረ ተነግሯል፡፡ የህፃኑ እናት ልጇን ከመውለዷ በፊት በተደረገላት ምርመራ ምንም እንኳን ቫይረሱ እንዳለባት የተረጋገጠ ቢሆንም የተወለደው ህፃን ግን በምን መልኩ ቫይረሱ ሊተላለፍበት እንደቻለ አለመታወቁን የሆስፒታሉ አዋላጆች ተናግረዋል፡፡
የሃገሪቱ የዜና አውታር ዢንዋ እንደዘገበው ህፃኑ በሚወለድበት ጊዜ ምንም አይነት ችግር እንዳልነበረ ጠቅሶ በሰዓታት ልዩነት ውሰጥ ግን በቫይረሱ እንዴት ሊጠቃ እንደቻለ ግልፅ አለመሆኑን በትላንትናው ዕለት ይፋ አድረጓል፡፡ የተወለደው ህፃን አሁን ላይ በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኝ የዘገበው ዢንዋ እሰካሁን ቫይረሱ ካለባቸው ውስን ህጻናት ውስጥም በእድሜ ትንሹ እንደሆነ ገልጿል፡፡
ውሃን በሚገኘው የህፃናት ሆስፒታል ያሉት ሃኪሞች ቫይረሱ ከእናት ወደ ልጅ የተላለፈበትን ምክንያት በግልፅ ለማወቅ ቢቸገሩም ምናልባት ገና በማህፀን እያለ ቫይሩሱ ተላልፎበት ይሆናል የሚል ግምት አላቸው፡፡ ይሁንና ሌሎች የጤና ባለሙያዎች ህፃኑ ከተወለደ በኋላ ከእናቱ ጋር በሚኖር የቅርብ ንክኪ በቫይረሱ ሳይያዝ እንዳልቀረ ግምታቸውን አስቀምጠዋል፡፡ በተለይም ዜንግ ሊንግሆንክ የተባሉት ሃኪም እንደገለፁት ይህ ሁኔታ የኮሮና ቫይረስ ከእናት ወደ ልጅ በከፍተኛ ሁኔታ የመተላለፍ እድል እንዳለው ተረድተን ተገቢውን ጥንቃቄ እንድንወስድ የጠቆመን ነው ብለዋል፡፡
የኮሮና ቫይረስ አሁን ላይ ከ49 እስከ 50 ባሉት የእድሜ ክልሎች ላይ በስፋት ቢስተዋልም አልፎ አልፎ ግን ህፃናት ላይ የመታየት እድል እንዳለው ተጠቁሟል፡፡ ቫይረሱ አሁን ባለው ዘገባ የስርጭት መጠኑ ጨምሮ 28 የሚጠጉ ሰዎችን የያዘ ሲሆን በጠቅላለውም 560 የሚሆኑት ደግሞ ህይወታቸውን ያጡ ሆነዋል፡፡
ቢቢሲ
#########################
በቻይና አዲስ የተወለደ ህፃን ባልታሰበ ሁኔታ የቫይረሱ ተጠቂ መሆኑ እያነጋገረ ይገኛል፡፡ በየካቲት ሁለት ቫይረሱ በተስፋፋበት ዉሃን ከተማ ወስጥ በሚገኝ በአንድ ሆስፒታል የተወለደው ይህ ህፃን በ30 ሰዓቱ በቫይረሱ መጠቃቱ እጅግ ድንጋጤን እንደፈጠረ ተነግሯል፡፡ የህፃኑ እናት ልጇን ከመውለዷ በፊት በተደረገላት ምርመራ ምንም እንኳን ቫይረሱ እንዳለባት የተረጋገጠ ቢሆንም የተወለደው ህፃን ግን በምን መልኩ ቫይረሱ ሊተላለፍበት እንደቻለ አለመታወቁን የሆስፒታሉ አዋላጆች ተናግረዋል፡፡
የሃገሪቱ የዜና አውታር ዢንዋ እንደዘገበው ህፃኑ በሚወለድበት ጊዜ ምንም አይነት ችግር እንዳልነበረ ጠቅሶ በሰዓታት ልዩነት ውሰጥ ግን በቫይረሱ እንዴት ሊጠቃ እንደቻለ ግልፅ አለመሆኑን በትላንትናው ዕለት ይፋ አድረጓል፡፡ የተወለደው ህፃን አሁን ላይ በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኝ የዘገበው ዢንዋ እሰካሁን ቫይረሱ ካለባቸው ውስን ህጻናት ውስጥም በእድሜ ትንሹ እንደሆነ ገልጿል፡፡
ውሃን በሚገኘው የህፃናት ሆስፒታል ያሉት ሃኪሞች ቫይረሱ ከእናት ወደ ልጅ የተላለፈበትን ምክንያት በግልፅ ለማወቅ ቢቸገሩም ምናልባት ገና በማህፀን እያለ ቫይሩሱ ተላልፎበት ይሆናል የሚል ግምት አላቸው፡፡ ይሁንና ሌሎች የጤና ባለሙያዎች ህፃኑ ከተወለደ በኋላ ከእናቱ ጋር በሚኖር የቅርብ ንክኪ በቫይረሱ ሳይያዝ እንዳልቀረ ግምታቸውን አስቀምጠዋል፡፡ በተለይም ዜንግ ሊንግሆንክ የተባሉት ሃኪም እንደገለፁት ይህ ሁኔታ የኮሮና ቫይረስ ከእናት ወደ ልጅ በከፍተኛ ሁኔታ የመተላለፍ እድል እንዳለው ተረድተን ተገቢውን ጥንቃቄ እንድንወስድ የጠቆመን ነው ብለዋል፡፡
የኮሮና ቫይረስ አሁን ላይ ከ49 እስከ 50 ባሉት የእድሜ ክልሎች ላይ በስፋት ቢስተዋልም አልፎ አልፎ ግን ህፃናት ላይ የመታየት እድል እንዳለው ተጠቁሟል፡፡ ቫይረሱ አሁን ባለው ዘገባ የስርጭት መጠኑ ጨምሮ 28 የሚጠጉ ሰዎችን የያዘ ሲሆን በጠቅላለውም 560 የሚሆኑት ደግሞ ህይወታቸውን ያጡ ሆነዋል፡፡
ቢቢሲ
ባዮሜትሪክስ ቴክኖሎጂ ምንድን ነው?
*************************
ባዮሜትሪክስ የሚለው ቃሉ ቀጥታ ከግሪክ የተወሰደ ሲሆን “ባዮ” ማለት ህይወት፣ “ሜትሪክስ” ደግሞ መለካት ወይም ልኬት ማለት ነው። ሁለቱ ቃላት በአንድነት ሲነበቡ ደግሞ የህይወት መለኪያ/ልኬት የሚለውን ትርጉም ይሰጣሉ። ባዮሜትሪክስ የአንድን ነገር ተፈጥሯዊ ባህሪ ማለትም የዲ ኤን ኤ አደራደር፣ የዓይን ቀለምና ምጣኔ፣ የእጅ አሻራ፣ የድምፅ ሞገድ፣ የልብና ነርቭ መንገድ እንቅስቃሴ የሚያጠና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ነው። ወይም ደግሞ ባዮሜትሪክስ የአንድን ሰው ማንነት በግልጥ በሰውነት ገፅታው ወይም በውስጣዊ ሥነ ህይወታዊ ባህሪው መረጃ ላይ በመመስረት ስለ ሰውየው አጠቃላይ ሁኔታ ማውራት የሚያስችል የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ነው። እነዚህ ባህሪያት በቀላሉ የማይረሱ፤ የማይጋሩና የማይሰረቁ መሆናቸው ልዩ የሚያደርገው ጉዳይ ነው፡፡
የባዮሜትሪክስ ቴክኖሎጂ በጥንት ጊዜ ከክስቶስ ልደት በፊት ከ500BC ጀምሮ የባቢሎናውያን የንግድ ልውውጦች የጣት አሻራዎችን ሸክላ ላይ በማስቀመጥ ይጠቀሙ የነበረ ቢሆንም በትክክል በዘማናዊ ቴክኖሎጂ መልክ ይዞ ግን በስፋትና በረቀቀ መልኩ አገልግሎት መስጠት የተጀመረው እኤአ ከ1981 በኋላ ስለመሆኑ ይነገራል፡፡ በዚህም መሰረት ባዮሜትሪክስ ቴክኖሎጂ አሁን ካለንበት የቴክኖሎጂ ጣሪያ ላይ ደርሶ የረቀቁ ወንጀሎች ሲፈፀሙ የሰዎችን ማንነት ለማወቅ የሚጠቅም የአሻራ ቴክኖሎጂ በመሆን በስፋት አገልግሎት ላይ እየዋለ ይገኛል፡፡
በአሁኑ ጊዜ ባዮሜትሪክስ ትልቅ ፋይዳ ያለው የቴክኖሎጂ ውጤት ሲሆን፤ አስፈላጊነቱም ከጊዜ ወደ ጊዜ በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ የመጣውን የዓለም የደህንነት ጥያቄ በመመለስ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል። በተለይም በትምህርት ተቋማት፣ ህክምና ተቋማት፣ በታላላቅ ኢንዱስትሪዎች፣ መንግስታዊ በሆኑና ባልሆኑ ድርጅቶች፣ በደህንነት ተቋማት እና በሌሎችም ተቋማት ውስጥ ከፍተኛ ሚና በመጫወት ላይ ይገኛል።
የባዮሜትሪክ ቴክኖሎጂዎች መገለጫዎች
* ዩኒቨርሳሊቲ፡ በአለም ላይ ያለ እያንዳንዱ ሰው የራሱ የሆነ ልዩ ባህሪ ሊኖረው ይገባል
* ልዩነት፡ በአጠቃላይ ሁለት ሰዎች አንድ ዓይነት ባሕርይ የላቸውም ፡፡ ሆኖም ተመሳሳይ የሆኑ መንትዮች ለመለየት ከባድ ናቸው ፡፡
* ዘላቂነት፡ የሰዎች የባዮሜትሪክስ ባህሪ ከጊዜ ጋር ልዩነት ሊኖራቸው አይገባም ለምሳሌ ፣ የአንድ ሰው ፊት ከእድሜ ጋር ሊለወጥ ቢችልም በቴክኖሎጂው የመለየት እድሉ ሰፊ ነው።
* ተቀባይነት፡ በሁሉም አለማት ላይ ተመሳሳይ መሆኑና ሁሉም የተቀበሉት መሆኑ
* አስቸጋሪነት፡ ይህም ማለት ሰዎች ለመሸወድ ወይም ለማጭበርብር የማይሞክሩት መሆኑ
ባዮሜትሪክ ቴክኖሎጂ ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች መካከል፡-
1. የጣት አሻራ ቴክኖሎጂ
2. የፊት ገፅታን የሚለይ ቴክኖሎጂ
3. የአይን እይታ ቴክኖሎጂ
4. የድምፅ ቴክኖሎጂ የሚሉት ከብዙዎች መካከል ጥቂቶች ናቸው፡፡
የባዮሜትሪክስ ጠቀሜታ
* የወንጀል ድርጊት ከመፈፀሙ በፊትና ከተፈፀመ በኋላ የሰዎችን ማንነት ለመለየት የሚያገለግል ቴክኖሎጂ ሲሆን ለምሳሌ አንድ ሰው የተለያዩ አለማትን በሚዞርበት ወይም በሚጎበኝበት ወቅት በሚዳረስባቸው ቦታዎች በሚገኙ የኢሚግሬሽን ጣቢያዎች ላይ የጣት አሻራ እንዲሰጥ ይጠየቃል ይህም በሀገር እና ግለሰብ ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን ወይም የወንጀል ድርጊቶችን ለመቆጣጠር ያስችላል፡፡
* በበርካታ የመንግስትና የግል ድርጅቶች፣ ባንኮች እና የገንዘብ ተቋማት እንደ ሰዓት መቆጣጠሪያ ይጠቅማል
* የባዮሜትሪክ ሥርዓቶች ሰዎችን በፍጥነት፣ በቋሚነት እና በአስተማማኝ ሁኔታ በመለየት ከፍተኛ ጥቅም ይሰጣሉ
ምንጭ፡ biometricupdate.com እና Si Tech Bufe
*************************
ባዮሜትሪክስ የሚለው ቃሉ ቀጥታ ከግሪክ የተወሰደ ሲሆን “ባዮ” ማለት ህይወት፣ “ሜትሪክስ” ደግሞ መለካት ወይም ልኬት ማለት ነው። ሁለቱ ቃላት በአንድነት ሲነበቡ ደግሞ የህይወት መለኪያ/ልኬት የሚለውን ትርጉም ይሰጣሉ። ባዮሜትሪክስ የአንድን ነገር ተፈጥሯዊ ባህሪ ማለትም የዲ ኤን ኤ አደራደር፣ የዓይን ቀለምና ምጣኔ፣ የእጅ አሻራ፣ የድምፅ ሞገድ፣ የልብና ነርቭ መንገድ እንቅስቃሴ የሚያጠና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ነው። ወይም ደግሞ ባዮሜትሪክስ የአንድን ሰው ማንነት በግልጥ በሰውነት ገፅታው ወይም በውስጣዊ ሥነ ህይወታዊ ባህሪው መረጃ ላይ በመመስረት ስለ ሰውየው አጠቃላይ ሁኔታ ማውራት የሚያስችል የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ነው። እነዚህ ባህሪያት በቀላሉ የማይረሱ፤ የማይጋሩና የማይሰረቁ መሆናቸው ልዩ የሚያደርገው ጉዳይ ነው፡፡
የባዮሜትሪክስ ቴክኖሎጂ በጥንት ጊዜ ከክስቶስ ልደት በፊት ከ500BC ጀምሮ የባቢሎናውያን የንግድ ልውውጦች የጣት አሻራዎችን ሸክላ ላይ በማስቀመጥ ይጠቀሙ የነበረ ቢሆንም በትክክል በዘማናዊ ቴክኖሎጂ መልክ ይዞ ግን በስፋትና በረቀቀ መልኩ አገልግሎት መስጠት የተጀመረው እኤአ ከ1981 በኋላ ስለመሆኑ ይነገራል፡፡ በዚህም መሰረት ባዮሜትሪክስ ቴክኖሎጂ አሁን ካለንበት የቴክኖሎጂ ጣሪያ ላይ ደርሶ የረቀቁ ወንጀሎች ሲፈፀሙ የሰዎችን ማንነት ለማወቅ የሚጠቅም የአሻራ ቴክኖሎጂ በመሆን በስፋት አገልግሎት ላይ እየዋለ ይገኛል፡፡
በአሁኑ ጊዜ ባዮሜትሪክስ ትልቅ ፋይዳ ያለው የቴክኖሎጂ ውጤት ሲሆን፤ አስፈላጊነቱም ከጊዜ ወደ ጊዜ በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ የመጣውን የዓለም የደህንነት ጥያቄ በመመለስ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል። በተለይም በትምህርት ተቋማት፣ ህክምና ተቋማት፣ በታላላቅ ኢንዱስትሪዎች፣ መንግስታዊ በሆኑና ባልሆኑ ድርጅቶች፣ በደህንነት ተቋማት እና በሌሎችም ተቋማት ውስጥ ከፍተኛ ሚና በመጫወት ላይ ይገኛል።
የባዮሜትሪክ ቴክኖሎጂዎች መገለጫዎች
* ዩኒቨርሳሊቲ፡ በአለም ላይ ያለ እያንዳንዱ ሰው የራሱ የሆነ ልዩ ባህሪ ሊኖረው ይገባል
* ልዩነት፡ በአጠቃላይ ሁለት ሰዎች አንድ ዓይነት ባሕርይ የላቸውም ፡፡ ሆኖም ተመሳሳይ የሆኑ መንትዮች ለመለየት ከባድ ናቸው ፡፡
* ዘላቂነት፡ የሰዎች የባዮሜትሪክስ ባህሪ ከጊዜ ጋር ልዩነት ሊኖራቸው አይገባም ለምሳሌ ፣ የአንድ ሰው ፊት ከእድሜ ጋር ሊለወጥ ቢችልም በቴክኖሎጂው የመለየት እድሉ ሰፊ ነው።
* ተቀባይነት፡ በሁሉም አለማት ላይ ተመሳሳይ መሆኑና ሁሉም የተቀበሉት መሆኑ
* አስቸጋሪነት፡ ይህም ማለት ሰዎች ለመሸወድ ወይም ለማጭበርብር የማይሞክሩት መሆኑ
ባዮሜትሪክ ቴክኖሎጂ ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች መካከል፡-
1. የጣት አሻራ ቴክኖሎጂ
2. የፊት ገፅታን የሚለይ ቴክኖሎጂ
3. የአይን እይታ ቴክኖሎጂ
4. የድምፅ ቴክኖሎጂ የሚሉት ከብዙዎች መካከል ጥቂቶች ናቸው፡፡
የባዮሜትሪክስ ጠቀሜታ
* የወንጀል ድርጊት ከመፈፀሙ በፊትና ከተፈፀመ በኋላ የሰዎችን ማንነት ለመለየት የሚያገለግል ቴክኖሎጂ ሲሆን ለምሳሌ አንድ ሰው የተለያዩ አለማትን በሚዞርበት ወይም በሚጎበኝበት ወቅት በሚዳረስባቸው ቦታዎች በሚገኙ የኢሚግሬሽን ጣቢያዎች ላይ የጣት አሻራ እንዲሰጥ ይጠየቃል ይህም በሀገር እና ግለሰብ ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን ወይም የወንጀል ድርጊቶችን ለመቆጣጠር ያስችላል፡፡
* በበርካታ የመንግስትና የግል ድርጅቶች፣ ባንኮች እና የገንዘብ ተቋማት እንደ ሰዓት መቆጣጠሪያ ይጠቅማል
* የባዮሜትሪክ ሥርዓቶች ሰዎችን በፍጥነት፣ በቋሚነት እና በአስተማማኝ ሁኔታ በመለየት ከፍተኛ ጥቅም ይሰጣሉ
ምንጭ፡ biometricupdate.com እና Si Tech Bufe
ስኪዞፍሬኒያ (Schizophrenia)
***************
ስኪዞፍሬኒያ ከሁለት የግሪክ ቃላት ጥምረት የተገኘ ቃል ሲኾን በደምሳሳው “የተበታተነ አእምሮ” የሚል ትርጉምን የያዘ ነው፡፡ ብዙ ሰዎች ይህን በሽታ በቅጡ አይረዱትም፡፡ ስኪዞፎርኒያ “እብደት” ነው ብለው የሚያስቡ ሰዎች አሉ፡፡ ይህ ስህተት ነው፡፡ ስኮዞፎርኒያ በቤተሰብ እንክብካቤ ማጣት የሚመጣ ደዌ ነው ብለው የሚያስቡ ሰዎች አሉ፤ ይህም ትክክል አይደለም፡፡
በሽታው በአንድ ሰው ሰነፍ ኾኖ መገኘት ወይም ደግሞ ስኬታማ ባለመኾኑ ምክንያት የሚመጣም አይደለም፡፡ ስኪዞፍሬኒያ አእምሮ በሚፈጥራቸው ባዕድ ምስሎች የመሰቃየት በሽታ ነው፡፡ ከፍ ሲልም በአእምሮ አስተካክሎ የማሰብ ችሎታ ባለመኖሩ ከውጭው ዓለም ጋር መግባባት መቸገር ማለት ነው፡፡
በሽታው በዓለም አቀፍ ደረጃ ሥር የሰደደ ሲሆን በተለይ በታዳጊ አገሮች በስፋት የሚስተዋል ነው፡፡ የአገራችንን ትተን እንደ ታላቋ ብሪታኒያ ባሉ ያደጉ አገሮች እንኳ ከ100 ሰዎች አንዱ በዚህ በሽታ የተጠቃ ኾኖ እናገኘዋለን፡፡ ይህን ቁጥር ወደኛ ብንመነዝረው ስኪዞፎርኒያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን እያሰቃየ የሚገኝ በሽታ እንደኾነ መገመት እንችላለን፡፡
ስኪዞፍሬኒያ የብቸኝነት ሕመም ከመሆኑም ባለፈ ከውጭው ዓለም ጋር የመግባባት አቅምን የሚያሳጣ ነው፡፡ በሽታው አስተሳሰባችንን ክፉኛ ስለሚበታትነው እውነታንና እውነት ያልኾነን ነገር የምንለካበትን ሚዛን ያስተናል፡፡ በዚህም የተነሳ ብዙ ሰዎች ስኪዞፍሬኒያ “የመቀወስ” በሽታ ነው ብለው ለመደምደም ይገደዳሉ፡፡ በእርግጥ እስኪዞፎርኒያ የአእምሮ መታወክ አድርገን እንድንመለከተው የሚያደርገን ነገሮችን በጠራ መልኩ ለማየትና ለማገናዘብ መቸገርን ስለሚያስከትል ነው፡፡ ኾኖም በሐኪም እገዛና በቤተሰብ ክትትል በሂደት ማገገም የሚቻልበትና ሙሉ በሙሉ ሊድን የሚችል በሽታ መኾኑን መረዳት ያሻል፡፡
የስኪዞፍሬኒያ ተጠቂዎች ከሚታይባቸው ዋና ዋና ምልክቶች መካካል ሁሉም ሰዎች ሰለኔ እያወሩ ነው ብሎ ማሰብ፣ ራስን መጣል፣ ለነገሮች ምንም ግድ ማጣት፣ ለዓለም ችግሮችና ሰማያዊ ጥያቄዎች ለሁሉም መልስ ለመስጠት መሞከር፣ መንገድ ላይ ሰዎች ይጠቋቆሙብኛል ብሎ መስጋት እና ከቤተሰብና ከጓደኞች መገለል በሽታው የሚያሳያቸው ምልክቶች ናቸው፡፡
የስኪዞፍሬኒያ ምልክቶች ከሰው ሰው የተለያየ ባሕሪ ሊኖራቸው ቢችልም ታካሚው ምን ሁኔታ ላይ ሲኾን የተሻለ ስሜት እንደሚሰማው ለመረዳት መሞከር መልካም ተግባር ነው፡፡ በሽታው ከምንም በላይ የሰዎችን እንክብካቤ ስለሚሻ ከህክምና በተጨማሪ በዚህ ላይ ትኩረት ማድረግ ትልቅ እርዳታ ይኖረዋል፡፡
ምንጭ፡ www.alodokter.com
***************
ስኪዞፍሬኒያ ከሁለት የግሪክ ቃላት ጥምረት የተገኘ ቃል ሲኾን በደምሳሳው “የተበታተነ አእምሮ” የሚል ትርጉምን የያዘ ነው፡፡ ብዙ ሰዎች ይህን በሽታ በቅጡ አይረዱትም፡፡ ስኪዞፎርኒያ “እብደት” ነው ብለው የሚያስቡ ሰዎች አሉ፡፡ ይህ ስህተት ነው፡፡ ስኮዞፎርኒያ በቤተሰብ እንክብካቤ ማጣት የሚመጣ ደዌ ነው ብለው የሚያስቡ ሰዎች አሉ፤ ይህም ትክክል አይደለም፡፡
በሽታው በአንድ ሰው ሰነፍ ኾኖ መገኘት ወይም ደግሞ ስኬታማ ባለመኾኑ ምክንያት የሚመጣም አይደለም፡፡ ስኪዞፍሬኒያ አእምሮ በሚፈጥራቸው ባዕድ ምስሎች የመሰቃየት በሽታ ነው፡፡ ከፍ ሲልም በአእምሮ አስተካክሎ የማሰብ ችሎታ ባለመኖሩ ከውጭው ዓለም ጋር መግባባት መቸገር ማለት ነው፡፡
በሽታው በዓለም አቀፍ ደረጃ ሥር የሰደደ ሲሆን በተለይ በታዳጊ አገሮች በስፋት የሚስተዋል ነው፡፡ የአገራችንን ትተን እንደ ታላቋ ብሪታኒያ ባሉ ያደጉ አገሮች እንኳ ከ100 ሰዎች አንዱ በዚህ በሽታ የተጠቃ ኾኖ እናገኘዋለን፡፡ ይህን ቁጥር ወደኛ ብንመነዝረው ስኪዞፎርኒያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን እያሰቃየ የሚገኝ በሽታ እንደኾነ መገመት እንችላለን፡፡
ስኪዞፍሬኒያ የብቸኝነት ሕመም ከመሆኑም ባለፈ ከውጭው ዓለም ጋር የመግባባት አቅምን የሚያሳጣ ነው፡፡ በሽታው አስተሳሰባችንን ክፉኛ ስለሚበታትነው እውነታንና እውነት ያልኾነን ነገር የምንለካበትን ሚዛን ያስተናል፡፡ በዚህም የተነሳ ብዙ ሰዎች ስኪዞፍሬኒያ “የመቀወስ” በሽታ ነው ብለው ለመደምደም ይገደዳሉ፡፡ በእርግጥ እስኪዞፎርኒያ የአእምሮ መታወክ አድርገን እንድንመለከተው የሚያደርገን ነገሮችን በጠራ መልኩ ለማየትና ለማገናዘብ መቸገርን ስለሚያስከትል ነው፡፡ ኾኖም በሐኪም እገዛና በቤተሰብ ክትትል በሂደት ማገገም የሚቻልበትና ሙሉ በሙሉ ሊድን የሚችል በሽታ መኾኑን መረዳት ያሻል፡፡
የስኪዞፍሬኒያ ተጠቂዎች ከሚታይባቸው ዋና ዋና ምልክቶች መካካል ሁሉም ሰዎች ሰለኔ እያወሩ ነው ብሎ ማሰብ፣ ራስን መጣል፣ ለነገሮች ምንም ግድ ማጣት፣ ለዓለም ችግሮችና ሰማያዊ ጥያቄዎች ለሁሉም መልስ ለመስጠት መሞከር፣ መንገድ ላይ ሰዎች ይጠቋቆሙብኛል ብሎ መስጋት እና ከቤተሰብና ከጓደኞች መገለል በሽታው የሚያሳያቸው ምልክቶች ናቸው፡፡
የስኪዞፍሬኒያ ምልክቶች ከሰው ሰው የተለያየ ባሕሪ ሊኖራቸው ቢችልም ታካሚው ምን ሁኔታ ላይ ሲኾን የተሻለ ስሜት እንደሚሰማው ለመረዳት መሞከር መልካም ተግባር ነው፡፡ በሽታው ከምንም በላይ የሰዎችን እንክብካቤ ስለሚሻ ከህክምና በተጨማሪ በዚህ ላይ ትኩረት ማድረግ ትልቅ እርዳታ ይኖረዋል፡፡
ምንጭ፡ www.alodokter.com
አውሮፓ ወደ ኢትዮጵያ ታማትር ይሆን?
======================
በአብዛሀው ሰው ሰራሽ የሆነው የአየር ንብረት ለውጥ እያስከተለው የሚገኘውን ከባቢያዊ ጉዳቶች ለመገደብ ያለሙ እንቅስቃሴዎች በዓለም ሀገራት ዘንድ እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ ከነዚህ ውስጥ ከካርበን ልቀት የፀዳ ምጣኔ-ሐብትን በአውሮፓውያኑ 2050 ይፈጥር ዘንድ የአውሮፓ ህብረት ይዞት የመጣው “European Green Deal” የተሰኘ ዕቅድ አንዱ ነው፡፡ በተቀመጠው ዓመት ሰፊ የስራ መፍጠር እና የኑሮ ደረጃ ማሻሻልን ያካተተው ይህ የ1.1 ትሪሊዮን ዶላር ዕቅድ በአውሮፓ ብቻ የሚተገበር አይደለም ይልቁንም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ታዳጊ ሀገራት እንጂ፡፡
ለዚህ ድጋፍ በተለይ ኢትዮጵያ ተቀዳሚ ምርጫ ሆና እንደምትገኝ ተገልጿል፡፡ ለዚህ መነሻው ኢትዮጵያ ለብዙ ጊዜያት ከዓለማችን ደሀ ሀገራት ትመደብ የነበረች ቢሆንም ላለፉት አመታት ግን ምጣኔ-ሐብታዊ ዕድገትን እያስመዘገበች እንድትቆይ መሆኗ ነው፡፡ ይህም የድህነት ምጣኔን በ40 በመቶ እንድትቀንስ ሲያስችላት የዜጎች የመኖሪያ የዕድሜ ጣሪያም በ8 ዓመታት በማደግ ወደ 66 ዓመታት ከፍ እንዲል አድርጓል፡፡
ከዚህም ባለፈ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማት ላይ ሰፊ እርምጃዎችን ስትወስድ ቆይታለች፡፡ በቅርቡ እንኳን ባለ ራዕይ መሆናቸው የሚነገርላቸው የኖቤል አሸናፊው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በአንድ ቀን ውስጥ ብቻ 350 ሚሊዮን ችግኞችን እንዲተከሉ ያስደረጉበት ሁነትም ለዚህ ማሳያ ነው፡፡ በኃይል ዘርፉም ቢሆን የአረንጓዴ ልማትን የሚያጠናክሩ የኃይል ምንጮችን በመገንባት ላይ ነች፡፡ በግንባታ እንቅስቃሴ ላይ የሚገኙት የኮይሻና ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድቦች ሲጠናቀቁ በጋራ 20ሺ ጊጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይልን በየሰዓቱ እንደሚሰጡ ይጠበቃል፡፡ ይህም 21.5 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን የካርበን ዳይ ኦክሳይድ ልቀትን ያድናሉ እንደማለት ነው፡፡ ሆኖም እነዚህን ስራዎች ለፍፃሜ የሚያበቃ የገንዘብ ምንጭን በማረጋገጥ ረገድ ክፍተቶች አሉ፤ ሁለቱ ፕሮጀክቶችም ከታለመላቸው ጊዜ ወደኋላ ቀርተዋል፡፡ የኮይሻ ግድብን ያየን እንደሆን የጣልያኑ SACE ባንክ ለግድቡ ግንባታ ይውል የነበረውን የ1.5 ቢሊዮን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ አቁሟል፡፡ በውስጣዊ አቅም መስራት ደግሞ ቀላል የማይባል የምጣኔ-ሐብት መዛባትን ሊፈጥር እንደሚችል ይገመታል፡፡ ታድያ የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት በቅርቡ ለኢትዮጵያ የሰጠው ድጋፍ ለአውሮፓም ሆነ SACE ማረጋገጫ ሊሆናቸው እና ድጋፋቸውን በመቀጠል የተቋረጡት ስራዎች ዳግም እንዲጀመሩ ሊያደርግ እንደሚገባ ተገልጿል፡፡
ምንጭ፡- Project Syndicate
======================
በአብዛሀው ሰው ሰራሽ የሆነው የአየር ንብረት ለውጥ እያስከተለው የሚገኘውን ከባቢያዊ ጉዳቶች ለመገደብ ያለሙ እንቅስቃሴዎች በዓለም ሀገራት ዘንድ እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ ከነዚህ ውስጥ ከካርበን ልቀት የፀዳ ምጣኔ-ሐብትን በአውሮፓውያኑ 2050 ይፈጥር ዘንድ የአውሮፓ ህብረት ይዞት የመጣው “European Green Deal” የተሰኘ ዕቅድ አንዱ ነው፡፡ በተቀመጠው ዓመት ሰፊ የስራ መፍጠር እና የኑሮ ደረጃ ማሻሻልን ያካተተው ይህ የ1.1 ትሪሊዮን ዶላር ዕቅድ በአውሮፓ ብቻ የሚተገበር አይደለም ይልቁንም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ታዳጊ ሀገራት እንጂ፡፡
ለዚህ ድጋፍ በተለይ ኢትዮጵያ ተቀዳሚ ምርጫ ሆና እንደምትገኝ ተገልጿል፡፡ ለዚህ መነሻው ኢትዮጵያ ለብዙ ጊዜያት ከዓለማችን ደሀ ሀገራት ትመደብ የነበረች ቢሆንም ላለፉት አመታት ግን ምጣኔ-ሐብታዊ ዕድገትን እያስመዘገበች እንድትቆይ መሆኗ ነው፡፡ ይህም የድህነት ምጣኔን በ40 በመቶ እንድትቀንስ ሲያስችላት የዜጎች የመኖሪያ የዕድሜ ጣሪያም በ8 ዓመታት በማደግ ወደ 66 ዓመታት ከፍ እንዲል አድርጓል፡፡
ከዚህም ባለፈ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማት ላይ ሰፊ እርምጃዎችን ስትወስድ ቆይታለች፡፡ በቅርቡ እንኳን ባለ ራዕይ መሆናቸው የሚነገርላቸው የኖቤል አሸናፊው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በአንድ ቀን ውስጥ ብቻ 350 ሚሊዮን ችግኞችን እንዲተከሉ ያስደረጉበት ሁነትም ለዚህ ማሳያ ነው፡፡ በኃይል ዘርፉም ቢሆን የአረንጓዴ ልማትን የሚያጠናክሩ የኃይል ምንጮችን በመገንባት ላይ ነች፡፡ በግንባታ እንቅስቃሴ ላይ የሚገኙት የኮይሻና ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድቦች ሲጠናቀቁ በጋራ 20ሺ ጊጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይልን በየሰዓቱ እንደሚሰጡ ይጠበቃል፡፡ ይህም 21.5 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን የካርበን ዳይ ኦክሳይድ ልቀትን ያድናሉ እንደማለት ነው፡፡ ሆኖም እነዚህን ስራዎች ለፍፃሜ የሚያበቃ የገንዘብ ምንጭን በማረጋገጥ ረገድ ክፍተቶች አሉ፤ ሁለቱ ፕሮጀክቶችም ከታለመላቸው ጊዜ ወደኋላ ቀርተዋል፡፡ የኮይሻ ግድብን ያየን እንደሆን የጣልያኑ SACE ባንክ ለግድቡ ግንባታ ይውል የነበረውን የ1.5 ቢሊዮን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ አቁሟል፡፡ በውስጣዊ አቅም መስራት ደግሞ ቀላል የማይባል የምጣኔ-ሐብት መዛባትን ሊፈጥር እንደሚችል ይገመታል፡፡ ታድያ የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት በቅርቡ ለኢትዮጵያ የሰጠው ድጋፍ ለአውሮፓም ሆነ SACE ማረጋገጫ ሊሆናቸው እና ድጋፋቸውን በመቀጠል የተቋረጡት ስራዎች ዳግም እንዲጀመሩ ሊያደርግ እንደሚገባ ተገልጿል፡፡
ምንጭ፡- Project Syndicate
ቴክ-ሳይንስ
• ታዳጊ ፈጣሪዎቻችንን የሚያበረታቱ
• ቴክኖሎጂዎች የተጓዙባቸው የፈጠራ ጎዳናዎች መለስ ብለው የሚቃኙ
• ለኢትዮጵያም ሆነ መላው ዓለም ጉልህ አስተዋፅዖ ያደረጉ ግለሰቦችን የሚመለከቱ
• ወቅታዊና አንገብጋቢ ጉዳዮች የሚዳስሱ
• እንዲሁም ሌሎች በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ዙርያ ከተጠናቀሩ ዝግጅቶቻችን ጋራ በቅርቡ በ #MOE #TV ይጠብቁን፡፡
ዩትዩብ youtube.com/channel/
UC6jvUOLRSkVEQtc5Annfwvg
ፌስቡክ facebook.com/TechinEthiopia/ ትዊተር twitter.com/TechinEthiopia
• ታዳጊ ፈጣሪዎቻችንን የሚያበረታቱ
• ቴክኖሎጂዎች የተጓዙባቸው የፈጠራ ጎዳናዎች መለስ ብለው የሚቃኙ
• ለኢትዮጵያም ሆነ መላው ዓለም ጉልህ አስተዋፅዖ ያደረጉ ግለሰቦችን የሚመለከቱ
• ወቅታዊና አንገብጋቢ ጉዳዮች የሚዳስሱ
• እንዲሁም ሌሎች በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ዙርያ ከተጠናቀሩ ዝግጅቶቻችን ጋራ በቅርቡ በ #MOE #TV ይጠብቁን፡፡
ዩትዩብ youtube.com/channel/
UC6jvUOLRSkVEQtc5Annfwvg
ፌስቡክ facebook.com/TechinEthiopia/ ትዊተር twitter.com/TechinEthiopia
ኮሮናቫይረስ እና ኤች.አይ.ቪን በስልክ አማካኝነት የሚመረምር መሳሪያ ተሰራ
=========================
ብዙ ጊዜ በሀኪም ቤቶች ውስጥ ካሉት አሰልቺ ነገሮች አንዱ የቤተ-ሙከራ ምርመራ ውጤትን መጠበቅ ነው፡፡ በሽታው ሳይታወቅ ስር የሰደደ ከሆነ ደግሞ የቤተ-ሙከራ ውጤትን በሚጠበቅ ወቅት በሽታው ምን እንደሆነ ገና ሳይታወቅ ለከፋ ችግር የሚዳረጉ ህመምተኞች ይኖራሉ፡፡
ይህን ችግር ሊቀርፍ የሚችል የቴክኖሎጂ ግኝት ከቀናት በፊት ከወደ ሲንሲናቲ ዩኒቨርሲቲ ተሰምቷል፡፡ መሐንዲሶች ከሲንሲናቲ ዩኒቨርስቲ ጋር በመሆን አነስ ያለች ተንቀሳቃሽ የስማርት ስልክ ቤተ-ሙከራ ፈጥረዋል፡፡ ይህች የኤ.ቲ.ኤም ካርድ መጠን ያላት መሳሪያ ስልኩ ላይ ተሰክታ የምትሰራ ናት፡፡ በዩኒቨርሲቲው የኤሌክትሪካል ምህንድስና ፕሮፌሰር ሆነው እያገለገሉ የሚገኙት ቾንግ አህን ከምርምር ቡድናቸው ጋራ በመሆን የስማርት ስልክ መሣሪያዋን ለወባ በሽታ መመርመሪያነት የተጠቀሙባት ቢሆንም ሌሎች ስር የሰደዱ እና ተላላፊ በሽታዎችን ብሎም ከድብርት ጋራ የተያያዙ ሆርሞኖችን መመርመር እንደምትችል ተገልጿል፡፡ መሳሪያዋ መመርመር ከምችላቸው ከነዚህ በሽታዎች ውስጥ ኤች. አይ. ቪ እና አሳሳቢው የኮሮና ቫይረስ ተጠቃሾች ናቸው፡፡
ምርመራውን ለማድረግ ታማሚው በቀላሉ የፕላስቲክ ከነዚህ ቺፑን ወደ አፉ በማስገባት የምራቅ ናሙና መውሰድና የወሰደውን ምራቅ ለፍተሻ መሳሪያዋ ላይ ወዳለው ማስገቢያ መክተት ይኖርበታል፡፡ የተወሰዱት ናሙናዎች መሳሪያዋ ላይ ካሉ ሁለት መተላለፊያዎች እንዲሰርጉ ይደረጋል፡፡ አንደኛው መተላለፊያ ናሙናውን ቀዝቅቀዘው ከደረቁ ተከላካይ ፀረ-እንግዳ አካላት (Antibodies) ጋራ ሲያቀላቅለው ሌላኛው ደግሞ የተለያዩት ናሙናዎች በሶስት ሴንሰሮች ላይ መልሰው በሚደባለቁበት ወቅት የሚያሳዩትን ውጤት የሚያነብ በቅዝቃዜ የደረቀ ሙቀት አልባ መብራትን (Luminescent) ይዟል፡፡ መሳሪያዋ በዚህ መልክ ምርመራውን ካከናወነች በኋላ ውጤቱን ለዚህ ተብሎ በተሰራ መተግበሪያ ወይም አፕሊኬሽን አማካኝነት ወደ ሀኪሙ እንዲደርስ ታደርጋለች፡፡
እንደ ተመራማሪዎቹ ከሆነ ከተለምዷዊው ቤተ-ሙከራ አንፃር ይህች መሳሪያ ተመሰሳሳይ ውጤትን የምትሰጥ ቢሆንም ከዋጋ እና አጠቃቀም ቅለት አንፃር ግን የተሻለች ናት፡፡ ከዚህ ባሻገር ግንየመሳሪያውትልቁ ግኝት ናሙናዎቹን ተፈጥሮአዊ መንገድን በመጠቀም በሁለቱ እጅግ ጠባባብ መተላለፊያዎች በማሳለፍ ከሴንሰሮቹ ማድረሷ ላይ መሆኑን የጥናቱ ዋና ፀሐፊ ስትሂቶድሂ ጎሆሽ ገልፀዋል፡፡ ምንም እንኳን መሳሪያዋ የተሰራችው የተጠቀሱት አይነት በሽታዎችን ለመመርመር ቢሆንም ስማርት ስልኮች ጥቅም ላይ እየዋሉበት ባለው የአዕምሮ ጤና ህክምና ዘርፍ የማገልገል አቅም እንዳላት የተመራማሪዎቹ እምነት ነው፡፡
ምንጭ፡ SciTechDaily
ዩትዩብ youtube.com/channel/UC6jvUOLRSkVEQtc
5Annfwvg
ፌስቡክ facebook.com/TechinEthiopia/
ትዊተር twitter.com/TechinEthiopia
=========================
ብዙ ጊዜ በሀኪም ቤቶች ውስጥ ካሉት አሰልቺ ነገሮች አንዱ የቤተ-ሙከራ ምርመራ ውጤትን መጠበቅ ነው፡፡ በሽታው ሳይታወቅ ስር የሰደደ ከሆነ ደግሞ የቤተ-ሙከራ ውጤትን በሚጠበቅ ወቅት በሽታው ምን እንደሆነ ገና ሳይታወቅ ለከፋ ችግር የሚዳረጉ ህመምተኞች ይኖራሉ፡፡
ይህን ችግር ሊቀርፍ የሚችል የቴክኖሎጂ ግኝት ከቀናት በፊት ከወደ ሲንሲናቲ ዩኒቨርሲቲ ተሰምቷል፡፡ መሐንዲሶች ከሲንሲናቲ ዩኒቨርስቲ ጋር በመሆን አነስ ያለች ተንቀሳቃሽ የስማርት ስልክ ቤተ-ሙከራ ፈጥረዋል፡፡ ይህች የኤ.ቲ.ኤም ካርድ መጠን ያላት መሳሪያ ስልኩ ላይ ተሰክታ የምትሰራ ናት፡፡ በዩኒቨርሲቲው የኤሌክትሪካል ምህንድስና ፕሮፌሰር ሆነው እያገለገሉ የሚገኙት ቾንግ አህን ከምርምር ቡድናቸው ጋራ በመሆን የስማርት ስልክ መሣሪያዋን ለወባ በሽታ መመርመሪያነት የተጠቀሙባት ቢሆንም ሌሎች ስር የሰደዱ እና ተላላፊ በሽታዎችን ብሎም ከድብርት ጋራ የተያያዙ ሆርሞኖችን መመርመር እንደምትችል ተገልጿል፡፡ መሳሪያዋ መመርመር ከምችላቸው ከነዚህ በሽታዎች ውስጥ ኤች. አይ. ቪ እና አሳሳቢው የኮሮና ቫይረስ ተጠቃሾች ናቸው፡፡
ምርመራውን ለማድረግ ታማሚው በቀላሉ የፕላስቲክ ከነዚህ ቺፑን ወደ አፉ በማስገባት የምራቅ ናሙና መውሰድና የወሰደውን ምራቅ ለፍተሻ መሳሪያዋ ላይ ወዳለው ማስገቢያ መክተት ይኖርበታል፡፡ የተወሰዱት ናሙናዎች መሳሪያዋ ላይ ካሉ ሁለት መተላለፊያዎች እንዲሰርጉ ይደረጋል፡፡ አንደኛው መተላለፊያ ናሙናውን ቀዝቅቀዘው ከደረቁ ተከላካይ ፀረ-እንግዳ አካላት (Antibodies) ጋራ ሲያቀላቅለው ሌላኛው ደግሞ የተለያዩት ናሙናዎች በሶስት ሴንሰሮች ላይ መልሰው በሚደባለቁበት ወቅት የሚያሳዩትን ውጤት የሚያነብ በቅዝቃዜ የደረቀ ሙቀት አልባ መብራትን (Luminescent) ይዟል፡፡ መሳሪያዋ በዚህ መልክ ምርመራውን ካከናወነች በኋላ ውጤቱን ለዚህ ተብሎ በተሰራ መተግበሪያ ወይም አፕሊኬሽን አማካኝነት ወደ ሀኪሙ እንዲደርስ ታደርጋለች፡፡
እንደ ተመራማሪዎቹ ከሆነ ከተለምዷዊው ቤተ-ሙከራ አንፃር ይህች መሳሪያ ተመሰሳሳይ ውጤትን የምትሰጥ ቢሆንም ከዋጋ እና አጠቃቀም ቅለት አንፃር ግን የተሻለች ናት፡፡ ከዚህ ባሻገር ግንየመሳሪያውትልቁ ግኝት ናሙናዎቹን ተፈጥሮአዊ መንገድን በመጠቀም በሁለቱ እጅግ ጠባባብ መተላለፊያዎች በማሳለፍ ከሴንሰሮቹ ማድረሷ ላይ መሆኑን የጥናቱ ዋና ፀሐፊ ስትሂቶድሂ ጎሆሽ ገልፀዋል፡፡ ምንም እንኳን መሳሪያዋ የተሰራችው የተጠቀሱት አይነት በሽታዎችን ለመመርመር ቢሆንም ስማርት ስልኮች ጥቅም ላይ እየዋሉበት ባለው የአዕምሮ ጤና ህክምና ዘርፍ የማገልገል አቅም እንዳላት የተመራማሪዎቹ እምነት ነው፡፡
ምንጭ፡ SciTechDaily
ዩትዩብ youtube.com/channel/UC6jvUOLRSkVEQtc
5Annfwvg
ፌስቡክ facebook.com/TechinEthiopia/
ትዊተር twitter.com/TechinEthiopia
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
ካሉበት ሆነው ዕውቀትን ይሸምቱ፤ የብሄራዊ ዲጂታል ቤተ-መጽሐፍትን ይጠቀሙ!!!
=======================
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት የብሔራዊ ዲጂታል ቤተ-መጽሐፍት በመገንባት ባለፉት ዓመታት ለተጠቃሚዎች ከፍተኛ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ ዲጂታል ቤተ-መጽሐፍቱ የተለያዩና ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን መረጃዎችን ሰብስቦ ያካተተና በሃገር አቀፍ ደረጃ አገልግሎት መስጠት በሚችል መልኩ የተገነባ ሲሆን፤ library.techin.et ብለው በመግባት በቀላሉ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን ይችላሉ፡፡
ዲጂታል ቤተ-መጽሐፍቱ በይዘቱ ሁሉንም የዕድሜ ክፍል፣ የትምህርትና የዕውቀት ደረጃ ያማከለ መሆኑ እና ለአጠቃቀም ምቹ ሆኖ መሰናዳቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ቁጥር ባላቸው ተጠቃሚዎች እንዲጎበኝና አገልግሎት እንዲሰጥ አድርጎታል፡፡ እርስዎም በስራዎ፣ በትምህርትዎ፣ በልጆችዎ ውጤታማነት ላይ አስተዋፅኦ ለማድረግ የብሔራዊ ዲጂታል ቤተ-መጽሐፍትን ይጠቀሙ፤ ለሌሎችም ይጋብዙ!!!
ዩትዩብ youtube.com/channel/UC6jvUOLRSkVEQtc
5Annfwvg
ፌስቡክ facebook.com/TechinEthiopia/
ትዊተር twitter.com/TechinEthiopia
=======================
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት የብሔራዊ ዲጂታል ቤተ-መጽሐፍት በመገንባት ባለፉት ዓመታት ለተጠቃሚዎች ከፍተኛ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ ዲጂታል ቤተ-መጽሐፍቱ የተለያዩና ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን መረጃዎችን ሰብስቦ ያካተተና በሃገር አቀፍ ደረጃ አገልግሎት መስጠት በሚችል መልኩ የተገነባ ሲሆን፤ library.techin.et ብለው በመግባት በቀላሉ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን ይችላሉ፡፡
ዲጂታል ቤተ-መጽሐፍቱ በይዘቱ ሁሉንም የዕድሜ ክፍል፣ የትምህርትና የዕውቀት ደረጃ ያማከለ መሆኑ እና ለአጠቃቀም ምቹ ሆኖ መሰናዳቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ቁጥር ባላቸው ተጠቃሚዎች እንዲጎበኝና አገልግሎት እንዲሰጥ አድርጎታል፡፡ እርስዎም በስራዎ፣ በትምህርትዎ፣ በልጆችዎ ውጤታማነት ላይ አስተዋፅኦ ለማድረግ የብሔራዊ ዲጂታል ቤተ-መጽሐፍትን ይጠቀሙ፤ ለሌሎችም ይጋብዙ!!!
ዩትዩብ youtube.com/channel/UC6jvUOLRSkVEQtc
5Annfwvg
ፌስቡክ facebook.com/TechinEthiopia/
ትዊተር twitter.com/TechinEthiopia
ይቅርታ ወይስ በቀል፡ የትኛው ደስታን ይሰጥዎታል?
===============
ብዙዎቻችን ስለ ይቅርታ አስፈላጊነት ሲነገር ሰምተናል፤ እኛም ተናግረናል፡፡ በመዝናኛው ዘርፍ ላይ ተሰርቶ የተሰራ አዲስ ጥናት ግን ሰዎች ከይቅርታ ይልቅ ለመጥፎ ስራ ቅጣት ሲሰጥ ማየት እንደሚስደስታቸው ያስረዳል፡፡
በጆርናል ኦፍ ኮምዩኒኬሽን ሪሰርች ላይ የወጣው ይህ ጥናት 184 የኮሌጀ ተማሪዎችን ማዕከል በማድረግ የተሰራ ነው፡፡ ለእያንዳንዳቸው ለቴሌቪዥን ሊቀርብ እንደሚችል ተነግሮ 15 አጫጭር ታሪኮች እንዲያነቡ ሲሰጣቸው፤ ከነዚህ መካከል የመጀመሪያ አምስቱ ክፉ ሰው ከበደላቸው ሰዎች ዘንድ በቅንነት ሲስተናገድ፣ ሁለተኛዎቹ አምስት ታሪኮች በደለኛው ተመጣጣኝ ቅጣትን ሲቀበል፣ ሶስተኛዎቹ ደግሞ በደለኛው ላጠፋው ጥፋት ከሚገባው በላይ ቅጣትን ሲቀበል የሚያሳዩ ናቸው፡፡ ከአጫጭር ታሪኮቹ ውስጥ በአንዱ የሆነ ሰው 50 ዶላርን ከስራ ባልደረባው እንደሰረቀ ይተርካል፡፡ ተሳታፊዎቹ ለዚህ ታሪክ ከተሰጠው ሶስት አይነት መቋጫ ውስጥ አንዱ እንዲደርሳቸው ተደርጓል፡፡ በአንደኛው የታሪኩ መቋጫ ተበዳዩ ለሰራቂ ጓደኛው ይቅርታን ሰጥቶ ቡና እደሚጋብዘው ይተርካል፡፡ በሁለተኛው አፈፃፀም ተበዳዩ ከሰራቂው 50 ዶላር የሚያወጣ አንድ ጠርሙስ ውስኪ ሲወስድበት፤ ሶስተኛው ደግሞ ውስኪውንም ወስዶ የተሰረቀበትን ገንዘብ ሲያስመልስ ይተርካል፡፡
እነዚህን አጨራረሶች ካነበቡ በኋላ ተሳታፊዎቹ ታሪኩን መውደድ ወይ መጥላታቸውን እነዲገልፁ ይጠየቃሉ፡፡ በዚህ ሰዓት ተበዳዩ ይቅርታን ከሰጠውም ሆነ ከሚገባው በላይ መልስ ከሰጠው በላቀ ተመጣጣኝ ቅጣት ለተሰጠበት ትረካ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል፡፡ ተሳታፊዎቹ ባነበቧቸው 15 ታሪኮች ውስጥ ያለው የአዝናኝነት ደረጃ በሚገልፁበት ወቅት ደግሞ የይቅርታ ታሪኮቹ የመጨረሻውን ደረጃ ሲይዙ የልተመጣጠነ ቅጣት የሚሰጥባቸው ደግሞ ከሁሉም በበለጠ አዝናኝ ሆነው እንዳገኟቸው የሰጡት መልስ ያሳያል፡፡
ግን ምንም እንኳን ይቅርታ በበቀል ልክ ባያስደስታቸውም ይቅርታን ከበቀል በላይ ጥልቅና ስሜት የሚሰጥ እንደሆነ የተሳታፊዎቹ ዕምነት ነው፡፡ እንደ ግምገማ ከሆነ ሰዎች ላጠፉት ጥፋት ተመጣጣኝ ቅጣት እንዲያገኙ መታሰቡ የሰዎች ተፈጥሮአዊ እሳቤ ሲሆን የፍርድ መጓደልን መዳኘት ግን ለሁላችንም እኩል ያልተሰጠ ማመዛዘንን ይጠይቃል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ መውደድ አለመውደዳቸውን በሚያመነቡበት ኮምፒውተር ላይ የሚገልፁበት ፍጥነትም የተመዘገበ ሲሆን በዚህም መሰረት ጥናቱ ተሳታፊዎች ለተመጣጣኝ ቅጣቱ ትረካ የሚሰጡት ምላሽ ከከፍተኛ አፀፋም ሆነ የይቅርታ ትረካዎቹ የዘገየ ነበረ፡፡ እንደ ጥናቱ ዋና ፀሐፊ ፐሮፌሰር ማቲው ግሪዛርድ ከሆነ ሰዎች የበዳይ ተበዳይ ታሪክ በጠበቁት መልኩ ተጠናቆ ሲገኙት በፍጥነት ምላሽ ይሰጣሉ፡፡ ይህ ሳይሆን ቀርቶ ቅጣቱ ወንጀሉን የማይመጥን ሆኖ ሲያገኙት ግን መውደድ መጥላታቸውን ለመግለፅ ረዘም ያለ ጊዜ ሲወስድባቸው ታይቷል፡፡ ሆኖም ፍጥነታቸው ታሪኩ በይቅርታ አሊያም በበዛ አፀፋ ከመጠናቀቁ ጋራ ተያይዞ የተለያየ ነው፡፡ ይህ ግን በሚቀጥሉ ጥናቶች የሚሸፈን ይሆናል፡፡
ምንጭ፡ Medical Xpress
ዩትዩብ youtube.com/channel/UC6jvUOLRSkVEQtc
5Annfwvg
ትዊተር twitter.com/TechinEthiopia
===============
ብዙዎቻችን ስለ ይቅርታ አስፈላጊነት ሲነገር ሰምተናል፤ እኛም ተናግረናል፡፡ በመዝናኛው ዘርፍ ላይ ተሰርቶ የተሰራ አዲስ ጥናት ግን ሰዎች ከይቅርታ ይልቅ ለመጥፎ ስራ ቅጣት ሲሰጥ ማየት እንደሚስደስታቸው ያስረዳል፡፡
በጆርናል ኦፍ ኮምዩኒኬሽን ሪሰርች ላይ የወጣው ይህ ጥናት 184 የኮሌጀ ተማሪዎችን ማዕከል በማድረግ የተሰራ ነው፡፡ ለእያንዳንዳቸው ለቴሌቪዥን ሊቀርብ እንደሚችል ተነግሮ 15 አጫጭር ታሪኮች እንዲያነቡ ሲሰጣቸው፤ ከነዚህ መካከል የመጀመሪያ አምስቱ ክፉ ሰው ከበደላቸው ሰዎች ዘንድ በቅንነት ሲስተናገድ፣ ሁለተኛዎቹ አምስት ታሪኮች በደለኛው ተመጣጣኝ ቅጣትን ሲቀበል፣ ሶስተኛዎቹ ደግሞ በደለኛው ላጠፋው ጥፋት ከሚገባው በላይ ቅጣትን ሲቀበል የሚያሳዩ ናቸው፡፡ ከአጫጭር ታሪኮቹ ውስጥ በአንዱ የሆነ ሰው 50 ዶላርን ከስራ ባልደረባው እንደሰረቀ ይተርካል፡፡ ተሳታፊዎቹ ለዚህ ታሪክ ከተሰጠው ሶስት አይነት መቋጫ ውስጥ አንዱ እንዲደርሳቸው ተደርጓል፡፡ በአንደኛው የታሪኩ መቋጫ ተበዳዩ ለሰራቂ ጓደኛው ይቅርታን ሰጥቶ ቡና እደሚጋብዘው ይተርካል፡፡ በሁለተኛው አፈፃፀም ተበዳዩ ከሰራቂው 50 ዶላር የሚያወጣ አንድ ጠርሙስ ውስኪ ሲወስድበት፤ ሶስተኛው ደግሞ ውስኪውንም ወስዶ የተሰረቀበትን ገንዘብ ሲያስመልስ ይተርካል፡፡
እነዚህን አጨራረሶች ካነበቡ በኋላ ተሳታፊዎቹ ታሪኩን መውደድ ወይ መጥላታቸውን እነዲገልፁ ይጠየቃሉ፡፡ በዚህ ሰዓት ተበዳዩ ይቅርታን ከሰጠውም ሆነ ከሚገባው በላይ መልስ ከሰጠው በላቀ ተመጣጣኝ ቅጣት ለተሰጠበት ትረካ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል፡፡ ተሳታፊዎቹ ባነበቧቸው 15 ታሪኮች ውስጥ ያለው የአዝናኝነት ደረጃ በሚገልፁበት ወቅት ደግሞ የይቅርታ ታሪኮቹ የመጨረሻውን ደረጃ ሲይዙ የልተመጣጠነ ቅጣት የሚሰጥባቸው ደግሞ ከሁሉም በበለጠ አዝናኝ ሆነው እንዳገኟቸው የሰጡት መልስ ያሳያል፡፡
ግን ምንም እንኳን ይቅርታ በበቀል ልክ ባያስደስታቸውም ይቅርታን ከበቀል በላይ ጥልቅና ስሜት የሚሰጥ እንደሆነ የተሳታፊዎቹ ዕምነት ነው፡፡ እንደ ግምገማ ከሆነ ሰዎች ላጠፉት ጥፋት ተመጣጣኝ ቅጣት እንዲያገኙ መታሰቡ የሰዎች ተፈጥሮአዊ እሳቤ ሲሆን የፍርድ መጓደልን መዳኘት ግን ለሁላችንም እኩል ያልተሰጠ ማመዛዘንን ይጠይቃል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ መውደድ አለመውደዳቸውን በሚያመነቡበት ኮምፒውተር ላይ የሚገልፁበት ፍጥነትም የተመዘገበ ሲሆን በዚህም መሰረት ጥናቱ ተሳታፊዎች ለተመጣጣኝ ቅጣቱ ትረካ የሚሰጡት ምላሽ ከከፍተኛ አፀፋም ሆነ የይቅርታ ትረካዎቹ የዘገየ ነበረ፡፡ እንደ ጥናቱ ዋና ፀሐፊ ፐሮፌሰር ማቲው ግሪዛርድ ከሆነ ሰዎች የበዳይ ተበዳይ ታሪክ በጠበቁት መልኩ ተጠናቆ ሲገኙት በፍጥነት ምላሽ ይሰጣሉ፡፡ ይህ ሳይሆን ቀርቶ ቅጣቱ ወንጀሉን የማይመጥን ሆኖ ሲያገኙት ግን መውደድ መጥላታቸውን ለመግለፅ ረዘም ያለ ጊዜ ሲወስድባቸው ታይቷል፡፡ ሆኖም ፍጥነታቸው ታሪኩ በይቅርታ አሊያም በበዛ አፀፋ ከመጠናቀቁ ጋራ ተያይዞ የተለያየ ነው፡፡ ይህ ግን በሚቀጥሉ ጥናቶች የሚሸፈን ይሆናል፡፡
ምንጭ፡ Medical Xpress
ዩትዩብ youtube.com/channel/UC6jvUOLRSkVEQtc
5Annfwvg
ትዊተር twitter.com/TechinEthiopia
Twitter
TechinEthiopia (@TechinEthiopia) | Twitter
The latest Tweets from TechinEthiopia (@TechinEthiopia). Technology and Innovation Institute. Addis Ababa
የምድር በ habitable zone መገኘት
********************
ማንኛውም ኮከብ (ፀሀያችንን ጨምሮ) የራሱ የሆነ ሀቢቴብል ዞን (habitable zone) አለው። ሀቢቴብል ዞን ማለት ከኮከቡ በጣም ያልራቀ ወይንም ለኮከቡ በጣም ያልቀረበ የመኖሪያ ዞን ማለት ነው። ፀሀይ ወደ እኛ የተወሰነ የቀረበች ብትሆን ኖሮ ልክ እንደሜርኩሪ ሁሉ በመሬት ላይ ያለው ነገር በሙሉ በመድረቅ ይቃጠል ነበር፡፡ ከመሬት ትንሽ የራቀች ቢሆን ኖሮ ደግሞ ሁሉም ነገር በበረዶ ይሸፈን ነበር፡፡
በሁለቱም ሁኔታዎች መኖር አይቻልም፡፡ ከፀሀይ ጥቂት ሙቀትን የሚያገኙት የዋልታ አካባቢዎች ሁል ጊዜም በበረዶ የተሸፈኑ ሲሆኑ ከዛ የተሻለ ሙቀትን የሚያገኙት የምድር ወገብ አከባቢዎች ሁሌም ሞቃታማ ናቸው፡፡ በዋልታው እና በምድር ወገብ አካባቢ ያለው የሙቀት ልዩነት መሬት ላይ መጠነኛ ሙቀት እንዲኖር በማስቻል መሬት ለህይወት አመቺ እንድትሆን አድርጓታል፡፡
በዚህ ዞን የምትገኘው መሬት በምድር ወገብ ላይ 12,756 ኪሎሜትሮች የምትረዝም ቢሆንም በራሱዋ ዛቢያ ላይ የምትዞርበት ፍጥነት ግን ከግዜ ወደ ግዜ በጣም በዝግታ እየቀነሰ እንደሚገኝ የስነ ፈለክ ሊቃውንት ያስረዳሉ። ይሁንና እንደተመራማሪዎቹ ትንታኔ ከሆነ ይህ ብዙም የሚያሰጋ አይደለም ምክንያቱም በ 100 አመታት ውስጥ በ17 ሚሊ ሰኮንድ ብቻ ነው የሚቀንሰው። ይህም ማለት ከ 140 ሚሊየን አመታት በኋላ ምድር ላይ 25ኛ ሰአት ይጨመራል ማለት ነው።
ምድራችን ከ7 ትላልቅ አለቶች ተገጣጥማ ነው የተሰራችው። እነዚህን አለቶች ቴክቶኒክ ፕሌት (tectonic plates) እንላቸዋለን። ከሌሎች ፕላኔቶች በተለየ ለፀሃይ ብዙም ያልራቀች እና ያለቀረበችው መሬት በተመጣጠነ የህይወት ኡደቷ የእነዚህ አለቶች ተከፋፍሎ መቀመጥን በማስቻል፤ አንዱ ክፍለ መሬት ላይ የተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ ሌላኛው ላይ እንዳይሰማ ሆኗል። እዛው አለት ላይ ያሉ ሀገራት ብች ነው ሊሰማቸው የሚችለው። ምድር እንደሌሎቹ ከ 1 ወጥ አለት ተሰርታ ቢሆን ኖሮ ህንድ ላይ የተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ ኢትዪጲያ ላይ ይሰማ ነበር።
ምድር በጠቅላላው በውስጡዋ 32.1%ብረት፣ 30.1% ኦክስጂን፣ 15.1% ሲልኮን እና 13.9% ማግኒዝየም ይዛለች። ከዚህ የምድር የተመጣጠነ የህይወት ኡደት ጀርባ ከፍተኛ ሚና ከሚጫወቱ የጠፈር አካለት መካከል ጨረቃ ዋነኛዋ ስትሆን ከዛ ውጪ ደግሞ እንዲሁ ምድርን የሚዞሩ 2 አስትሮይዶች አሉ።
ምንጭ፡ Airtable universe እና E.A
********************
ማንኛውም ኮከብ (ፀሀያችንን ጨምሮ) የራሱ የሆነ ሀቢቴብል ዞን (habitable zone) አለው። ሀቢቴብል ዞን ማለት ከኮከቡ በጣም ያልራቀ ወይንም ለኮከቡ በጣም ያልቀረበ የመኖሪያ ዞን ማለት ነው። ፀሀይ ወደ እኛ የተወሰነ የቀረበች ብትሆን ኖሮ ልክ እንደሜርኩሪ ሁሉ በመሬት ላይ ያለው ነገር በሙሉ በመድረቅ ይቃጠል ነበር፡፡ ከመሬት ትንሽ የራቀች ቢሆን ኖሮ ደግሞ ሁሉም ነገር በበረዶ ይሸፈን ነበር፡፡
በሁለቱም ሁኔታዎች መኖር አይቻልም፡፡ ከፀሀይ ጥቂት ሙቀትን የሚያገኙት የዋልታ አካባቢዎች ሁል ጊዜም በበረዶ የተሸፈኑ ሲሆኑ ከዛ የተሻለ ሙቀትን የሚያገኙት የምድር ወገብ አከባቢዎች ሁሌም ሞቃታማ ናቸው፡፡ በዋልታው እና በምድር ወገብ አካባቢ ያለው የሙቀት ልዩነት መሬት ላይ መጠነኛ ሙቀት እንዲኖር በማስቻል መሬት ለህይወት አመቺ እንድትሆን አድርጓታል፡፡
በዚህ ዞን የምትገኘው መሬት በምድር ወገብ ላይ 12,756 ኪሎሜትሮች የምትረዝም ቢሆንም በራሱዋ ዛቢያ ላይ የምትዞርበት ፍጥነት ግን ከግዜ ወደ ግዜ በጣም በዝግታ እየቀነሰ እንደሚገኝ የስነ ፈለክ ሊቃውንት ያስረዳሉ። ይሁንና እንደተመራማሪዎቹ ትንታኔ ከሆነ ይህ ብዙም የሚያሰጋ አይደለም ምክንያቱም በ 100 አመታት ውስጥ በ17 ሚሊ ሰኮንድ ብቻ ነው የሚቀንሰው። ይህም ማለት ከ 140 ሚሊየን አመታት በኋላ ምድር ላይ 25ኛ ሰአት ይጨመራል ማለት ነው።
ምድራችን ከ7 ትላልቅ አለቶች ተገጣጥማ ነው የተሰራችው። እነዚህን አለቶች ቴክቶኒክ ፕሌት (tectonic plates) እንላቸዋለን። ከሌሎች ፕላኔቶች በተለየ ለፀሃይ ብዙም ያልራቀች እና ያለቀረበችው መሬት በተመጣጠነ የህይወት ኡደቷ የእነዚህ አለቶች ተከፋፍሎ መቀመጥን በማስቻል፤ አንዱ ክፍለ መሬት ላይ የተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ ሌላኛው ላይ እንዳይሰማ ሆኗል። እዛው አለት ላይ ያሉ ሀገራት ብች ነው ሊሰማቸው የሚችለው። ምድር እንደሌሎቹ ከ 1 ወጥ አለት ተሰርታ ቢሆን ኖሮ ህንድ ላይ የተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ ኢትዪጲያ ላይ ይሰማ ነበር።
ምድር በጠቅላላው በውስጡዋ 32.1%ብረት፣ 30.1% ኦክስጂን፣ 15.1% ሲልኮን እና 13.9% ማግኒዝየም ይዛለች። ከዚህ የምድር የተመጣጠነ የህይወት ኡደት ጀርባ ከፍተኛ ሚና ከሚጫወቱ የጠፈር አካለት መካከል ጨረቃ ዋነኛዋ ስትሆን ከዛ ውጪ ደግሞ እንዲሁ ምድርን የሚዞሩ 2 አስትሮይዶች አሉ።
ምንጭ፡ Airtable universe እና E.A