በማቴሪያል ሳይንስ የትምህርት ዘርፍ ፈርቀዳጅ የሆነችው ኢትዮጵያዊት ተመራማሪ፡ ፕሮፌሰር ሶስና ሃይሌ
==================================
ፕሮፌሰር ሶስና ሃይሌ እ.ኢ.አ በ 1958 ከአዲስ አባባ የተገኘች ኢትዮጵያዊት ሳይንቲስት ናት፡፡ በ1967 በሃገሪቱ የመንግስት ለውጥ መምጣት ተከትሎ ከቤተሰቦቿ ጋር ወደ አሜሪካ ለመሰደድ የተገደደችው ፐሮፌሰር ሶስና አብዛኛውን የህይወት ጊዜዋንም በዚህ አንድታሳልፍ ሆናለች፡፡ ፐሮፌሰር ሶስና ከቤተሰቦቿ ጋር አብራ በመሆን የልጅነት ጊዜዋን በሚኒሶታ ሃገረ ግዛት ገጠራማ አካባቢ ካደረገች በኋላ በ1986 የመጀመሪያ ዲግሪዋን በማሳቹሴትስ የቴክኖሎጂ ኢኒስቲትዩት በማቴሪያል ሳይንስና በኢንጂነሪንግ ማግኘት የቻለች ሲሆን፤ ሁለተኛ ዲግሪዋን ደግሞ በካሊፎርኒያ ዩኒቨርስቲ በተመሳሳይ የትምህርት ዘርፍ ማሳካት ችላለች፡፡
ፐሮፌሰር ሶስና በቀጣዮቹ ጥቂት ዓመታት የፒችዲ ትምህርቷን ለመማር እንዲያስችላት የመጀመሪያ ዲግሪዋን ካገኘችበት የማሳቹሴትስ የቴክኒሎጂ ኢኒስቲትዩት ያቀናች ሲሆን፤ በዚህም እንዲሁ በምትወደው የማቴሪያል ሳይንስና ኢንጂነሪንግ ዘርፍ መመረቅ ችላለች፡፡ ፐሮፌሰር ሶስና ከዚህ የተሳካ የትምህርት ጉዞዋ በኋላ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ካገኘችበት የካልቴክ ፋካልቲ ከማምራቷ በፊት ሲያትል በሚገኘው የዋሽንግተን ዩኒቨርስቲ በረዳት ፕሮፌሰርነት የሰራች ሲሆን በዚህ የሶስት ዓመት ቆይታዋም ሀገሯን የሚያኮራና አፍሪካንም የሚያስጠራ ትልልቅ የምርምር ስራዎችን ለመስራት በቅታለች፡፡
ፐሮፌሰር ሶስና ድምራቸው ከ150 በላይ የሆነ የጥናትና ምርምር ፅሁፎችን በግል እና ከሌሎች ምሁራን ጋር በጋራ በመቀናጀት ሰርታ ለህትመት አብቅታለች፡፡ በስሟ የተመዘገቡላት ፓተንቶችም ቢሆን አስራ አምስትን ተሻግረዋል፡፡
ከነዚህ የህትመት እና ምርምር ውጤቶች ውስጥ ብዙሃኑ በጠጣር የአዮን ቁስ እና መሳሪያዎች ላይ ያጠነጠኑ ናቸው፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ከሚያጠነጥኑት የፕሮፌሰር ሶስና ስራዎች መካከል ደግሞ ከዓመታት በፊት የሰሩት አዲስ ዓይነት የፊውል ሴል ከሌሎች ፈጠራዎቿ ይጠቀሳል፡፡ በወቅቱ ሶስና ኬሚካሎችን ወደ ኤሌክትሪክ ሃይል በመቀየር ለመኪኖች፣ ሃይል ማመንጫዎች እንዲሁም ሌሎች ሃይልን ለሚጠይቁ ተግባራት ንፁህ የሃይል ምንጭ በመሆን እንዲያገለግለ፤ በማሰብ የፊውል ሴሎችን በከፍተኛ ደረጃ የሚያሻሽል ቁስን ለመስራት አልማ ተነሳች፡፡ ይህ ሃሳቧም በአይነቱ አዲስ የሆነ የኃይል ማመንጫን ዋጋ በከፍተኛ ደረጃ ሊቀንስ የሚችል የሱፐርፕሮቶኒክ ቅንብር መስራትን ያጠቃልላል፡፡ ሆኖም ይህ ሃሳቧን ተቀብለው የአሰራር ስርዓታቸውን ሙሉ በሙሉ ወደ አዲስ ከመቀየር የታቀቡት የፊውል ሴል አምራቾች የራሷን ቤተ-ሙከራ ተጠቅማ በዓለም የመጀመሪያውን ጠጣር የአሲድ ፊውል ሴል ቁስ አካል እንድትፈበርክ ምክንያት ሆኗት፡፡ ኋላ ላይ ይህን አዲስ ፈጠራዋን የቀድሞ ተማሪዎቿ በንግድ ሰርቶ ማሳያነት የተጠቀመበት ሲሆን ለተመራሪዋም በአረንጓዴ የሃይል ልማት ዘርፍ ዕውቅናን እንድትሸምትበት አስችሏታል፡፡
ፕሮፌሰር ሶስና በአሁኑ ሰዓት ጠጣር ፊውል ሴሎችን በተለይም ለከባቢ ተስማሚ የሃይል ምንጭ መሆን በሚችሉት ላይ አተኩሮ የሚሰራን የምርምር ቡድን በሃላፊነት በመምራት ላይ ትገኛለች፡፡ በዚህ ረገድ ይህ ቡድን የተለያዩ ስኬቶችን በማስመዝገብ ላይ ሲገኝ ከቅርብ ስኬቶቹ መካከልም ውሃና ካርቦን ዳይ ኦክሳይድን በቴርሞ ኬሚካል ሂደት አማካኝነት በመጠቀም የፀሐይን ኃይል ጥቅም ላይ በማዋል ረገድ ሌላ ምዕራፍን የከፈተ ነበር፡፡ በፕሮፌሰር ሃና እና ቡድኗ እየተሰራባቸው ካሉት ስራዎች ውስጥ ፕሩቶንን አስተላላፊ ጠጣር አሲድ እና ፐሮቭስካይት ኤሌክትሮይቶች፣ የኤሌክትሮን እና ኦክስጅን ድብልቅን አስተላላፊ ፍሎሪት እና ፐሮቭስካይት እንዲሁም ኢ-ስቶይኪዮሜትሪክ ኦክሳይዶችን ማበልፀግ ይገኝበታል፡፡
ይህች ኢትዮጵያዊት እንቁ ተመራማሪ በትልቁ ስሟን ከሚያስጠሩ ስራዎቿ አንዱ ከሆነው የፊውል ሴል ፈጠራዋ በተጨማሪ በሴራሚክ ሳይንስ፣ በኤሌክትሮኬሚካል እና በፋንክሽናል ሶሊድ (electrochemical and functional solids) የደረገቻቸው ምርምሮች እና ያሳተመቻቸው ፅሁፎች በተሰማራችበት የሳይንስ ዘርፍ ከሚኖረው አበርክቶት ባለፈ ለብዙ ወጣት ኢትዮጵያውያን እና ሴት ተመራማሪዎች የሚኖረው ጠንካራ መልእክት ቀላል የሚባል አይደለም፡፡
ከዚህ ጋር ተያይዞ ፐሮፌሰር ሶስና ለሰራቸው ስራና ላበረከተችው የምርምር ውጤት እውቅና የሚሆን ሽልማቶችን ከተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች ያገኘች ሲሆን ከእንዚህ ውስጥም በ1989 በማቴሪያል ሳይንስ ባደረገችው ሰፊ ምርምር ያገኘችው የሃርዲ አዋርድ፣ በ2002 በፊውል ሴል ፈጠራዋ ያገኘችው የኬሚካል ፖይነር አዋርድ እንዲሁም በ2004 በሴራሚክ ሳይንስ ምርምሯ ያገኘቸው የዓለም አቀፍ የሴራሚክ ፕራይዝ በጥቂቱ የሚጠቀሱ የእውቅና ሽልማቶቿ ናቸው፡፡
ምንጭ፡ ቴክ-ሳይንስ ቅፅ 15 (ሙሉ መፅሐፉን በዚህ ሊንክ ያገኙታል=http://library.techin.gov.et/web/dl-site/stic-resources/-/document_library/Y9QR0tiVPdYe/view_file/4710001?_com_liferay_document_library_web_portlet_DLPortlet_INSTANCE_Y9QR0tiVPdYe_redirect=http%3A%2F%2Flibrary.techin.gov.et%2Fweb%2Fdl-site%2Fstic-resources%3Fp_p_id%3Dcom_liferay_document_library_web_portlet_DLPortlet_INSTANCE_Y9QR0tiVPdYe%26p_p_lifecycle%3D0%26p_p_state%3Dnormal%26p_p_mode%3Dview%26p_r_p_categoryId%3D672548)
==================================
ፕሮፌሰር ሶስና ሃይሌ እ.ኢ.አ በ 1958 ከአዲስ አባባ የተገኘች ኢትዮጵያዊት ሳይንቲስት ናት፡፡ በ1967 በሃገሪቱ የመንግስት ለውጥ መምጣት ተከትሎ ከቤተሰቦቿ ጋር ወደ አሜሪካ ለመሰደድ የተገደደችው ፐሮፌሰር ሶስና አብዛኛውን የህይወት ጊዜዋንም በዚህ አንድታሳልፍ ሆናለች፡፡ ፐሮፌሰር ሶስና ከቤተሰቦቿ ጋር አብራ በመሆን የልጅነት ጊዜዋን በሚኒሶታ ሃገረ ግዛት ገጠራማ አካባቢ ካደረገች በኋላ በ1986 የመጀመሪያ ዲግሪዋን በማሳቹሴትስ የቴክኖሎጂ ኢኒስቲትዩት በማቴሪያል ሳይንስና በኢንጂነሪንግ ማግኘት የቻለች ሲሆን፤ ሁለተኛ ዲግሪዋን ደግሞ በካሊፎርኒያ ዩኒቨርስቲ በተመሳሳይ የትምህርት ዘርፍ ማሳካት ችላለች፡፡
ፐሮፌሰር ሶስና በቀጣዮቹ ጥቂት ዓመታት የፒችዲ ትምህርቷን ለመማር እንዲያስችላት የመጀመሪያ ዲግሪዋን ካገኘችበት የማሳቹሴትስ የቴክኒሎጂ ኢኒስቲትዩት ያቀናች ሲሆን፤ በዚህም እንዲሁ በምትወደው የማቴሪያል ሳይንስና ኢንጂነሪንግ ዘርፍ መመረቅ ችላለች፡፡ ፐሮፌሰር ሶስና ከዚህ የተሳካ የትምህርት ጉዞዋ በኋላ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ካገኘችበት የካልቴክ ፋካልቲ ከማምራቷ በፊት ሲያትል በሚገኘው የዋሽንግተን ዩኒቨርስቲ በረዳት ፕሮፌሰርነት የሰራች ሲሆን በዚህ የሶስት ዓመት ቆይታዋም ሀገሯን የሚያኮራና አፍሪካንም የሚያስጠራ ትልልቅ የምርምር ስራዎችን ለመስራት በቅታለች፡፡
ፐሮፌሰር ሶስና ድምራቸው ከ150 በላይ የሆነ የጥናትና ምርምር ፅሁፎችን በግል እና ከሌሎች ምሁራን ጋር በጋራ በመቀናጀት ሰርታ ለህትመት አብቅታለች፡፡ በስሟ የተመዘገቡላት ፓተንቶችም ቢሆን አስራ አምስትን ተሻግረዋል፡፡
ከነዚህ የህትመት እና ምርምር ውጤቶች ውስጥ ብዙሃኑ በጠጣር የአዮን ቁስ እና መሳሪያዎች ላይ ያጠነጠኑ ናቸው፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ከሚያጠነጥኑት የፕሮፌሰር ሶስና ስራዎች መካከል ደግሞ ከዓመታት በፊት የሰሩት አዲስ ዓይነት የፊውል ሴል ከሌሎች ፈጠራዎቿ ይጠቀሳል፡፡ በወቅቱ ሶስና ኬሚካሎችን ወደ ኤሌክትሪክ ሃይል በመቀየር ለመኪኖች፣ ሃይል ማመንጫዎች እንዲሁም ሌሎች ሃይልን ለሚጠይቁ ተግባራት ንፁህ የሃይል ምንጭ በመሆን እንዲያገለግለ፤ በማሰብ የፊውል ሴሎችን በከፍተኛ ደረጃ የሚያሻሽል ቁስን ለመስራት አልማ ተነሳች፡፡ ይህ ሃሳቧም በአይነቱ አዲስ የሆነ የኃይል ማመንጫን ዋጋ በከፍተኛ ደረጃ ሊቀንስ የሚችል የሱፐርፕሮቶኒክ ቅንብር መስራትን ያጠቃልላል፡፡ ሆኖም ይህ ሃሳቧን ተቀብለው የአሰራር ስርዓታቸውን ሙሉ በሙሉ ወደ አዲስ ከመቀየር የታቀቡት የፊውል ሴል አምራቾች የራሷን ቤተ-ሙከራ ተጠቅማ በዓለም የመጀመሪያውን ጠጣር የአሲድ ፊውል ሴል ቁስ አካል እንድትፈበርክ ምክንያት ሆኗት፡፡ ኋላ ላይ ይህን አዲስ ፈጠራዋን የቀድሞ ተማሪዎቿ በንግድ ሰርቶ ማሳያነት የተጠቀመበት ሲሆን ለተመራሪዋም በአረንጓዴ የሃይል ልማት ዘርፍ ዕውቅናን እንድትሸምትበት አስችሏታል፡፡
ፕሮፌሰር ሶስና በአሁኑ ሰዓት ጠጣር ፊውል ሴሎችን በተለይም ለከባቢ ተስማሚ የሃይል ምንጭ መሆን በሚችሉት ላይ አተኩሮ የሚሰራን የምርምር ቡድን በሃላፊነት በመምራት ላይ ትገኛለች፡፡ በዚህ ረገድ ይህ ቡድን የተለያዩ ስኬቶችን በማስመዝገብ ላይ ሲገኝ ከቅርብ ስኬቶቹ መካከልም ውሃና ካርቦን ዳይ ኦክሳይድን በቴርሞ ኬሚካል ሂደት አማካኝነት በመጠቀም የፀሐይን ኃይል ጥቅም ላይ በማዋል ረገድ ሌላ ምዕራፍን የከፈተ ነበር፡፡ በፕሮፌሰር ሃና እና ቡድኗ እየተሰራባቸው ካሉት ስራዎች ውስጥ ፕሩቶንን አስተላላፊ ጠጣር አሲድ እና ፐሮቭስካይት ኤሌክትሮይቶች፣ የኤሌክትሮን እና ኦክስጅን ድብልቅን አስተላላፊ ፍሎሪት እና ፐሮቭስካይት እንዲሁም ኢ-ስቶይኪዮሜትሪክ ኦክሳይዶችን ማበልፀግ ይገኝበታል፡፡
ይህች ኢትዮጵያዊት እንቁ ተመራማሪ በትልቁ ስሟን ከሚያስጠሩ ስራዎቿ አንዱ ከሆነው የፊውል ሴል ፈጠራዋ በተጨማሪ በሴራሚክ ሳይንስ፣ በኤሌክትሮኬሚካል እና በፋንክሽናል ሶሊድ (electrochemical and functional solids) የደረገቻቸው ምርምሮች እና ያሳተመቻቸው ፅሁፎች በተሰማራችበት የሳይንስ ዘርፍ ከሚኖረው አበርክቶት ባለፈ ለብዙ ወጣት ኢትዮጵያውያን እና ሴት ተመራማሪዎች የሚኖረው ጠንካራ መልእክት ቀላል የሚባል አይደለም፡፡
ከዚህ ጋር ተያይዞ ፐሮፌሰር ሶስና ለሰራቸው ስራና ላበረከተችው የምርምር ውጤት እውቅና የሚሆን ሽልማቶችን ከተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች ያገኘች ሲሆን ከእንዚህ ውስጥም በ1989 በማቴሪያል ሳይንስ ባደረገችው ሰፊ ምርምር ያገኘችው የሃርዲ አዋርድ፣ በ2002 በፊውል ሴል ፈጠራዋ ያገኘችው የኬሚካል ፖይነር አዋርድ እንዲሁም በ2004 በሴራሚክ ሳይንስ ምርምሯ ያገኘቸው የዓለም አቀፍ የሴራሚክ ፕራይዝ በጥቂቱ የሚጠቀሱ የእውቅና ሽልማቶቿ ናቸው፡፡
ምንጭ፡ ቴክ-ሳይንስ ቅፅ 15 (ሙሉ መፅሐፉን በዚህ ሊንክ ያገኙታል=http://library.techin.gov.et/web/dl-site/stic-resources/-/document_library/Y9QR0tiVPdYe/view_file/4710001?_com_liferay_document_library_web_portlet_DLPortlet_INSTANCE_Y9QR0tiVPdYe_redirect=http%3A%2F%2Flibrary.techin.gov.et%2Fweb%2Fdl-site%2Fstic-resources%3Fp_p_id%3Dcom_liferay_document_library_web_portlet_DLPortlet_INSTANCE_Y9QR0tiVPdYe%26p_p_lifecycle%3D0%26p_p_state%3Dnormal%26p_p_mode%3Dview%26p_r_p_categoryId%3D672548)
የወንዶች የወሊድ መቆጣጠሪያ
******************************************************************
የአሜሪካን የኬሚካል ሶሳቲ የሴቶችን ሸክም ለመቀነስ ሌት ተቀን እሰራን ነው ሲል ተደምጧል፡፡ ሴቶች ለዘመናት ወሊድ የመቆጣጠር ጣጣን ለብቻቸው ሲወጡት የነበረ ሲሆን ይህ ጤናቸው ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ ከመሆኑም ባሻገር አሁን አሁን የጡት ካንሰር እና የደም መርጋት ችግሮች በስፋት እየታየ በመሆኑ ለረዥም ጊዜ የሚወሰድ እርግዝና መከላከያ እንክብል ለጤና የሚመከር እድዳይሆን እያረው ነው፡፡
ምንም እንኳን ወንዶች ወሊድ ለመቆጣጠር እንዲችሉ ባንድ በኩል ኮንዶምን በሌላ በኩል ደግሞ vasectomyን(የዘር መተላለፊያ ቱቦን መዝጋት) ለዘመናት እንደ አማራጭ እየተወሰደ የነበረ ነገር ቢሆኑም ሁለቱም አስተማማኝ የወሊድ መቆጣጠሪያ አይደሉም ሲሉ የአሜሪካን የኬሚካ ሶሳይቲ ተመራማሪዎች ገልጸዋል፡፡
ኮንዶም በበኩሉ ሊቀደድ እና እክል ሊገጥመው የሚችል በመሆኑ እና በሌሎች አንዳንድ ምክኒያች ተመራጭ ማይሆንበት በርካታ ምክኒያት አለ ያሉ ሲሆን በሌላ በኩል የዘር ቱቦን ማቋረጥ ደግሞ ዘላለማዊ የሆነ እና መመለሻ የሌለው በመሆኑ ከባድ ውሳኔን የሚጠይቅ ተግባር ነው ብለዋል፡፡
በመሆኑም ልክ ሴቶች እንደሚጠቀሙት ዓይነት ባለብዙ አማራጭ የወሊድ መቆጣጠሪያዎች ያሉ በርካታ የወንዶች የወሊድ መቆጣጠሪያ ዘዴዎች ሊበጁ ይገባል የሚሉ ድምጾች እየተስተጋቡ ነው፡፡ እንደ የአሜሪካን የኬሚካል ሶሳይቲ ያሉ የምርምር ተቋማትም ሌት ተቀን ይህንን እውን ለመድረግ እየተጉ ይገኛሉ፡፡ በተደጋጋሚም በተለያየ መልኩ ለወንዶች የሚሆን የወሊድ መቆጣጠሪያ ዘዴዎች እየሞከሩ ያሉ ሲሆን በቅርቡም የኬሚካል ድርብርቦሽን በመስራት እና በማህጸን ውስጥ ግርዶሽ በመፍጠር እርግዝና እንዳይፈጠር ሊረዳ የሚችል አዲስ ግኝትን ለማጠናቀቅ ጥቂት ጊዜ ብቻ ቀርቶኛል ያለው የአሜሪካን የኬሚካ ሶሳይቲ ተመራማሪ ቡድን አየሩን ተቆጣጥሮታል፡፡
ይሁንና በሌላ በኩል የወሊድ መቆጣጠሪያ በራሱ ችግር ያለበት እና ተጠያቂነት የጎደለው አብዮት ነው የሚሉ ሳይንቲስቶች እየተደመጡ ነው፡፡ የወሊድ መቆጣጠሪያ የማይታወቅ አብዮትን በሴቶች ሰውነት ውስጥ የፈጠረ ሲሆን በተለያየ መንገድ ጤናቸውን አደጋ ውስጥ እየከከተ ያለ ጉዳይ ነው ብለዋል፡፡
የወሊድ መቆጣጠሪያ የሴቶችን ጤና እየጎዳ ባለበት ሁኔታ መልሶ ወንዶችንም የገፈቱ ተቃማሽ ማድረግ መፍትሄ አይሆንም ያሉ ሲሆን ያልተገባ ጾታዊ ግንኙነቶችን መቀነስ እና ትዳርን ማበረታታት የተሻለ አማራጭ ነው የሚል ምክር ሰጥተዋል አክለውም በአሜሪካን በትዳር ውስጥ ካሉ ይልቅ በትዳር ውስጥ ያልሆኑ ሴቶች 90 በመቶ የወሊድ መቆጣጠሪያ የሚወስዱ በመሆኑ ሰዎች እንዲህ ያለ ያልተገባ የጾታዊ ግንኙነቶችን መግታት ቢችሉ ከወሊድ መቆጣጠሪያ ጋር ያለ የጎንዮሽ ጉዳትን ማስቀረት ይቻላል ብለዋል፡፡
ምንጭ፡- Science daily and Guttmacher Institute
******************************************************************
የአሜሪካን የኬሚካል ሶሳቲ የሴቶችን ሸክም ለመቀነስ ሌት ተቀን እሰራን ነው ሲል ተደምጧል፡፡ ሴቶች ለዘመናት ወሊድ የመቆጣጠር ጣጣን ለብቻቸው ሲወጡት የነበረ ሲሆን ይህ ጤናቸው ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ ከመሆኑም ባሻገር አሁን አሁን የጡት ካንሰር እና የደም መርጋት ችግሮች በስፋት እየታየ በመሆኑ ለረዥም ጊዜ የሚወሰድ እርግዝና መከላከያ እንክብል ለጤና የሚመከር እድዳይሆን እያረው ነው፡፡
ምንም እንኳን ወንዶች ወሊድ ለመቆጣጠር እንዲችሉ ባንድ በኩል ኮንዶምን በሌላ በኩል ደግሞ vasectomyን(የዘር መተላለፊያ ቱቦን መዝጋት) ለዘመናት እንደ አማራጭ እየተወሰደ የነበረ ነገር ቢሆኑም ሁለቱም አስተማማኝ የወሊድ መቆጣጠሪያ አይደሉም ሲሉ የአሜሪካን የኬሚካ ሶሳይቲ ተመራማሪዎች ገልጸዋል፡፡
ኮንዶም በበኩሉ ሊቀደድ እና እክል ሊገጥመው የሚችል በመሆኑ እና በሌሎች አንዳንድ ምክኒያች ተመራጭ ማይሆንበት በርካታ ምክኒያት አለ ያሉ ሲሆን በሌላ በኩል የዘር ቱቦን ማቋረጥ ደግሞ ዘላለማዊ የሆነ እና መመለሻ የሌለው በመሆኑ ከባድ ውሳኔን የሚጠይቅ ተግባር ነው ብለዋል፡፡
በመሆኑም ልክ ሴቶች እንደሚጠቀሙት ዓይነት ባለብዙ አማራጭ የወሊድ መቆጣጠሪያዎች ያሉ በርካታ የወንዶች የወሊድ መቆጣጠሪያ ዘዴዎች ሊበጁ ይገባል የሚሉ ድምጾች እየተስተጋቡ ነው፡፡ እንደ የአሜሪካን የኬሚካል ሶሳይቲ ያሉ የምርምር ተቋማትም ሌት ተቀን ይህንን እውን ለመድረግ እየተጉ ይገኛሉ፡፡ በተደጋጋሚም በተለያየ መልኩ ለወንዶች የሚሆን የወሊድ መቆጣጠሪያ ዘዴዎች እየሞከሩ ያሉ ሲሆን በቅርቡም የኬሚካል ድርብርቦሽን በመስራት እና በማህጸን ውስጥ ግርዶሽ በመፍጠር እርግዝና እንዳይፈጠር ሊረዳ የሚችል አዲስ ግኝትን ለማጠናቀቅ ጥቂት ጊዜ ብቻ ቀርቶኛል ያለው የአሜሪካን የኬሚካ ሶሳይቲ ተመራማሪ ቡድን አየሩን ተቆጣጥሮታል፡፡
ይሁንና በሌላ በኩል የወሊድ መቆጣጠሪያ በራሱ ችግር ያለበት እና ተጠያቂነት የጎደለው አብዮት ነው የሚሉ ሳይንቲስቶች እየተደመጡ ነው፡፡ የወሊድ መቆጣጠሪያ የማይታወቅ አብዮትን በሴቶች ሰውነት ውስጥ የፈጠረ ሲሆን በተለያየ መንገድ ጤናቸውን አደጋ ውስጥ እየከከተ ያለ ጉዳይ ነው ብለዋል፡፡
የወሊድ መቆጣጠሪያ የሴቶችን ጤና እየጎዳ ባለበት ሁኔታ መልሶ ወንዶችንም የገፈቱ ተቃማሽ ማድረግ መፍትሄ አይሆንም ያሉ ሲሆን ያልተገባ ጾታዊ ግንኙነቶችን መቀነስ እና ትዳርን ማበረታታት የተሻለ አማራጭ ነው የሚል ምክር ሰጥተዋል አክለውም በአሜሪካን በትዳር ውስጥ ካሉ ይልቅ በትዳር ውስጥ ያልሆኑ ሴቶች 90 በመቶ የወሊድ መቆጣጠሪያ የሚወስዱ በመሆኑ ሰዎች እንዲህ ያለ ያልተገባ የጾታዊ ግንኙነቶችን መግታት ቢችሉ ከወሊድ መቆጣጠሪያ ጋር ያለ የጎንዮሽ ጉዳትን ማስቀረት ይቻላል ብለዋል፡፡
ምንጭ፡- Science daily and Guttmacher Institute
ሳይሞቱ መሞት
*****************************************************************
ድካም ሲደጋገምቦት እና ማረፍ ሲያሰኞ ምናለ ለአንድ ሳምንት ያህል ለጥ ባልኩ አልያም ደግሞ ምናለ ምግቡም መጠጡም ቀርቶብኝ ለተከታታይ ቀናት በተኛሁ ብለው ያውቃሉ? እንግዲያውስ ከወደ ኮሎቢያ አከባቢ ስለተከሰተው ነገር ሹክ እንበሎት የ17 ዓመቷ ታዳጊ ከቀናት እና ከሳምንታትም አልፋ ለወራት ሳትነቃ ለጥ እንዳለች ናት፡፡
ሻሪክ ቶቫር ትባላለች ከሚሊዮኖች ቢያንስ 5 ሰዎች ብቻ ሊጠቁበት ይችላሉ ተብሎ በሚታወቀው Kleine-Levin syndrome ወይንም የተኛችው ቆንጆ ሲንድረም ተጠቅታለች፡፡ ምናልባትም እንደ National Organization for Rare Disorders ገለጻ ከሆነ በዚህ በሽታ የተጠቁ ሰዎች ከተኛችው ቆንጆ ታሪክ የሚለዩት በሆነ ጊዜ መሀል ላይ እየተነሱ ሽንት ቤት ሊጠቀሙ አልያም ሊመገቡ ይችላሉ፡፡
በታሪክ በዚህ በሽታ ተጠቅተው የሚያውቁ 500 ሰዎች ብቻ እንደሆኑ የህክምና መዛግብቶች የሚያስረዱ ሲሆን ሃኪም ቤት ያልደረሱ እና ያልታወቁ ሊኖሩ እንደሚችል ይጠረጠራል፡፡
ይህ ሲንድረም ከሴቶች ይልቅ ወንዶች ላይ የሚበዛ ቢሆንም በተለያየ እድሜ ክልል ላይ የሚገኙ ሴቶች ላይም አልፎ አልፎ ታይቷል፡፡ የታቮር እናት እንዳስረዱት ከሆነ ለመጀመሪያ ጊዜ ታቮር ይህ ነገር ያጋጠማት የ2ዓመት ህጻን ልጅ እያለች ሲሆን ለተከታታይ 2 ወራት ተኝታለች፡፡ በተኛችበት ወቅትም እንዳትጎዳ በማለት በየሁለት ሰዓት እየጠበቁ ይመግቧት እንደነበር ተናግረዋል፡፡
ተጠቂዎቹ ከተኙበት ሲነቁ አደገኛ ውዝግብ ውስጥ የሚገቡ ሲሆን መብራት እና ድምፅ እንደሚረብሻቸው ይናገራሉ፡፡ በተጨማሪም ሙሉ ለሙሉ አቅም ማጣት እና ስሜት አልባ መሆን ይስተዋልባቸዋል፡፡ በሚነቁበት ሰዓት ትውስታቸውን ሙሉ ለሙሉ የሚያጡ ሲሆን ታቮር የእናቷን ፊት እንኳን መለየት አልቻለችም ነበር፡፡
ሀኪሞች እንደሚሉት ከሆነ ይህ ሃይፖታለመስ የተሰኘው የአዕምሮ ክፍል መጎዳት ውጤት ነው ያሉ ሲሆን ይህ የአዕምሮ ክፍል እንቅልፋችንን የሚቆጣጠረው ክፍል ነው፡፡
ምንጭ፡Live Science
*****************************************************************
ድካም ሲደጋገምቦት እና ማረፍ ሲያሰኞ ምናለ ለአንድ ሳምንት ያህል ለጥ ባልኩ አልያም ደግሞ ምናለ ምግቡም መጠጡም ቀርቶብኝ ለተከታታይ ቀናት በተኛሁ ብለው ያውቃሉ? እንግዲያውስ ከወደ ኮሎቢያ አከባቢ ስለተከሰተው ነገር ሹክ እንበሎት የ17 ዓመቷ ታዳጊ ከቀናት እና ከሳምንታትም አልፋ ለወራት ሳትነቃ ለጥ እንዳለች ናት፡፡
ሻሪክ ቶቫር ትባላለች ከሚሊዮኖች ቢያንስ 5 ሰዎች ብቻ ሊጠቁበት ይችላሉ ተብሎ በሚታወቀው Kleine-Levin syndrome ወይንም የተኛችው ቆንጆ ሲንድረም ተጠቅታለች፡፡ ምናልባትም እንደ National Organization for Rare Disorders ገለጻ ከሆነ በዚህ በሽታ የተጠቁ ሰዎች ከተኛችው ቆንጆ ታሪክ የሚለዩት በሆነ ጊዜ መሀል ላይ እየተነሱ ሽንት ቤት ሊጠቀሙ አልያም ሊመገቡ ይችላሉ፡፡
በታሪክ በዚህ በሽታ ተጠቅተው የሚያውቁ 500 ሰዎች ብቻ እንደሆኑ የህክምና መዛግብቶች የሚያስረዱ ሲሆን ሃኪም ቤት ያልደረሱ እና ያልታወቁ ሊኖሩ እንደሚችል ይጠረጠራል፡፡
ይህ ሲንድረም ከሴቶች ይልቅ ወንዶች ላይ የሚበዛ ቢሆንም በተለያየ እድሜ ክልል ላይ የሚገኙ ሴቶች ላይም አልፎ አልፎ ታይቷል፡፡ የታቮር እናት እንዳስረዱት ከሆነ ለመጀመሪያ ጊዜ ታቮር ይህ ነገር ያጋጠማት የ2ዓመት ህጻን ልጅ እያለች ሲሆን ለተከታታይ 2 ወራት ተኝታለች፡፡ በተኛችበት ወቅትም እንዳትጎዳ በማለት በየሁለት ሰዓት እየጠበቁ ይመግቧት እንደነበር ተናግረዋል፡፡
ተጠቂዎቹ ከተኙበት ሲነቁ አደገኛ ውዝግብ ውስጥ የሚገቡ ሲሆን መብራት እና ድምፅ እንደሚረብሻቸው ይናገራሉ፡፡ በተጨማሪም ሙሉ ለሙሉ አቅም ማጣት እና ስሜት አልባ መሆን ይስተዋልባቸዋል፡፡ በሚነቁበት ሰዓት ትውስታቸውን ሙሉ ለሙሉ የሚያጡ ሲሆን ታቮር የእናቷን ፊት እንኳን መለየት አልቻለችም ነበር፡፡
ሀኪሞች እንደሚሉት ከሆነ ይህ ሃይፖታለመስ የተሰኘው የአዕምሮ ክፍል መጎዳት ውጤት ነው ያሉ ሲሆን ይህ የአዕምሮ ክፍል እንቅልፋችንን የሚቆጣጠረው ክፍል ነው፡፡
ምንጭ፡Live Science
አበባ እስክትሆን ድረስ ዘር ነህ
****************************************************************
"ማንም ሁን ፤የትም ሁን፤ በየትኛው እድሜ ክልል ውስጥም ተገኝ አንተ ሁሌም የተግዳሮት ሰለባ ነህ " ሲሉ የሳይኮሎጂው ታለቅ ሰው ፕሮፌሰር በርን በርንሰቴን የስነልቦና ምክራቸውን ጀምረዋል፡፡
የምትወደው ሰው ህይወት አደጋ ውስጥ እንደገባ ሰምተሃል፣ ከመስራቤትሽ ያልጠበቅሽው ደብዳቤ ደርሶሻል፣ የምርመራ ውጤትህ አስደሳች ዜና ይዞ አልመጣም፣ ይዘህ መምጣት የሚኖርብህን ሰነድ ረስተሃል ፣ትራንስፖርት አጥተህ ተሰቃይተሃል ወይንም ሌላ ብዙ እንዲሆን ማትፈልገው ነገር እንዲሆን ተገደሃል እናም እንዲህ ያለው ነገር በየስንት ጊዜው ሂወትህ ውስጥ የሚከሰት ይመስልሃል? ብትባል መልሱ ሁሌም በየቀኑ የሚለው እንደሚሆን አያጠራጥርም፡፡
እነዚህ ተግዳሮቶች ሁሌም አብረውህ ያሉ ወደፊትም የሚኖሩ ናቸው ምናልባትም ተጋፍጠሃቸው እያሸነፍክ መሻገር አልያም እያየሃቸው ወንዙ ዳር ተገትሮ መቅረት የግል ምርጫህ እና ውሳኔ ነው፡፡ ነገር ግን እነዚህ ተግዳሮቶች የቀን ተቀን ፈተናዎችህ ናቸው፡፡
ምናልባትም የህይወት ዓለማ ምንድነው ብለህ ጠይቀህ ታውቅ ይሆን? የህይወት ዓለማ ደስታ፣ ስኬት አልያም እርካታ እና የመሳሰሉትን በጎ ምኞቶች እንደሆኑ የሚዘረዝሩ የተለያዩ ሰዎች ይኖራሉ ለእኔ ግን ይላሉ ፕሮፌሰሩ "የህይወትህ ዓለማ በየቀኑ የሚገጥሙህን ፈተናዎች ማለፍ ነው፡፡" መሆን የምትፈልገው ምንም ይሁን ፤ መድረስ የምታልመውም የትም ይሁን ፊት ለፊትህ ሁሌም ፈተና አለ ያንን ማለፍ ካልቻልክ የትም መድረስ አትችልም፡፡
ህይወት ታላቁን አንተነትህን ትሆን ዘንድ የተሰጠችህ ፈተና ናት!
እቤትህ ውስጥ አበባ ለመትከል እና ለማሳደግ አስበህ ከሆነ እንኳን በቀላሉ ሊሆን የሚችል እንዳልሆነ ልብ ማለት አለብህ ዘር ከማምጣት አንስቶ ቦታ ማዘጋጀት ፣ውሃ ማጠጣት፣ በየቀኑ መንከባከብ እና አንዳንዴም ከዚህ ሁላ ድካም በኋላ የሚደርቅ ካለ ተስፋ ሳይቆርጡ ቀሪውን በህይወት ማቆየት የራሱ የሆነ ፈተና ነው፡፡
አንተ ውስጥ ያንተን ሙሉ ምስል የያዘ ዘር አለ ፤ ይህንን ዘር ወደ አበባነት መቀየር ቀላል አይደለም በመንገዱ ላይ ቀላል ያልሆኑ ችግሮች ይገጥማሉ እነዚህን ችግሮች እየተጋፈጡ እና ከሁኔታው እየተማሩ ማለፍ ካልተቻለ እርከኑን መሻገር የሚቻል አይሆንም ይህ መንገድ ሙሉውን አበባነትህን እንድትተዋወቀው ይረዳሃል፡፡
አበባ አበባ ሁኖ ለመውጣት በብዙ ነገሮች ውስጥ ያልፋል የትናንት ዘርነቱን አይቶም ዛሬ እንዲህ ያለ መልክ ይኖረዋል ብሎ የሚገምት አይኖርም ፤ነገር ግን አበባ ስሩን ከመሬት ውስጥ በመስደድ እና ለራሱ የማይነቃነቅ መሰረትን በመያዝ ከላይ ደገሞ ርቀቷ ሳይገድበው እና እራሱን ዝቅ አድርጎ ሳይመለከት ከፀሃይ ማግኘት የሚኖርበትን ሁሉ ለማግኘት በመጣር አበባነቱን ያውጃል፡፡
ስለዚህ እኛም በዚህ ምድር ላይ በሚኖረን ቆይታ የራሳችንን ቦታ መፈለግ ይኖርብናል በዚህ ውስጥ አካላዊ እና ስነልቦናዊ የሆኑ ፈተናዎች የሚገጥሙን መሆኑ እሙን ቢሆንም ችግሮቻችን የማስቀረት ስልጣን የለንም፡፡ እኛ ችግሮቻችን ላይ ያለን ስልጣን እንዴት አድርገን እንደምንጋጠማቸው እና እነርሱን እንዴት እንደምናያቸው መወሰን ላይ ነው፡፡
ደብርት እና አዘቅጥ ውስጥ ከተውን እንዲሄዱ እንፈቅድላቸዋልን ወይስ ተምረንባቸውና አሸንፈናቸው ጉዞዋችንን እንቀጥላለን? ችግርን በትክክለኛው ሰዓት እና በትክክለኛው መንገድ መጋፈጥ ለትልቁ እኛነታችን ትልቅ ዕድል ነው፡፡ በስተመጨረሻም ፕሮፌሰሩ እንዲህ ሲሉ አጠቃለዋል፡- ችግሮች ከጠላትነታቸው ይልቅ ጓደኝነታቸው ያመዝናል ከእነሱ ጋር የሚኖረንን ግንኙነት ካሳመርን እና በትክክለኛው መንገድ ካስተናገድናቸው እኛ ውስጥ ያሉ እና የማይታዩ ድብቅ ችሎታዎቻችን ለማውጣት ዓይነተኛ አቅም አላቸው፡፡
ስለዚህ ህይወትን እንደፈተና እራሳችንን ደግሞ እንደ ዘር በመቁጠር ቆንጆውን አበባችንን በትዕግስት መጠባበቅ ይኖርብናል፡፡
ምንጭ፡ Psychology Today
****************************************************************
"ማንም ሁን ፤የትም ሁን፤ በየትኛው እድሜ ክልል ውስጥም ተገኝ አንተ ሁሌም የተግዳሮት ሰለባ ነህ " ሲሉ የሳይኮሎጂው ታለቅ ሰው ፕሮፌሰር በርን በርንሰቴን የስነልቦና ምክራቸውን ጀምረዋል፡፡
የምትወደው ሰው ህይወት አደጋ ውስጥ እንደገባ ሰምተሃል፣ ከመስራቤትሽ ያልጠበቅሽው ደብዳቤ ደርሶሻል፣ የምርመራ ውጤትህ አስደሳች ዜና ይዞ አልመጣም፣ ይዘህ መምጣት የሚኖርብህን ሰነድ ረስተሃል ፣ትራንስፖርት አጥተህ ተሰቃይተሃል ወይንም ሌላ ብዙ እንዲሆን ማትፈልገው ነገር እንዲሆን ተገደሃል እናም እንዲህ ያለው ነገር በየስንት ጊዜው ሂወትህ ውስጥ የሚከሰት ይመስልሃል? ብትባል መልሱ ሁሌም በየቀኑ የሚለው እንደሚሆን አያጠራጥርም፡፡
እነዚህ ተግዳሮቶች ሁሌም አብረውህ ያሉ ወደፊትም የሚኖሩ ናቸው ምናልባትም ተጋፍጠሃቸው እያሸነፍክ መሻገር አልያም እያየሃቸው ወንዙ ዳር ተገትሮ መቅረት የግል ምርጫህ እና ውሳኔ ነው፡፡ ነገር ግን እነዚህ ተግዳሮቶች የቀን ተቀን ፈተናዎችህ ናቸው፡፡
ምናልባትም የህይወት ዓለማ ምንድነው ብለህ ጠይቀህ ታውቅ ይሆን? የህይወት ዓለማ ደስታ፣ ስኬት አልያም እርካታ እና የመሳሰሉትን በጎ ምኞቶች እንደሆኑ የሚዘረዝሩ የተለያዩ ሰዎች ይኖራሉ ለእኔ ግን ይላሉ ፕሮፌሰሩ "የህይወትህ ዓለማ በየቀኑ የሚገጥሙህን ፈተናዎች ማለፍ ነው፡፡" መሆን የምትፈልገው ምንም ይሁን ፤ መድረስ የምታልመውም የትም ይሁን ፊት ለፊትህ ሁሌም ፈተና አለ ያንን ማለፍ ካልቻልክ የትም መድረስ አትችልም፡፡
ህይወት ታላቁን አንተነትህን ትሆን ዘንድ የተሰጠችህ ፈተና ናት!
እቤትህ ውስጥ አበባ ለመትከል እና ለማሳደግ አስበህ ከሆነ እንኳን በቀላሉ ሊሆን የሚችል እንዳልሆነ ልብ ማለት አለብህ ዘር ከማምጣት አንስቶ ቦታ ማዘጋጀት ፣ውሃ ማጠጣት፣ በየቀኑ መንከባከብ እና አንዳንዴም ከዚህ ሁላ ድካም በኋላ የሚደርቅ ካለ ተስፋ ሳይቆርጡ ቀሪውን በህይወት ማቆየት የራሱ የሆነ ፈተና ነው፡፡
አንተ ውስጥ ያንተን ሙሉ ምስል የያዘ ዘር አለ ፤ ይህንን ዘር ወደ አበባነት መቀየር ቀላል አይደለም በመንገዱ ላይ ቀላል ያልሆኑ ችግሮች ይገጥማሉ እነዚህን ችግሮች እየተጋፈጡ እና ከሁኔታው እየተማሩ ማለፍ ካልተቻለ እርከኑን መሻገር የሚቻል አይሆንም ይህ መንገድ ሙሉውን አበባነትህን እንድትተዋወቀው ይረዳሃል፡፡
አበባ አበባ ሁኖ ለመውጣት በብዙ ነገሮች ውስጥ ያልፋል የትናንት ዘርነቱን አይቶም ዛሬ እንዲህ ያለ መልክ ይኖረዋል ብሎ የሚገምት አይኖርም ፤ነገር ግን አበባ ስሩን ከመሬት ውስጥ በመስደድ እና ለራሱ የማይነቃነቅ መሰረትን በመያዝ ከላይ ደገሞ ርቀቷ ሳይገድበው እና እራሱን ዝቅ አድርጎ ሳይመለከት ከፀሃይ ማግኘት የሚኖርበትን ሁሉ ለማግኘት በመጣር አበባነቱን ያውጃል፡፡
ስለዚህ እኛም በዚህ ምድር ላይ በሚኖረን ቆይታ የራሳችንን ቦታ መፈለግ ይኖርብናል በዚህ ውስጥ አካላዊ እና ስነልቦናዊ የሆኑ ፈተናዎች የሚገጥሙን መሆኑ እሙን ቢሆንም ችግሮቻችን የማስቀረት ስልጣን የለንም፡፡ እኛ ችግሮቻችን ላይ ያለን ስልጣን እንዴት አድርገን እንደምንጋጠማቸው እና እነርሱን እንዴት እንደምናያቸው መወሰን ላይ ነው፡፡
ደብርት እና አዘቅጥ ውስጥ ከተውን እንዲሄዱ እንፈቅድላቸዋልን ወይስ ተምረንባቸውና አሸንፈናቸው ጉዞዋችንን እንቀጥላለን? ችግርን በትክክለኛው ሰዓት እና በትክክለኛው መንገድ መጋፈጥ ለትልቁ እኛነታችን ትልቅ ዕድል ነው፡፡ በስተመጨረሻም ፕሮፌሰሩ እንዲህ ሲሉ አጠቃለዋል፡- ችግሮች ከጠላትነታቸው ይልቅ ጓደኝነታቸው ያመዝናል ከእነሱ ጋር የሚኖረንን ግንኙነት ካሳመርን እና በትክክለኛው መንገድ ካስተናገድናቸው እኛ ውስጥ ያሉ እና የማይታዩ ድብቅ ችሎታዎቻችን ለማውጣት ዓይነተኛ አቅም አላቸው፡፡
ስለዚህ ህይወትን እንደፈተና እራሳችንን ደግሞ እንደ ዘር በመቁጠር ቆንጆውን አበባችንን በትዕግስት መጠባበቅ ይኖርብናል፡፡
ምንጭ፡ Psychology Today
የክላውድ ኮምፕዩቲንግ መሰረታዊነት
***********************************
በኮምፒውተር ኢንዳስትሪ ማርሽ ቀያሪ ሊባሉ የሚችሉ ቴክኖሎጂዎች በየግዜው ይከሰታሉ። ክላውድ ኮምፕዩቲንግ ምናልባት ከነዚህ ተጠቃሽ ቴክኖሎጂ ውስጥ አንዱ ሊሆን ይችላል። ቃሉን በቀጥታ ወደ አማርኛ ከተረጎምነው ዳመና ላይ ማስላት ሊሆን ይችላል፤ ይሁንና ይህን ዓይነት ትርጉም መስጠት ከቴክኖሎጂው መሰረታዊ ፅንሰ ሃሳብ ጋር ይበልጥ ስለማይጎዳኝ የእንግሊዘኛውን ስያሜ መጠቀም የተሻለ ነው።
ክላውድ ኮምፒዩቲንግ በአጭሩ ሲገለጽ የኮምፒውተር አገልግሎቶች ማለትም ሰርቨሮች፣ የውሂብ (data) ማጠራቀምያዎች፣ አውታር መረቦች፣ ሶፍትዌሮች እና ሌሎች አገልግሎቶችን ኢንተርኔት (ክላውድ) ተጠቅሞ የሚያቀርብልን ቴክኖሎጂ ነው። ይህ ማለት ውሂብ ወይም ዳታ የምናስቀምጠው በኮምፒተራችን ሳይሆን፤ ሌሎች ድርጅቶች በሚቆጣጠሩት ኮምፒውተር ነው ማለት ነው። ያስቀመጥነውን ውሂብ ማግኘት ስንፈልግ፣ ኢንተርኔትን ተጠቅመን ወደ የግላችን ኮምፒውተር መገልበጥ ወይም እዛው ክላውድ ላይ እያለ በማሰሻ (browser) ከፍተን ማየት እንችላለን። ይሁንና ክላውድ ኮምፒዩቲንግ ውሂብ ማከማቻ ጎተራዎች ብቻ አይደለም በአገልግሎት መልክ የሚያቀርብልን፤ ማንኛውም ኮምፒውተራችን ላይ ማድረግ የምንችለውን ተግባር በተሻለ ፍጥነት እና ዋጋ ማከናወን የሚይስችለን ቴክኖሎጂ ነው።
ከክላውድ ኮምፕዩቲንግ መምጣት በፊት፤ ሶፍትዌር የሚያመርቱ እና የሚጠቀሙ ግለሰቦች እና ድርጅቶች ብዙ ዓይነት ሶፍትዌር እና ሃርድዌር ገዝተው ይጠቀሙ ነበር። ይህ ውድና ውስብስብ ከመሆኑም በላይ፤ ለአጭር ግዜ ብቻ መጠቀም የምንፈልገውን ሃርድዌር ከመግዛት ውጪ ሌላ አማራጭ አልነበረም። በዚህም ምክንያት ወደ ገበያ ለመግባት የሚፈልጉ ድርጅቶች ከጅምሩ ብዙ ወጪ ማውጣት ግድ ይላቸው ነበር። ድርጅቶች ከጅምሩ ምን ያክል የውሂብ ማጠራቀምያ (storage)፣ የማስያ ጉልበት (processing power) ወዘተ…. እንደሚያስፈልጋቸው በቀላሉ መገመት አይችሉም። ድርጅታቸው ከሚፈልገው በላይ ጉልበት ያላቸው ሃርድዌር ከገዙ ለአላስፈላጊ ወጪ ይጋለጣሉ፤ ካሳነሱት ደግሞ ሲስተማቸው ተገቢውን አገልግሎት ለመስጠት ይቸገራል። ይህንን ዓይነት ችግር ለመፍታት ክላውድ ኮምፒዩቲንግ እጅግ ወሳኝ ቴክኖሎጂ ነው።
እንደ አማዞን፤ ማይክሮሶፍት እና ጉግል የመሳሰሉ ድርጅቶች ብዙ ክፍተኛ አቅም ያላቸውን ኮምፒውተሮችን አዘጋጅተው ለድርጅቶች እና ግለሰቦች ያከራያሉ። ለምሳሌ አንድ ሰው 100 ኮምፒተሮችን ተጠቅሞ ውስብስብ የሆነ የኮምፒውተር ሲሙሌሽን መስራት ቢፈልግ፤ 100 ኮምፒተሮችን መግዛት አይጠበቅበትም ማለት ነው። ከ አማዞን እነዛን ኮምፒተሮች ተከራይቶ ተገቢውን ሶፍትዌር ኮምፒተሮቹ ላይ በርቀት (ኢንተርኔት ተጠቅሞ) ይጭናል። የፈለገውን ስራ አከናውኖ የተገኘውን ውጤት ወደ ራሱ ኮምፒተር መውስድ ይችላል። ይህ ሰውዬ እንደዚህ በማድረጉ ብዙ ነገር አትርፏል። አንደኛ ስራው መጀመርያ እንዳሰበው በ 100 ኮምፒተሮች ብቻ የማይከናወን ከሆነ በቀላሉ ተጨማሪ ኮምፒተሮችን ማሰማራት ይችላል። ሁለተኛ ደግሞ ሰውዬው ክላውድ ኮምፕዩቲንግ ሲጠቀም የሚከፍለው ብር ልክ እንደ ውሃና ኤሌክትሪክ በተጠቀመበት መጠን በመሆኑ እነዛን 100 ኮምፒተሮች ለ አንድ ሰዓት ብቻ ከተጠቀመ የሚከፍለው በዛ ልክ ብቻ ነው። ይህም ክላውድ ኮምፕዩቲንግን እጅግ አስፈላጊ ከማድረጉም በተጨማሪ ተለጣጭ ወይም (elastic) ባህሪ ያለው ቴክኖሎጂ ያደርገዋል።
የክላውድ ኮምፒዊቲንግ ቀላል ምሳሌ ከፈለግን በሞባይላችን ውሂብ መጠባበቅያ (backup) ስናስቀምጥ፤ ኢሜል ስንጠቀም እና ሌሎች ነገሮችን ስናደርግ መረጃችን ያለምንም መጨናነቅ መቀመጣቸው የክላውድ አስፈላጊነትን በሚገባ ያሳዩናል። ስልካችን ቢጠፋም አስፈላጊውን ቅጽ በመሙላት የጠፉብንን ውሂቦች የምናገኘው በክላውድ የተነሳ ነው። ለምሳሌ ፌስቡክን ካየነው ሙሉ በሙሉ ክላውድ መሰረት ያደረገ አፕሊኬሽን በመሆኑ ኢንተርኔት እስካለን ድረስ ማንኛውንም ፌስቡክ ላይ ያደረግነውን እንቅስቃሴ በየትኛውም የዓለም ክፍል ሆነን ማየት እንችላለን።
ምንጭ፡ AD. Information Technology እና tech viral
***********************************
በኮምፒውተር ኢንዳስትሪ ማርሽ ቀያሪ ሊባሉ የሚችሉ ቴክኖሎጂዎች በየግዜው ይከሰታሉ። ክላውድ ኮምፕዩቲንግ ምናልባት ከነዚህ ተጠቃሽ ቴክኖሎጂ ውስጥ አንዱ ሊሆን ይችላል። ቃሉን በቀጥታ ወደ አማርኛ ከተረጎምነው ዳመና ላይ ማስላት ሊሆን ይችላል፤ ይሁንና ይህን ዓይነት ትርጉም መስጠት ከቴክኖሎጂው መሰረታዊ ፅንሰ ሃሳብ ጋር ይበልጥ ስለማይጎዳኝ የእንግሊዘኛውን ስያሜ መጠቀም የተሻለ ነው።
ክላውድ ኮምፒዩቲንግ በአጭሩ ሲገለጽ የኮምፒውተር አገልግሎቶች ማለትም ሰርቨሮች፣ የውሂብ (data) ማጠራቀምያዎች፣ አውታር መረቦች፣ ሶፍትዌሮች እና ሌሎች አገልግሎቶችን ኢንተርኔት (ክላውድ) ተጠቅሞ የሚያቀርብልን ቴክኖሎጂ ነው። ይህ ማለት ውሂብ ወይም ዳታ የምናስቀምጠው በኮምፒተራችን ሳይሆን፤ ሌሎች ድርጅቶች በሚቆጣጠሩት ኮምፒውተር ነው ማለት ነው። ያስቀመጥነውን ውሂብ ማግኘት ስንፈልግ፣ ኢንተርኔትን ተጠቅመን ወደ የግላችን ኮምፒውተር መገልበጥ ወይም እዛው ክላውድ ላይ እያለ በማሰሻ (browser) ከፍተን ማየት እንችላለን። ይሁንና ክላውድ ኮምፒዩቲንግ ውሂብ ማከማቻ ጎተራዎች ብቻ አይደለም በአገልግሎት መልክ የሚያቀርብልን፤ ማንኛውም ኮምፒውተራችን ላይ ማድረግ የምንችለውን ተግባር በተሻለ ፍጥነት እና ዋጋ ማከናወን የሚይስችለን ቴክኖሎጂ ነው።
ከክላውድ ኮምፕዩቲንግ መምጣት በፊት፤ ሶፍትዌር የሚያመርቱ እና የሚጠቀሙ ግለሰቦች እና ድርጅቶች ብዙ ዓይነት ሶፍትዌር እና ሃርድዌር ገዝተው ይጠቀሙ ነበር። ይህ ውድና ውስብስብ ከመሆኑም በላይ፤ ለአጭር ግዜ ብቻ መጠቀም የምንፈልገውን ሃርድዌር ከመግዛት ውጪ ሌላ አማራጭ አልነበረም። በዚህም ምክንያት ወደ ገበያ ለመግባት የሚፈልጉ ድርጅቶች ከጅምሩ ብዙ ወጪ ማውጣት ግድ ይላቸው ነበር። ድርጅቶች ከጅምሩ ምን ያክል የውሂብ ማጠራቀምያ (storage)፣ የማስያ ጉልበት (processing power) ወዘተ…. እንደሚያስፈልጋቸው በቀላሉ መገመት አይችሉም። ድርጅታቸው ከሚፈልገው በላይ ጉልበት ያላቸው ሃርድዌር ከገዙ ለአላስፈላጊ ወጪ ይጋለጣሉ፤ ካሳነሱት ደግሞ ሲስተማቸው ተገቢውን አገልግሎት ለመስጠት ይቸገራል። ይህንን ዓይነት ችግር ለመፍታት ክላውድ ኮምፒዩቲንግ እጅግ ወሳኝ ቴክኖሎጂ ነው።
እንደ አማዞን፤ ማይክሮሶፍት እና ጉግል የመሳሰሉ ድርጅቶች ብዙ ክፍተኛ አቅም ያላቸውን ኮምፒውተሮችን አዘጋጅተው ለድርጅቶች እና ግለሰቦች ያከራያሉ። ለምሳሌ አንድ ሰው 100 ኮምፒተሮችን ተጠቅሞ ውስብስብ የሆነ የኮምፒውተር ሲሙሌሽን መስራት ቢፈልግ፤ 100 ኮምፒተሮችን መግዛት አይጠበቅበትም ማለት ነው። ከ አማዞን እነዛን ኮምፒተሮች ተከራይቶ ተገቢውን ሶፍትዌር ኮምፒተሮቹ ላይ በርቀት (ኢንተርኔት ተጠቅሞ) ይጭናል። የፈለገውን ስራ አከናውኖ የተገኘውን ውጤት ወደ ራሱ ኮምፒተር መውስድ ይችላል። ይህ ሰውዬ እንደዚህ በማድረጉ ብዙ ነገር አትርፏል። አንደኛ ስራው መጀመርያ እንዳሰበው በ 100 ኮምፒተሮች ብቻ የማይከናወን ከሆነ በቀላሉ ተጨማሪ ኮምፒተሮችን ማሰማራት ይችላል። ሁለተኛ ደግሞ ሰውዬው ክላውድ ኮምፕዩቲንግ ሲጠቀም የሚከፍለው ብር ልክ እንደ ውሃና ኤሌክትሪክ በተጠቀመበት መጠን በመሆኑ እነዛን 100 ኮምፒተሮች ለ አንድ ሰዓት ብቻ ከተጠቀመ የሚከፍለው በዛ ልክ ብቻ ነው። ይህም ክላውድ ኮምፕዩቲንግን እጅግ አስፈላጊ ከማድረጉም በተጨማሪ ተለጣጭ ወይም (elastic) ባህሪ ያለው ቴክኖሎጂ ያደርገዋል።
የክላውድ ኮምፒዊቲንግ ቀላል ምሳሌ ከፈለግን በሞባይላችን ውሂብ መጠባበቅያ (backup) ስናስቀምጥ፤ ኢሜል ስንጠቀም እና ሌሎች ነገሮችን ስናደርግ መረጃችን ያለምንም መጨናነቅ መቀመጣቸው የክላውድ አስፈላጊነትን በሚገባ ያሳዩናል። ስልካችን ቢጠፋም አስፈላጊውን ቅጽ በመሙላት የጠፉብንን ውሂቦች የምናገኘው በክላውድ የተነሳ ነው። ለምሳሌ ፌስቡክን ካየነው ሙሉ በሙሉ ክላውድ መሰረት ያደረገ አፕሊኬሽን በመሆኑ ኢንተርኔት እስካለን ድረስ ማንኛውንም ፌስቡክ ላይ ያደረግነውን እንቅስቃሴ በየትኛውም የዓለም ክፍል ሆነን ማየት እንችላለን።
ምንጭ፡ AD. Information Technology እና tech viral
ፍሬያማ ምርት
*****
ወደ አንድ ቢሊዮን የሚጠጋ ህዝብ በረሃብ እየማቀቀ ይገኛል፡፡ ምናልባትም ለዚህ ጥያቄ መልስ የሚሆነን በቂ እህል ማምረት ብቻ ሊሆን ይችላል ነገር ግን ይህ በቀላሉ የሚሳካ አይደለም፡፡ የማዳበሪያ አጠቃቀም፣ የውሃ እጥረት እና ሰብልን የማሾር(Crop rotation) ልምድ አናሳ መሆን ይህ እውን እንዳሆን እንቅፋት ሆኗል፡፡
ሰብልን ማሾር፡- በአንድ ቦታ ላይ ለረዥም ጊዜ አንድ አይነት ሰብሎችን አለመዝራት እና በዙር በዙር የተለያዩ ሰብሎችን እየዘሩ የአፈሩን ደህንነት የማስጠበቅ ሂደት፡፡
ይህንን በተመለከተም የ Global Landscapes Initiative at the University of Minnesota ተመራማሪ እና ዳይሬክተር ፖል.ሲ ዌስት እና ባልደረቦቹ ሰፊ ጥናት በማካሄድ የዓለምን የምግብ ዋስትና ለመረጋገጥ ያስችላል ያሏቸውን 5 ዋና ነጥቦች በጥናት ፅሁፋቸው ውስጥ ያቀረቡ ሲሆን እኛ ለዛሬ 3ቱን እንካችሁ እያልን ቀሪዎቹን በሌላ ጊዜ የምናቀርባቸው ይናል፡፡
ፖል ለTreeHugger(ዌብሳይት) በሰጠው መግለጫ ላይም እንዳለው ከሆነ በጥናታችን ውስጥ የጠቀስናቸው ጉዳዮች ላይ አፅንዖት ተሰጥቶ ቢሰራበት 3ቢሊዮበን የሚሆንን ህዝብ በስርዓቱ መመገብ የሚቻል ከመሆኑም በላይ ከባቢውን አዎንታዊ በሆነ መንገድ የመለወጥ ትሩፋት አለው ብለዋል፡፡
1- የምርት ልዩነትን ማጥበብ
እንደ (World Wildlife Fund) ግምት ከሆነ በ2050 120 ሚሊዮን ሄክታር የሚጠጋ ተፈጥሯዊ የመኖሪያ ቦታ ወደ እርሻ ቦታነት ይቀየራል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ዓለም ላይ ያሉ የእርሻ ቦታዎች ማምረት ከሚገባቸው እና ከሚችሉት በ50 ፐርሰንት ያነሰ እያመረቱ ነው፡፡ በመሆኑም አሁን ላይ ምንም ተጨማሪ የእርሻ መሬት ሳንጠቀም የእርሻ መሬቶች ማምረት የሚገባቸውን ያህል ማምረት የሚችሉበትን ሁኔታ ብናመቻች እና ጋፑን/ልዩነቱን ማጥበብ ከቻልን ተጨማሪ 850ሚሊዮን ህዝብ መመገብ ይችላሉ፡፡ ሰለዚህ ቀጣዩ ጥያቄ የሚሆነው ልዩነቱን እንዴት እናጥብብ የሚለው ነው፡፡
2- ማዳበሪያዎችን በብቃት እና በትክክል መጠቀም
ምንም እንኳን እኛ እንደ TreeHugger አርቴፊሻል ማዳበሪያዎችን መጠቀምን ባናበረታታም አሁን ላይ በዓለም ዙሪያ ከፍተኛ ተጠቃሚነት አለ ፡፡ ይሁንና ይህ ጥናት ማዳበሪያን በተመለከተ ጥሩ ዜና ይዞ ብቅ ያለ ሲሆን እሱም ዓለም ስንዴ፣ሩዝ እና በቆሎ ለማምረት እየጠቀመች ያለችውን የናይትሮጂን እና የፎስፈረስ ማዳበሪያ መጠን ከ13 -29 ፐርሰንት ቀንሳም ቢሆን ከዚህ በፊት የምታመርተውን ያህል ማምረት ትችላለች ፡፡ በተጨማሪም የማዳበሪያ አጠቃቀም እውቀትን በማሳደግ መች እና እንዴት መጠቀም እንዳለብን ካወቅን ትርፋማ የመሆን እድላችን ሰፊ ይሆናል፡፡
3- አነስተኛ ውሃ የሚፈልጉ ምርቶች ላይ ማተኮር
በግብርና ዓለም ውስጥ ውሃ ትልቁ ተግዳሮት ነው፡፡ ይህንን ለመዋጋትም መስኖን መጠቀም እና እምብዛም ውሃ የማይሹ ምርቶችን ማበረታታት እንደ ዓይነተኛ አማራጭ መታየት አለበት ያሉ ሲሆን ለምሳሌ ያህል እንደ ሩዝ እና እንደ ስኳር ድንች ያሉ ምርቶች ከፍተኛ ውሃ የሚሹ ምርቶች በመሆናቸው ትልቅ እክል ይገጥማቸዋል፡፡
ይሁንና የምግብ ምርት የብዙ ነገር ተፅዕኖ የሚያርፍበት ስራ ነው፤ አንድ ገበሬ የሚያመርተው ገበያውን እና ባህሉን ተንተርሶ በመሆኑ በቀላሉ የሚያመርተውን ነገር መቀየር የሚችል አይደለም ይህ ደግሞ አነስተኛ ውሃ የሚሹ ምርቶችን ተመራጭ ላያደርጋቸው ይችላል ሲሉ ተግዳሮቱን ጠቆም አድርገው አልፈዋል፡፡
ምንጭ፡- TreeHugger
*****
ወደ አንድ ቢሊዮን የሚጠጋ ህዝብ በረሃብ እየማቀቀ ይገኛል፡፡ ምናልባትም ለዚህ ጥያቄ መልስ የሚሆነን በቂ እህል ማምረት ብቻ ሊሆን ይችላል ነገር ግን ይህ በቀላሉ የሚሳካ አይደለም፡፡ የማዳበሪያ አጠቃቀም፣ የውሃ እጥረት እና ሰብልን የማሾር(Crop rotation) ልምድ አናሳ መሆን ይህ እውን እንዳሆን እንቅፋት ሆኗል፡፡
ሰብልን ማሾር፡- በአንድ ቦታ ላይ ለረዥም ጊዜ አንድ አይነት ሰብሎችን አለመዝራት እና በዙር በዙር የተለያዩ ሰብሎችን እየዘሩ የአፈሩን ደህንነት የማስጠበቅ ሂደት፡፡
ይህንን በተመለከተም የ Global Landscapes Initiative at the University of Minnesota ተመራማሪ እና ዳይሬክተር ፖል.ሲ ዌስት እና ባልደረቦቹ ሰፊ ጥናት በማካሄድ የዓለምን የምግብ ዋስትና ለመረጋገጥ ያስችላል ያሏቸውን 5 ዋና ነጥቦች በጥናት ፅሁፋቸው ውስጥ ያቀረቡ ሲሆን እኛ ለዛሬ 3ቱን እንካችሁ እያልን ቀሪዎቹን በሌላ ጊዜ የምናቀርባቸው ይናል፡፡
ፖል ለTreeHugger(ዌብሳይት) በሰጠው መግለጫ ላይም እንዳለው ከሆነ በጥናታችን ውስጥ የጠቀስናቸው ጉዳዮች ላይ አፅንዖት ተሰጥቶ ቢሰራበት 3ቢሊዮበን የሚሆንን ህዝብ በስርዓቱ መመገብ የሚቻል ከመሆኑም በላይ ከባቢውን አዎንታዊ በሆነ መንገድ የመለወጥ ትሩፋት አለው ብለዋል፡፡
1- የምርት ልዩነትን ማጥበብ
እንደ (World Wildlife Fund) ግምት ከሆነ በ2050 120 ሚሊዮን ሄክታር የሚጠጋ ተፈጥሯዊ የመኖሪያ ቦታ ወደ እርሻ ቦታነት ይቀየራል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ዓለም ላይ ያሉ የእርሻ ቦታዎች ማምረት ከሚገባቸው እና ከሚችሉት በ50 ፐርሰንት ያነሰ እያመረቱ ነው፡፡ በመሆኑም አሁን ላይ ምንም ተጨማሪ የእርሻ መሬት ሳንጠቀም የእርሻ መሬቶች ማምረት የሚገባቸውን ያህል ማምረት የሚችሉበትን ሁኔታ ብናመቻች እና ጋፑን/ልዩነቱን ማጥበብ ከቻልን ተጨማሪ 850ሚሊዮን ህዝብ መመገብ ይችላሉ፡፡ ሰለዚህ ቀጣዩ ጥያቄ የሚሆነው ልዩነቱን እንዴት እናጥብብ የሚለው ነው፡፡
2- ማዳበሪያዎችን በብቃት እና በትክክል መጠቀም
ምንም እንኳን እኛ እንደ TreeHugger አርቴፊሻል ማዳበሪያዎችን መጠቀምን ባናበረታታም አሁን ላይ በዓለም ዙሪያ ከፍተኛ ተጠቃሚነት አለ ፡፡ ይሁንና ይህ ጥናት ማዳበሪያን በተመለከተ ጥሩ ዜና ይዞ ብቅ ያለ ሲሆን እሱም ዓለም ስንዴ፣ሩዝ እና በቆሎ ለማምረት እየጠቀመች ያለችውን የናይትሮጂን እና የፎስፈረስ ማዳበሪያ መጠን ከ13 -29 ፐርሰንት ቀንሳም ቢሆን ከዚህ በፊት የምታመርተውን ያህል ማምረት ትችላለች ፡፡ በተጨማሪም የማዳበሪያ አጠቃቀም እውቀትን በማሳደግ መች እና እንዴት መጠቀም እንዳለብን ካወቅን ትርፋማ የመሆን እድላችን ሰፊ ይሆናል፡፡
3- አነስተኛ ውሃ የሚፈልጉ ምርቶች ላይ ማተኮር
በግብርና ዓለም ውስጥ ውሃ ትልቁ ተግዳሮት ነው፡፡ ይህንን ለመዋጋትም መስኖን መጠቀም እና እምብዛም ውሃ የማይሹ ምርቶችን ማበረታታት እንደ ዓይነተኛ አማራጭ መታየት አለበት ያሉ ሲሆን ለምሳሌ ያህል እንደ ሩዝ እና እንደ ስኳር ድንች ያሉ ምርቶች ከፍተኛ ውሃ የሚሹ ምርቶች በመሆናቸው ትልቅ እክል ይገጥማቸዋል፡፡
ይሁንና የምግብ ምርት የብዙ ነገር ተፅዕኖ የሚያርፍበት ስራ ነው፤ አንድ ገበሬ የሚያመርተው ገበያውን እና ባህሉን ተንተርሶ በመሆኑ በቀላሉ የሚያመርተውን ነገር መቀየር የሚችል አይደለም ይህ ደግሞ አነስተኛ ውሃ የሚሹ ምርቶችን ተመራጭ ላያደርጋቸው ይችላል ሲሉ ተግዳሮቱን ጠቆም አድርገው አልፈዋል፡፡
ምንጭ፡- TreeHugger
የኢትዮጵያ የሳይንስ ሳምንት በመካሄድ ላይ ነው
##########################
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ፣ ከኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ፣ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ከትምህርት ሚኒስቴር እና ከሌሎች አጋር ተቋማት ጋር በመተባበር ለአራት ቀናት የሚቆይ የሳይንስ ሳምንት ከዛሬው ዕለተ አንስቶ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ መካሄድ ጀምሯል፡፡ እንደአውሮፓውያኑ አቆጣጠር በየዓመቱ ህዳር 10 የሚከበረውን ዓለም አቀፍ የሳይንስ ቀን ምክንያት በማድረግ በሃገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄደው ይህ የሳይንስ ሳምንት በተለያዩ የፈጠራ ወድድሮችና የአውደ ርዕይ ስነ ስርዓቶች በመከበር ላይ ይገኛል፡፡
በዚህ ስነ ስርዓት ከሁሉም የሃገሪቱ ክፍሎች የተወጣጡ የመጀመሪያ ደረጃ (7ኛ እና 8ኛ) ፣ የሁለተኛ ደረጃ እና የመሰናዶ ተማሪዎች በየክፍል ደረጃቸው በሚያቀርቡት የፈጠራ ፕሮጀክት የሚወዳደሩ ሲሆን፤ ከዚህ በተጨማሪም ከ7ኛ እስከ 12ኛ ክፍል የሚያስተምሩ መምህራን እና ከተለያዩ ስቴም ማዕከላት የተወጣጡ የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች በኢንጂነሪንግ፣ ሮቦቲክስ እና ሌሎች መሰል ዘርፎች ላይ ፈጠራቸውን ያቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በዚህ ውድድር በአጠቃላይ የትምህርት ዘርፍ በተማሪዎች ብቻ ከ100 በላይ ፕሮጀክቶች የሚቀርቡ ሲሆን የመምህራን እና የስቴም ማዕከለት ሲጨመር ደግሞ ከ187 በላይ ፕሮጀክቶች ለውድድር ያቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በተዘጋጀው በዚህ የሳይንስ ሳምንት ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ፅዮን ተክሉ እንዳሉት የተዘጋጀው ይህ የውድድር መድረክ ተማሪዎች በክፍል ውስጥ የቀሰሙትን የንድፈ ሃሳብ ትምህርት ችግሮችን ሊፈታ ወደሚችል ጠቃሚ ፈጠራ እንዲቀይሩ ከማገዙም ባለፈ በመጪው ጊዜ ለሚኖራቸው የስራ ክህሎት ጥሩ ልምድ እና መልካም አጋጣሚ እንደሚፈጥርላቸው አንስተዋል፡፡
በአለም አቀፍ ደረጃ ለ17ኛ ጊዜ በሃገራችን ደግሞ ለአራተኛ ጊዜ የሚከበረው የሳይንስ ሳምንት “Open Scienece, Leaving No One Behined” በሚል መሪ ቃል በአለም አቀፍ ደረጃ እየተከበረ ሲሆን በኢትዮጵያም በተለያዩ የፈጠራ ውድድሮች እና የአውደ ርዕይ ስነ ስርዓቶች ዛሬን ጨምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት እንደሚከበር አዘጋጆቹ አስታውቀዋል፡፡
##########################
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ፣ ከኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ፣ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ከትምህርት ሚኒስቴር እና ከሌሎች አጋር ተቋማት ጋር በመተባበር ለአራት ቀናት የሚቆይ የሳይንስ ሳምንት ከዛሬው ዕለተ አንስቶ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ መካሄድ ጀምሯል፡፡ እንደአውሮፓውያኑ አቆጣጠር በየዓመቱ ህዳር 10 የሚከበረውን ዓለም አቀፍ የሳይንስ ቀን ምክንያት በማድረግ በሃገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄደው ይህ የሳይንስ ሳምንት በተለያዩ የፈጠራ ወድድሮችና የአውደ ርዕይ ስነ ስርዓቶች በመከበር ላይ ይገኛል፡፡
በዚህ ስነ ስርዓት ከሁሉም የሃገሪቱ ክፍሎች የተወጣጡ የመጀመሪያ ደረጃ (7ኛ እና 8ኛ) ፣ የሁለተኛ ደረጃ እና የመሰናዶ ተማሪዎች በየክፍል ደረጃቸው በሚያቀርቡት የፈጠራ ፕሮጀክት የሚወዳደሩ ሲሆን፤ ከዚህ በተጨማሪም ከ7ኛ እስከ 12ኛ ክፍል የሚያስተምሩ መምህራን እና ከተለያዩ ስቴም ማዕከላት የተወጣጡ የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች በኢንጂነሪንግ፣ ሮቦቲክስ እና ሌሎች መሰል ዘርፎች ላይ ፈጠራቸውን ያቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በዚህ ውድድር በአጠቃላይ የትምህርት ዘርፍ በተማሪዎች ብቻ ከ100 በላይ ፕሮጀክቶች የሚቀርቡ ሲሆን የመምህራን እና የስቴም ማዕከለት ሲጨመር ደግሞ ከ187 በላይ ፕሮጀክቶች ለውድድር ያቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በተዘጋጀው በዚህ የሳይንስ ሳምንት ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ፅዮን ተክሉ እንዳሉት የተዘጋጀው ይህ የውድድር መድረክ ተማሪዎች በክፍል ውስጥ የቀሰሙትን የንድፈ ሃሳብ ትምህርት ችግሮችን ሊፈታ ወደሚችል ጠቃሚ ፈጠራ እንዲቀይሩ ከማገዙም ባለፈ በመጪው ጊዜ ለሚኖራቸው የስራ ክህሎት ጥሩ ልምድ እና መልካም አጋጣሚ እንደሚፈጥርላቸው አንስተዋል፡፡
በአለም አቀፍ ደረጃ ለ17ኛ ጊዜ በሃገራችን ደግሞ ለአራተኛ ጊዜ የሚከበረው የሳይንስ ሳምንት “Open Scienece, Leaving No One Behined” በሚል መሪ ቃል በአለም አቀፍ ደረጃ እየተከበረ ሲሆን በኢትዮጵያም በተለያዩ የፈጠራ ውድድሮች እና የአውደ ርዕይ ስነ ስርዓቶች ዛሬን ጨምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት እንደሚከበር አዘጋጆቹ አስታውቀዋል፡፡
በዓይን የማይታየው ዓለም
********************
የሰው ልጅ በየዘመኑ በፈለሰፋቸው የቴክኖሎጂ አቅሞች በመታገዝ በዙሪያው የሚገኙትን በዓይን የሚታዩ ሕይወት ያላቸውንና የሌላቸውን አካላት አፈጣጠር፣ አኗኗርና ጠቀሜታ ሳይንሳዊ ትንታኔ በመስጠት ረገድ ዘመናትን ያስቆጠረ ሲሆን፣ ከተለመደውና ከሚታወቀው ባሻገር ያለውን በዓይን መታየት የማይችለውን የደቂቅ አካላት ዓለም (microbial world) የማወቅ አቅም የፈጠረው ዘግይቶ ነው፡፡
ስለ ደቂቅ አካላት መኖር መነገር የጀመረው ከ5ኛው ክፍለ ዘመን (BC) ጀምሮ ቢሆንም በ17ኛው ክፍለ ዘመን የታዋቂዎቹ ሳይንቲስቶች የሮበርት ሁክና የአንቶኒዮ ቫን ሊቨንሆክ በማስረጃ የተደገፈ አዲስ ግኝት በዓይን የማይታዩ አካለት መኖራቸውን ያበሰረ ነበር፡፡ በ1663 ዓ.ም በሮበረት ሁክ በባለ አንድ ሌንስ ትንሽ ማይክሮስኮፕ በመታገዝ ለመጀመሪያ ጊዜ ሙከር (Mucor) የተባለውን የፈንገስ ዘር በማግኘት የተጀመረው በዓይን የማይተየውን ዓለም የማወቅ ጅማሬ ከ1677-1678 ዓ.ም ባለው ጊዜ አንቶኒዮ ቫን ሊቨንሆክ ባሻሻለው ማይክሮስኮፕ “little animalcules” በመባል የተጠሩትን ባክቴሪያ ለማየት በመቻሉ የበለጠ ወደ መታወቅ የተሸጋገረበት ወቅት እንደነበር ታሪክ ያስረዳል::
አሁን ላይ በተደረሰበት ሳይንሳዊ ውጤት መሰረት በዚህ በዓይን በማይታየው የፍጥረት ዓለም ውስጥ የተመደቡት በወል ስማቸው ደቂቅ አካላት1 (microorganisms/microbes) ተብለው የሚታወቁት ፍጥረቶች በየዘርፋቸው ሲዘረዘሩ አርኪያ (Archae)፣ ባክቴሪያ (bacteria)፣ ፈንገስ (Fungus)፣ ማይክሮአልጌ (Microalgae)፣ ፕሮቶዞዋ (Protozoa) እና ቫይረስ (virus) የተባሉት ናቸው፡፡
ደቂቅ አካላት ሕይወት ካላቸው የምድር ፍጥረታት ከ3.5 ቢሊዮን ዓመታት በፊት ቀድመው የተፈጠሩ የፍጥረት ዓይነቶች ናቸው፡፡ እነዚህ በዓይን የማይታዩ የምድራችን ፍጥረታት ከነሱ በኋላ ለመጡት በሕይወት መቀጠል ከፍተኛ አስተዋጽኦ የነበራቸው እንደሆኑ ሳይንሳዊ የምርምር ውጤቶች ያስረዳሉ፡፡ ዛሬም ቢሆን ካለነዚህ ደቂቅ ፍጥረታት አስተዋጽዖ ሌሎች በሕይወት መቀጠል እንደማይችሉ ሳይንቲስቶች ያምናሉ፡፡ በምድር ላይ ለ3.5 ቢሊዮን ዓመታት ባደረጉት ዝግመተ ለውጥና መላመድ በምድራችን በየትኛውም አካባቢ ለመኖር ችለዋል፡፡፡ በዚህም የተነሳ ሌሎች ፍጥረታት ሊኖሩ በማይችሉባቸው አስቸጋሪ ቦታዎች ምግብ ሳይቸግራቸውና በሕይወት ለመኖር ስጋት ሳይገባቸው ኖረዋል፣ እየኖሩም ነው፡፡ ለእነርሱ በሚኖሩባቸው ቦታዎች ሁሉ ምግብ አለ፣ ሕይወት አለ፡፡
የደቂቅ አካላት ልከት (size) በጣም ትንሽ መሆን በዓይን እንዳይታዩ ያደረጋቸው ሲሆን፣ ዛሬም ቢሆን በዘመናዊ ቴክኖሎጂም እንኳን በመታገዝ መታየት የቻሉት በጣም ጥቂቶቹ ብቻ ናቸው፡፡ ያላቸው መጠንና የክብ አጋማሻቸውም ከሰው ህዋስ ጋር ሲነጻጸር በተዋረድ 1/8000ኛ እና 1/100ኛ እንደሆነ ነው የታወቀው፡፡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ባክቴሪያዎች በድምር ሊኖራቸው የሚችለው መጠን ሲገመትም የስፒል ጭንቅላት ያህል እንደሚሆን ነው፡፡ ብዛታቸውም በቁጥር ለመግለጽ ከሚቻለው በላይም እንደሆነ ነው፡፡ ለማሳያ ያህል በምድራችን ያሉ የባክቴሪያዎች ቁጥር ብቻ አምስት ኖኒሊዮን (5x1030) እንደሚደርስና የፕላኔታችን አብዛኛው ግዝፈ ሕይወት (biomass) የባክቴሪያ እንደሆነ ሳይንቲስቶች ያስረዳሉ፡፡ በጥቅል ሲታይ ደቂቅ አካላት በድምር መጠናቸው ከምድር ፍጥረታት አጠቃላይ መጠን የ2/3ኛውን ድርሻ የሚወስዱና 50% የሚሆነውን ፕሮቶፕላዝም የያዙ እንደሆኑ ይገመታል፡፡
በቅርብ ዓመታት የተደረጉ ጥናቶች እንደሚያሳዩት ደቂቅ አካላት ከሰው ጋር ያላቸውን ቁርኝት ስንመለከት በሰው አካል ውስጥ ከሚገኘው ህዋስ 90%ቱን የሚሸፍኑት ባክቴሪያና ፈንገሶች እንደሆኑ አሳይተዋል፡፡ የሰው አንጀት ብቻ 40 ሺህ የባክቴሪያ ዝርያዎችን፣ 9 ሚሊዮን ልዩ የሆኑ የባክቴሪያ በራሂዎችን (genes) እና 100 ትሪሊዮን የደቂቅ አካላት ህዋሶችን (cells) እንደያዘም ተገምቷዋል፡፡ በአጠገባችን ያለ አንድ ግራም አፈር 40 ሚሊዮን እንዲሁም አንድ ሚሊ ሊትር ንጹህ ውኃ አንድ ሚሊዮን የባክቴሪያ ህዋሶችን እንደያዘ በጥናቱ ተመላክቷል፡፡ ይህ የሚያሳየው በዓይናችን ስለማናያቸው እንጂ ደቂቅ አካላት ከኛ ጋር እና በዙሪያችን በየትኛውም ስፍራና አካባቢ እንደሚገኙ ነው፡፡ ለምን? በአጭሩ ሊጠቅሙን!
ከፍጥረታት እጅግ ጉልበተኛውና ኃይለኛው ማነው የሚል ጥያቄ ቢነሳ የምድራችን ምላሽ ደቂቅ አካላ
********************
የሰው ልጅ በየዘመኑ በፈለሰፋቸው የቴክኖሎጂ አቅሞች በመታገዝ በዙሪያው የሚገኙትን በዓይን የሚታዩ ሕይወት ያላቸውንና የሌላቸውን አካላት አፈጣጠር፣ አኗኗርና ጠቀሜታ ሳይንሳዊ ትንታኔ በመስጠት ረገድ ዘመናትን ያስቆጠረ ሲሆን፣ ከተለመደውና ከሚታወቀው ባሻገር ያለውን በዓይን መታየት የማይችለውን የደቂቅ አካላት ዓለም (microbial world) የማወቅ አቅም የፈጠረው ዘግይቶ ነው፡፡
ስለ ደቂቅ አካላት መኖር መነገር የጀመረው ከ5ኛው ክፍለ ዘመን (BC) ጀምሮ ቢሆንም በ17ኛው ክፍለ ዘመን የታዋቂዎቹ ሳይንቲስቶች የሮበርት ሁክና የአንቶኒዮ ቫን ሊቨንሆክ በማስረጃ የተደገፈ አዲስ ግኝት በዓይን የማይታዩ አካለት መኖራቸውን ያበሰረ ነበር፡፡ በ1663 ዓ.ም በሮበረት ሁክ በባለ አንድ ሌንስ ትንሽ ማይክሮስኮፕ በመታገዝ ለመጀመሪያ ጊዜ ሙከር (Mucor) የተባለውን የፈንገስ ዘር በማግኘት የተጀመረው በዓይን የማይተየውን ዓለም የማወቅ ጅማሬ ከ1677-1678 ዓ.ም ባለው ጊዜ አንቶኒዮ ቫን ሊቨንሆክ ባሻሻለው ማይክሮስኮፕ “little animalcules” በመባል የተጠሩትን ባክቴሪያ ለማየት በመቻሉ የበለጠ ወደ መታወቅ የተሸጋገረበት ወቅት እንደነበር ታሪክ ያስረዳል::
አሁን ላይ በተደረሰበት ሳይንሳዊ ውጤት መሰረት በዚህ በዓይን በማይታየው የፍጥረት ዓለም ውስጥ የተመደቡት በወል ስማቸው ደቂቅ አካላት1 (microorganisms/microbes) ተብለው የሚታወቁት ፍጥረቶች በየዘርፋቸው ሲዘረዘሩ አርኪያ (Archae)፣ ባክቴሪያ (bacteria)፣ ፈንገስ (Fungus)፣ ማይክሮአልጌ (Microalgae)፣ ፕሮቶዞዋ (Protozoa) እና ቫይረስ (virus) የተባሉት ናቸው፡፡
ደቂቅ አካላት ሕይወት ካላቸው የምድር ፍጥረታት ከ3.5 ቢሊዮን ዓመታት በፊት ቀድመው የተፈጠሩ የፍጥረት ዓይነቶች ናቸው፡፡ እነዚህ በዓይን የማይታዩ የምድራችን ፍጥረታት ከነሱ በኋላ ለመጡት በሕይወት መቀጠል ከፍተኛ አስተዋጽኦ የነበራቸው እንደሆኑ ሳይንሳዊ የምርምር ውጤቶች ያስረዳሉ፡፡ ዛሬም ቢሆን ካለነዚህ ደቂቅ ፍጥረታት አስተዋጽዖ ሌሎች በሕይወት መቀጠል እንደማይችሉ ሳይንቲስቶች ያምናሉ፡፡ በምድር ላይ ለ3.5 ቢሊዮን ዓመታት ባደረጉት ዝግመተ ለውጥና መላመድ በምድራችን በየትኛውም አካባቢ ለመኖር ችለዋል፡፡፡ በዚህም የተነሳ ሌሎች ፍጥረታት ሊኖሩ በማይችሉባቸው አስቸጋሪ ቦታዎች ምግብ ሳይቸግራቸውና በሕይወት ለመኖር ስጋት ሳይገባቸው ኖረዋል፣ እየኖሩም ነው፡፡ ለእነርሱ በሚኖሩባቸው ቦታዎች ሁሉ ምግብ አለ፣ ሕይወት አለ፡፡
የደቂቅ አካላት ልከት (size) በጣም ትንሽ መሆን በዓይን እንዳይታዩ ያደረጋቸው ሲሆን፣ ዛሬም ቢሆን በዘመናዊ ቴክኖሎጂም እንኳን በመታገዝ መታየት የቻሉት በጣም ጥቂቶቹ ብቻ ናቸው፡፡ ያላቸው መጠንና የክብ አጋማሻቸውም ከሰው ህዋስ ጋር ሲነጻጸር በተዋረድ 1/8000ኛ እና 1/100ኛ እንደሆነ ነው የታወቀው፡፡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ባክቴሪያዎች በድምር ሊኖራቸው የሚችለው መጠን ሲገመትም የስፒል ጭንቅላት ያህል እንደሚሆን ነው፡፡ ብዛታቸውም በቁጥር ለመግለጽ ከሚቻለው በላይም እንደሆነ ነው፡፡ ለማሳያ ያህል በምድራችን ያሉ የባክቴሪያዎች ቁጥር ብቻ አምስት ኖኒሊዮን (5x1030) እንደሚደርስና የፕላኔታችን አብዛኛው ግዝፈ ሕይወት (biomass) የባክቴሪያ እንደሆነ ሳይንቲስቶች ያስረዳሉ፡፡ በጥቅል ሲታይ ደቂቅ አካላት በድምር መጠናቸው ከምድር ፍጥረታት አጠቃላይ መጠን የ2/3ኛውን ድርሻ የሚወስዱና 50% የሚሆነውን ፕሮቶፕላዝም የያዙ እንደሆኑ ይገመታል፡፡
በቅርብ ዓመታት የተደረጉ ጥናቶች እንደሚያሳዩት ደቂቅ አካላት ከሰው ጋር ያላቸውን ቁርኝት ስንመለከት በሰው አካል ውስጥ ከሚገኘው ህዋስ 90%ቱን የሚሸፍኑት ባክቴሪያና ፈንገሶች እንደሆኑ አሳይተዋል፡፡ የሰው አንጀት ብቻ 40 ሺህ የባክቴሪያ ዝርያዎችን፣ 9 ሚሊዮን ልዩ የሆኑ የባክቴሪያ በራሂዎችን (genes) እና 100 ትሪሊዮን የደቂቅ አካላት ህዋሶችን (cells) እንደያዘም ተገምቷዋል፡፡ በአጠገባችን ያለ አንድ ግራም አፈር 40 ሚሊዮን እንዲሁም አንድ ሚሊ ሊትር ንጹህ ውኃ አንድ ሚሊዮን የባክቴሪያ ህዋሶችን እንደያዘ በጥናቱ ተመላክቷል፡፡ ይህ የሚያሳየው በዓይናችን ስለማናያቸው እንጂ ደቂቅ አካላት ከኛ ጋር እና በዙሪያችን በየትኛውም ስፍራና አካባቢ እንደሚገኙ ነው፡፡ ለምን? በአጭሩ ሊጠቅሙን!
ከፍጥረታት እጅግ ጉልበተኛውና ኃይለኛው ማነው የሚል ጥያቄ ቢነሳ የምድራችን ምላሽ ደቂቅ አካላ
የሰመር ካምፕ ተወዳዳሪዎች እውቅና እና ሽልማት ተበረከተላቸው
****************************************************************
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ያዘጋጀው እና ከሃምሌ ወር ጀምሮ እስከ አሁን ሲካሄድ የቆየው የሰመር ካምፕ ፕሮግራም በዛሬው ዕለት በእውቅና እና የሽልማት ስነ ስርዓቶች ፍፃሜውን አግኝቷል፡፡ የሰመር ካምፕ ፕሮግራሙ በዋናነት የመንግስት ተቋማት የአሰራር ስርዓትን የሚያዘምኑ የሶፍትዌር ፕሮጀክቶች ማበልጸግ እና ማቅረብ በሚለው የትግበራ ዘርፍ ላይ አተኩሮ የተሰናደ ሲሆን፣ ከሶስት መቶ በላይ የሚሆኑ አመልካቾችም በመነሻነት መሳተፋቸውን በስነ ስርዓቱ ላይ ተጠቅሷል፡፡
በተዘጋጀው በዚህ የእውቅና እና ሽልማት ስነ ስርዓት ላይ የመክፈቻና የአንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳንዶካን ደበበ የሰመር ካምፑ መዘጋጀት የሚኖረውን ከፍተኛ ጥቅም አንስተው ወደ ፊት ይበልጥ ተጠናከሮ እንደሚቀጥል እና ድጋፎችም በሰፊው እንደሚደረጉ ገልፀዋል፡፡ ተቋሙ በአዲስ የመዋቅር መስረታ እና የሽግግር ሂደት ላይ ከመሆኑ አኳያ ተግዳሮቶችን ተቋቁሞ እንደዚህ ያለ ፕሮግራምን በስኬት ማጠናቀቁ ጥሩ መነሻ ተደርጎ ሊወሰድ እንደሚችልም ተናግረዋል፡፡
የሰመር ካምፕ ዝግጅቱን አጠቃላይ ሂደት እና የውድድር መስፈርት አስመልክቶ ገለፃ ያደረጉት የኮምፒውቲንግ እና አናሊሲስ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ገብሬ አላምነ በጥቅሉ ከሶስት መቶ በላይ ተማሪዎች ለውድድሩ ማመልከታቸውን ጠቅሰው በተዘጋጀው መስፈርትም 27 የሚሆኑት ተወዳዳሪዎች ወደ ስራ እንዲገቡ እና ፕሮጀክታቸውን እንዲያከናውኑ መደረጋቸውን ተናግረዋል፡፡ በተዘጋጀው የሰመር ካምፕ ፕሮግራም ላይ ምንም እንኳን ጊዜን ጨምሮ የፋይናንስ እና የቁሳቁስ ችግሮች እንደነበሩ ያነሱት አቶ ገብሬ የሚቻለውን ድጋፍ ለተማሪዎቹ በማድረግ የመንግስት ተቋማትን የሚያዘምኑ ችግር ፈቺ ሶፍትዌሮች እንዲሰሩ መደረጋቸው በስኬት ደረጃ የሚታይ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
በተዘጋጀው የመስፈርት ሁኔታ ሶስት ተወዳዳሪዎች አሸናፊ ሲሆኑ ፕሮጀክታቸውን በስኬት ያጠናቀቁ 14 ተማሪዎችም የእውቅና ሽልማት እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡ በዚህም አንደኛ በመሆን ያጠናቀቀው ፕሮጀክት በናትናኤል ዘነበ እና ሳምሶን ተከስተ የተሰራው Employe Attendance System የተሰኘው ፕሮጀክት ሲሆን በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ በአላዛር ደምሴ የተሰራው General Safty የተሰኘው ችግር ፈቺ ሶፍትዌር አሸናፊ ሆኗል፡፡ በሶስተኛ ደረጃ ያጠናቀቀው ቢታኒያ ናስር እና ናትናኤል ሙሉጌታ የሰሩት Storage Management System የተሰኛው ፕሮጀክት ሲሆን ለሶስቱም አሸናፊች የማበረታቻ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡ በስነ ስርዓቱ ማጠናቀቂያ ላይ የመዝጊያ ንግግር ያደረጉት የኢንቲትዩቱ ምክትል ዳይሬክተር አቶ ተሾመ ሳህለ ማሪያም በተማሪዎቹ የተሰራው ችግር ፈቺ ሶፍትዌር ብዙ የመንግስት ተቋማት ሊጠቀሙባቸው የሚችሉ ጠቃሚ ፕሮጀክቶች መሆናቸውን ጠቅሰው ለወደፊቱም የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ሶፍትዌሮቹ ወደ ተግባር የሚገቡበትን ሁኔታ ለመፍጠር እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡
****************************************************************
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ያዘጋጀው እና ከሃምሌ ወር ጀምሮ እስከ አሁን ሲካሄድ የቆየው የሰመር ካምፕ ፕሮግራም በዛሬው ዕለት በእውቅና እና የሽልማት ስነ ስርዓቶች ፍፃሜውን አግኝቷል፡፡ የሰመር ካምፕ ፕሮግራሙ በዋናነት የመንግስት ተቋማት የአሰራር ስርዓትን የሚያዘምኑ የሶፍትዌር ፕሮጀክቶች ማበልጸግ እና ማቅረብ በሚለው የትግበራ ዘርፍ ላይ አተኩሮ የተሰናደ ሲሆን፣ ከሶስት መቶ በላይ የሚሆኑ አመልካቾችም በመነሻነት መሳተፋቸውን በስነ ስርዓቱ ላይ ተጠቅሷል፡፡
በተዘጋጀው በዚህ የእውቅና እና ሽልማት ስነ ስርዓት ላይ የመክፈቻና የአንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳንዶካን ደበበ የሰመር ካምፑ መዘጋጀት የሚኖረውን ከፍተኛ ጥቅም አንስተው ወደ ፊት ይበልጥ ተጠናከሮ እንደሚቀጥል እና ድጋፎችም በሰፊው እንደሚደረጉ ገልፀዋል፡፡ ተቋሙ በአዲስ የመዋቅር መስረታ እና የሽግግር ሂደት ላይ ከመሆኑ አኳያ ተግዳሮቶችን ተቋቁሞ እንደዚህ ያለ ፕሮግራምን በስኬት ማጠናቀቁ ጥሩ መነሻ ተደርጎ ሊወሰድ እንደሚችልም ተናግረዋል፡፡
የሰመር ካምፕ ዝግጅቱን አጠቃላይ ሂደት እና የውድድር መስፈርት አስመልክቶ ገለፃ ያደረጉት የኮምፒውቲንግ እና አናሊሲስ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ገብሬ አላምነ በጥቅሉ ከሶስት መቶ በላይ ተማሪዎች ለውድድሩ ማመልከታቸውን ጠቅሰው በተዘጋጀው መስፈርትም 27 የሚሆኑት ተወዳዳሪዎች ወደ ስራ እንዲገቡ እና ፕሮጀክታቸውን እንዲያከናውኑ መደረጋቸውን ተናግረዋል፡፡ በተዘጋጀው የሰመር ካምፕ ፕሮግራም ላይ ምንም እንኳን ጊዜን ጨምሮ የፋይናንስ እና የቁሳቁስ ችግሮች እንደነበሩ ያነሱት አቶ ገብሬ የሚቻለውን ድጋፍ ለተማሪዎቹ በማድረግ የመንግስት ተቋማትን የሚያዘምኑ ችግር ፈቺ ሶፍትዌሮች እንዲሰሩ መደረጋቸው በስኬት ደረጃ የሚታይ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
በተዘጋጀው የመስፈርት ሁኔታ ሶስት ተወዳዳሪዎች አሸናፊ ሲሆኑ ፕሮጀክታቸውን በስኬት ያጠናቀቁ 14 ተማሪዎችም የእውቅና ሽልማት እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡ በዚህም አንደኛ በመሆን ያጠናቀቀው ፕሮጀክት በናትናኤል ዘነበ እና ሳምሶን ተከስተ የተሰራው Employe Attendance System የተሰኘው ፕሮጀክት ሲሆን በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ በአላዛር ደምሴ የተሰራው General Safty የተሰኘው ችግር ፈቺ ሶፍትዌር አሸናፊ ሆኗል፡፡ በሶስተኛ ደረጃ ያጠናቀቀው ቢታኒያ ናስር እና ናትናኤል ሙሉጌታ የሰሩት Storage Management System የተሰኛው ፕሮጀክት ሲሆን ለሶስቱም አሸናፊች የማበረታቻ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡ በስነ ስርዓቱ ማጠናቀቂያ ላይ የመዝጊያ ንግግር ያደረጉት የኢንቲትዩቱ ምክትል ዳይሬክተር አቶ ተሾመ ሳህለ ማሪያም በተማሪዎቹ የተሰራው ችግር ፈቺ ሶፍትዌር ብዙ የመንግስት ተቋማት ሊጠቀሙባቸው የሚችሉ ጠቃሚ ፕሮጀክቶች መሆናቸውን ጠቅሰው ለወደፊቱም የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ሶፍትዌሮቹ ወደ ተግባር የሚገቡበትን ሁኔታ ለመፍጠር እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡