የአፍሪካ ሶፍትዌር አበልፃጊዎች ጉባዬ እየተካሄደ ነው
*****************************************
AFRICAN DEVELOPERS CONFERENCE በማባል የሚታወቀውና በዋናነት በገበያ (Gebeya) የቴክኖሎጂ ኩባንያ እና በተባባሪነት ደግሞ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ኢን ቴክ (Ethiopians in Tech) ጋር የሚዘጋጀው የአፍሪካውያን ደቨሎፐርስ ኮንፈረንስ በዛሬው ዕለት በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) መካሄድ ጀምሯል፡፡
ለሁለት ቀን የሚዘልቀው ይህ ጉባዬ የዲጂታል ኢንዱስትሪን ዋና ትኩረቱ አድርጎ የተዘጋጀ ሲሆን ከተለያዩ የአፍሪካ ሃገራት የተወጣጡ ሶፍትዌር ኢንጂነሮች፣ ቴክኖሎጂስቶች፣ የSTEM ተማሪዎች እና ስራ ፈጠሪዎች የሚሳተፉበት ነው፡፡
በጉባዬው ላይ ተጽዕኖ ፈጠሪ የሚባሉ እና በዘርፉ ስኬት ያስመዘጉ ድርጅቶች በተወካዮቻቸው በኩል የፓናል ውይይት እና የልምድ ልውውት ያደረጉ ሲሆን በዋናነትም በሳይበር ደህንነት፣ ክላውድ ኮምፒዊቲንግ፣ ዳታ ሳይንስ እና የሞባይል ቴክኖሎጂ በመሳሰሉ የዲጂታል ዘርፎች ላይ ሰፊ ገለፃ እና ምክክር አድርገዋል፡፡
ጉባዬው በነገው ዕለትም በተለያዩ የፓናል ውይይቶች፣ የስልጠና መርሃግብሮች እና የአውደ ርዕይ ትዕይንቶች ሲቀጥል በዘርፉ ስኬታማ ተብለው የሚጠሩት እንደ Orbithealth፣ ዜናይሲስ፣ አይኮ ግላብስ እና ሌሎች መሰል የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ልምዳቸውን እና እይታቸውን ለተሳታፊዎች ያቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
*****************************************
AFRICAN DEVELOPERS CONFERENCE በማባል የሚታወቀውና በዋናነት በገበያ (Gebeya) የቴክኖሎጂ ኩባንያ እና በተባባሪነት ደግሞ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ኢን ቴክ (Ethiopians in Tech) ጋር የሚዘጋጀው የአፍሪካውያን ደቨሎፐርስ ኮንፈረንስ በዛሬው ዕለት በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) መካሄድ ጀምሯል፡፡
ለሁለት ቀን የሚዘልቀው ይህ ጉባዬ የዲጂታል ኢንዱስትሪን ዋና ትኩረቱ አድርጎ የተዘጋጀ ሲሆን ከተለያዩ የአፍሪካ ሃገራት የተወጣጡ ሶፍትዌር ኢንጂነሮች፣ ቴክኖሎጂስቶች፣ የSTEM ተማሪዎች እና ስራ ፈጠሪዎች የሚሳተፉበት ነው፡፡
በጉባዬው ላይ ተጽዕኖ ፈጠሪ የሚባሉ እና በዘርፉ ስኬት ያስመዘጉ ድርጅቶች በተወካዮቻቸው በኩል የፓናል ውይይት እና የልምድ ልውውት ያደረጉ ሲሆን በዋናነትም በሳይበር ደህንነት፣ ክላውድ ኮምፒዊቲንግ፣ ዳታ ሳይንስ እና የሞባይል ቴክኖሎጂ በመሳሰሉ የዲጂታል ዘርፎች ላይ ሰፊ ገለፃ እና ምክክር አድርገዋል፡፡
ጉባዬው በነገው ዕለትም በተለያዩ የፓናል ውይይቶች፣ የስልጠና መርሃግብሮች እና የአውደ ርዕይ ትዕይንቶች ሲቀጥል በዘርፉ ስኬታማ ተብለው የሚጠሩት እንደ Orbithealth፣ ዜናይሲስ፣ አይኮ ግላብስ እና ሌሎች መሰል የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ልምዳቸውን እና እይታቸውን ለተሳታፊዎች ያቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
የከንፈር ቁስለት
==========
የከንፈር ቁስለት የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴን የሚያውክ የጤና እክል ነው፡፡ ሲከሰትም እንደ ምግብ መመገብ እና ጥርስን መፋቅ የመሳሰሉ ተግባራትን ያከብድብናል፡፡ ብዙውን ጊዜ ከንፈር ቁስለት ንክሻን በመሳሰሉ ቀላል ምክንያቶች ሊከሰት ቢችልም እንደ ካንሰር እና ሌሎች ቀላል እና ከበድ ያሉ የጤና እክሎችንም ተከትሎ ሊመጣ ይችላል፡፡ እነዚህ የአፍ ቁስለቶች ተላላፊ እና የህክምና እርዳታን የሚሹም ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ የአፍ ቁስለትን ያመጣሉ ከሚባሉ ሌሎች ምክንያቶች ውስጥ የሚከተሉት ይገኙበታል፡፡
• ያልተመጠነ የጥርስ ተከላ
• ሹል ወይም የተሰበረ ጥርስ
• ብሬስ እና መሰል ቁሶች
• ትኩስ ምግብ እና መጠጥ
• ሲጋራ (ማጨስም ማቋረጥም)
• አንዳንድ ህክምናዎች
• ከፍተኛ የአሲድ መጠን ያላቸው ምግቦች
• ጭንቀት
• የቫይታሚን እና ሌሎች ንጥረ ነገሮች እጥረት
ህክምና
***
አብዛኛውን ጊዜ የከንፈር ቁስሎች በራሳቸው ይድናሉ፡፡ ለምሳሌ በቀላል ጉዳቶች አማካኝነት የሚመጡ ቁስለቶች ከሁለት ሳምንት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ድህነታቸውን ይጨርሳሉ፡፡ ከዚህ ጎን ለጎን ቁስሉን ለማጥፋት የሚከተሉት መንገዶች ይመከራሉ፤
• በጨው ውሃ ማጠብ
• ትኩስ እና የሚያቃጥሉ ምግቦችን አለመመገብ
• ሲጋራን ከማጨስ መቆጠብ
• ከአልኮል መራቅ
• እንደ ብርቱካን እና ሎሚ ያሉ ፍራፍሬዎችን አለመመገብ
ሆኖም በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ውስጥ የማይሻለን አሊያም የኢንፌክሽን ምልክት ካሳዩ፣ ከነጡ እና ህክምናን ተከትለው የተከሰቱ ከሆኑ ወደ ህክምና ተቋም በመሄድ መታከም ይኖርብናል፡፡
ምንጭ፡ Medical News Today
==========
የከንፈር ቁስለት የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴን የሚያውክ የጤና እክል ነው፡፡ ሲከሰትም እንደ ምግብ መመገብ እና ጥርስን መፋቅ የመሳሰሉ ተግባራትን ያከብድብናል፡፡ ብዙውን ጊዜ ከንፈር ቁስለት ንክሻን በመሳሰሉ ቀላል ምክንያቶች ሊከሰት ቢችልም እንደ ካንሰር እና ሌሎች ቀላል እና ከበድ ያሉ የጤና እክሎችንም ተከትሎ ሊመጣ ይችላል፡፡ እነዚህ የአፍ ቁስለቶች ተላላፊ እና የህክምና እርዳታን የሚሹም ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ የአፍ ቁስለትን ያመጣሉ ከሚባሉ ሌሎች ምክንያቶች ውስጥ የሚከተሉት ይገኙበታል፡፡
• ያልተመጠነ የጥርስ ተከላ
• ሹል ወይም የተሰበረ ጥርስ
• ብሬስ እና መሰል ቁሶች
• ትኩስ ምግብ እና መጠጥ
• ሲጋራ (ማጨስም ማቋረጥም)
• አንዳንድ ህክምናዎች
• ከፍተኛ የአሲድ መጠን ያላቸው ምግቦች
• ጭንቀት
• የቫይታሚን እና ሌሎች ንጥረ ነገሮች እጥረት
ህክምና
***
አብዛኛውን ጊዜ የከንፈር ቁስሎች በራሳቸው ይድናሉ፡፡ ለምሳሌ በቀላል ጉዳቶች አማካኝነት የሚመጡ ቁስለቶች ከሁለት ሳምንት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ድህነታቸውን ይጨርሳሉ፡፡ ከዚህ ጎን ለጎን ቁስሉን ለማጥፋት የሚከተሉት መንገዶች ይመከራሉ፤
• በጨው ውሃ ማጠብ
• ትኩስ እና የሚያቃጥሉ ምግቦችን አለመመገብ
• ሲጋራን ከማጨስ መቆጠብ
• ከአልኮል መራቅ
• እንደ ብርቱካን እና ሎሚ ያሉ ፍራፍሬዎችን አለመመገብ
ሆኖም በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ውስጥ የማይሻለን አሊያም የኢንፌክሽን ምልክት ካሳዩ፣ ከነጡ እና ህክምናን ተከትለው የተከሰቱ ከሆኑ ወደ ህክምና ተቋም በመሄድ መታከም ይኖርብናል፡፡
ምንጭ፡ Medical News Today
ኢትዮጵያና ሩሲያ የኒውክሌር ሃይልን ለሰላማዊ ጥቅም ለማዋል ስምምነት ተፈራረሙ
ኢትዮጵያ እና ሩሲያ የኒውክሌር ሃይልን ለሰላማዊ ጥቅም ለማዋል የሚያስችላቸውን የሁለትዮሽ ስምምነት በሩሲያ ሶቺ ተፈራረሙ።
የሁለትዮሽ ስምምነቱ በሩሲያ ሶቺ እየተካሄደ ካለው የአፍሪካ ሩሲያ የኢኮኖሚ ፎረም ጎን ለጎን ነው የተፈረመው፡፡
የስምምነቱን ፊርማ በኢትዮጵያ በኩል የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጅነር ጌታሁን መኩሪያ በዛሬው ዕለት ፈርመዋል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክ በፎረሙ ላይ እየተሳተፈ የሚገኝ ሲሆን፥ በቀጣይ ከሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሜር ፑቲን ጋር የሁለትዮሽ ውይይት ይካሄዳል።
ኢትዮጵያ በቅርቡ የኒውክሌር ቴክኖሎጂን ለሃይል ምንጭነት መጠቀም የሚያስችላትን ተጨማሪ ፕሮቶኮል ፊርማ መፈረሟ የሚታወስ ነው።
ኢትዮጵያ ኒውክሌርን ለማናቸውም ሰላማዊ ጥቅም በተለይም ለጤና፣ ለግብርና፣ ለኢንዱስትሪ እና የኤሌክትሪክ ሃይልን ለማመንጨት ጭምር እቅድ አላት።
Source.........FBC
ኢትዮጵያ እና ሩሲያ የኒውክሌር ሃይልን ለሰላማዊ ጥቅም ለማዋል የሚያስችላቸውን የሁለትዮሽ ስምምነት በሩሲያ ሶቺ ተፈራረሙ።
የሁለትዮሽ ስምምነቱ በሩሲያ ሶቺ እየተካሄደ ካለው የአፍሪካ ሩሲያ የኢኮኖሚ ፎረም ጎን ለጎን ነው የተፈረመው፡፡
የስምምነቱን ፊርማ በኢትዮጵያ በኩል የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጅነር ጌታሁን መኩሪያ በዛሬው ዕለት ፈርመዋል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክ በፎረሙ ላይ እየተሳተፈ የሚገኝ ሲሆን፥ በቀጣይ ከሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሜር ፑቲን ጋር የሁለትዮሽ ውይይት ይካሄዳል።
ኢትዮጵያ በቅርቡ የኒውክሌር ቴክኖሎጂን ለሃይል ምንጭነት መጠቀም የሚያስችላትን ተጨማሪ ፕሮቶኮል ፊርማ መፈረሟ የሚታወስ ነው።
ኢትዮጵያ ኒውክሌርን ለማናቸውም ሰላማዊ ጥቅም በተለይም ለጤና፣ ለግብርና፣ ለኢንዱስትሪ እና የኤሌክትሪክ ሃይልን ለማመንጨት ጭምር እቅድ አላት።
Source.........FBC
ሳይጠጡ መስከርን ምን ይሉታል?
=====================
የ46 ኣመቱ ጎልማሳ አሜሪካዊ ምንም ዓይነት አልኮል በምላሱ ሳይዞር ይሰክራል፤ የቁጡነት ባህርይንም ያሳያል፡፡ ጠጥቶ በማሽከርከርም ተይዞ ወህኒ ከመግባት ቢሆን አላመለጠም፡፡ ምክንያቱም ምርመራዎች በደሙ መኖር ካለበት ሁለት እጥፍ የአልኮል መጠን መኖሩን በመናገራቸው፡፡ አለመጠጣቱን በየፖሊስ ጣቢያው እና ሆስፒታሉ ደጋግሞ ቢናገርም ማንም ሊያምነው አልቻለም፡፡ ግን ይህ ቀልድ ሊመስል ቢችልም አውቶ ብሪወሪ ሲንድረም (ABS) በተባለ በሽታ ከመጠቃት የሚመጣ ነው፡፡
አውቶ ብሪወሪ ሲንድረም በአንጀት ውስጥ ያለው ባክቴሪያ ካርቦሀይድሬትን ወደ ስካር አምጪ አልኮልነት እንዲለውጥ የሚያደርግ የጤና እክል ነው፡፡ ይህ ሁኔታ ታማሚዎቹ ስኳር ወይም ካርቦሀይድሬት የበዛባቸውን ምግቦች በሚመገቡበት ወቅት አረቄ ወይም ቢራ እንደጠጣ ሰው ሁሉ ወደ ስካር መንፈስ ይወረውራቸዋል፡፡ ከላይ የጠቀስነው ሰውም ታድያ ምግቡን ከተመገበ በኋላ መንቀሳቀስ ያቅተው እንደነበር ጉዳዩን የተከታተሉት ዶ/ር ፋርሀድ ማሊክ ገልፀዋል፡፡ ታማሚው ይህ ሁኔታ ያጋጥም የጀመረው እጁ ላይ ለደረሰበት የተወሳሰበ ጉዳት ይሆንለት ዘንድ በፈረንጆቹ 2011 የፀረ ባክቴሪያ መድሀኒት መውሰድ ከመጀመሩ ጋር ተያይዞ ነው፡፡ ሆኖም ይህ መድሀኒት ከተወሰደበት ዓላማ ጎን ለጎን በአንጀቱ ውስጥ ያሉትን ባክቴሪያ፣ ፈንገስ ወይም ሌሎች ጥቃቅን ህዋሳትን ተግባር ረብሾ ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል፡፡
ይህ ሰው ህመሙ ባመጣበት ጦስ ታስሮ ሳለ አንድ ግለሰብ በተመሳሳይ ህመም ህክምናውን እንደተከታተለ የሰማችው የዚህ ሰው አክስት ህክምናውን እንዲከታተል ነገሩ ወደተሰማበት ጤና ተቋም ትወስደዋለች፡፡ እዚያ ባከናወነው የሰገራ ምርመራ ሀኪሞቹ የቢራ እርሾ የመሰለ ነገርን በማግኘታቸው በተገለፀው በሽታ ለመጠቃቱ ይጠቁማቸዋል፡፡ ከስምንት ሰዓታት በኋላ ግን በሰውየው ደም ውስጥ ያለው የአልኮል ምጣኔ ወደ 0.05 በመቶ ሊያድግ ቻለ፡፡ ይህን ተከትሎ የምግብ እና ፀረ-ፈንገስ ህክምናን ብሎም ሳይካትሪስት እና ኒሮሎጂስቶችን ጨምሮ በተለያዩ የህክምና ባለሙያዎች እርዳታ ቢሰጠውም ከመስከር ሊድን አልተቻለውም፡፡ በአንድ አጋጣሚም በደሙ ውስጥ ያለው የአልኮል መጠን እጅጉን አሻቅቦ ለሞት ሊያበቃ በሚችል 0.4 በመቶ ደርሶ ነበር፡፡ ሁኔታውን የተመለከቱት ሀኪሞች መጠጥ አለመጠጣቱን መናገሩን ከውሸት ቆጠሩበት፡፡
ከዚህ በኋላ ነበር በሪችሞንድ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ማዕከል ባለሙያዎች ዕርዳታን ለማግኘት ወደዚያው ያቀናው፡፡ የማዕከሉ ሀኪሞች ታማሚውን ለሁለት ወራት በቅርበት ሲመረምሩት ቆይተው በአንጀቱ ውስጥ ያሉትን ተህዋሲያን ማስወገድ ቻሉ፡፡ ሀኪሞቹ በማስከተል ታማሚውን የሚረዱ ባክቴሪያዎችን እንዲያሳድግለት መድሀኒት የተሰጠው ሲሆን በአሁኑ ሰዓትም ወደጤነኝነት ሊመለስና ያማረውን አማርጦ ለመብላት በቅቷል፡፡ መቼስ አጃይብ ነው!!!
ምንጭ፡ Live Science
=====================
የ46 ኣመቱ ጎልማሳ አሜሪካዊ ምንም ዓይነት አልኮል በምላሱ ሳይዞር ይሰክራል፤ የቁጡነት ባህርይንም ያሳያል፡፡ ጠጥቶ በማሽከርከርም ተይዞ ወህኒ ከመግባት ቢሆን አላመለጠም፡፡ ምክንያቱም ምርመራዎች በደሙ መኖር ካለበት ሁለት እጥፍ የአልኮል መጠን መኖሩን በመናገራቸው፡፡ አለመጠጣቱን በየፖሊስ ጣቢያው እና ሆስፒታሉ ደጋግሞ ቢናገርም ማንም ሊያምነው አልቻለም፡፡ ግን ይህ ቀልድ ሊመስል ቢችልም አውቶ ብሪወሪ ሲንድረም (ABS) በተባለ በሽታ ከመጠቃት የሚመጣ ነው፡፡
አውቶ ብሪወሪ ሲንድረም በአንጀት ውስጥ ያለው ባክቴሪያ ካርቦሀይድሬትን ወደ ስካር አምጪ አልኮልነት እንዲለውጥ የሚያደርግ የጤና እክል ነው፡፡ ይህ ሁኔታ ታማሚዎቹ ስኳር ወይም ካርቦሀይድሬት የበዛባቸውን ምግቦች በሚመገቡበት ወቅት አረቄ ወይም ቢራ እንደጠጣ ሰው ሁሉ ወደ ስካር መንፈስ ይወረውራቸዋል፡፡ ከላይ የጠቀስነው ሰውም ታድያ ምግቡን ከተመገበ በኋላ መንቀሳቀስ ያቅተው እንደነበር ጉዳዩን የተከታተሉት ዶ/ር ፋርሀድ ማሊክ ገልፀዋል፡፡ ታማሚው ይህ ሁኔታ ያጋጥም የጀመረው እጁ ላይ ለደረሰበት የተወሳሰበ ጉዳት ይሆንለት ዘንድ በፈረንጆቹ 2011 የፀረ ባክቴሪያ መድሀኒት መውሰድ ከመጀመሩ ጋር ተያይዞ ነው፡፡ ሆኖም ይህ መድሀኒት ከተወሰደበት ዓላማ ጎን ለጎን በአንጀቱ ውስጥ ያሉትን ባክቴሪያ፣ ፈንገስ ወይም ሌሎች ጥቃቅን ህዋሳትን ተግባር ረብሾ ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል፡፡
ይህ ሰው ህመሙ ባመጣበት ጦስ ታስሮ ሳለ አንድ ግለሰብ በተመሳሳይ ህመም ህክምናውን እንደተከታተለ የሰማችው የዚህ ሰው አክስት ህክምናውን እንዲከታተል ነገሩ ወደተሰማበት ጤና ተቋም ትወስደዋለች፡፡ እዚያ ባከናወነው የሰገራ ምርመራ ሀኪሞቹ የቢራ እርሾ የመሰለ ነገርን በማግኘታቸው በተገለፀው በሽታ ለመጠቃቱ ይጠቁማቸዋል፡፡ ከስምንት ሰዓታት በኋላ ግን በሰውየው ደም ውስጥ ያለው የአልኮል ምጣኔ ወደ 0.05 በመቶ ሊያድግ ቻለ፡፡ ይህን ተከትሎ የምግብ እና ፀረ-ፈንገስ ህክምናን ብሎም ሳይካትሪስት እና ኒሮሎጂስቶችን ጨምሮ በተለያዩ የህክምና ባለሙያዎች እርዳታ ቢሰጠውም ከመስከር ሊድን አልተቻለውም፡፡ በአንድ አጋጣሚም በደሙ ውስጥ ያለው የአልኮል መጠን እጅጉን አሻቅቦ ለሞት ሊያበቃ በሚችል 0.4 በመቶ ደርሶ ነበር፡፡ ሁኔታውን የተመለከቱት ሀኪሞች መጠጥ አለመጠጣቱን መናገሩን ከውሸት ቆጠሩበት፡፡
ከዚህ በኋላ ነበር በሪችሞንድ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ማዕከል ባለሙያዎች ዕርዳታን ለማግኘት ወደዚያው ያቀናው፡፡ የማዕከሉ ሀኪሞች ታማሚውን ለሁለት ወራት በቅርበት ሲመረምሩት ቆይተው በአንጀቱ ውስጥ ያሉትን ተህዋሲያን ማስወገድ ቻሉ፡፡ ሀኪሞቹ በማስከተል ታማሚውን የሚረዱ ባክቴሪያዎችን እንዲያሳድግለት መድሀኒት የተሰጠው ሲሆን በአሁኑ ሰዓትም ወደጤነኝነት ሊመለስና ያማረውን አማርጦ ለመብላት በቅቷል፡፡ መቼስ አጃይብ ነው!!!
ምንጭ፡ Live Science
በማቴሪያል ሳይንስ የትምህርት ዘርፍ ፈርቀዳጅ የሆነችው ኢትዮጵያዊት ተመራማሪ፡ ፕሮፌሰር ሶስና ሃይሌ
==================================
ፕሮፌሰር ሶስና ሃይሌ እ.ኢ.አ በ 1958 ከአዲስ አባባ የተገኘች ኢትዮጵያዊት ሳይንቲስት ናት፡፡ በ1967 በሃገሪቱ የመንግስት ለውጥ መምጣት ተከትሎ ከቤተሰቦቿ ጋር ወደ አሜሪካ ለመሰደድ የተገደደችው ፐሮፌሰር ሶስና አብዛኛውን የህይወት ጊዜዋንም በዚህ አንድታሳልፍ ሆናለች፡፡ ፐሮፌሰር ሶስና ከቤተሰቦቿ ጋር አብራ በመሆን የልጅነት ጊዜዋን በሚኒሶታ ሃገረ ግዛት ገጠራማ አካባቢ ካደረገች በኋላ በ1986 የመጀመሪያ ዲግሪዋን በማሳቹሴትስ የቴክኖሎጂ ኢኒስቲትዩት በማቴሪያል ሳይንስና በኢንጂነሪንግ ማግኘት የቻለች ሲሆን፤ ሁለተኛ ዲግሪዋን ደግሞ በካሊፎርኒያ ዩኒቨርስቲ በተመሳሳይ የትምህርት ዘርፍ ማሳካት ችላለች፡፡
ፐሮፌሰር ሶስና በቀጣዮቹ ጥቂት ዓመታት የፒችዲ ትምህርቷን ለመማር እንዲያስችላት የመጀመሪያ ዲግሪዋን ካገኘችበት የማሳቹሴትስ የቴክኒሎጂ ኢኒስቲትዩት ያቀናች ሲሆን፤ በዚህም እንዲሁ በምትወደው የማቴሪያል ሳይንስና ኢንጂነሪንግ ዘርፍ መመረቅ ችላለች፡፡ ፐሮፌሰር ሶስና ከዚህ የተሳካ የትምህርት ጉዞዋ በኋላ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ካገኘችበት የካልቴክ ፋካልቲ ከማምራቷ በፊት ሲያትል በሚገኘው የዋሽንግተን ዩኒቨርስቲ በረዳት ፕሮፌሰርነት የሰራች ሲሆን በዚህ የሶስት ዓመት ቆይታዋም ሀገሯን የሚያኮራና አፍሪካንም የሚያስጠራ ትልልቅ የምርምር ስራዎችን ለመስራት በቅታለች፡፡
ፐሮፌሰር ሶስና ድምራቸው ከ150 በላይ የሆነ የጥናትና ምርምር ፅሁፎችን በግል እና ከሌሎች ምሁራን ጋር በጋራ በመቀናጀት ሰርታ ለህትመት አብቅታለች፡፡ በስሟ የተመዘገቡላት ፓተንቶችም ቢሆን አስራ አምስትን ተሻግረዋል፡፡
ከነዚህ የህትመት እና ምርምር ውጤቶች ውስጥ ብዙሃኑ በጠጣር የአዮን ቁስ እና መሳሪያዎች ላይ ያጠነጠኑ ናቸው፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ከሚያጠነጥኑት የፕሮፌሰር ሶስና ስራዎች መካከል ደግሞ ከዓመታት በፊት የሰሩት አዲስ ዓይነት የፊውል ሴል ከሌሎች ፈጠራዎቿ ይጠቀሳል፡፡ በወቅቱ ሶስና ኬሚካሎችን ወደ ኤሌክትሪክ ሃይል በመቀየር ለመኪኖች፣ ሃይል ማመንጫዎች እንዲሁም ሌሎች ሃይልን ለሚጠይቁ ተግባራት ንፁህ የሃይል ምንጭ በመሆን እንዲያገለግለ፤ በማሰብ የፊውል ሴሎችን በከፍተኛ ደረጃ የሚያሻሽል ቁስን ለመስራት አልማ ተነሳች፡፡ ይህ ሃሳቧም በአይነቱ አዲስ የሆነ የኃይል ማመንጫን ዋጋ በከፍተኛ ደረጃ ሊቀንስ የሚችል የሱፐርፕሮቶኒክ ቅንብር መስራትን ያጠቃልላል፡፡ ሆኖም ይህ ሃሳቧን ተቀብለው የአሰራር ስርዓታቸውን ሙሉ በሙሉ ወደ አዲስ ከመቀየር የታቀቡት የፊውል ሴል አምራቾች የራሷን ቤተ-ሙከራ ተጠቅማ በዓለም የመጀመሪያውን ጠጣር የአሲድ ፊውል ሴል ቁስ አካል እንድትፈበርክ ምክንያት ሆኗት፡፡ ኋላ ላይ ይህን አዲስ ፈጠራዋን የቀድሞ ተማሪዎቿ በንግድ ሰርቶ ማሳያነት የተጠቀመበት ሲሆን ለተመራሪዋም በአረንጓዴ የሃይል ልማት ዘርፍ ዕውቅናን እንድትሸምትበት አስችሏታል፡፡
ፕሮፌሰር ሶስና በአሁኑ ሰዓት ጠጣር ፊውል ሴሎችን በተለይም ለከባቢ ተስማሚ የሃይል ምንጭ መሆን በሚችሉት ላይ አተኩሮ የሚሰራን የምርምር ቡድን በሃላፊነት በመምራት ላይ ትገኛለች፡፡ በዚህ ረገድ ይህ ቡድን የተለያዩ ስኬቶችን በማስመዝገብ ላይ ሲገኝ ከቅርብ ስኬቶቹ መካከልም ውሃና ካርቦን ዳይ ኦክሳይድን በቴርሞ ኬሚካል ሂደት አማካኝነት በመጠቀም የፀሐይን ኃይል ጥቅም ላይ በማዋል ረገድ ሌላ ምዕራፍን የከፈተ ነበር፡፡ በፕሮፌሰር ሃና እና ቡድኗ እየተሰራባቸው ካሉት ስራዎች ውስጥ ፕሩቶንን አስተላላፊ ጠጣር አሲድ እና ፐሮቭስካይት ኤሌክትሮይቶች፣ የኤሌክትሮን እና ኦክስጅን ድብልቅን አስተላላፊ ፍሎሪት እና ፐሮቭስካይት እንዲሁም ኢ-ስቶይኪዮሜትሪክ ኦክሳይዶችን ማበልፀግ ይገኝበታል፡፡
ይህች ኢትዮጵያዊት እንቁ ተመራማሪ በትልቁ ስሟን ከሚያስጠሩ ስራዎቿ አንዱ ከሆነው የፊውል ሴል ፈጠራዋ በተጨማሪ በሴራሚክ ሳይንስ፣ በኤሌክትሮኬሚካል እና በፋንክሽናል ሶሊድ (electrochemical and functional solids) የደረገቻቸው ምርምሮች እና ያሳተመቻቸው ፅሁፎች በተሰማራችበት የሳይንስ ዘርፍ ከሚኖረው አበርክቶት ባለፈ ለብዙ ወጣት ኢትዮጵያውያን እና ሴት ተመራማሪዎች የሚኖረው ጠንካራ መልእክት ቀላል የሚባል አይደለም፡፡
ከዚህ ጋር ተያይዞ ፐሮፌሰር ሶስና ለሰራቸው ስራና ላበረከተችው የምርምር ውጤት እውቅና የሚሆን ሽልማቶችን ከተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች ያገኘች ሲሆን ከእንዚህ ውስጥም በ1989 በማቴሪያል ሳይንስ ባደረገችው ሰፊ ምርምር ያገኘችው የሃርዲ አዋርድ፣ በ2002 በፊውል ሴል ፈጠራዋ ያገኘችው የኬሚካል ፖይነር አዋርድ እንዲሁም በ2004 በሴራሚክ ሳይንስ ምርምሯ ያገኘቸው የዓለም አቀፍ የሴራሚክ ፕራይዝ በጥቂቱ የሚጠቀሱ የእውቅና ሽልማቶቿ ናቸው፡፡
ምንጭ፡ ቴክ-ሳይንስ ቅፅ 15 (ሙሉ መፅሐፉን በዚህ ሊንክ ያገኙታል=http://library.techin.gov.et/web/dl-site/stic-resources/-/document_library/Y9QR0tiVPdYe/view_file/4710001?_com_liferay_document_library_web_portlet_DLPortlet_INSTANCE_Y9QR0tiVPdYe_redirect=http%3A%2F%2Flibrary.techin.gov.et%2Fweb%2Fdl-site%2Fstic-resources%3Fp_p_id%3Dcom_liferay_document_library_web_portlet_DLPortlet_INSTANCE_Y9QR0tiVPdYe%26p_p_lifecycle%3D0%26p_p_state%3Dnormal%26p_p_mode%3Dview%26p_r_p_categoryId%3D672548)
==================================
ፕሮፌሰር ሶስና ሃይሌ እ.ኢ.አ በ 1958 ከአዲስ አባባ የተገኘች ኢትዮጵያዊት ሳይንቲስት ናት፡፡ በ1967 በሃገሪቱ የመንግስት ለውጥ መምጣት ተከትሎ ከቤተሰቦቿ ጋር ወደ አሜሪካ ለመሰደድ የተገደደችው ፐሮፌሰር ሶስና አብዛኛውን የህይወት ጊዜዋንም በዚህ አንድታሳልፍ ሆናለች፡፡ ፐሮፌሰር ሶስና ከቤተሰቦቿ ጋር አብራ በመሆን የልጅነት ጊዜዋን በሚኒሶታ ሃገረ ግዛት ገጠራማ አካባቢ ካደረገች በኋላ በ1986 የመጀመሪያ ዲግሪዋን በማሳቹሴትስ የቴክኖሎጂ ኢኒስቲትዩት በማቴሪያል ሳይንስና በኢንጂነሪንግ ማግኘት የቻለች ሲሆን፤ ሁለተኛ ዲግሪዋን ደግሞ በካሊፎርኒያ ዩኒቨርስቲ በተመሳሳይ የትምህርት ዘርፍ ማሳካት ችላለች፡፡
ፐሮፌሰር ሶስና በቀጣዮቹ ጥቂት ዓመታት የፒችዲ ትምህርቷን ለመማር እንዲያስችላት የመጀመሪያ ዲግሪዋን ካገኘችበት የማሳቹሴትስ የቴክኒሎጂ ኢኒስቲትዩት ያቀናች ሲሆን፤ በዚህም እንዲሁ በምትወደው የማቴሪያል ሳይንስና ኢንጂነሪንግ ዘርፍ መመረቅ ችላለች፡፡ ፐሮፌሰር ሶስና ከዚህ የተሳካ የትምህርት ጉዞዋ በኋላ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ካገኘችበት የካልቴክ ፋካልቲ ከማምራቷ በፊት ሲያትል በሚገኘው የዋሽንግተን ዩኒቨርስቲ በረዳት ፕሮፌሰርነት የሰራች ሲሆን በዚህ የሶስት ዓመት ቆይታዋም ሀገሯን የሚያኮራና አፍሪካንም የሚያስጠራ ትልልቅ የምርምር ስራዎችን ለመስራት በቅታለች፡፡
ፐሮፌሰር ሶስና ድምራቸው ከ150 በላይ የሆነ የጥናትና ምርምር ፅሁፎችን በግል እና ከሌሎች ምሁራን ጋር በጋራ በመቀናጀት ሰርታ ለህትመት አብቅታለች፡፡ በስሟ የተመዘገቡላት ፓተንቶችም ቢሆን አስራ አምስትን ተሻግረዋል፡፡
ከነዚህ የህትመት እና ምርምር ውጤቶች ውስጥ ብዙሃኑ በጠጣር የአዮን ቁስ እና መሳሪያዎች ላይ ያጠነጠኑ ናቸው፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ከሚያጠነጥኑት የፕሮፌሰር ሶስና ስራዎች መካከል ደግሞ ከዓመታት በፊት የሰሩት አዲስ ዓይነት የፊውል ሴል ከሌሎች ፈጠራዎቿ ይጠቀሳል፡፡ በወቅቱ ሶስና ኬሚካሎችን ወደ ኤሌክትሪክ ሃይል በመቀየር ለመኪኖች፣ ሃይል ማመንጫዎች እንዲሁም ሌሎች ሃይልን ለሚጠይቁ ተግባራት ንፁህ የሃይል ምንጭ በመሆን እንዲያገለግለ፤ በማሰብ የፊውል ሴሎችን በከፍተኛ ደረጃ የሚያሻሽል ቁስን ለመስራት አልማ ተነሳች፡፡ ይህ ሃሳቧም በአይነቱ አዲስ የሆነ የኃይል ማመንጫን ዋጋ በከፍተኛ ደረጃ ሊቀንስ የሚችል የሱፐርፕሮቶኒክ ቅንብር መስራትን ያጠቃልላል፡፡ ሆኖም ይህ ሃሳቧን ተቀብለው የአሰራር ስርዓታቸውን ሙሉ በሙሉ ወደ አዲስ ከመቀየር የታቀቡት የፊውል ሴል አምራቾች የራሷን ቤተ-ሙከራ ተጠቅማ በዓለም የመጀመሪያውን ጠጣር የአሲድ ፊውል ሴል ቁስ አካል እንድትፈበርክ ምክንያት ሆኗት፡፡ ኋላ ላይ ይህን አዲስ ፈጠራዋን የቀድሞ ተማሪዎቿ በንግድ ሰርቶ ማሳያነት የተጠቀመበት ሲሆን ለተመራሪዋም በአረንጓዴ የሃይል ልማት ዘርፍ ዕውቅናን እንድትሸምትበት አስችሏታል፡፡
ፕሮፌሰር ሶስና በአሁኑ ሰዓት ጠጣር ፊውል ሴሎችን በተለይም ለከባቢ ተስማሚ የሃይል ምንጭ መሆን በሚችሉት ላይ አተኩሮ የሚሰራን የምርምር ቡድን በሃላፊነት በመምራት ላይ ትገኛለች፡፡ በዚህ ረገድ ይህ ቡድን የተለያዩ ስኬቶችን በማስመዝገብ ላይ ሲገኝ ከቅርብ ስኬቶቹ መካከልም ውሃና ካርቦን ዳይ ኦክሳይድን በቴርሞ ኬሚካል ሂደት አማካኝነት በመጠቀም የፀሐይን ኃይል ጥቅም ላይ በማዋል ረገድ ሌላ ምዕራፍን የከፈተ ነበር፡፡ በፕሮፌሰር ሃና እና ቡድኗ እየተሰራባቸው ካሉት ስራዎች ውስጥ ፕሩቶንን አስተላላፊ ጠጣር አሲድ እና ፐሮቭስካይት ኤሌክትሮይቶች፣ የኤሌክትሮን እና ኦክስጅን ድብልቅን አስተላላፊ ፍሎሪት እና ፐሮቭስካይት እንዲሁም ኢ-ስቶይኪዮሜትሪክ ኦክሳይዶችን ማበልፀግ ይገኝበታል፡፡
ይህች ኢትዮጵያዊት እንቁ ተመራማሪ በትልቁ ስሟን ከሚያስጠሩ ስራዎቿ አንዱ ከሆነው የፊውል ሴል ፈጠራዋ በተጨማሪ በሴራሚክ ሳይንስ፣ በኤሌክትሮኬሚካል እና በፋንክሽናል ሶሊድ (electrochemical and functional solids) የደረገቻቸው ምርምሮች እና ያሳተመቻቸው ፅሁፎች በተሰማራችበት የሳይንስ ዘርፍ ከሚኖረው አበርክቶት ባለፈ ለብዙ ወጣት ኢትዮጵያውያን እና ሴት ተመራማሪዎች የሚኖረው ጠንካራ መልእክት ቀላል የሚባል አይደለም፡፡
ከዚህ ጋር ተያይዞ ፐሮፌሰር ሶስና ለሰራቸው ስራና ላበረከተችው የምርምር ውጤት እውቅና የሚሆን ሽልማቶችን ከተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች ያገኘች ሲሆን ከእንዚህ ውስጥም በ1989 በማቴሪያል ሳይንስ ባደረገችው ሰፊ ምርምር ያገኘችው የሃርዲ አዋርድ፣ በ2002 በፊውል ሴል ፈጠራዋ ያገኘችው የኬሚካል ፖይነር አዋርድ እንዲሁም በ2004 በሴራሚክ ሳይንስ ምርምሯ ያገኘቸው የዓለም አቀፍ የሴራሚክ ፕራይዝ በጥቂቱ የሚጠቀሱ የእውቅና ሽልማቶቿ ናቸው፡፡
ምንጭ፡ ቴክ-ሳይንስ ቅፅ 15 (ሙሉ መፅሐፉን በዚህ ሊንክ ያገኙታል=http://library.techin.gov.et/web/dl-site/stic-resources/-/document_library/Y9QR0tiVPdYe/view_file/4710001?_com_liferay_document_library_web_portlet_DLPortlet_INSTANCE_Y9QR0tiVPdYe_redirect=http%3A%2F%2Flibrary.techin.gov.et%2Fweb%2Fdl-site%2Fstic-resources%3Fp_p_id%3Dcom_liferay_document_library_web_portlet_DLPortlet_INSTANCE_Y9QR0tiVPdYe%26p_p_lifecycle%3D0%26p_p_state%3Dnormal%26p_p_mode%3Dview%26p_r_p_categoryId%3D672548)
የወንዶች የወሊድ መቆጣጠሪያ
******************************************************************
የአሜሪካን የኬሚካል ሶሳቲ የሴቶችን ሸክም ለመቀነስ ሌት ተቀን እሰራን ነው ሲል ተደምጧል፡፡ ሴቶች ለዘመናት ወሊድ የመቆጣጠር ጣጣን ለብቻቸው ሲወጡት የነበረ ሲሆን ይህ ጤናቸው ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ ከመሆኑም ባሻገር አሁን አሁን የጡት ካንሰር እና የደም መርጋት ችግሮች በስፋት እየታየ በመሆኑ ለረዥም ጊዜ የሚወሰድ እርግዝና መከላከያ እንክብል ለጤና የሚመከር እድዳይሆን እያረው ነው፡፡
ምንም እንኳን ወንዶች ወሊድ ለመቆጣጠር እንዲችሉ ባንድ በኩል ኮንዶምን በሌላ በኩል ደግሞ vasectomyን(የዘር መተላለፊያ ቱቦን መዝጋት) ለዘመናት እንደ አማራጭ እየተወሰደ የነበረ ነገር ቢሆኑም ሁለቱም አስተማማኝ የወሊድ መቆጣጠሪያ አይደሉም ሲሉ የአሜሪካን የኬሚካ ሶሳይቲ ተመራማሪዎች ገልጸዋል፡፡
ኮንዶም በበኩሉ ሊቀደድ እና እክል ሊገጥመው የሚችል በመሆኑ እና በሌሎች አንዳንድ ምክኒያች ተመራጭ ማይሆንበት በርካታ ምክኒያት አለ ያሉ ሲሆን በሌላ በኩል የዘር ቱቦን ማቋረጥ ደግሞ ዘላለማዊ የሆነ እና መመለሻ የሌለው በመሆኑ ከባድ ውሳኔን የሚጠይቅ ተግባር ነው ብለዋል፡፡
በመሆኑም ልክ ሴቶች እንደሚጠቀሙት ዓይነት ባለብዙ አማራጭ የወሊድ መቆጣጠሪያዎች ያሉ በርካታ የወንዶች የወሊድ መቆጣጠሪያ ዘዴዎች ሊበጁ ይገባል የሚሉ ድምጾች እየተስተጋቡ ነው፡፡ እንደ የአሜሪካን የኬሚካል ሶሳይቲ ያሉ የምርምር ተቋማትም ሌት ተቀን ይህንን እውን ለመድረግ እየተጉ ይገኛሉ፡፡ በተደጋጋሚም በተለያየ መልኩ ለወንዶች የሚሆን የወሊድ መቆጣጠሪያ ዘዴዎች እየሞከሩ ያሉ ሲሆን በቅርቡም የኬሚካል ድርብርቦሽን በመስራት እና በማህጸን ውስጥ ግርዶሽ በመፍጠር እርግዝና እንዳይፈጠር ሊረዳ የሚችል አዲስ ግኝትን ለማጠናቀቅ ጥቂት ጊዜ ብቻ ቀርቶኛል ያለው የአሜሪካን የኬሚካ ሶሳይቲ ተመራማሪ ቡድን አየሩን ተቆጣጥሮታል፡፡
ይሁንና በሌላ በኩል የወሊድ መቆጣጠሪያ በራሱ ችግር ያለበት እና ተጠያቂነት የጎደለው አብዮት ነው የሚሉ ሳይንቲስቶች እየተደመጡ ነው፡፡ የወሊድ መቆጣጠሪያ የማይታወቅ አብዮትን በሴቶች ሰውነት ውስጥ የፈጠረ ሲሆን በተለያየ መንገድ ጤናቸውን አደጋ ውስጥ እየከከተ ያለ ጉዳይ ነው ብለዋል፡፡
የወሊድ መቆጣጠሪያ የሴቶችን ጤና እየጎዳ ባለበት ሁኔታ መልሶ ወንዶችንም የገፈቱ ተቃማሽ ማድረግ መፍትሄ አይሆንም ያሉ ሲሆን ያልተገባ ጾታዊ ግንኙነቶችን መቀነስ እና ትዳርን ማበረታታት የተሻለ አማራጭ ነው የሚል ምክር ሰጥተዋል አክለውም በአሜሪካን በትዳር ውስጥ ካሉ ይልቅ በትዳር ውስጥ ያልሆኑ ሴቶች 90 በመቶ የወሊድ መቆጣጠሪያ የሚወስዱ በመሆኑ ሰዎች እንዲህ ያለ ያልተገባ የጾታዊ ግንኙነቶችን መግታት ቢችሉ ከወሊድ መቆጣጠሪያ ጋር ያለ የጎንዮሽ ጉዳትን ማስቀረት ይቻላል ብለዋል፡፡
ምንጭ፡- Science daily and Guttmacher Institute
******************************************************************
የአሜሪካን የኬሚካል ሶሳቲ የሴቶችን ሸክም ለመቀነስ ሌት ተቀን እሰራን ነው ሲል ተደምጧል፡፡ ሴቶች ለዘመናት ወሊድ የመቆጣጠር ጣጣን ለብቻቸው ሲወጡት የነበረ ሲሆን ይህ ጤናቸው ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ ከመሆኑም ባሻገር አሁን አሁን የጡት ካንሰር እና የደም መርጋት ችግሮች በስፋት እየታየ በመሆኑ ለረዥም ጊዜ የሚወሰድ እርግዝና መከላከያ እንክብል ለጤና የሚመከር እድዳይሆን እያረው ነው፡፡
ምንም እንኳን ወንዶች ወሊድ ለመቆጣጠር እንዲችሉ ባንድ በኩል ኮንዶምን በሌላ በኩል ደግሞ vasectomyን(የዘር መተላለፊያ ቱቦን መዝጋት) ለዘመናት እንደ አማራጭ እየተወሰደ የነበረ ነገር ቢሆኑም ሁለቱም አስተማማኝ የወሊድ መቆጣጠሪያ አይደሉም ሲሉ የአሜሪካን የኬሚካ ሶሳይቲ ተመራማሪዎች ገልጸዋል፡፡
ኮንዶም በበኩሉ ሊቀደድ እና እክል ሊገጥመው የሚችል በመሆኑ እና በሌሎች አንዳንድ ምክኒያች ተመራጭ ማይሆንበት በርካታ ምክኒያት አለ ያሉ ሲሆን በሌላ በኩል የዘር ቱቦን ማቋረጥ ደግሞ ዘላለማዊ የሆነ እና መመለሻ የሌለው በመሆኑ ከባድ ውሳኔን የሚጠይቅ ተግባር ነው ብለዋል፡፡
በመሆኑም ልክ ሴቶች እንደሚጠቀሙት ዓይነት ባለብዙ አማራጭ የወሊድ መቆጣጠሪያዎች ያሉ በርካታ የወንዶች የወሊድ መቆጣጠሪያ ዘዴዎች ሊበጁ ይገባል የሚሉ ድምጾች እየተስተጋቡ ነው፡፡ እንደ የአሜሪካን የኬሚካል ሶሳይቲ ያሉ የምርምር ተቋማትም ሌት ተቀን ይህንን እውን ለመድረግ እየተጉ ይገኛሉ፡፡ በተደጋጋሚም በተለያየ መልኩ ለወንዶች የሚሆን የወሊድ መቆጣጠሪያ ዘዴዎች እየሞከሩ ያሉ ሲሆን በቅርቡም የኬሚካል ድርብርቦሽን በመስራት እና በማህጸን ውስጥ ግርዶሽ በመፍጠር እርግዝና እንዳይፈጠር ሊረዳ የሚችል አዲስ ግኝትን ለማጠናቀቅ ጥቂት ጊዜ ብቻ ቀርቶኛል ያለው የአሜሪካን የኬሚካ ሶሳይቲ ተመራማሪ ቡድን አየሩን ተቆጣጥሮታል፡፡
ይሁንና በሌላ በኩል የወሊድ መቆጣጠሪያ በራሱ ችግር ያለበት እና ተጠያቂነት የጎደለው አብዮት ነው የሚሉ ሳይንቲስቶች እየተደመጡ ነው፡፡ የወሊድ መቆጣጠሪያ የማይታወቅ አብዮትን በሴቶች ሰውነት ውስጥ የፈጠረ ሲሆን በተለያየ መንገድ ጤናቸውን አደጋ ውስጥ እየከከተ ያለ ጉዳይ ነው ብለዋል፡፡
የወሊድ መቆጣጠሪያ የሴቶችን ጤና እየጎዳ ባለበት ሁኔታ መልሶ ወንዶችንም የገፈቱ ተቃማሽ ማድረግ መፍትሄ አይሆንም ያሉ ሲሆን ያልተገባ ጾታዊ ግንኙነቶችን መቀነስ እና ትዳርን ማበረታታት የተሻለ አማራጭ ነው የሚል ምክር ሰጥተዋል አክለውም በአሜሪካን በትዳር ውስጥ ካሉ ይልቅ በትዳር ውስጥ ያልሆኑ ሴቶች 90 በመቶ የወሊድ መቆጣጠሪያ የሚወስዱ በመሆኑ ሰዎች እንዲህ ያለ ያልተገባ የጾታዊ ግንኙነቶችን መግታት ቢችሉ ከወሊድ መቆጣጠሪያ ጋር ያለ የጎንዮሽ ጉዳትን ማስቀረት ይቻላል ብለዋል፡፡
ምንጭ፡- Science daily and Guttmacher Institute
ሳይሞቱ መሞት
*****************************************************************
ድካም ሲደጋገምቦት እና ማረፍ ሲያሰኞ ምናለ ለአንድ ሳምንት ያህል ለጥ ባልኩ አልያም ደግሞ ምናለ ምግቡም መጠጡም ቀርቶብኝ ለተከታታይ ቀናት በተኛሁ ብለው ያውቃሉ? እንግዲያውስ ከወደ ኮሎቢያ አከባቢ ስለተከሰተው ነገር ሹክ እንበሎት የ17 ዓመቷ ታዳጊ ከቀናት እና ከሳምንታትም አልፋ ለወራት ሳትነቃ ለጥ እንዳለች ናት፡፡
ሻሪክ ቶቫር ትባላለች ከሚሊዮኖች ቢያንስ 5 ሰዎች ብቻ ሊጠቁበት ይችላሉ ተብሎ በሚታወቀው Kleine-Levin syndrome ወይንም የተኛችው ቆንጆ ሲንድረም ተጠቅታለች፡፡ ምናልባትም እንደ National Organization for Rare Disorders ገለጻ ከሆነ በዚህ በሽታ የተጠቁ ሰዎች ከተኛችው ቆንጆ ታሪክ የሚለዩት በሆነ ጊዜ መሀል ላይ እየተነሱ ሽንት ቤት ሊጠቀሙ አልያም ሊመገቡ ይችላሉ፡፡
በታሪክ በዚህ በሽታ ተጠቅተው የሚያውቁ 500 ሰዎች ብቻ እንደሆኑ የህክምና መዛግብቶች የሚያስረዱ ሲሆን ሃኪም ቤት ያልደረሱ እና ያልታወቁ ሊኖሩ እንደሚችል ይጠረጠራል፡፡
ይህ ሲንድረም ከሴቶች ይልቅ ወንዶች ላይ የሚበዛ ቢሆንም በተለያየ እድሜ ክልል ላይ የሚገኙ ሴቶች ላይም አልፎ አልፎ ታይቷል፡፡ የታቮር እናት እንዳስረዱት ከሆነ ለመጀመሪያ ጊዜ ታቮር ይህ ነገር ያጋጠማት የ2ዓመት ህጻን ልጅ እያለች ሲሆን ለተከታታይ 2 ወራት ተኝታለች፡፡ በተኛችበት ወቅትም እንዳትጎዳ በማለት በየሁለት ሰዓት እየጠበቁ ይመግቧት እንደነበር ተናግረዋል፡፡
ተጠቂዎቹ ከተኙበት ሲነቁ አደገኛ ውዝግብ ውስጥ የሚገቡ ሲሆን መብራት እና ድምፅ እንደሚረብሻቸው ይናገራሉ፡፡ በተጨማሪም ሙሉ ለሙሉ አቅም ማጣት እና ስሜት አልባ መሆን ይስተዋልባቸዋል፡፡ በሚነቁበት ሰዓት ትውስታቸውን ሙሉ ለሙሉ የሚያጡ ሲሆን ታቮር የእናቷን ፊት እንኳን መለየት አልቻለችም ነበር፡፡
ሀኪሞች እንደሚሉት ከሆነ ይህ ሃይፖታለመስ የተሰኘው የአዕምሮ ክፍል መጎዳት ውጤት ነው ያሉ ሲሆን ይህ የአዕምሮ ክፍል እንቅልፋችንን የሚቆጣጠረው ክፍል ነው፡፡
ምንጭ፡Live Science
*****************************************************************
ድካም ሲደጋገምቦት እና ማረፍ ሲያሰኞ ምናለ ለአንድ ሳምንት ያህል ለጥ ባልኩ አልያም ደግሞ ምናለ ምግቡም መጠጡም ቀርቶብኝ ለተከታታይ ቀናት በተኛሁ ብለው ያውቃሉ? እንግዲያውስ ከወደ ኮሎቢያ አከባቢ ስለተከሰተው ነገር ሹክ እንበሎት የ17 ዓመቷ ታዳጊ ከቀናት እና ከሳምንታትም አልፋ ለወራት ሳትነቃ ለጥ እንዳለች ናት፡፡
ሻሪክ ቶቫር ትባላለች ከሚሊዮኖች ቢያንስ 5 ሰዎች ብቻ ሊጠቁበት ይችላሉ ተብሎ በሚታወቀው Kleine-Levin syndrome ወይንም የተኛችው ቆንጆ ሲንድረም ተጠቅታለች፡፡ ምናልባትም እንደ National Organization for Rare Disorders ገለጻ ከሆነ በዚህ በሽታ የተጠቁ ሰዎች ከተኛችው ቆንጆ ታሪክ የሚለዩት በሆነ ጊዜ መሀል ላይ እየተነሱ ሽንት ቤት ሊጠቀሙ አልያም ሊመገቡ ይችላሉ፡፡
በታሪክ በዚህ በሽታ ተጠቅተው የሚያውቁ 500 ሰዎች ብቻ እንደሆኑ የህክምና መዛግብቶች የሚያስረዱ ሲሆን ሃኪም ቤት ያልደረሱ እና ያልታወቁ ሊኖሩ እንደሚችል ይጠረጠራል፡፡
ይህ ሲንድረም ከሴቶች ይልቅ ወንዶች ላይ የሚበዛ ቢሆንም በተለያየ እድሜ ክልል ላይ የሚገኙ ሴቶች ላይም አልፎ አልፎ ታይቷል፡፡ የታቮር እናት እንዳስረዱት ከሆነ ለመጀመሪያ ጊዜ ታቮር ይህ ነገር ያጋጠማት የ2ዓመት ህጻን ልጅ እያለች ሲሆን ለተከታታይ 2 ወራት ተኝታለች፡፡ በተኛችበት ወቅትም እንዳትጎዳ በማለት በየሁለት ሰዓት እየጠበቁ ይመግቧት እንደነበር ተናግረዋል፡፡
ተጠቂዎቹ ከተኙበት ሲነቁ አደገኛ ውዝግብ ውስጥ የሚገቡ ሲሆን መብራት እና ድምፅ እንደሚረብሻቸው ይናገራሉ፡፡ በተጨማሪም ሙሉ ለሙሉ አቅም ማጣት እና ስሜት አልባ መሆን ይስተዋልባቸዋል፡፡ በሚነቁበት ሰዓት ትውስታቸውን ሙሉ ለሙሉ የሚያጡ ሲሆን ታቮር የእናቷን ፊት እንኳን መለየት አልቻለችም ነበር፡፡
ሀኪሞች እንደሚሉት ከሆነ ይህ ሃይፖታለመስ የተሰኘው የአዕምሮ ክፍል መጎዳት ውጤት ነው ያሉ ሲሆን ይህ የአዕምሮ ክፍል እንቅልፋችንን የሚቆጣጠረው ክፍል ነው፡፡
ምንጭ፡Live Science
አበባ እስክትሆን ድረስ ዘር ነህ
****************************************************************
"ማንም ሁን ፤የትም ሁን፤ በየትኛው እድሜ ክልል ውስጥም ተገኝ አንተ ሁሌም የተግዳሮት ሰለባ ነህ " ሲሉ የሳይኮሎጂው ታለቅ ሰው ፕሮፌሰር በርን በርንሰቴን የስነልቦና ምክራቸውን ጀምረዋል፡፡
የምትወደው ሰው ህይወት አደጋ ውስጥ እንደገባ ሰምተሃል፣ ከመስራቤትሽ ያልጠበቅሽው ደብዳቤ ደርሶሻል፣ የምርመራ ውጤትህ አስደሳች ዜና ይዞ አልመጣም፣ ይዘህ መምጣት የሚኖርብህን ሰነድ ረስተሃል ፣ትራንስፖርት አጥተህ ተሰቃይተሃል ወይንም ሌላ ብዙ እንዲሆን ማትፈልገው ነገር እንዲሆን ተገደሃል እናም እንዲህ ያለው ነገር በየስንት ጊዜው ሂወትህ ውስጥ የሚከሰት ይመስልሃል? ብትባል መልሱ ሁሌም በየቀኑ የሚለው እንደሚሆን አያጠራጥርም፡፡
እነዚህ ተግዳሮቶች ሁሌም አብረውህ ያሉ ወደፊትም የሚኖሩ ናቸው ምናልባትም ተጋፍጠሃቸው እያሸነፍክ መሻገር አልያም እያየሃቸው ወንዙ ዳር ተገትሮ መቅረት የግል ምርጫህ እና ውሳኔ ነው፡፡ ነገር ግን እነዚህ ተግዳሮቶች የቀን ተቀን ፈተናዎችህ ናቸው፡፡
ምናልባትም የህይወት ዓለማ ምንድነው ብለህ ጠይቀህ ታውቅ ይሆን? የህይወት ዓለማ ደስታ፣ ስኬት አልያም እርካታ እና የመሳሰሉትን በጎ ምኞቶች እንደሆኑ የሚዘረዝሩ የተለያዩ ሰዎች ይኖራሉ ለእኔ ግን ይላሉ ፕሮፌሰሩ "የህይወትህ ዓለማ በየቀኑ የሚገጥሙህን ፈተናዎች ማለፍ ነው፡፡" መሆን የምትፈልገው ምንም ይሁን ፤ መድረስ የምታልመውም የትም ይሁን ፊት ለፊትህ ሁሌም ፈተና አለ ያንን ማለፍ ካልቻልክ የትም መድረስ አትችልም፡፡
ህይወት ታላቁን አንተነትህን ትሆን ዘንድ የተሰጠችህ ፈተና ናት!
እቤትህ ውስጥ አበባ ለመትከል እና ለማሳደግ አስበህ ከሆነ እንኳን በቀላሉ ሊሆን የሚችል እንዳልሆነ ልብ ማለት አለብህ ዘር ከማምጣት አንስቶ ቦታ ማዘጋጀት ፣ውሃ ማጠጣት፣ በየቀኑ መንከባከብ እና አንዳንዴም ከዚህ ሁላ ድካም በኋላ የሚደርቅ ካለ ተስፋ ሳይቆርጡ ቀሪውን በህይወት ማቆየት የራሱ የሆነ ፈተና ነው፡፡
አንተ ውስጥ ያንተን ሙሉ ምስል የያዘ ዘር አለ ፤ ይህንን ዘር ወደ አበባነት መቀየር ቀላል አይደለም በመንገዱ ላይ ቀላል ያልሆኑ ችግሮች ይገጥማሉ እነዚህን ችግሮች እየተጋፈጡ እና ከሁኔታው እየተማሩ ማለፍ ካልተቻለ እርከኑን መሻገር የሚቻል አይሆንም ይህ መንገድ ሙሉውን አበባነትህን እንድትተዋወቀው ይረዳሃል፡፡
አበባ አበባ ሁኖ ለመውጣት በብዙ ነገሮች ውስጥ ያልፋል የትናንት ዘርነቱን አይቶም ዛሬ እንዲህ ያለ መልክ ይኖረዋል ብሎ የሚገምት አይኖርም ፤ነገር ግን አበባ ስሩን ከመሬት ውስጥ በመስደድ እና ለራሱ የማይነቃነቅ መሰረትን በመያዝ ከላይ ደገሞ ርቀቷ ሳይገድበው እና እራሱን ዝቅ አድርጎ ሳይመለከት ከፀሃይ ማግኘት የሚኖርበትን ሁሉ ለማግኘት በመጣር አበባነቱን ያውጃል፡፡
ስለዚህ እኛም በዚህ ምድር ላይ በሚኖረን ቆይታ የራሳችንን ቦታ መፈለግ ይኖርብናል በዚህ ውስጥ አካላዊ እና ስነልቦናዊ የሆኑ ፈተናዎች የሚገጥሙን መሆኑ እሙን ቢሆንም ችግሮቻችን የማስቀረት ስልጣን የለንም፡፡ እኛ ችግሮቻችን ላይ ያለን ስልጣን እንዴት አድርገን እንደምንጋጠማቸው እና እነርሱን እንዴት እንደምናያቸው መወሰን ላይ ነው፡፡
ደብርት እና አዘቅጥ ውስጥ ከተውን እንዲሄዱ እንፈቅድላቸዋልን ወይስ ተምረንባቸውና አሸንፈናቸው ጉዞዋችንን እንቀጥላለን? ችግርን በትክክለኛው ሰዓት እና በትክክለኛው መንገድ መጋፈጥ ለትልቁ እኛነታችን ትልቅ ዕድል ነው፡፡ በስተመጨረሻም ፕሮፌሰሩ እንዲህ ሲሉ አጠቃለዋል፡- ችግሮች ከጠላትነታቸው ይልቅ ጓደኝነታቸው ያመዝናል ከእነሱ ጋር የሚኖረንን ግንኙነት ካሳመርን እና በትክክለኛው መንገድ ካስተናገድናቸው እኛ ውስጥ ያሉ እና የማይታዩ ድብቅ ችሎታዎቻችን ለማውጣት ዓይነተኛ አቅም አላቸው፡፡
ስለዚህ ህይወትን እንደፈተና እራሳችንን ደግሞ እንደ ዘር በመቁጠር ቆንጆውን አበባችንን በትዕግስት መጠባበቅ ይኖርብናል፡፡
ምንጭ፡ Psychology Today
****************************************************************
"ማንም ሁን ፤የትም ሁን፤ በየትኛው እድሜ ክልል ውስጥም ተገኝ አንተ ሁሌም የተግዳሮት ሰለባ ነህ " ሲሉ የሳይኮሎጂው ታለቅ ሰው ፕሮፌሰር በርን በርንሰቴን የስነልቦና ምክራቸውን ጀምረዋል፡፡
የምትወደው ሰው ህይወት አደጋ ውስጥ እንደገባ ሰምተሃል፣ ከመስራቤትሽ ያልጠበቅሽው ደብዳቤ ደርሶሻል፣ የምርመራ ውጤትህ አስደሳች ዜና ይዞ አልመጣም፣ ይዘህ መምጣት የሚኖርብህን ሰነድ ረስተሃል ፣ትራንስፖርት አጥተህ ተሰቃይተሃል ወይንም ሌላ ብዙ እንዲሆን ማትፈልገው ነገር እንዲሆን ተገደሃል እናም እንዲህ ያለው ነገር በየስንት ጊዜው ሂወትህ ውስጥ የሚከሰት ይመስልሃል? ብትባል መልሱ ሁሌም በየቀኑ የሚለው እንደሚሆን አያጠራጥርም፡፡
እነዚህ ተግዳሮቶች ሁሌም አብረውህ ያሉ ወደፊትም የሚኖሩ ናቸው ምናልባትም ተጋፍጠሃቸው እያሸነፍክ መሻገር አልያም እያየሃቸው ወንዙ ዳር ተገትሮ መቅረት የግል ምርጫህ እና ውሳኔ ነው፡፡ ነገር ግን እነዚህ ተግዳሮቶች የቀን ተቀን ፈተናዎችህ ናቸው፡፡
ምናልባትም የህይወት ዓለማ ምንድነው ብለህ ጠይቀህ ታውቅ ይሆን? የህይወት ዓለማ ደስታ፣ ስኬት አልያም እርካታ እና የመሳሰሉትን በጎ ምኞቶች እንደሆኑ የሚዘረዝሩ የተለያዩ ሰዎች ይኖራሉ ለእኔ ግን ይላሉ ፕሮፌሰሩ "የህይወትህ ዓለማ በየቀኑ የሚገጥሙህን ፈተናዎች ማለፍ ነው፡፡" መሆን የምትፈልገው ምንም ይሁን ፤ መድረስ የምታልመውም የትም ይሁን ፊት ለፊትህ ሁሌም ፈተና አለ ያንን ማለፍ ካልቻልክ የትም መድረስ አትችልም፡፡
ህይወት ታላቁን አንተነትህን ትሆን ዘንድ የተሰጠችህ ፈተና ናት!
እቤትህ ውስጥ አበባ ለመትከል እና ለማሳደግ አስበህ ከሆነ እንኳን በቀላሉ ሊሆን የሚችል እንዳልሆነ ልብ ማለት አለብህ ዘር ከማምጣት አንስቶ ቦታ ማዘጋጀት ፣ውሃ ማጠጣት፣ በየቀኑ መንከባከብ እና አንዳንዴም ከዚህ ሁላ ድካም በኋላ የሚደርቅ ካለ ተስፋ ሳይቆርጡ ቀሪውን በህይወት ማቆየት የራሱ የሆነ ፈተና ነው፡፡
አንተ ውስጥ ያንተን ሙሉ ምስል የያዘ ዘር አለ ፤ ይህንን ዘር ወደ አበባነት መቀየር ቀላል አይደለም በመንገዱ ላይ ቀላል ያልሆኑ ችግሮች ይገጥማሉ እነዚህን ችግሮች እየተጋፈጡ እና ከሁኔታው እየተማሩ ማለፍ ካልተቻለ እርከኑን መሻገር የሚቻል አይሆንም ይህ መንገድ ሙሉውን አበባነትህን እንድትተዋወቀው ይረዳሃል፡፡
አበባ አበባ ሁኖ ለመውጣት በብዙ ነገሮች ውስጥ ያልፋል የትናንት ዘርነቱን አይቶም ዛሬ እንዲህ ያለ መልክ ይኖረዋል ብሎ የሚገምት አይኖርም ፤ነገር ግን አበባ ስሩን ከመሬት ውስጥ በመስደድ እና ለራሱ የማይነቃነቅ መሰረትን በመያዝ ከላይ ደገሞ ርቀቷ ሳይገድበው እና እራሱን ዝቅ አድርጎ ሳይመለከት ከፀሃይ ማግኘት የሚኖርበትን ሁሉ ለማግኘት በመጣር አበባነቱን ያውጃል፡፡
ስለዚህ እኛም በዚህ ምድር ላይ በሚኖረን ቆይታ የራሳችንን ቦታ መፈለግ ይኖርብናል በዚህ ውስጥ አካላዊ እና ስነልቦናዊ የሆኑ ፈተናዎች የሚገጥሙን መሆኑ እሙን ቢሆንም ችግሮቻችን የማስቀረት ስልጣን የለንም፡፡ እኛ ችግሮቻችን ላይ ያለን ስልጣን እንዴት አድርገን እንደምንጋጠማቸው እና እነርሱን እንዴት እንደምናያቸው መወሰን ላይ ነው፡፡
ደብርት እና አዘቅጥ ውስጥ ከተውን እንዲሄዱ እንፈቅድላቸዋልን ወይስ ተምረንባቸውና አሸንፈናቸው ጉዞዋችንን እንቀጥላለን? ችግርን በትክክለኛው ሰዓት እና በትክክለኛው መንገድ መጋፈጥ ለትልቁ እኛነታችን ትልቅ ዕድል ነው፡፡ በስተመጨረሻም ፕሮፌሰሩ እንዲህ ሲሉ አጠቃለዋል፡- ችግሮች ከጠላትነታቸው ይልቅ ጓደኝነታቸው ያመዝናል ከእነሱ ጋር የሚኖረንን ግንኙነት ካሳመርን እና በትክክለኛው መንገድ ካስተናገድናቸው እኛ ውስጥ ያሉ እና የማይታዩ ድብቅ ችሎታዎቻችን ለማውጣት ዓይነተኛ አቅም አላቸው፡፡
ስለዚህ ህይወትን እንደፈተና እራሳችንን ደግሞ እንደ ዘር በመቁጠር ቆንጆውን አበባችንን በትዕግስት መጠባበቅ ይኖርብናል፡፡
ምንጭ፡ Psychology Today