የመጀመሪያው የክህሎት ውድድር ተጀመረ
************************************
የመጀመሪያው ሐገር ዓቀፍ የቴክኖሎጂ ክህሎት እና ተግባራዊ ምርምር ውድድር በተለያዩ ኪነ ጥበባዊ ስራዎች ታጅቦ ትናንት ተጀምሯል፡፡ በፌደራል ቴክኒክ እና ሙያ ትምህርት ስልጠና ኤጀንሲና በፌደራል ቴክኒክ እና ሙያ ትምህርት ስልጠና ኢንስትቲውት በጋራ የሚዘጋጀው ይህ ውድድር “በክህሎትና ስነ ምግባር የታነፀ ትውልድ ለሰላምና ልማታችን ዋስትና ናቸው” በሚል መሪ ቃል እስከ ሰኔ 11 የሚዘልቅ ይሆናል፡፡ በተሳታፊነትም የተለያዩ የቴክኒክ እና ሙያ ሰልጣኞች፣ አሰልጣኞች እና ኢንተርፕራይዝ ኦፕሬተሮች ተካፋይ ያደርጋል፡፡
የዕለቱ የክብር ዕንግዳ የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር እና የፌደራል ቴክኒክ እና ሙያ ትምህርት ስልጠና ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ አህመድ ሺዴ መንግስት ትምህርት እና ስልጠና ለሐገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት መሰረታዊ መሆኑን ተረድቶ ለዘርፉ ልዩ ትኩረት በመስጠት መንቀሳቀሱን ገልፀዋል፡፡ ክቡር ሚንስትሩ “ስራ ፈላጊ ብቻ ሳይሆን ስራ ፈጣሪ ዜጎችንም ያፈራል” ባሉት ቴክኒክ እና ሙያ ተቋም ላይ በህብረተሰቡ ዘንድ ያለውን አመለካከት ለማሻሻል የአተያይና የግንዛቤ ስራዎች መስራት እንደሚገባ አስቀምጠዋል፡፡ በመጨረሻም ዘርፉን ለማጎልበት እና የህብረተሰብን ተጠቃሚ ለማድረግ ስራዎችን በጥናትና ምርምር መደገፍ እንደሚገባ በማሳሰብ በውድድሩ ለተሳተፉ ሰልጣኝ፣ አሰልጣኞች እና እና የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በዝግጅቱ የእንኳን ደህና መጣችው ንግግሩን ያቀረቡት የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚኒስቴር ሚንስትር ደኤታው ዶክተር አብዲዋሳ አብዱላሂ ትምህርት ለአንድን ሐገር የልማት መሳሪያና የእድገት ፍትሐዊነት ማረጋገጫ እንደሆነ ሲገልፁ፤ የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠናም የሰው ልጆችን ድህነትና ስራ አጥትን ለማስወገድ እንዲሁም ሰላምን ለማረገገጥ የቁልፎች ሁሉ ቁልፍ ነው ብለዋል፡፡ የቴክኒክና ሙያ ትምህርት እና ስልጠና አንዱ ተልዕኮ የቴክሎጂ አቅምን በመገንባት ኢንዱስትሪዎችን ተወዳዳሪ ማድረግ ቢሆንም ባለው የቅንጅት አሰራር፣ የማበረታቻ ስርዓት፣ የእይታ መድረኮች እና ኢንዱስትሪዎች ላይ መተግበሪያ መንገዶች አለመኖር ሳቢያ ይህ ሚናቸውን በብቃት መወጣት እንዳልቻሉ የተናገሩት ዶክተር አብዲዋሳ እነዚህን ተግዳሮቶች በመፍታት እና መሰል የቴክኖሎጂ ክህሎት እና ተግባራዊ ምርምር ውድድሮችን ከታች ከወረዳ አንስቶ እስከ ሐገር ዓቀፍ ድረስ ማከናወን ይገባል ብለዋል፡፡
ውድድሩ የተወዳዳሪዎቹን ስራዎች በዓውደ ርዕይ መልክ በማሳየት እና የዘርፉን አቋም የሚገመግሙ የፓናል ውይይቶች በማካሄድ የሚቀጥል ሲሆን ከፍተኛ ውጤት ላሳዩ 11 ተወዳዳሪዎችም የሚበረከትላቸው ይሆናል፡፡
************************************
የመጀመሪያው ሐገር ዓቀፍ የቴክኖሎጂ ክህሎት እና ተግባራዊ ምርምር ውድድር በተለያዩ ኪነ ጥበባዊ ስራዎች ታጅቦ ትናንት ተጀምሯል፡፡ በፌደራል ቴክኒክ እና ሙያ ትምህርት ስልጠና ኤጀንሲና በፌደራል ቴክኒክ እና ሙያ ትምህርት ስልጠና ኢንስትቲውት በጋራ የሚዘጋጀው ይህ ውድድር “በክህሎትና ስነ ምግባር የታነፀ ትውልድ ለሰላምና ልማታችን ዋስትና ናቸው” በሚል መሪ ቃል እስከ ሰኔ 11 የሚዘልቅ ይሆናል፡፡ በተሳታፊነትም የተለያዩ የቴክኒክ እና ሙያ ሰልጣኞች፣ አሰልጣኞች እና ኢንተርፕራይዝ ኦፕሬተሮች ተካፋይ ያደርጋል፡፡
የዕለቱ የክብር ዕንግዳ የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር እና የፌደራል ቴክኒክ እና ሙያ ትምህርት ስልጠና ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ አህመድ ሺዴ መንግስት ትምህርት እና ስልጠና ለሐገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት መሰረታዊ መሆኑን ተረድቶ ለዘርፉ ልዩ ትኩረት በመስጠት መንቀሳቀሱን ገልፀዋል፡፡ ክቡር ሚንስትሩ “ስራ ፈላጊ ብቻ ሳይሆን ስራ ፈጣሪ ዜጎችንም ያፈራል” ባሉት ቴክኒክ እና ሙያ ተቋም ላይ በህብረተሰቡ ዘንድ ያለውን አመለካከት ለማሻሻል የአተያይና የግንዛቤ ስራዎች መስራት እንደሚገባ አስቀምጠዋል፡፡ በመጨረሻም ዘርፉን ለማጎልበት እና የህብረተሰብን ተጠቃሚ ለማድረግ ስራዎችን በጥናትና ምርምር መደገፍ እንደሚገባ በማሳሰብ በውድድሩ ለተሳተፉ ሰልጣኝ፣ አሰልጣኞች እና እና የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በዝግጅቱ የእንኳን ደህና መጣችው ንግግሩን ያቀረቡት የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚኒስቴር ሚንስትር ደኤታው ዶክተር አብዲዋሳ አብዱላሂ ትምህርት ለአንድን ሐገር የልማት መሳሪያና የእድገት ፍትሐዊነት ማረጋገጫ እንደሆነ ሲገልፁ፤ የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠናም የሰው ልጆችን ድህነትና ስራ አጥትን ለማስወገድ እንዲሁም ሰላምን ለማረገገጥ የቁልፎች ሁሉ ቁልፍ ነው ብለዋል፡፡ የቴክኒክና ሙያ ትምህርት እና ስልጠና አንዱ ተልዕኮ የቴክሎጂ አቅምን በመገንባት ኢንዱስትሪዎችን ተወዳዳሪ ማድረግ ቢሆንም ባለው የቅንጅት አሰራር፣ የማበረታቻ ስርዓት፣ የእይታ መድረኮች እና ኢንዱስትሪዎች ላይ መተግበሪያ መንገዶች አለመኖር ሳቢያ ይህ ሚናቸውን በብቃት መወጣት እንዳልቻሉ የተናገሩት ዶክተር አብዲዋሳ እነዚህን ተግዳሮቶች በመፍታት እና መሰል የቴክኖሎጂ ክህሎት እና ተግባራዊ ምርምር ውድድሮችን ከታች ከወረዳ አንስቶ እስከ ሐገር ዓቀፍ ድረስ ማከናወን ይገባል ብለዋል፡፡
ውድድሩ የተወዳዳሪዎቹን ስራዎች በዓውደ ርዕይ መልክ በማሳየት እና የዘርፉን አቋም የሚገመግሙ የፓናል ውይይቶች በማካሄድ የሚቀጥል ሲሆን ከፍተኛ ውጤት ላሳዩ 11 ተወዳዳሪዎችም የሚበረከትላቸው ይሆናል፡፡
“ሐገር የምትገነባው ከታች ጀምሮ ነው !” ክብርት ፕሬዘዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ
************************************
የኢፌድሪ ፕሬዘዳንት ክብርት ሳህለወርቅ ዘውዴ በመጀመሪያው ሐገራዊ የክህሎት ውድድር መቋጫ ላይ የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና ስኬቶችን ቢመዘገቡም ዘርፉ ላይ የሚታየውን ሰፊ ክፍተት ለመድፈን የሁሉም አካላት ተሳትፎን እንደሚሻ ተናግረዋል፡፡ ሐገር የምትገነባው ከታች ጀምሮ ነው ያሉት ክብርት ፕሬዘዳንቷ ህብረተሰቡ በቴክኒክ እና ሙያ ላይ ያለውን አመለካከት የሚለውጡ የተግባርና ግንዛቤ ስራዎች እንደሚሰሩ ገልፀዋል፡፡
Technology Installation እና Database Administration ጨምሮ በአስራ አንድ ምድቦች ተከፍለው ከተወዳደሩት የቴክኒክ እና ሙያ ሰልጣኝ፣ አሰልጣን እና ኢንተርፕራይዞች መካከል በየምድባቸው ከአንድ እስከ ሶስተኛ ለወጡት ተወዳዳሪዎች እንደየ ደረጃቸው የሜዳሊያ፣ ገንዘብ እና ሰርተፊኬት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡
በዕለቱ ክብርት ፕሬዘዳንቷን ጨምሮ የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር እና ሚኒስትር ደኤታዎቹ ዶክተር ሂሩት እና ዶክተር አብዲዋሳ፣ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ት ፍሬህይወት፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት እና ሌሎችም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ሲገኙ የተሳታፊዎቹን ስራንም ለመጎብኘት ችለዋል፡፡
************************************
የኢፌድሪ ፕሬዘዳንት ክብርት ሳህለወርቅ ዘውዴ በመጀመሪያው ሐገራዊ የክህሎት ውድድር መቋጫ ላይ የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና ስኬቶችን ቢመዘገቡም ዘርፉ ላይ የሚታየውን ሰፊ ክፍተት ለመድፈን የሁሉም አካላት ተሳትፎን እንደሚሻ ተናግረዋል፡፡ ሐገር የምትገነባው ከታች ጀምሮ ነው ያሉት ክብርት ፕሬዘዳንቷ ህብረተሰቡ በቴክኒክ እና ሙያ ላይ ያለውን አመለካከት የሚለውጡ የተግባርና ግንዛቤ ስራዎች እንደሚሰሩ ገልፀዋል፡፡
Technology Installation እና Database Administration ጨምሮ በአስራ አንድ ምድቦች ተከፍለው ከተወዳደሩት የቴክኒክ እና ሙያ ሰልጣኝ፣ አሰልጣን እና ኢንተርፕራይዞች መካከል በየምድባቸው ከአንድ እስከ ሶስተኛ ለወጡት ተወዳዳሪዎች እንደየ ደረጃቸው የሜዳሊያ፣ ገንዘብ እና ሰርተፊኬት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡
በዕለቱ ክብርት ፕሬዘዳንቷን ጨምሮ የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር እና ሚኒስትር ደኤታዎቹ ዶክተር ሂሩት እና ዶክተር አብዲዋሳ፣ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ት ፍሬህይወት፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት እና ሌሎችም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ሲገኙ የተሳታፊዎቹን ስራንም ለመጎብኘት ችለዋል፡፡
የሰመር ካምፕ ጥሪ ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎች በሙሉ
************************************
የመንግስት ተቋማት የአሰራር ስርዓትን በሶፍትዌር የማዘመን ፕሮጀክት አካል መሆን ይፈልጋሉ?
እንግዲያውስ የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ከሃምሌ 1 እስከ ነሀሴ 30 የሚቆይ የሰመር ካምፕ ፕሮግራም አዘጋጅቷል፡፡
ተሳታፊዎች፡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ሆነው በሶፍትዌር ማበልጸግ ዙሪያ ችግር ፈቺ የሆኑ ፕሮጀክቶችና የፕሮጀክት ሃሳብ ያላቸውና ከተቋሙ ተማሪ መሆናቸውን የሚገልጽ ማስረጃ ማምጣት የሚችሉ
የመመዝገቢያ አድራሻ፡- http://www.techin.gov.et/web/sticsite/techinsummercamp
ወይም ሊሴ ገ/ማርያም ት/ቤት ጀርባ በሚገኘው የኢንስቲትዩቱ ቅጥር ግቢ
የምዝገባ ጊዜ፡- ከሰኔ 20- ሰኔ 29/2011ዓ.ም
ለበለጠ መረጃ፡- በ09-66-24-16-85
09-24-24-57-66
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት
************************************
የመንግስት ተቋማት የአሰራር ስርዓትን በሶፍትዌር የማዘመን ፕሮጀክት አካል መሆን ይፈልጋሉ?
እንግዲያውስ የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ከሃምሌ 1 እስከ ነሀሴ 30 የሚቆይ የሰመር ካምፕ ፕሮግራም አዘጋጅቷል፡፡
ተሳታፊዎች፡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ሆነው በሶፍትዌር ማበልጸግ ዙሪያ ችግር ፈቺ የሆኑ ፕሮጀክቶችና የፕሮጀክት ሃሳብ ያላቸውና ከተቋሙ ተማሪ መሆናቸውን የሚገልጽ ማስረጃ ማምጣት የሚችሉ
የመመዝገቢያ አድራሻ፡- http://www.techin.gov.et/web/sticsite/techinsummercamp
ወይም ሊሴ ገ/ማርያም ት/ቤት ጀርባ በሚገኘው የኢንስቲትዩቱ ቅጥር ግቢ
የምዝገባ ጊዜ፡- ከሰኔ 20- ሰኔ 29/2011ዓ.ም
ለበለጠ መረጃ፡- በ09-66-24-16-85
09-24-24-57-66
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት
ኢትዮጵያዊው የአዕምሮ ጤና ምሁር በሀርቫርድ ተሸለሙ
====================
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሳይካትሪ ምሁር ሆነው እያገለገሉ ያሉት ፕሮፌሰር አታላይ አለም የ2019 የሀርቫርድ Psychiatric Epidemiology and Biostatistics አዋርድ አሸናፊ ሆነዋል፡፡ ፕሮፌሰሩ ይህ ሽልማት የተበረከተላቸው በሳይካትሪ ዘርፍ ኢትዮጵያ ውስጥ ባበረከቷቸው በጎ አስተዋፅዖዎች አማካኝነት ነው፡፡
ፕሮፌሰር አታላይ የቅዱስ አማኑኤል የአዕምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ በሳይካትሪስት እና ሜዲካል ዳይሬክተርነት እንዲሁም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ኮሌጅ በዋና ዳይሬክተርነት እና ሌሎች ኃላፊነቶች ላይ አገልግሎት ሰጥተዋል፡፡ መሰል እውቅናና ሽልማቶችን ለመጎናፀፍ አዲስ ያልሆኑት እኚህ ኢትዮጵያዊ ምሁር ከአሜሪካኑ የቴዎዶር እና ቫዳ ስታንሌይ ፋውንዴሽን ሰርተፊኬት ሲበረከትላቸው በአዕምሮ ጤና ዙሪያ ኢትዮጵያ ውስጥ ላከናወኑት የትምህርት፣ አገልግሎት ብሎም ጥናትና ምርምር ተግባራት ደግሞ የሮበርት ግሬል አዋርድን ማሸነፍ ችለዋል፡፡
ይህ አዋርድ በህይወት ዘመናቸው በሳይካትሪክ ኤፒዲሚዮሎጂ ወይም ባዮስታትስቲክስ ዙሪያ ከፍተኛ አበርክቶዎችን ላደረጉ የዘርፉ ምሁራን በየዓመቱ የሚሰጥ ሲሆን አሸናፊዎችም ወደ ቦስተን በማምራት ለሳይንሱ ዓለም ታዳሚዎች ሌክቸር እንዲያቀርቡና በተለያዩ ዝግጅቶችም ተሳታፊ እንዲሆኑ ይደረጋል፡፡
ምንጭ፡ የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ
====================
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሳይካትሪ ምሁር ሆነው እያገለገሉ ያሉት ፕሮፌሰር አታላይ አለም የ2019 የሀርቫርድ Psychiatric Epidemiology and Biostatistics አዋርድ አሸናፊ ሆነዋል፡፡ ፕሮፌሰሩ ይህ ሽልማት የተበረከተላቸው በሳይካትሪ ዘርፍ ኢትዮጵያ ውስጥ ባበረከቷቸው በጎ አስተዋፅዖዎች አማካኝነት ነው፡፡
ፕሮፌሰር አታላይ የቅዱስ አማኑኤል የአዕምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ በሳይካትሪስት እና ሜዲካል ዳይሬክተርነት እንዲሁም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ኮሌጅ በዋና ዳይሬክተርነት እና ሌሎች ኃላፊነቶች ላይ አገልግሎት ሰጥተዋል፡፡ መሰል እውቅናና ሽልማቶችን ለመጎናፀፍ አዲስ ያልሆኑት እኚህ ኢትዮጵያዊ ምሁር ከአሜሪካኑ የቴዎዶር እና ቫዳ ስታንሌይ ፋውንዴሽን ሰርተፊኬት ሲበረከትላቸው በአዕምሮ ጤና ዙሪያ ኢትዮጵያ ውስጥ ላከናወኑት የትምህርት፣ አገልግሎት ብሎም ጥናትና ምርምር ተግባራት ደግሞ የሮበርት ግሬል አዋርድን ማሸነፍ ችለዋል፡፡
ይህ አዋርድ በህይወት ዘመናቸው በሳይካትሪክ ኤፒዲሚዮሎጂ ወይም ባዮስታትስቲክስ ዙሪያ ከፍተኛ አበርክቶዎችን ላደረጉ የዘርፉ ምሁራን በየዓመቱ የሚሰጥ ሲሆን አሸናፊዎችም ወደ ቦስተን በማምራት ለሳይንሱ ዓለም ታዳሚዎች ሌክቸር እንዲያቀርቡና በተለያዩ ዝግጅቶችም ተሳታፊ እንዲሆኑ ይደረጋል፡፡
ምንጭ፡ የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ
የኢትዮጵያን 50 በመቶ የዘይት ፍላጎት ያሟላል የተባለው ፋብሪካ ሊጠናቀቅ ነው
****************************************************
በኢትዮጵያ በየዓመቱ ለምርት የሚቀርበው የቅባት ዘር እና የምግብ ዘይት አቅርቦት በሃገሪቱ ካለው ከፍተኛ ፍላጎት ጋር ያልተመጣጠነ በመሆኑ በየጊዜው ቀላል ሊባል የማይችል የውጭ ምንዛሬ ወደ ሌሎች ሃገራት በግዢ መልክ እንደሚወጣ ይታወቃል፡፡ በሃገሪቱ ያሉት አብዛኞቹ የምግብ ዘይት ማቀናበሪያ ፋበሪካዎች በአነስተኛ ደረጃ የሚንቀሳቀሱ በመሆናቸውና የግብዓት አጠቃቀም ሰንሰለታቸው በሚገባ ያልተጠናከረ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የጥራት ችግር እንዲነሳባቸው እና ለሌሎች ተያያዥ እክሎችም በር እንዲከፍቱ አስገድዷል፡፡
ከዚህ ጋር ተያይዞ በየጊዚያቱ ወደ ዘርፉ የሚቀላለቀሉ ግዙፍ ፋብሪካዎች በአንስተኛ ደረጃም ቢሆን ቁጥራቸው እየጨመረ የሚገኝ ሲሆን ከሰሞኑም በአማራ ክልል በመጠናቀቅ ላይ ያለው የምግብ ዘይት ማምረቻ ፋብሪካ ከእነዚህ ውስጥ እንደአንዱ ሊጠቀስ የሚችል ነው፡፡ ይህ አዲስ ፋብሪካ በምዕራብ ጎጃም ዞን ቡሬ ከተማ ውስጥ በ30 ሄክታር መሬት ላይ የሚያርፍ ሲሆን ከ2,000 በላይ ለሚሆኑ ዜጎችም የስራ እድል እነደሚፈጥር ይጠበቃል፡፡
የፋብሪካው ግንባታ ሙሉ ለሙሉ እየተጠናቀቀ መምጣቱን እና የተለያዩ የማሽነሪ ግብዓቶች እየተሟሉለት እንደሚገኝ የሚናገሩት የፋብሪካው ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ዳኛቸው ዋሴ በጠቅላለውም ለኢንቨስትመንት ወጪው ከ2.1 ቢሊዮን ብር ባላይ መፍጀቱን ጠቅሰዋል፡፡ ፋብሪካው የዘይት ምርቱን ለማስኬድ የሱፍ አበባ እና የሶያ ቢን ግብዓቶችን በዋናነት እንደሚጠቀም የተናገሩት ኢንጅነሩ፤ እንደመነሻም 1,400 ቶን የሚጠጋ የምግብ ዘይት በየቀኑ ለማምረት የሚስችል አቅም እንዳለው ጠቅሰዋል፡፡ ፋብሪካው ምርታማነትን በማሳደግ እና የአቅርቦት ሰንሰለቱን በማዘመን በኩል በከፍተኛ ደረጃ እየተንቀሳቀሰ በመሆኑ ከ50 በመቶ በላይ ለሚሆነው የሃገሪቱ ህዝብ በቂ የምግብ ዘይት ለማቅረብ የሚስችለውን አቅም እንደፈጠረ ተነግሯል፡፡
ፋብሪካው በአግሮቢዝነስ እና ሌሎች ተያያዥ የስራ ዘርፎች ላይ በሰፊው እየሰራ በሚገኘው ቢ.ኬ ቢዝነስ ግሩፕ የሚከናወን ሲሆን በጥቂት አመታት ውስጥም በምግብ ዘይት አቅርቦት ዙሪያ የሚወጣውን ከፍተኛ የወጪ ምንዛሬ እንደሚያድን ይጠበቃል፡፡
ምንጭ፡ SNV እና New Business Ethiopia
****************************************************
በኢትዮጵያ በየዓመቱ ለምርት የሚቀርበው የቅባት ዘር እና የምግብ ዘይት አቅርቦት በሃገሪቱ ካለው ከፍተኛ ፍላጎት ጋር ያልተመጣጠነ በመሆኑ በየጊዜው ቀላል ሊባል የማይችል የውጭ ምንዛሬ ወደ ሌሎች ሃገራት በግዢ መልክ እንደሚወጣ ይታወቃል፡፡ በሃገሪቱ ያሉት አብዛኞቹ የምግብ ዘይት ማቀናበሪያ ፋበሪካዎች በአነስተኛ ደረጃ የሚንቀሳቀሱ በመሆናቸውና የግብዓት አጠቃቀም ሰንሰለታቸው በሚገባ ያልተጠናከረ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የጥራት ችግር እንዲነሳባቸው እና ለሌሎች ተያያዥ እክሎችም በር እንዲከፍቱ አስገድዷል፡፡
ከዚህ ጋር ተያይዞ በየጊዚያቱ ወደ ዘርፉ የሚቀላለቀሉ ግዙፍ ፋብሪካዎች በአንስተኛ ደረጃም ቢሆን ቁጥራቸው እየጨመረ የሚገኝ ሲሆን ከሰሞኑም በአማራ ክልል በመጠናቀቅ ላይ ያለው የምግብ ዘይት ማምረቻ ፋብሪካ ከእነዚህ ውስጥ እንደአንዱ ሊጠቀስ የሚችል ነው፡፡ ይህ አዲስ ፋብሪካ በምዕራብ ጎጃም ዞን ቡሬ ከተማ ውስጥ በ30 ሄክታር መሬት ላይ የሚያርፍ ሲሆን ከ2,000 በላይ ለሚሆኑ ዜጎችም የስራ እድል እነደሚፈጥር ይጠበቃል፡፡
የፋብሪካው ግንባታ ሙሉ ለሙሉ እየተጠናቀቀ መምጣቱን እና የተለያዩ የማሽነሪ ግብዓቶች እየተሟሉለት እንደሚገኝ የሚናገሩት የፋብሪካው ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ዳኛቸው ዋሴ በጠቅላለውም ለኢንቨስትመንት ወጪው ከ2.1 ቢሊዮን ብር ባላይ መፍጀቱን ጠቅሰዋል፡፡ ፋብሪካው የዘይት ምርቱን ለማስኬድ የሱፍ አበባ እና የሶያ ቢን ግብዓቶችን በዋናነት እንደሚጠቀም የተናገሩት ኢንጅነሩ፤ እንደመነሻም 1,400 ቶን የሚጠጋ የምግብ ዘይት በየቀኑ ለማምረት የሚስችል አቅም እንዳለው ጠቅሰዋል፡፡ ፋብሪካው ምርታማነትን በማሳደግ እና የአቅርቦት ሰንሰለቱን በማዘመን በኩል በከፍተኛ ደረጃ እየተንቀሳቀሰ በመሆኑ ከ50 በመቶ በላይ ለሚሆነው የሃገሪቱ ህዝብ በቂ የምግብ ዘይት ለማቅረብ የሚስችለውን አቅም እንደፈጠረ ተነግሯል፡፡
ፋብሪካው በአግሮቢዝነስ እና ሌሎች ተያያዥ የስራ ዘርፎች ላይ በሰፊው እየሰራ በሚገኘው ቢ.ኬ ቢዝነስ ግሩፕ የሚከናወን ሲሆን በጥቂት አመታት ውስጥም በምግብ ዘይት አቅርቦት ዙሪያ የሚወጣውን ከፍተኛ የወጪ ምንዛሬ እንደሚያድን ይጠበቃል፡፡
ምንጭ፡ SNV እና New Business Ethiopia
የሳይንስ ማዕከል በአዲስ አበባ ተከፈተ
=================
ህፃናት በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና እና ሂሳብ ትምህርቶች ላይ ያላቸውን አቅም የሚያሳድግ ማዕከል በኢትዮጵያ የሳይንስ አካዳሚ ተገንብቶ ዛሬ ተመርቋል፡፡ ከስቴም ሲነርጂ ጋር በመተባበር የተገነባው ማዕከሉ የተለያዩ የሳይንስ ዘርፎችን ያካትታል፤ ለጊዜውም ሁለት የኤሌክትሮኒክስ እና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቤተ-ሙከራዎችን አቅፎ የያዘ ነው፡፡
በምርቃት ስነ-ስርዓቱ የኢትዮያ ሳይንስ አካዳሚ ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ማስረሻ እንዲሁም የሳይንስ ማዕከለሉ ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ኤፍሬም እንግዳወርቅ በሳይንስ አካዳሚው እና የሳይንስ ማዕከላት ዙሪያ ለእንግዶች ገለፃ አድርገዋል፡፡ በተጨማሪም የክብር እንግዳው ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ ሳይንስን ከንባብ በዘለለ ወደ ተግባር ስራ እንደሚለውጥ በማመላከት ማዕከሉን ግንባታ አድንቀዋል፡፡
መሰል የሳይንስ ማዕከላት በስቴም ሲነርጂ አማካኝነት በመላው ሐገራችን 14 ስፍራዎች ተከፍተው እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ፡፡ ከነዚህም ውስጥ አብዛኛው ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር ተያይዘው የተገነቡ ናቸው፡፡ በቀጣዮቹ ጊዜያትም ሀረማያ እና ቀብሪደሃርን ጨምሮ በሰባት የሐገራችን ዩኒቨርሲቲዎች ማዕከላቱን እንደሚገነባ የስቴም ሲነርጂ ዋና ዳይሬክተር አቶ ፀጋዬ ለገሰ ተናግረዋል፡፡
=================
ህፃናት በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና እና ሂሳብ ትምህርቶች ላይ ያላቸውን አቅም የሚያሳድግ ማዕከል በኢትዮጵያ የሳይንስ አካዳሚ ተገንብቶ ዛሬ ተመርቋል፡፡ ከስቴም ሲነርጂ ጋር በመተባበር የተገነባው ማዕከሉ የተለያዩ የሳይንስ ዘርፎችን ያካትታል፤ ለጊዜውም ሁለት የኤሌክትሮኒክስ እና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቤተ-ሙከራዎችን አቅፎ የያዘ ነው፡፡
በምርቃት ስነ-ስርዓቱ የኢትዮያ ሳይንስ አካዳሚ ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ማስረሻ እንዲሁም የሳይንስ ማዕከለሉ ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ኤፍሬም እንግዳወርቅ በሳይንስ አካዳሚው እና የሳይንስ ማዕከላት ዙሪያ ለእንግዶች ገለፃ አድርገዋል፡፡ በተጨማሪም የክብር እንግዳው ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ ሳይንስን ከንባብ በዘለለ ወደ ተግባር ስራ እንደሚለውጥ በማመላከት ማዕከሉን ግንባታ አድንቀዋል፡፡
መሰል የሳይንስ ማዕከላት በስቴም ሲነርጂ አማካኝነት በመላው ሐገራችን 14 ስፍራዎች ተከፍተው እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ፡፡ ከነዚህም ውስጥ አብዛኛው ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር ተያይዘው የተገነቡ ናቸው፡፡ በቀጣዮቹ ጊዜያትም ሀረማያ እና ቀብሪደሃርን ጨምሮ በሰባት የሐገራችን ዩኒቨርሲቲዎች ማዕከላቱን እንደሚገነባ የስቴም ሲነርጂ ዋና ዳይሬክተር አቶ ፀጋዬ ለገሰ ተናግረዋል፡፡
ዛፍን መትከል እንደዋነኛ የመፍትሄ አማራጭ መውሰድ ይገባል፤ ጥናት። =======================
የአየር ንብረት ለውጥን ለመቆጣጠር ኢትዮጵያን ጨምሮ በመላው ዓለም የዛፍ ተከላዎች በመረግ ላይ ነው፡፡ የኢትዮጵያን እንኳን ብናይ ከሁለት ዛፍ ለሁለት ሺህ አንስቶ እስከ አሁኑ የአራት ቢሊዮን ዕፅዋት ተከላ መርሀ ግብር ያለውን እንቅስቃሴ መጥቀስ ይቻላል፡፡ ሆኖም በግቡ ውጤታማነት ላይ ጥያቄዎች ሲነሱ ቆየተተዋል፡፡
ከቀናት በፊት የወጣው ጥናት ለዚህ በጎ ምላሽ የሚሰጥ ሆኗል፡፡ እንደጥናቱ ከሆነ ዕፅዋት በተገቢው አፈር ላይ ከተተከሉ 205 ጊጋ ቶን የሚሆን የሚሆን ካርቦን ዳይ ኦክሳይድን በሚቀጥሉት ከ40 እስከ መቶ ዓመታት ውስጥ መሰብሰብ ይችላሉ፡፡ ይህን አሀዝ ለንፅፅር ስናቀርበው የሰው ልጆች ከኢንዱስትሪ አብዮት መፈንዳት አንስቶ ካመነጨነው ሁለት ሶስተኛው ጋር የሚስተካከል ነው፡፡ በተጓዳኝም በእጅጉ እየተጎዳ የሚገኘውን የዓለማችን ስነ-ምህዳር ይጠገናል፡፡
ጥናቱ 80,000 የሳተላይት ምስሎችን በመሰብሰብ የመረመረ ሲሆን ምድራችን ምን ያህል ዕፅዋትን፤ በየትኛው ስፍራና የአየር እንዲሁም አፈር ሁኔታ ማቀበል እንደምትችልም ጭምር የሚያሳይ ነው፡፡ በዚህም መሰረት የተገለጸውን ውጤት ያስገኝ ዘንድ ከኢትዮጵያ አጠቃላይ ቆዳ ስፋት ዘጠኝ እጥፍ በሚበልጥ መሬት ላይ ዕፅዋትን መትከል እንደሚቻልና እንደሚገባ አስቀምጧል፡፡ ሆኖም ተከላው ከወዲሁ መቀላጠፍ ይኖርበታል፡፡ ይህ ካልሆነ እየጨመረ በሚመጣው የዓለም ሙቀት አማካኝነት የሚከሰቱት ድርቅ እና የዛፎች አተነፋፈስ ለውጥ የዛፎቹን ዕድገት ሊገታ ይችላል፡፡
ሆኖም መንገዶች አልጋ በአልጋ አይሆኑም፡፡ ወደፊት እንደሚያጋጥሚ ከሚጠበቁ ችግሮች ውስጥ አንዱ የዋጋው ጉዳይ ነው፡፡ ዛፎችን በዚህ መጠን መትከል በትንሹ 300 ቢሊዮን ዶላርን ይጠይቃል፤ ምንም እንኳን እንደቡድኑ ግምት ከሌሎች የካርበን መምጠጫ መንገዶች አንፃር ርካሽ እንደሆነ ቢነገርም፡፡
ታድያ እርስዎስ ስንት ዛፎችን በዚህ ክረምት ስንት ዛፎችን ተክለዋል፤ ስንረትስ ለመትከል ዕቅድ ይዘዋል፡፡
ምንጭ፡ Scientific American
የአየር ንብረት ለውጥን ለመቆጣጠር ኢትዮጵያን ጨምሮ በመላው ዓለም የዛፍ ተከላዎች በመረግ ላይ ነው፡፡ የኢትዮጵያን እንኳን ብናይ ከሁለት ዛፍ ለሁለት ሺህ አንስቶ እስከ አሁኑ የአራት ቢሊዮን ዕፅዋት ተከላ መርሀ ግብር ያለውን እንቅስቃሴ መጥቀስ ይቻላል፡፡ ሆኖም በግቡ ውጤታማነት ላይ ጥያቄዎች ሲነሱ ቆየተተዋል፡፡
ከቀናት በፊት የወጣው ጥናት ለዚህ በጎ ምላሽ የሚሰጥ ሆኗል፡፡ እንደጥናቱ ከሆነ ዕፅዋት በተገቢው አፈር ላይ ከተተከሉ 205 ጊጋ ቶን የሚሆን የሚሆን ካርቦን ዳይ ኦክሳይድን በሚቀጥሉት ከ40 እስከ መቶ ዓመታት ውስጥ መሰብሰብ ይችላሉ፡፡ ይህን አሀዝ ለንፅፅር ስናቀርበው የሰው ልጆች ከኢንዱስትሪ አብዮት መፈንዳት አንስቶ ካመነጨነው ሁለት ሶስተኛው ጋር የሚስተካከል ነው፡፡ በተጓዳኝም በእጅጉ እየተጎዳ የሚገኘውን የዓለማችን ስነ-ምህዳር ይጠገናል፡፡
ጥናቱ 80,000 የሳተላይት ምስሎችን በመሰብሰብ የመረመረ ሲሆን ምድራችን ምን ያህል ዕፅዋትን፤ በየትኛው ስፍራና የአየር እንዲሁም አፈር ሁኔታ ማቀበል እንደምትችልም ጭምር የሚያሳይ ነው፡፡ በዚህም መሰረት የተገለጸውን ውጤት ያስገኝ ዘንድ ከኢትዮጵያ አጠቃላይ ቆዳ ስፋት ዘጠኝ እጥፍ በሚበልጥ መሬት ላይ ዕፅዋትን መትከል እንደሚቻልና እንደሚገባ አስቀምጧል፡፡ ሆኖም ተከላው ከወዲሁ መቀላጠፍ ይኖርበታል፡፡ ይህ ካልሆነ እየጨመረ በሚመጣው የዓለም ሙቀት አማካኝነት የሚከሰቱት ድርቅ እና የዛፎች አተነፋፈስ ለውጥ የዛፎቹን ዕድገት ሊገታ ይችላል፡፡
ሆኖም መንገዶች አልጋ በአልጋ አይሆኑም፡፡ ወደፊት እንደሚያጋጥሚ ከሚጠበቁ ችግሮች ውስጥ አንዱ የዋጋው ጉዳይ ነው፡፡ ዛፎችን በዚህ መጠን መትከል በትንሹ 300 ቢሊዮን ዶላርን ይጠይቃል፤ ምንም እንኳን እንደቡድኑ ግምት ከሌሎች የካርበን መምጠጫ መንገዶች አንፃር ርካሽ እንደሆነ ቢነገርም፡፡
ታድያ እርስዎስ ስንት ዛፎችን በዚህ ክረምት ስንት ዛፎችን ተክለዋል፤ ስንረትስ ለመትከል ዕቅድ ይዘዋል፡፡
ምንጭ፡ Scientific American
ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ
=================
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት በሥሩ በሚገኙት ሦስት ማዕከላት ላሉ የምርምር ዳይሬክቶሬቶች ከዚህ ቀጥሎ በተዘረዘሩት የስራ መስኮች ላይ ባለሙያዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን የሚያሟሉ ባለሙያዎች እንዲያመለክቱ ይጋብዛል፡፡
ማሳሰቢያ፡-
• ተወዳዳሪዎች ማሟላት ያለባቸው፡-
• ለሚወዳደሩበት የሥራ መደብ ማመልከቻ/Application Letter/፣ካሪኩለምቪቴ(CV)፣ የተሟላ የትምህርትና የሥራ ልምድ የThesis/Dissertation እና የሌሎች ሕትመቶች Abstract፣ አያይዘው መላክ ይኖርባቸዋል፤ በተጨማሪም ስልክ ቁጥር እና ኢሜይል በማመልከቻቸው ላይ መግለጽ ይኖርበታል፡፡
• የምዝገባ ሁኔታ በOnline http://www.techin.gov.et/am/web/sticsite/techin12
ብቻ ሲሆን አስፈላጊ የሆኑ ሰነዶችን በኢሜል Vacancy@techin.gov.et አያይዘው መላክ ይኖርባቸዋል፤
• ሴት ተወዳዳሪዎች እንዲያመለክቱ ይበረታታሉ፤
• ለፈተና የሚቀርቡትን ተወዳዳሪዎች በአድራሻቸው የምናሳውቅ መሆኑን እንገልጻለን::
• ተቋሙን የተመለከቱ ተጨማሪ መረጃ ቢያስፈልግ የፌሥቡክ አድራሻችን Technology and Innovation Institute, Ethiopia ወይም የኢንስቲትዩቱን ድረ-ገፅ
www.techin.gov.et በመጠቀም ማግኘት የሚቻል መሆኑን እንገልፃለን::
=================
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት በሥሩ በሚገኙት ሦስት ማዕከላት ላሉ የምርምር ዳይሬክቶሬቶች ከዚህ ቀጥሎ በተዘረዘሩት የስራ መስኮች ላይ ባለሙያዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን የሚያሟሉ ባለሙያዎች እንዲያመለክቱ ይጋብዛል፡፡
ማሳሰቢያ፡-
• ተወዳዳሪዎች ማሟላት ያለባቸው፡-
• ለሚወዳደሩበት የሥራ መደብ ማመልከቻ/Application Letter/፣ካሪኩለምቪቴ(CV)፣ የተሟላ የትምህርትና የሥራ ልምድ የThesis/Dissertation እና የሌሎች ሕትመቶች Abstract፣ አያይዘው መላክ ይኖርባቸዋል፤ በተጨማሪም ስልክ ቁጥር እና ኢሜይል በማመልከቻቸው ላይ መግለጽ ይኖርበታል፡፡
• የምዝገባ ሁኔታ በOnline http://www.techin.gov.et/am/web/sticsite/techin12
ብቻ ሲሆን አስፈላጊ የሆኑ ሰነዶችን በኢሜል Vacancy@techin.gov.et አያይዘው መላክ ይኖርባቸዋል፤
• ሴት ተወዳዳሪዎች እንዲያመለክቱ ይበረታታሉ፤
• ለፈተና የሚቀርቡትን ተወዳዳሪዎች በአድራሻቸው የምናሳውቅ መሆኑን እንገልጻለን::
• ተቋሙን የተመለከቱ ተጨማሪ መረጃ ቢያስፈልግ የፌሥቡክ አድራሻችን Technology and Innovation Institute, Ethiopia ወይም የኢንስቲትዩቱን ድረ-ገፅ
www.techin.gov.et በመጠቀም ማግኘት የሚቻል መሆኑን እንገልፃለን::