የዓለም ምርጥነት ክብርን ስለተቀናጀው ሲንጋፖራዊ ህንፃ
===================================
ዓለማችን አሁን ከደረሰችበት የብክለትም ሆነ የግንዛቤ ደረጃ ጋር በተገናኘ አረንጓዴ ልማት ወደ ቀዳሚ አጀንዳነት ተሸጋግል፡፡ ከዚህ ባህረ ሃሳብ ውስጥ ደግሞ የአረንጓዴ ህንፃዎች ግንባታ አንዱ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ከጥቂት ጊዜያት በፊት በተከናወነው የዓለም ኪነ ህንፃ ፌስቲቫል (WAF) ላይ የዓመቱ ምርጥ ህንፃ በመሰኘት የሲንጋፖሩ ካምፑንግ ማሸነፉ ይታወሳል፡፡ ይህ ህንፃ ሽልማቱን እንዲያገኝ ያስቻለው ታድያ ይህን የአረንጓዴነት ባህርይ ከሌሎች ማህበራዊ እሳቤዎች አስተሳስሮ በመሰራቱም ነው፡፡
በሰሜናዊው የከተማይቱ ክፍል የታነፀው ይህ ልዩ ልዩ አገልግሎቶችን ሰጪ ህንፃ ከአንድ ሄክታር ባነሰ መሬት ላይ የቆመ ነው፡፡ በውስጡም ክፍት የህዝብ ቦታ፣ የህዝብ ፓርክ እና የህክምና ዓገልግሎት መስጫን ከመኖሪያ ቤቶች አዋህዶ ይዟል፡፡ የህንፃው ዲዛይን በኪነ-ህንፃው አርቃቂዎች ዘንድ “club sandwich” ተብሎ የሚጠራ ሲሆን የተለያዩ አገልግሎቶችን በተለያዩ ወለሎች ላይ ይሰጣል፡፡ ህንፃው በዓጠቃላይ የታች፣ መካከለኛ እና የላይኛው በተባሉ ሶስት ክፍሎች የተከፋፈለ ሲሆን ባለ አስራ አንድ ወለል እና 104 አፓርታማዎችንም አቅፎ ያዘ ነው፡፡ የታችኛው ክፍል ለህዝብ ክፍት የተደረጉ መናፈሻ፣ ቴራሶችን እንዲሁም የመመገቢያ ስፍራዎችን ይዟል፡፡
የካምፑንግ ህንፃ በሃገሪቱን ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሰውን የእርጅና ጉዳይ ከግምት ውስጥ ማስገባቱ በታላላቅ የኪነ-ህንፃ ባለሙያዎች ዘንድ አድናቆትን ገዝቶለታል፡፡ ዕድሜው እየገፋ የመጣውን የሃገሪቱን ነዋሪ አካታች በሆነ መልኩ መገንባት እንደሚቻል ለማሳየት የታነፀ ሰርቶ ማሳያ መሆኑ ደግሞ ገና የአግራሞች መጀመሪያ እንጂ መቋጫ እንዳይሆን ያደርገዋል፡፡ መሰል ዘጠኝ የቤት ግንባታዎችን ለመስራትም የሃገሪቱ መንግስት እየተንቀሳቀሰ ነውና፡፡
ሐገርም ከተማም የሆነችው ሲንጋፖር በእርግጥ በግንባታ ጥበብ ፈር ቀዳጅ የሆኑ ህንፃዎችን ገንብታ ለአድናቆት እና ዓለም አቀፍ ዕውቅና ስታበቃ ይህ የመጀመሪያዋ አይደለም፡፡ ከዚህ አስቀድሞ ለሁለት ጊዜ ያህል ህንፃዎቿ በተመሳሳይ ሁኔታ ለሽልማት በቅተውላታል፡፡ ሆኖም እዛው ሃገሪቱ ላይ መሰረቱን ባደረገ ተቋም ዲዛይን ተደርጎ ለዚህ ክብር ሲበቃ ግን የመጀመሪያው ያደርገዋል፡፡
ምንጭ፡ CNN style
===================================
ዓለማችን አሁን ከደረሰችበት የብክለትም ሆነ የግንዛቤ ደረጃ ጋር በተገናኘ አረንጓዴ ልማት ወደ ቀዳሚ አጀንዳነት ተሸጋግል፡፡ ከዚህ ባህረ ሃሳብ ውስጥ ደግሞ የአረንጓዴ ህንፃዎች ግንባታ አንዱ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ከጥቂት ጊዜያት በፊት በተከናወነው የዓለም ኪነ ህንፃ ፌስቲቫል (WAF) ላይ የዓመቱ ምርጥ ህንፃ በመሰኘት የሲንጋፖሩ ካምፑንግ ማሸነፉ ይታወሳል፡፡ ይህ ህንፃ ሽልማቱን እንዲያገኝ ያስቻለው ታድያ ይህን የአረንጓዴነት ባህርይ ከሌሎች ማህበራዊ እሳቤዎች አስተሳስሮ በመሰራቱም ነው፡፡
በሰሜናዊው የከተማይቱ ክፍል የታነፀው ይህ ልዩ ልዩ አገልግሎቶችን ሰጪ ህንፃ ከአንድ ሄክታር ባነሰ መሬት ላይ የቆመ ነው፡፡ በውስጡም ክፍት የህዝብ ቦታ፣ የህዝብ ፓርክ እና የህክምና ዓገልግሎት መስጫን ከመኖሪያ ቤቶች አዋህዶ ይዟል፡፡ የህንፃው ዲዛይን በኪነ-ህንፃው አርቃቂዎች ዘንድ “club sandwich” ተብሎ የሚጠራ ሲሆን የተለያዩ አገልግሎቶችን በተለያዩ ወለሎች ላይ ይሰጣል፡፡ ህንፃው በዓጠቃላይ የታች፣ መካከለኛ እና የላይኛው በተባሉ ሶስት ክፍሎች የተከፋፈለ ሲሆን ባለ አስራ አንድ ወለል እና 104 አፓርታማዎችንም አቅፎ ያዘ ነው፡፡ የታችኛው ክፍል ለህዝብ ክፍት የተደረጉ መናፈሻ፣ ቴራሶችን እንዲሁም የመመገቢያ ስፍራዎችን ይዟል፡፡
የካምፑንግ ህንፃ በሃገሪቱን ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሰውን የእርጅና ጉዳይ ከግምት ውስጥ ማስገባቱ በታላላቅ የኪነ-ህንፃ ባለሙያዎች ዘንድ አድናቆትን ገዝቶለታል፡፡ ዕድሜው እየገፋ የመጣውን የሃገሪቱን ነዋሪ አካታች በሆነ መልኩ መገንባት እንደሚቻል ለማሳየት የታነፀ ሰርቶ ማሳያ መሆኑ ደግሞ ገና የአግራሞች መጀመሪያ እንጂ መቋጫ እንዳይሆን ያደርገዋል፡፡ መሰል ዘጠኝ የቤት ግንባታዎችን ለመስራትም የሃገሪቱ መንግስት እየተንቀሳቀሰ ነውና፡፡
ሐገርም ከተማም የሆነችው ሲንጋፖር በእርግጥ በግንባታ ጥበብ ፈር ቀዳጅ የሆኑ ህንፃዎችን ገንብታ ለአድናቆት እና ዓለም አቀፍ ዕውቅና ስታበቃ ይህ የመጀመሪያዋ አይደለም፡፡ ከዚህ አስቀድሞ ለሁለት ጊዜ ያህል ህንፃዎቿ በተመሳሳይ ሁኔታ ለሽልማት በቅተውላታል፡፡ ሆኖም እዛው ሃገሪቱ ላይ መሰረቱን ባደረገ ተቋም ዲዛይን ተደርጎ ለዚህ ክብር ሲበቃ ግን የመጀመሪያው ያደርገዋል፡፡
ምንጭ፡ CNN style
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት የሳይንስና ቴክኖሎጂ አመላካች ጥናቶችን ሊያከናውን ነው ====================================
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ሐገራዊ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሁኔታ-አመላካች የሆኑ የኢኖቬሽን ዳሰሳ እንዲሁም የማህበረሰቡን የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ግንዛቤ ዳሰሳ ጥናት ከመጋቢት 23 ጀምሮ ለሁለት ተከታታይ ወራት በመላው ሐገሪቱ በሚገኙ 408 ቀበሌዎች ይከናወናል፡፡
የኢኖቬሽን ዳሰሳ ጥናት፤ በሃገሪቱ በሚገኙ የንግድ ተቋማት የኢኖቬሽን ተግባራትን የሚዳስስ ሲሆን ጥናቱ ሲጠናቀቅ ለመንግስት አካላት፣ ፖሊሲ አውጪዎች እንዲሁም ለከፍተኛ የትምህርት እና የምርምር ተቋማት ግብዓት እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡
የማህበረሰቡን የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ግንዛቤ ላይ ትኩረት ተደርጎ የሚሰራው ጥናት ማህበረሰቡ በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ዙሪያ ያለውን ዕውቀት፣ ዝንባሌ፣ ፍላጎት እንዲሁም አመለካከት በመዳሰስ በሐገራችን ያለውን የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ ደረጃ ያመላክታል፡፡
ጥናቶቹ ለሐገሪቱ የውጪ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ዕድገት፤ በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ ሰጪነት ላይ የላቀ አስተዋፅም ይኖረዋል ተብሎ ይታመናል፡፡
ኢኒስቲትዩቱ ህብረተሰቡ ይህን በመገንዘብ ወደ እነርሱ ለሚመጡ የጥናት ቡድኖች ተገቢውን ድጋፍ እና መረጃ በመስጠት ሐገራዊ ሃላፊነቱን እንዲወጣ በአክብሮት ጠይቋል፡፡
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ሐገራዊ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሁኔታ-አመላካች የሆኑ የኢኖቬሽን ዳሰሳ እንዲሁም የማህበረሰቡን የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ግንዛቤ ዳሰሳ ጥናት ከመጋቢት 23 ጀምሮ ለሁለት ተከታታይ ወራት በመላው ሐገሪቱ በሚገኙ 408 ቀበሌዎች ይከናወናል፡፡
የኢኖቬሽን ዳሰሳ ጥናት፤ በሃገሪቱ በሚገኙ የንግድ ተቋማት የኢኖቬሽን ተግባራትን የሚዳስስ ሲሆን ጥናቱ ሲጠናቀቅ ለመንግስት አካላት፣ ፖሊሲ አውጪዎች እንዲሁም ለከፍተኛ የትምህርት እና የምርምር ተቋማት ግብዓት እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡
የማህበረሰቡን የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ግንዛቤ ላይ ትኩረት ተደርጎ የሚሰራው ጥናት ማህበረሰቡ በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ዙሪያ ያለውን ዕውቀት፣ ዝንባሌ፣ ፍላጎት እንዲሁም አመለካከት በመዳሰስ በሐገራችን ያለውን የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ ደረጃ ያመላክታል፡፡
ጥናቶቹ ለሐገሪቱ የውጪ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ዕድገት፤ በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ ሰጪነት ላይ የላቀ አስተዋፅም ይኖረዋል ተብሎ ይታመናል፡፡
ኢኒስቲትዩቱ ህብረተሰቡ ይህን በመገንዘብ ወደ እነርሱ ለሚመጡ የጥናት ቡድኖች ተገቢውን ድጋፍ እና መረጃ በመስጠት ሐገራዊ ሃላፊነቱን እንዲወጣ በአክብሮት ጠይቋል፡፡
የመጀመሪያ ደረጃ ዕርዳታ፤ ለትራፊክ አደጋ
=-=-=-=-=-=-=-=-=-=-=-=-=-=-=
ሐገራችንን ጨምሮ በመላው ዓለም ሚሊዮኖች በየዓመቱ ህይታቸውን በትራፊክ አደጋ ያጣሉ፡፡ ለዚህ የአደጋው መከሰት ዋነኛው ምክንያት ቢሆነም ከአደጋው በኋላ ያለ የተጎጂዎች ዕርዳታ አሰጣጥም የራሱን ድርሻ ይወስዳል፡፡ ለዛሬ የትራፊክ ዓደጋ ለሚያጋጥማቸው ሁሉ እንዴት የመጀመሪያ ዕርዳታ መስጠት እንዳለብን እንይ፡፡
• የመጀመሪያ ዕርዳታ በመስጠረት ውስጥ ቀዳሚው እርምጃ ሊሆን የሚገባው እራስን ከተጨማሪ አደጋ መጠበቅ ነው፡፡ ወደ አደጋው ስፍራ ሲያመሩ በዙሪያዎ የሚንቀሳቀሱ መኪኖች አለመኖራቸውን ያረጋግጡ፡፡
• ከደረሱም በኋላ የነዳጅ መፍሰስና ሌሎች እሳት አደጋን ሊያስከትሉ የሚችሉ ሁኔታዎች ካሉ የመኪናውን ሞተር ያጥፉ፡፡
• በአጠገብዎ ሌሎች ሰዎች ካሉ ወደ አንቡላንስ እንዲደውሉልዎ ያድርጉ፡፡ ሆኖም ብቻዎን ከሆኑ ተጎጂው ለህልፈት ሊያበቁ ከሚችሉ ሁናቴዎች ካላቀቁ በኋላ ወደ አንቡላንስ ይደውሉ፡፡ በዚህ ሁኔታ ውስጥ በአደጋው የተሳተፉ መኪኖችን እና በውስጣቸው ያለውን ተጎጂ ሁኔታ በአፅንዖት ይገምግሙ፡፡
• ቀዳሚ ትኩረትዎን ድምፅ እያሰሙ ያልሆኑ ወይም እንቅስቃሴ የማያደርጉ ተጎጂዎች ላይ በማድረግ መተንፈስ አለመተንፈሳቸውን ምላሽ መስጠት አለመስጠታቸውን ያረጋግጡ፡፡
• እየተነፈሱ ሳለ እንቅስቃሴ ካላከናወኑ በእርጋታ በትክክል በሚተነፍሱበት አቀማመጥ ላይ ያድርገዋቸው፡፡ ታድያ ይህን ሲያደርጉ ተጎጂውን ለማዋራት መሞከርዎን እንዳያቋርጡ፡፡
• ሆኖም ተጎጂው አደጋ ውስጥ (የእሳት፣ ጎርፍ፣ ፍንዳታ…) ካልሆኑ በስተቀረ የህክምና ባለሙያ እስከሚደርስ ካሉበት ባያወጧቸው ይመረጣል፡፡ የግድ ከሆነ ግን እንደ ስልክ ያሉ መንገዶችን በመጠቀም ከህክምና ባለሙያዎች እርዳታ በማግኘት ጭምር ያውጧዋቸው፡፡
• የጀርባ አጥንት ላይ ጉዳት ሊደርስ ስለሚችል የተጎጂዎቹን አንገት አያንቀሳቅሱ፤ እየደማ ያለ የሰውነት አካል ካለም ጓንትን ተጠቅመው በጨርቅ የደም ፍሰቱን ማስቆም፡፡
• በቦታው ላይ ማንም ሰው እንዳያጨስና ለተጎጂዎቹም ምንም አይነት መጠጥም ሆነ ምግብ እንዳይሰጥ ያድርጉ፡፡
• ተጎጂው የሞተር ሳይክል አሽከርካሪ ከሆነና እራሱን ከሳተ ሂልሜታቸውን በጥንቃቄ ያውልቁት፡፡ ሆኖም እራሳቸውን ካልሳቱ የፊት መስታውቱን በመክፈት ብቻ እርዳታ ይስጧቸው፡፡
• ተጎጂው በመኪና ተገጭቶ የወደቀ እግረኛ ከሆነ ከሌሎች ጋር በመተባበርና የጀርባ አጥንቱን በማይጎዳ አኳሃን ቀጥ ብለው እንዲተኙ በማድረግ ምቹ የአተነፋፈስ ሁኔታን መፍጠር ይገባል፡፡ ተጎጂው በመኪና ተገጭተው አሊያም ከመኪና ውስጥ በግጭቱ ተወርውረው የወጡ ከሆኑና እራሳቸውን ካልሳቱ እንደነቁ እንዲቆዩ ያበረታቷቸው፤ ሙቀት ወዳለበት ስፍራም ይውሰዷቸው፡፡
• ይህን ሁሉ ከሲያደርጉ ቀድሞ ለመጥቀስ እንደተሞከረው በዙሪያዎያለን የትራፊክ እንቅቃሴ በማስቆም አሊያም የሚያስተናብር ግለሰብ በመሰየም እራስዎን እና ተጎጂን ከተጨማሪ አደጋ ይታደጉ፡፡
ሼር በማድረግ ሃላፊነትዎን ይወጡ
ምንጭ፡ First Aid For Life
=-=-=-=-=-=-=-=-=-=-=-=-=-=-=
ሐገራችንን ጨምሮ በመላው ዓለም ሚሊዮኖች በየዓመቱ ህይታቸውን በትራፊክ አደጋ ያጣሉ፡፡ ለዚህ የአደጋው መከሰት ዋነኛው ምክንያት ቢሆነም ከአደጋው በኋላ ያለ የተጎጂዎች ዕርዳታ አሰጣጥም የራሱን ድርሻ ይወስዳል፡፡ ለዛሬ የትራፊክ ዓደጋ ለሚያጋጥማቸው ሁሉ እንዴት የመጀመሪያ ዕርዳታ መስጠት እንዳለብን እንይ፡፡
• የመጀመሪያ ዕርዳታ በመስጠረት ውስጥ ቀዳሚው እርምጃ ሊሆን የሚገባው እራስን ከተጨማሪ አደጋ መጠበቅ ነው፡፡ ወደ አደጋው ስፍራ ሲያመሩ በዙሪያዎ የሚንቀሳቀሱ መኪኖች አለመኖራቸውን ያረጋግጡ፡፡
• ከደረሱም በኋላ የነዳጅ መፍሰስና ሌሎች እሳት አደጋን ሊያስከትሉ የሚችሉ ሁኔታዎች ካሉ የመኪናውን ሞተር ያጥፉ፡፡
• በአጠገብዎ ሌሎች ሰዎች ካሉ ወደ አንቡላንስ እንዲደውሉልዎ ያድርጉ፡፡ ሆኖም ብቻዎን ከሆኑ ተጎጂው ለህልፈት ሊያበቁ ከሚችሉ ሁናቴዎች ካላቀቁ በኋላ ወደ አንቡላንስ ይደውሉ፡፡ በዚህ ሁኔታ ውስጥ በአደጋው የተሳተፉ መኪኖችን እና በውስጣቸው ያለውን ተጎጂ ሁኔታ በአፅንዖት ይገምግሙ፡፡
• ቀዳሚ ትኩረትዎን ድምፅ እያሰሙ ያልሆኑ ወይም እንቅስቃሴ የማያደርጉ ተጎጂዎች ላይ በማድረግ መተንፈስ አለመተንፈሳቸውን ምላሽ መስጠት አለመስጠታቸውን ያረጋግጡ፡፡
• እየተነፈሱ ሳለ እንቅስቃሴ ካላከናወኑ በእርጋታ በትክክል በሚተነፍሱበት አቀማመጥ ላይ ያድርገዋቸው፡፡ ታድያ ይህን ሲያደርጉ ተጎጂውን ለማዋራት መሞከርዎን እንዳያቋርጡ፡፡
• ሆኖም ተጎጂው አደጋ ውስጥ (የእሳት፣ ጎርፍ፣ ፍንዳታ…) ካልሆኑ በስተቀረ የህክምና ባለሙያ እስከሚደርስ ካሉበት ባያወጧቸው ይመረጣል፡፡ የግድ ከሆነ ግን እንደ ስልክ ያሉ መንገዶችን በመጠቀም ከህክምና ባለሙያዎች እርዳታ በማግኘት ጭምር ያውጧዋቸው፡፡
• የጀርባ አጥንት ላይ ጉዳት ሊደርስ ስለሚችል የተጎጂዎቹን አንገት አያንቀሳቅሱ፤ እየደማ ያለ የሰውነት አካል ካለም ጓንትን ተጠቅመው በጨርቅ የደም ፍሰቱን ማስቆም፡፡
• በቦታው ላይ ማንም ሰው እንዳያጨስና ለተጎጂዎቹም ምንም አይነት መጠጥም ሆነ ምግብ እንዳይሰጥ ያድርጉ፡፡
• ተጎጂው የሞተር ሳይክል አሽከርካሪ ከሆነና እራሱን ከሳተ ሂልሜታቸውን በጥንቃቄ ያውልቁት፡፡ ሆኖም እራሳቸውን ካልሳቱ የፊት መስታውቱን በመክፈት ብቻ እርዳታ ይስጧቸው፡፡
• ተጎጂው በመኪና ተገጭቶ የወደቀ እግረኛ ከሆነ ከሌሎች ጋር በመተባበርና የጀርባ አጥንቱን በማይጎዳ አኳሃን ቀጥ ብለው እንዲተኙ በማድረግ ምቹ የአተነፋፈስ ሁኔታን መፍጠር ይገባል፡፡ ተጎጂው በመኪና ተገጭተው አሊያም ከመኪና ውስጥ በግጭቱ ተወርውረው የወጡ ከሆኑና እራሳቸውን ካልሳቱ እንደነቁ እንዲቆዩ ያበረታቷቸው፤ ሙቀት ወዳለበት ስፍራም ይውሰዷቸው፡፡
• ይህን ሁሉ ከሲያደርጉ ቀድሞ ለመጥቀስ እንደተሞከረው በዙሪያዎያለን የትራፊክ እንቅቃሴ በማስቆም አሊያም የሚያስተናብር ግለሰብ በመሰየም እራስዎን እና ተጎጂን ከተጨማሪ አደጋ ይታደጉ፡፡
ሼር በማድረግ ሃላፊነትዎን ይወጡ
ምንጭ፡ First Aid For Life
በዓይነቱ ልዩ የሆነው አውሮፕላን
=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=
ጀማሪ የቴክኖሎጂ ተቋም የሆነው ፋራዳየር ኤሮስፔስ በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን ባለ አስራ ስምንት መቀመጫ የባዮኤሌክትሪክ ሃይብሪድ (ቅልቅል) አውሮፕላን ዲዛይኑን ይፋ አድርጓል፡፡ ይህ አውሮፕላኑንም ባዮ ኤሌክትሪክ ሃይብሪድ ኤርክራፍት (BEHA) ሲል ሰይሞታል፡፡ ሞዴሉም ኤም 1 ኤች ሲባል ሶስት ባለ ሳጥን ቅርፅ ክንፍ ይኖረዋል፡፡
ኤም 1 ኤች በሚነሳበት እና በሚያርፍበት ወቅት የኤሌክትሪክ ሞተሩን ይጠቀማል፡፡ ይህም የተለምዶዎቹ የጀት አውሮፕላኖች ከሚያወጡት 140 ዴሲ ቤል በእጅጉ ያነሰ የ60 ዴሲ ቤል ድምፅ እንዲያወጣ ያደርገዋል፡፡ አውሮፕላኑ እንዲነሳና እንዲያርፍ የሚያስችለውን ሞተር ቻርጅ ለመሙላት እንዲሁም እንዲበር ያደርገው ዘንድ 1,600 የፈረስ ጉልበት ያለው የቱርቦፕሮፕ ሞተር ይገጠምለታል፡፡ እንደ ተቋሙ ገለፃ ከሆነ ከተለምዶው አውሮፕላን ያነሰ የመንደርደሪያ ቦታንም ይፈልጋል (ሶስት መቶ ሜትር ብቻ)፡፡ ይህ እንዲሆን ያስቻሉት በተቃረነ አቅጣጫ የሚዞሩ ሽክርክሮሾቹ በሚያመነጩት የቬክትረም ትረስት፣ የክንፎቹ ዲዛይን እና በተሰራበረት የካርበን ንጥረ-ነገሮች ሳቢያ አውሮፕላኑ የተላበሰው ቀላል ክብደት አማካኝነት ነው፡፡ በተጨሪም አውሮፕላኑ በሰዓት እስከ 370 ኪ.ሜ ድረስ የመክነፍ ብቃት እንደሚኖረው ታውቋል፡፡
በዚህ ስራ ላይ የስዋንሲዩኒቨርሲቲን በአጋርነት ያቀፈው ይህ ተቋም አውሮፕላኖቹን በ2025 ወደ አገልግሎት እንደሚያስገባ ገልጿል (አውሮፕላኖቹን አነስተኛ የአየር መንገዶች እንደሚሸምቱ በመጠበቅ መሆኑ ነው)፡፡ ከዚህ በተጓዳኝ አውሮፕላኑ የሚበረው የባዮፊውልን በመጠቀም መሆኑና የኤሌክትሪክ ሞተሩን ለማኮብኮብ መገልገሉ ለከባቢ አየር ተስማሚ ብሎም ወጪ ቆጣቢ አማራጭ እንደሚያደርገው ተነግሮለታል፡፡ በሚያጓጉዘው ጭነት ረገድም አውሮፕላኑ ከተሳፋሪዎች ጫኝ አውሮፕላንነት ወደ ዕቃ ጫኝ አውሮፕላንነት ለመለወጥ አስራ አምስት ደቂቃዎችን ብቻ መውሰዱ ልዩ ያደርገዋል፡፡
ምንጭ፡ Techxplore
=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=
ጀማሪ የቴክኖሎጂ ተቋም የሆነው ፋራዳየር ኤሮስፔስ በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን ባለ አስራ ስምንት መቀመጫ የባዮኤሌክትሪክ ሃይብሪድ (ቅልቅል) አውሮፕላን ዲዛይኑን ይፋ አድርጓል፡፡ ይህ አውሮፕላኑንም ባዮ ኤሌክትሪክ ሃይብሪድ ኤርክራፍት (BEHA) ሲል ሰይሞታል፡፡ ሞዴሉም ኤም 1 ኤች ሲባል ሶስት ባለ ሳጥን ቅርፅ ክንፍ ይኖረዋል፡፡
ኤም 1 ኤች በሚነሳበት እና በሚያርፍበት ወቅት የኤሌክትሪክ ሞተሩን ይጠቀማል፡፡ ይህም የተለምዶዎቹ የጀት አውሮፕላኖች ከሚያወጡት 140 ዴሲ ቤል በእጅጉ ያነሰ የ60 ዴሲ ቤል ድምፅ እንዲያወጣ ያደርገዋል፡፡ አውሮፕላኑ እንዲነሳና እንዲያርፍ የሚያስችለውን ሞተር ቻርጅ ለመሙላት እንዲሁም እንዲበር ያደርገው ዘንድ 1,600 የፈረስ ጉልበት ያለው የቱርቦፕሮፕ ሞተር ይገጠምለታል፡፡ እንደ ተቋሙ ገለፃ ከሆነ ከተለምዶው አውሮፕላን ያነሰ የመንደርደሪያ ቦታንም ይፈልጋል (ሶስት መቶ ሜትር ብቻ)፡፡ ይህ እንዲሆን ያስቻሉት በተቃረነ አቅጣጫ የሚዞሩ ሽክርክሮሾቹ በሚያመነጩት የቬክትረም ትረስት፣ የክንፎቹ ዲዛይን እና በተሰራበረት የካርበን ንጥረ-ነገሮች ሳቢያ አውሮፕላኑ የተላበሰው ቀላል ክብደት አማካኝነት ነው፡፡ በተጨሪም አውሮፕላኑ በሰዓት እስከ 370 ኪ.ሜ ድረስ የመክነፍ ብቃት እንደሚኖረው ታውቋል፡፡
በዚህ ስራ ላይ የስዋንሲዩኒቨርሲቲን በአጋርነት ያቀፈው ይህ ተቋም አውሮፕላኖቹን በ2025 ወደ አገልግሎት እንደሚያስገባ ገልጿል (አውሮፕላኖቹን አነስተኛ የአየር መንገዶች እንደሚሸምቱ በመጠበቅ መሆኑ ነው)፡፡ ከዚህ በተጓዳኝ አውሮፕላኑ የሚበረው የባዮፊውልን በመጠቀም መሆኑና የኤሌክትሪክ ሞተሩን ለማኮብኮብ መገልገሉ ለከባቢ አየር ተስማሚ ብሎም ወጪ ቆጣቢ አማራጭ እንደሚያደርገው ተነግሮለታል፡፡ በሚያጓጉዘው ጭነት ረገድም አውሮፕላኑ ከተሳፋሪዎች ጫኝ አውሮፕላንነት ወደ ዕቃ ጫኝ አውሮፕላንነት ለመለወጥ አስራ አምስት ደቂቃዎችን ብቻ መውሰዱ ልዩ ያደርገዋል፡፡
ምንጭ፡ Techxplore
አማዞን የፈጣን በይነ-መረብ አቅራቢ ሳተላይቶችን ሊያመጥቅ ነው
===============================================
ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በሳተላይት ላይ የተመሰረተ የበይነ-መረብ (Internet) ዓገልግሎትን ለማቅረብ ታላላቅ የቴክኖሎጂ ተቋማት በመሽቀዳደም ላይ ናቸው፡፡ በትናንትናው ዕለትም አማዞን የ3,236 ሳተላይቶች እርስበእርስ ግንኙነትን በመዘርጋት ፈጣን የበይነ-መረብ አገልግሎትን ለመላው ዓለም ለማዳረስ እንደሚሰራ በመግለፅ ሩጫውን ተቀላቅሏል፡፡ ፕሮጀክት ኩኢፐር የሚል ስያሜ የተሰጠው ይህ ስራ ሳተላይቶቹን በዝቅተኛው የምድራችን ምህዋር በማስፈር አነስተኛ የመዘግየት መጠን ያለውን ፈጣን የበይነ-መረብ ዓገልግሎት በይነ-መረብ በበቂ ሁኔታ አሊያም ሙሉ ለሙሉ ባልተዳረሰባቸው የዓለማችን ስፍራዎች ላይ ለማዳረስ እንደሚሰራ አማዞን ገልጿል፡፡
ታላላቆቹ የቴክኖሎጂ ተቋማትን ትኩረት እየሳበ በመጣው በዚህ ዘርፍ ላይ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች የበይነ-መረብ አገልግሎት ላልደረሳቸው 3.8 ቢሊዮን የዓለማችን ነዋሪዎች ከአገልግሎቱ እንደሚያስተዋውቁ ሲጠበቅ ለኩባንያዎቹም ጠቀም ያለ ትርፍን እንደሚያስገኙ ይነገርላቸዋል፡፡ በዚህ ረገድ ከወራት በፊትም ዋን ዌብ የተሰኘ ኩባንያ መሰል ፈጣን የበይነ-መረብ አገልግሎትን አቅራቢ የሳተላይቶች ትስስርን ለመመስረት ይረዳው ዘንድ የመጀመሪያ ሳተላይቱን ማምጠቁ ይታወሳል፡፡ ሌላኛው ስመ ጥር የህዋ ምርምር እና ቴክኖሎጂ ተቋም ስፔስ ኤክስም ለተቋማቱ ሳተላይቶችን የማምጠቅ ስራን ከመስራቱም በተጓዳኝ የራሱን መሰል የሳተላይት ትስስር ለመገንባት ሂደት ላይ ይገኛል፡፡ እስካሁንም ሁለት ሰርቶ ማሳያ ሳተላይቶችን ማምጠቅ ችሏል፡፡ ፌስቡከልም ቢሆን ከዚህ አልቦዘነም፤ ከስፔስ ኤክሱ የስታርሊንክ ሳተላይት አስር እጥፍ መረጃን የማስተላለፍ ፍጥነት ያለውን አተና የተሰኘ ሳተላይቱን ለዚህ ተግባር በማሰብ እያበለፀገ ይገኛል፡፡
ይህች የአማዞኗ ኩኢፐር ሳተላይት የንድፍ፣ ማበልፀግ እና ወደ ህዋ የማጓጓዝ ስራዋ በሌላኛው የጄፍ ቤዞስ ኩባንያ ብሉ ኦሪጅን አማካኝነት የሚከወን ይሆናል፡፡ ብሉ ኦሪጅን ከዚህ በተጓዳኝ ቴሳት ከተባለ ተመሳሳይ የበይነ መረብ አገልግሎትን ለማቅረብ ከሚሰራ ተቋም ጋር ሳተላይቶችን የማምጠቅ ውል አስሯል፡፡
ምንጭ፡ Tech Crunch
===============================================
ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በሳተላይት ላይ የተመሰረተ የበይነ-መረብ (Internet) ዓገልግሎትን ለማቅረብ ታላላቅ የቴክኖሎጂ ተቋማት በመሽቀዳደም ላይ ናቸው፡፡ በትናንትናው ዕለትም አማዞን የ3,236 ሳተላይቶች እርስበእርስ ግንኙነትን በመዘርጋት ፈጣን የበይነ-መረብ አገልግሎትን ለመላው ዓለም ለማዳረስ እንደሚሰራ በመግለፅ ሩጫውን ተቀላቅሏል፡፡ ፕሮጀክት ኩኢፐር የሚል ስያሜ የተሰጠው ይህ ስራ ሳተላይቶቹን በዝቅተኛው የምድራችን ምህዋር በማስፈር አነስተኛ የመዘግየት መጠን ያለውን ፈጣን የበይነ-መረብ ዓገልግሎት በይነ-መረብ በበቂ ሁኔታ አሊያም ሙሉ ለሙሉ ባልተዳረሰባቸው የዓለማችን ስፍራዎች ላይ ለማዳረስ እንደሚሰራ አማዞን ገልጿል፡፡
ታላላቆቹ የቴክኖሎጂ ተቋማትን ትኩረት እየሳበ በመጣው በዚህ ዘርፍ ላይ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች የበይነ-መረብ አገልግሎት ላልደረሳቸው 3.8 ቢሊዮን የዓለማችን ነዋሪዎች ከአገልግሎቱ እንደሚያስተዋውቁ ሲጠበቅ ለኩባንያዎቹም ጠቀም ያለ ትርፍን እንደሚያስገኙ ይነገርላቸዋል፡፡ በዚህ ረገድ ከወራት በፊትም ዋን ዌብ የተሰኘ ኩባንያ መሰል ፈጣን የበይነ-መረብ አገልግሎትን አቅራቢ የሳተላይቶች ትስስርን ለመመስረት ይረዳው ዘንድ የመጀመሪያ ሳተላይቱን ማምጠቁ ይታወሳል፡፡ ሌላኛው ስመ ጥር የህዋ ምርምር እና ቴክኖሎጂ ተቋም ስፔስ ኤክስም ለተቋማቱ ሳተላይቶችን የማምጠቅ ስራን ከመስራቱም በተጓዳኝ የራሱን መሰል የሳተላይት ትስስር ለመገንባት ሂደት ላይ ይገኛል፡፡ እስካሁንም ሁለት ሰርቶ ማሳያ ሳተላይቶችን ማምጠቅ ችሏል፡፡ ፌስቡከልም ቢሆን ከዚህ አልቦዘነም፤ ከስፔስ ኤክሱ የስታርሊንክ ሳተላይት አስር እጥፍ መረጃን የማስተላለፍ ፍጥነት ያለውን አተና የተሰኘ ሳተላይቱን ለዚህ ተግባር በማሰብ እያበለፀገ ይገኛል፡፡
ይህች የአማዞኗ ኩኢፐር ሳተላይት የንድፍ፣ ማበልፀግ እና ወደ ህዋ የማጓጓዝ ስራዋ በሌላኛው የጄፍ ቤዞስ ኩባንያ ብሉ ኦሪጅን አማካኝነት የሚከወን ይሆናል፡፡ ብሉ ኦሪጅን ከዚህ በተጓዳኝ ቴሳት ከተባለ ተመሳሳይ የበይነ መረብ አገልግሎትን ለማቅረብ ከሚሰራ ተቋም ጋር ሳተላይቶችን የማምጠቅ ውል አስሯል፡፡
ምንጭ፡ Tech Crunch
የአዎሮፓ ፓተንት ጽ/ቤት ልዕካን የቴክኖሎጂና ኢኖቬስን ኢንስቲትውትን ጎበኙ
በአውሮፓ ፓተንት ጽ/ቤት የዓለም አቀፍ ግንኝነት ኃላፊ ፈራንሳ ሃነርት ሚያዝያ 1/2011 ዓ.ም የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስቲትውትን ጎበኙ፡፡ በጉብኝታቸውም ወቅት የኢኒስቲትውቱ ዋና ዳሬክተር አቶ ሳንዱካን ደበበ ስለተቋሙ ሁለተናዊ አቋም ገለፃ ያደረጉላቻው ሲሆን ልኡካን ቡድኑም በሚስተር ኒኮላስ ኮርኒዠ አማካኝነት ስለ አውሮፓ ፓተንት ጽ/ቤት ገለፃ አድርጓል፡፡
በውይይቱ ወቅት ሁለቱም ተቋማት በትብብር ሊሰሩባቸው የሚችሉባቸውን መስኮች የለዩ ሲሆን፡- በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ የኢኖቬሽንና ክሬቲቪቲን ለማህበረሰብ በማስተዋወቅ፣ በስልጠናና ሰው ሀይል ልማት እንዲሁም በፓተንት መረጃዎች ላይ በትብብር ለመስራት ዕቅድ ተቀምጧል፡፡
በማጠቃለያውም የልዑካን ቡድኑ መሪ ሚስተር ፈራንሳ ሃነርት ከኢንስቲትውቱ ጋር በቀጣይ በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ዙሪያ ድጋፍ በማድረግ ግንኙነታቸውን እንደሚያጠናክሩ ገልፀዋል፡፡
በአውሮፓ ፓተንት ጽ/ቤት የዓለም አቀፍ ግንኝነት ኃላፊ ፈራንሳ ሃነርት ሚያዝያ 1/2011 ዓ.ም የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስቲትውትን ጎበኙ፡፡ በጉብኝታቸውም ወቅት የኢኒስቲትውቱ ዋና ዳሬክተር አቶ ሳንዱካን ደበበ ስለተቋሙ ሁለተናዊ አቋም ገለፃ ያደረጉላቻው ሲሆን ልኡካን ቡድኑም በሚስተር ኒኮላስ ኮርኒዠ አማካኝነት ስለ አውሮፓ ፓተንት ጽ/ቤት ገለፃ አድርጓል፡፡
በውይይቱ ወቅት ሁለቱም ተቋማት በትብብር ሊሰሩባቸው የሚችሉባቸውን መስኮች የለዩ ሲሆን፡- በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ የኢኖቬሽንና ክሬቲቪቲን ለማህበረሰብ በማስተዋወቅ፣ በስልጠናና ሰው ሀይል ልማት እንዲሁም በፓተንት መረጃዎች ላይ በትብብር ለመስራት ዕቅድ ተቀምጧል፡፡
በማጠቃለያውም የልዑካን ቡድኑ መሪ ሚስተር ፈራንሳ ሃነርት ከኢንስቲትውቱ ጋር በቀጣይ በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ዙሪያ ድጋፍ በማድረግ ግንኙነታቸውን እንደሚያጠናክሩ ገልፀዋል፡፡
የመጀመሪያው ብላክ ሆል ምስል እንዲገኝ ያስቻለችው ዕንስት
ከሰሞኑን በሳይንሱ ዓለም ከናኙት ወሬዎች መካከል ብላክ ሆልን ለመጀመሪያ ጊዜ በምስል ማየት መቻሉ ቀዳሚው ነው፡፡ ይህ ግኝት ከምዕተ ዓመቱ ምርጥ የሳይንስ ግኝቶች የተደመረውን ስራ ህልው እንዲሆን ያስቻለው የ29 አመቷ ዕንስት ተመራማሪ ዶ.ር ካቲ ቦውማን ባስቀመጠችው ቀመር አማካኝነት ነው፡፡ ካለእርሷ ስራ ቢሆን ኖሮማ አንድን ብላክ ሆል ለማየት አስር ሺህ ኪ.ሜ የሚሰፋ ቴሌስኮፕ ባስፈለገን ነበር፡፡ በተግባር ደረጃ ካየነው ይህ የማይቻል ተግባር ሆኖ ነወ፡፡ ከዚህ ይልቅ በኬቲ ቀመር መሰረት በምድር ላይ የሚገኙትን ቴሌስኮፖች አንድ ላይ በማጣመር 55 ሚሊዮን የብርሃን አመታት ርቆ የሚገኝ ብላክ ሆልን ምስል ማግኘት ተችሏል፡፡
ዶ.ር ካቲ CHIRP (Continuous High-resolution Image Reconstruction using Patch priors) ብላ የሰየመችው ይህ ቀመር በዓለም ዙሪያ በሚገኙት ስምንት ቴሌስኮፖች አማካኝነት በተነሱት ምስሎች መካከል የሚፈጠረውን ክፍተት መሙላት የሚያስችል ነው፡፡ ለስራውም በጠቅላላው ግማሽ ቶን የሚመዝኑ ሃርድ ድራይቮች ጥቅም ላይ ሲውሉ በእነርሱ አማካኝነትም 5 ፔታ ባይት የሚለካ ጥሬ ሃቅን ማሰባሰብ ተችሏል (ለአምስት ሺህ አመት ሳያቋርጥ የሚዘፍን ሙዚቃን የሚስተካከል መረጃ መሆኑን ልብ ይሏል)፡፡
ምንጭ፡ Daily Mail
ከሰሞኑን በሳይንሱ ዓለም ከናኙት ወሬዎች መካከል ብላክ ሆልን ለመጀመሪያ ጊዜ በምስል ማየት መቻሉ ቀዳሚው ነው፡፡ ይህ ግኝት ከምዕተ ዓመቱ ምርጥ የሳይንስ ግኝቶች የተደመረውን ስራ ህልው እንዲሆን ያስቻለው የ29 አመቷ ዕንስት ተመራማሪ ዶ.ር ካቲ ቦውማን ባስቀመጠችው ቀመር አማካኝነት ነው፡፡ ካለእርሷ ስራ ቢሆን ኖሮማ አንድን ብላክ ሆል ለማየት አስር ሺህ ኪ.ሜ የሚሰፋ ቴሌስኮፕ ባስፈለገን ነበር፡፡ በተግባር ደረጃ ካየነው ይህ የማይቻል ተግባር ሆኖ ነወ፡፡ ከዚህ ይልቅ በኬቲ ቀመር መሰረት በምድር ላይ የሚገኙትን ቴሌስኮፖች አንድ ላይ በማጣመር 55 ሚሊዮን የብርሃን አመታት ርቆ የሚገኝ ብላክ ሆልን ምስል ማግኘት ተችሏል፡፡
ዶ.ር ካቲ CHIRP (Continuous High-resolution Image Reconstruction using Patch priors) ብላ የሰየመችው ይህ ቀመር በዓለም ዙሪያ በሚገኙት ስምንት ቴሌስኮፖች አማካኝነት በተነሱት ምስሎች መካከል የሚፈጠረውን ክፍተት መሙላት የሚያስችል ነው፡፡ ለስራውም በጠቅላላው ግማሽ ቶን የሚመዝኑ ሃርድ ድራይቮች ጥቅም ላይ ሲውሉ በእነርሱ አማካኝነትም 5 ፔታ ባይት የሚለካ ጥሬ ሃቅን ማሰባሰብ ተችሏል (ለአምስት ሺህ አመት ሳያቋርጥ የሚዘፍን ሙዚቃን የሚስተካከል መረጃ መሆኑን ልብ ይሏል)፡፡
ምንጭ፡ Daily Mail
እጅግ ጠቃሚ የድረ-ገፅ ጥቆማ
****************************
ማናቸውንም ከትምህርት ጋር ተያያዥነት ያላቸውን ጉዳዮች ሲሹና ከዚያም አለፍ ሲል ለህይወቶ አዲስ መንገድና ክህሎት ለመማር ሲፈልጉ ልዩ ልዩ የኢንተርኔት ድረ-ገፆችን መጎብኘት እየተለመደ መጥቷል፡፡ በመሆኑም በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ላይ መሰልጠን ካስፈለጎት እና በተለይም አሁን ካለው የቴክኖሎጂ ዓለም ጋር ራሶን ይበልጥ ማጎዳኘት ከፈለጉ ከዚህ በታች የምትመለከቷቸው ልዩ ልዩ ድረ-ገፆች በእጅጉ ሊረዷችሁ ይችላሉና ይጎብኟቸው፡፡
ለሌሎች እንዲደርሳቸው ሼር ያድርጉ!!!
ነጻ የኦንላይን ትምህርቶችን ማግኛ (FREE ONLINE COURSES & CERTIFICATE)
• COURSERA
• MIT OPEB WARE
• UDACITY
• UDEMY
• EDX
ነፃ የስኮላርሺፕ እድሎች የሚሞክሩበት (FREE SCHOOLARSHIP FOR ETHIOPIAN STUDENT)
• ERASMUS MUNDUS (EUROPEAN COMMISSION)
• NUFFIC (HOLAND)
• EIFFEL (FRANCE)
• NEWZELAND DEVELOPMENT SCHOLARSHIP
• VLIROUS (BELGIUM)
• ITALIAN GOVERNMENT SCHOLARSHIP
የኮዲንግ ትምህርቶችን የሚያገኙበት (CODING SITES)
• THE ODIN PROJECT
• UPSKILL
• FREECODECAMP
• W3SCHOOLS
• TUTORIALSPOINT
• kHAN ACADEMY
• GA DASH
• SOLOLEARN
• CODE ACADEMY
• C4LEARNER
የሂሳብ ትምህርቶችን ማግኛ (MATHEMATHS
• https://amser.org
• https://www.brightstorm.com/math/
• https://www.doubledivision.org/
• http://www.mathtv.com
• http://mathforum.org
• http://www.aaamath.com/
ክራክ የተደረጉ መተግበሪያዎች የሚያገኙበት (Cracked software’s downloading sites)
• www.piratecity.net
• Igetintopc.com
• https://securityxploded.com/
• www.p30download.com
• www.downloadha.com
****************************
ማናቸውንም ከትምህርት ጋር ተያያዥነት ያላቸውን ጉዳዮች ሲሹና ከዚያም አለፍ ሲል ለህይወቶ አዲስ መንገድና ክህሎት ለመማር ሲፈልጉ ልዩ ልዩ የኢንተርኔት ድረ-ገፆችን መጎብኘት እየተለመደ መጥቷል፡፡ በመሆኑም በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ላይ መሰልጠን ካስፈለጎት እና በተለይም አሁን ካለው የቴክኖሎጂ ዓለም ጋር ራሶን ይበልጥ ማጎዳኘት ከፈለጉ ከዚህ በታች የምትመለከቷቸው ልዩ ልዩ ድረ-ገፆች በእጅጉ ሊረዷችሁ ይችላሉና ይጎብኟቸው፡፡
ለሌሎች እንዲደርሳቸው ሼር ያድርጉ!!!
ነጻ የኦንላይን ትምህርቶችን ማግኛ (FREE ONLINE COURSES & CERTIFICATE)
• COURSERA
• MIT OPEB WARE
• UDACITY
• UDEMY
• EDX
ነፃ የስኮላርሺፕ እድሎች የሚሞክሩበት (FREE SCHOOLARSHIP FOR ETHIOPIAN STUDENT)
• ERASMUS MUNDUS (EUROPEAN COMMISSION)
• NUFFIC (HOLAND)
• EIFFEL (FRANCE)
• NEWZELAND DEVELOPMENT SCHOLARSHIP
• VLIROUS (BELGIUM)
• ITALIAN GOVERNMENT SCHOLARSHIP
የኮዲንግ ትምህርቶችን የሚያገኙበት (CODING SITES)
• THE ODIN PROJECT
• UPSKILL
• FREECODECAMP
• W3SCHOOLS
• TUTORIALSPOINT
• kHAN ACADEMY
• GA DASH
• SOLOLEARN
• CODE ACADEMY
• C4LEARNER
የሂሳብ ትምህርቶችን ማግኛ (MATHEMATHS
• https://amser.org
• https://www.brightstorm.com/math/
• https://www.doubledivision.org/
• http://www.mathtv.com
• http://mathforum.org
• http://www.aaamath.com/
ክራክ የተደረጉ መተግበሪያዎች የሚያገኙበት (Cracked software’s downloading sites)
• www.piratecity.net
• Igetintopc.com
• https://securityxploded.com/
• www.p30download.com
• www.downloadha.com
የኤሌክትሮኒክስ ግብይት ስርዓትን ለማፋጠን በተዘጋጀ ረቂቅ አዋጅ ላይ ውይይት ተካሄደ
*************************
የኢትዮጵያን የንግድ ስርዓት፣ የታክስ አከፋፈል እና አጠቃላይ የክፍያ ስርዓት ወደ ኤሌክትሮኒክስ ለማሸጋገር በሚደረገው እንቅስቃሴ ላይ የህግ ማዕቀፍ የሚያበጅ ረቂቅ አዋጅ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ተዘጋጅቶ ወይይት ተካሄደበት፡፡ ለሁለተኛ ጊዜ በተዘጋጀው በዚህ የውይይት መድረክ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ.) ጨምሮ ጥሪ ተደረገላቸው የተለያዩ የመንግስት እና የግል ተቋማት ሃላፊዎች የተሳተፉ ሲሆን፤ በተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ላይም ሰፊ ውይይት ተደርጓል፡፡
በውይይቱ መነሻ ላይ የመግቢያ ንግግር ያደረጉት ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ.) ዓለማችን በዲጂታል ኢኮኖሚ ከሄደችበት ርቀት አኳያ ሃገራችን ወደ ኋላ የቀረች ቢሆንም፤ ባለው ሰፊ የሰው ሃይል በመጠቀም እና ከኋላ የመነሳት እድልን (late comer adventage) አንደመደላድል በመውሰድ ፈጣን ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ተናግረዋል፡፡
በተለይም ሚኒስተሩ እንደጠቀሱት በዓለማችን ከፍተኛ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ በሚደረግበት የአገልግሎት ዘርፍ ቴክኖሎጂን በማስተዋወቅ እና አውቀትን በመቀመር ወደ ዲጂታል ስርዓት መግባት ካልተቻለ ከሚያመጣው ጉዳት አንፃር፤ በኤሌክትሮኒክስ ትራንዛክሽን ላይ ያተኮረ አዋጅ መዘጋጀቱ ትልቅ መነሻ እንደሚሆን ጠቁመዋል፡፡
በመድረኩ ላይ እንደተገለፀው ረቂቅ አዋጁን ለማዘጋጀት የተለያዩ ሃገሮች ተሞክሮ እንደመነሻ ተወስዶ የተሰራ ሲሆን በተለይም የዓለም ባንክ ልዩ ቡድን ያቀረበው ሰፊ ግብዓት የረቂቅ አዋጁ ጠንካራ ጎን እንደነበር ተጠቅሷል፡፡ እንደ ውይይት መነሻ ዶክተር ማንደፍሮ የረቂቅ አዋጁን ይዘት በስድስት ምዕራፎች ከፋፍለው አቅርበዋል።
*************************
የኢትዮጵያን የንግድ ስርዓት፣ የታክስ አከፋፈል እና አጠቃላይ የክፍያ ስርዓት ወደ ኤሌክትሮኒክስ ለማሸጋገር በሚደረገው እንቅስቃሴ ላይ የህግ ማዕቀፍ የሚያበጅ ረቂቅ አዋጅ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ተዘጋጅቶ ወይይት ተካሄደበት፡፡ ለሁለተኛ ጊዜ በተዘጋጀው በዚህ የውይይት መድረክ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ.) ጨምሮ ጥሪ ተደረገላቸው የተለያዩ የመንግስት እና የግል ተቋማት ሃላፊዎች የተሳተፉ ሲሆን፤ በተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ላይም ሰፊ ውይይት ተደርጓል፡፡
በውይይቱ መነሻ ላይ የመግቢያ ንግግር ያደረጉት ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ.) ዓለማችን በዲጂታል ኢኮኖሚ ከሄደችበት ርቀት አኳያ ሃገራችን ወደ ኋላ የቀረች ቢሆንም፤ ባለው ሰፊ የሰው ሃይል በመጠቀም እና ከኋላ የመነሳት እድልን (late comer adventage) አንደመደላድል በመውሰድ ፈጣን ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ተናግረዋል፡፡
በተለይም ሚኒስተሩ እንደጠቀሱት በዓለማችን ከፍተኛ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ በሚደረግበት የአገልግሎት ዘርፍ ቴክኖሎጂን በማስተዋወቅ እና አውቀትን በመቀመር ወደ ዲጂታል ስርዓት መግባት ካልተቻለ ከሚያመጣው ጉዳት አንፃር፤ በኤሌክትሮኒክስ ትራንዛክሽን ላይ ያተኮረ አዋጅ መዘጋጀቱ ትልቅ መነሻ እንደሚሆን ጠቁመዋል፡፡
በመድረኩ ላይ እንደተገለፀው ረቂቅ አዋጁን ለማዘጋጀት የተለያዩ ሃገሮች ተሞክሮ እንደመነሻ ተወስዶ የተሰራ ሲሆን በተለይም የዓለም ባንክ ልዩ ቡድን ያቀረበው ሰፊ ግብዓት የረቂቅ አዋጁ ጠንካራ ጎን እንደነበር ተጠቅሷል፡፡ እንደ ውይይት መነሻ ዶክተር ማንደፍሮ የረቂቅ አዋጁን ይዘት በስድስት ምዕራፎች ከፋፍለው አቅርበዋል።