በሩሲያ ቅልጥ እሳተ ገሞራ የተገኘው አዲሱ ምስጢራዊ ማእድን
*********************
ተመራማሪዎች በሩሲያ ቅልጥ እሳተ ገሞራ አዲስ ማእድን ማግኘታቸው ተሰማ፡፡ እንደሚታወቀው በአለማችን አስጨናቂ ከሆኑና ብዙ ጥፋቶችን ከሚያስከትሉ ተፈጥሯዊ ክስተቶች መካከል እሳተ ገሞራ አንዱና ዋነናው ነው፡፡ ይሁን እንጂ ገሞራ ካለው ጉዳት በተቃራኒ የተፈጥሮ ምስጢራትን በመግለጥ በኩል የራሱ አስተዋጽኦ እንዳለው ተመራማሪዎች ይስማማሉ፡፡ ለዚህም ነው የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ ያጠፋልም ያለማልም የሚባለው፡፡
አዲስ በተሰራ ጥናት የሩሲያ ተመራማሪዎች በገሞራ ፍንዳታ ምክንያት የተፈጠረን አንድ አዲስና ያልተለመደ ማእድን ማግኘታቸውን አሳውቀዋል፡፡ ተመራማሪዎቹ ፔትሮቫይት ሲሉ የሰየሙት አስደናቂው ደማቅ ሰማያዊና አረንጓዴ ቀለም ያለው ጠጣር ንጥረ ነገር ከዚህ በፊት በሳይንስ ተመዝግበው ካሉት ማእድናት ሁሉ የተለየ እንደሆነ ተመስክሮለታል፡፡
ንጥረ ነገሩ የተገኘው በሩሲያ ሩቅ ምስራቅ በሚገኝ ካምቻትካ ከፍታ ቶልባቺክ በሚባል እሳተ ገሞራ ነው፡፡ ቶልባቺክ ገሞራ ከሺህ አመታት በላይ ታሪክ ያለው የገሞራ ፍንዳታ ሲሆን ሁለት በጣም የታወቁ ፍንዳታዎች አሉት፡፡ ከእነዚህም አንዱ ከ1975–1976 የተከሰተው ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ከ2012–2013 የተከሰተው ነው፡፡
በመጀመሪያው በነበረው ከፍተኛ ሀይል ያለው ፍንዳታ ብዛት ያላቸው የእሳት ፍንጥርጣሪዎች እና የትም ቦታ ታይተው የማይታወቁ ማእድናት ተገኝተዋል፡፡ በአጠቃላይ የቶለባቺክ ገሞራ 130 ዓይነት በዚህ አካባቢ ብቻ የሚገኙ ማእድናትን አስገኝቷል፡፡ ከእነዚህ ማእድናት የቅርብ ጊዜው ፔትሪቫይት ነው፡፡ ይህም ሰማያዊ ቀለም ያለው ባለ ድቦልቡል ቅርጽ ሰልፌት ማእድን ነው፡፡
በአዲሱ ማእድን የተገኘው የኮፐር ቅንጣት የልተለመደና በቀላሉ የማይገኝ ከ7 የኦክስጅን ቅንጣቶች ጋር የተጣመረ ነው፡፡ የዚህ አይነት ባህሪ የሚገኘው በውህዶች ብቻ እንደሆነ የSt Petersburg University የምርምሩ መሪ ተናግሯል፡፡ የፔተሮቫየት ሞሎኪዩላዊ ቀመሩ (molecular framework) ኦክስጅን፣ ሶዲየም፣ ሳልፈርና ኮፐር በተፈጥሮ አብረው የተሰሩ ናቸው፡፡
ምንጭ Science alert
*********************
ተመራማሪዎች በሩሲያ ቅልጥ እሳተ ገሞራ አዲስ ማእድን ማግኘታቸው ተሰማ፡፡ እንደሚታወቀው በአለማችን አስጨናቂ ከሆኑና ብዙ ጥፋቶችን ከሚያስከትሉ ተፈጥሯዊ ክስተቶች መካከል እሳተ ገሞራ አንዱና ዋነናው ነው፡፡ ይሁን እንጂ ገሞራ ካለው ጉዳት በተቃራኒ የተፈጥሮ ምስጢራትን በመግለጥ በኩል የራሱ አስተዋጽኦ እንዳለው ተመራማሪዎች ይስማማሉ፡፡ ለዚህም ነው የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ ያጠፋልም ያለማልም የሚባለው፡፡
አዲስ በተሰራ ጥናት የሩሲያ ተመራማሪዎች በገሞራ ፍንዳታ ምክንያት የተፈጠረን አንድ አዲስና ያልተለመደ ማእድን ማግኘታቸውን አሳውቀዋል፡፡ ተመራማሪዎቹ ፔትሮቫይት ሲሉ የሰየሙት አስደናቂው ደማቅ ሰማያዊና አረንጓዴ ቀለም ያለው ጠጣር ንጥረ ነገር ከዚህ በፊት በሳይንስ ተመዝግበው ካሉት ማእድናት ሁሉ የተለየ እንደሆነ ተመስክሮለታል፡፡
ንጥረ ነገሩ የተገኘው በሩሲያ ሩቅ ምስራቅ በሚገኝ ካምቻትካ ከፍታ ቶልባቺክ በሚባል እሳተ ገሞራ ነው፡፡ ቶልባቺክ ገሞራ ከሺህ አመታት በላይ ታሪክ ያለው የገሞራ ፍንዳታ ሲሆን ሁለት በጣም የታወቁ ፍንዳታዎች አሉት፡፡ ከእነዚህም አንዱ ከ1975–1976 የተከሰተው ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ከ2012–2013 የተከሰተው ነው፡፡
በመጀመሪያው በነበረው ከፍተኛ ሀይል ያለው ፍንዳታ ብዛት ያላቸው የእሳት ፍንጥርጣሪዎች እና የትም ቦታ ታይተው የማይታወቁ ማእድናት ተገኝተዋል፡፡ በአጠቃላይ የቶለባቺክ ገሞራ 130 ዓይነት በዚህ አካባቢ ብቻ የሚገኙ ማእድናትን አስገኝቷል፡፡ ከእነዚህ ማእድናት የቅርብ ጊዜው ፔትሪቫይት ነው፡፡ ይህም ሰማያዊ ቀለም ያለው ባለ ድቦልቡል ቅርጽ ሰልፌት ማእድን ነው፡፡
በአዲሱ ማእድን የተገኘው የኮፐር ቅንጣት የልተለመደና በቀላሉ የማይገኝ ከ7 የኦክስጅን ቅንጣቶች ጋር የተጣመረ ነው፡፡ የዚህ አይነት ባህሪ የሚገኘው በውህዶች ብቻ እንደሆነ የSt Petersburg University የምርምሩ መሪ ተናግሯል፡፡ የፔተሮቫየት ሞሎኪዩላዊ ቀመሩ (molecular framework) ኦክስጅን፣ ሶዲየም፣ ሳልፈርና ኮፐር በተፈጥሮ አብረው የተሰሩ ናቸው፡፡
ምንጭ Science alert
ስለ አርዲ እና ቀደምት የሰው ቅሪተ አካላት የተጻፈው መጽሀፍ
**************
በKermit Pattison የተጻፈው ‘Fossil Men’ የተሰኘው መጽሐፍ ሳይንስንና ድራማን በማዋሀድ ስለ ጥንታዊው ስነ-ሰብ የሚተርክ ሲሆን በአለማችን እጅግ ታዋቂ የሆኑት ቅሪተ አካላት የታሪኩ ክፍል ሆነዋል፡፡ እንደ ዘገባ ምንጫችን Science News እጅግ አስገራሚዋ እና በስነ ቁፋሮ ሳይንስ እስካሁን ከተገኙ ጥንታዊ የሰው ዘር ቅሪተ አካት መካከል ልዩ የሆነችው አርዲ እና ተመራማሪዎቿ በመጽሀፉ ውስጥ ተካትተዋል፡፡
በመጽሐፉ ውስጥ ጋዜጠኛው Kermit Pattison በአርዲ ፍለጋ ላይ የተሳተፉ ተመራማሪዎች በሰው ዘር ዝግመተ ለውጥ ታሪክ ውስጥ የታወቀውን እሳቤ ለመሞገት የሄዱበትን መንገድ ማራኪ ታሪኮችን በመጠቀም ያስነብባል፡፡ በተጨማሪም የአርዲ ቅሬተ አካል ከሌሎች ቅሬተ አካላት የተለየ የሆነበትን ምክንያትም መጽሀፉ ያስረዳል፡፡
የቁፋሮ ምርምር ቡድኑ በምርምር ሂደቱ የያዛቸውን ፎቶዎች ቪዲዮዎችና ልዩ ልዩ ማስታዎሻዎች ያካተተው መጽሐፉ አርዲ የተገኘችበትን የመጀመሪያ ቅጽበት የገለጸበት መንገድ ሳቢ ነው፡፡ ጋዜጠኛው ሁኔታውን ሲያስረዳ የምርምር ቡድኑ ብቸኛ ጥበቃ የሆነው የአፋሩ ጋዲ ከምርምር ቡድኑ ጋር አብሮ ይንቀሳቀስ በነበረበት ወቅት ከቁፋሮው ስፍራ አንድ ጥርስ እንዳገኘ ይናገራል፡፡ ይህ ጋዲ ያገኘው ጥርስ በቁፋሮ ከተገኙት የአርዲ አስር ጥርሶች መካከል አንዱ ነበር፡፡
ምንጭ Science News Magazine
**************
በKermit Pattison የተጻፈው ‘Fossil Men’ የተሰኘው መጽሐፍ ሳይንስንና ድራማን በማዋሀድ ስለ ጥንታዊው ስነ-ሰብ የሚተርክ ሲሆን በአለማችን እጅግ ታዋቂ የሆኑት ቅሪተ አካላት የታሪኩ ክፍል ሆነዋል፡፡ እንደ ዘገባ ምንጫችን Science News እጅግ አስገራሚዋ እና በስነ ቁፋሮ ሳይንስ እስካሁን ከተገኙ ጥንታዊ የሰው ዘር ቅሪተ አካት መካከል ልዩ የሆነችው አርዲ እና ተመራማሪዎቿ በመጽሀፉ ውስጥ ተካትተዋል፡፡
በመጽሐፉ ውስጥ ጋዜጠኛው Kermit Pattison በአርዲ ፍለጋ ላይ የተሳተፉ ተመራማሪዎች በሰው ዘር ዝግመተ ለውጥ ታሪክ ውስጥ የታወቀውን እሳቤ ለመሞገት የሄዱበትን መንገድ ማራኪ ታሪኮችን በመጠቀም ያስነብባል፡፡ በተጨማሪም የአርዲ ቅሬተ አካል ከሌሎች ቅሬተ አካላት የተለየ የሆነበትን ምክንያትም መጽሀፉ ያስረዳል፡፡
የቁፋሮ ምርምር ቡድኑ በምርምር ሂደቱ የያዛቸውን ፎቶዎች ቪዲዮዎችና ልዩ ልዩ ማስታዎሻዎች ያካተተው መጽሐፉ አርዲ የተገኘችበትን የመጀመሪያ ቅጽበት የገለጸበት መንገድ ሳቢ ነው፡፡ ጋዜጠኛው ሁኔታውን ሲያስረዳ የምርምር ቡድኑ ብቸኛ ጥበቃ የሆነው የአፋሩ ጋዲ ከምርምር ቡድኑ ጋር አብሮ ይንቀሳቀስ በነበረበት ወቅት ከቁፋሮው ስፍራ አንድ ጥርስ እንዳገኘ ይናገራል፡፡ ይህ ጋዲ ያገኘው ጥርስ በቁፋሮ ከተገኙት የአርዲ አስር ጥርሶች መካከል አንዱ ነበር፡፡
ምንጭ Science News Magazine
ሲንጋፖር የቴክኖሎጂ ፈጠራ ተሰጥኦ ላላቸው ሰዎች አዲስ ቪዛ አዘጋጀች
*********************
ለባለ ተሰጥኦዎች የተዘረጋ ቀይ ምንጣፍ ያላት ሲንጋፖር 500 ሰዎች የሚሳተፉበት ልዩ የተሰጥኦ ማሳያ ዝግጅት አቅዳለች፡፡ ለዝግጅቱም በቴክኖሎጂው አለም ተሞክሮ ያለፈ አስተዋጽኦ ያላቸው ሰዎች እንደሚሳተፉ ተገልጧል፡፡ Tech.Pass program በተሰኘው እቅድ አዲስ ቪዛ የተዘጋጀላቸው ሰዎች ብቃታቸው የተረጋገጠ እና ወደ ከተማዋ መጥተው ከአንድ በላይ ተቋም ገንብተው አልሚዎች እንዲሆኑ ወይም ለጀማሪ ተቋማት አማካሪ እና አሰልጣኝ እንዲሆኑ የታሰበ ነው፡፡ይህም ድርጅቶች የሚፈልጉትን ሰው ስፖንሰር በማድረግ ብቻ ወደከተማዋ እንዲያስገቡ የሚፈቅደው የመንግስት መመሪያ እየተሸሻለ መሄዱን የሚያሳይ ነው፡፡
የሁለት አመታት የጊዜ ርዝማኔ ያለው ቪዛ የተፈቀደው መካከለኛ ክህሎት ላላቸውና የአካባቢውን ገበያ ለሚሻሙ የፈጠራ ሙያተኞች ሳይሆን ከተማዋ የቀጠናው የቴክኖሎጂ ማእከል ለመሆን የምታደርገውን ጉዞ ሊያቀላትፉ የሚችሉ ከፍተኛ ብቃት ያላቸውን የቴክኖሎጂ ሰዎች ለማምጣት ያለመ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ስራ ለውጭ ዜጎች የሚሰጥበትን መመሪያ እንዲጠብቅ በመንግስት ላይ ከፍተኛ ጫና ስላደረበትም እንደሆነ የዘገባችን ምንጭ ገልጧል፡፡
የከተማዋ የገበያና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የሆኑት Chan Chun Sing ፕሮግራሙ በቀጠናው የምንፈልገውን ቴክኖሎጂ የበላይነት እንድናመጣ ከፍተኛ ሚና ያለውና መንገዱንም ቀላል የሚያደርግልን ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡ የፊታችን ጥር በሚጀምረው ምልመላ ተወዳዳሪዎች ለውድድር ከማመልከታቸው በፊት ካሉት ሶስት መስፈርቶች መካከል ቢያንስ ሁለቱን ማሟላት እንዳለባቸው ተነግሯል፡፡
ለማመልከትም ቢያንስ አምስት አመት የስራ ልምድ የቴክኖሎጆ ተቋምን በመምራት ወይም በቴክኖሎጂ ተቋም በመስራት ተቋሙ ቢያን 500 ሚሊዮን ዶላር ትርፍ እንዲያገኝ ያደረገ/ች ወይም በባለሙያነት በተሰራ ስራ ቢያንስ 100,000 ተጠቃሚዎች ያሉት ፈጠራን የሰራ/ች እና በስራ ዘመን ከ14,800 ዶላር ያላነሰ ተከፋይ የሆነ/ች መሆን እንዳለበት ተገልጧል፡፡
ምንጭ Bloomberg Technology
*********************
ለባለ ተሰጥኦዎች የተዘረጋ ቀይ ምንጣፍ ያላት ሲንጋፖር 500 ሰዎች የሚሳተፉበት ልዩ የተሰጥኦ ማሳያ ዝግጅት አቅዳለች፡፡ ለዝግጅቱም በቴክኖሎጂው አለም ተሞክሮ ያለፈ አስተዋጽኦ ያላቸው ሰዎች እንደሚሳተፉ ተገልጧል፡፡ Tech.Pass program በተሰኘው እቅድ አዲስ ቪዛ የተዘጋጀላቸው ሰዎች ብቃታቸው የተረጋገጠ እና ወደ ከተማዋ መጥተው ከአንድ በላይ ተቋም ገንብተው አልሚዎች እንዲሆኑ ወይም ለጀማሪ ተቋማት አማካሪ እና አሰልጣኝ እንዲሆኑ የታሰበ ነው፡፡ይህም ድርጅቶች የሚፈልጉትን ሰው ስፖንሰር በማድረግ ብቻ ወደከተማዋ እንዲያስገቡ የሚፈቅደው የመንግስት መመሪያ እየተሸሻለ መሄዱን የሚያሳይ ነው፡፡
የሁለት አመታት የጊዜ ርዝማኔ ያለው ቪዛ የተፈቀደው መካከለኛ ክህሎት ላላቸውና የአካባቢውን ገበያ ለሚሻሙ የፈጠራ ሙያተኞች ሳይሆን ከተማዋ የቀጠናው የቴክኖሎጂ ማእከል ለመሆን የምታደርገውን ጉዞ ሊያቀላትፉ የሚችሉ ከፍተኛ ብቃት ያላቸውን የቴክኖሎጂ ሰዎች ለማምጣት ያለመ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ስራ ለውጭ ዜጎች የሚሰጥበትን መመሪያ እንዲጠብቅ በመንግስት ላይ ከፍተኛ ጫና ስላደረበትም እንደሆነ የዘገባችን ምንጭ ገልጧል፡፡
የከተማዋ የገበያና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የሆኑት Chan Chun Sing ፕሮግራሙ በቀጠናው የምንፈልገውን ቴክኖሎጂ የበላይነት እንድናመጣ ከፍተኛ ሚና ያለውና መንገዱንም ቀላል የሚያደርግልን ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡ የፊታችን ጥር በሚጀምረው ምልመላ ተወዳዳሪዎች ለውድድር ከማመልከታቸው በፊት ካሉት ሶስት መስፈርቶች መካከል ቢያንስ ሁለቱን ማሟላት እንዳለባቸው ተነግሯል፡፡
ለማመልከትም ቢያንስ አምስት አመት የስራ ልምድ የቴክኖሎጆ ተቋምን በመምራት ወይም በቴክኖሎጂ ተቋም በመስራት ተቋሙ ቢያን 500 ሚሊዮን ዶላር ትርፍ እንዲያገኝ ያደረገ/ች ወይም በባለሙያነት በተሰራ ስራ ቢያንስ 100,000 ተጠቃሚዎች ያሉት ፈጠራን የሰራ/ች እና በስራ ዘመን ከ14,800 ዶላር ያላነሰ ተከፋይ የሆነ/ች መሆን እንዳለበት ተገልጧል፡፡
ምንጭ Bloomberg Technology
ከምድር የመጥፋት አደጋ የተጋረጠበት የዱር ህይወት 9 አሳዛኝ እውነታዎች
የምድር እጣፈንታ እና የአለማችን የተፈጥሮ ገፅታ ከመቼውም ጊዜ በላይ በከባድ ስጋት ውስጥ እንደሚገኝ የማያጠራጥር ነው፡፡ የምድርን የተፈጥሮ ሚዛኗ ሊያስቱ የሚችሉ አያሌ አደጋዎች በሰው ልጆች የህይወት ዘመን ውስጥ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መፈፀማቸው የአደባባይ ሚስጥር ነው፡፡ ዓለማችን ከዕለት ወደ ዕለት የሙቀት መጠኗ እየጨመረ፣ አቅፋ የያዘቻቸው የተለያዩ ሰብሎችና እንስሳት የመጥፋት አደጋ እየተጋረጠባቸው ይገኛል፡፡
ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ዘጠኝ እውነታዎች ወይም ምክንያቶች መኖሪያችን ብለን በምንጠራት መሬት እየተከሰቱ ያሉ እና የኛን ፈጣን ምላሽ የሚጠብቁ አሳዛኛ ሁኔታዎች ናቸው፡፡
1 - አሁን ላይ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ዝርያዎች የመጥፋት አደጋ ተጋርጦባቸዋል
የአለም አቀፉ የብዛ ህይወትና ስነምህዳር አገልግሎት በሳይንስ ፖሊሲ ፕላትፎርም ላይ እንዳስታወቀው በሰው ልጆች ታሪክ እስካሁን ያልታየ የእንስሳትና የእፅዋት ዝርያ የመጥፋት አደጋ ተደቅኗል፡፡ የተቋሙ መረጃ እንደሚያሳየው ከአንድ ሚሊዮን በላይ ዝርያዎች የመጥፋት አደጋ ተጋርጦባቸዋል፡፡
2 - የዱር አንስሳት ብዛት ከ1970 በኋላ በ2/3ኛ ቀንሷል
የዓለም የዱር እንስሳት ፈንድ ሊቪንግ ፕላኔት ኢንዴክስ በተባለው የ2020 አመታዊ ሪፖርቱ እንዳመለከተው እንደአውሮፓውያኑ ከ1970 አንስቶ እስከ 2018 ድረስ የዱር አንስሳ ብዛት መጠን በአማካይ በ68% መቀነስ አሳይቷል፡፡ በዚህ የእንስሳት መጠን ውስጥ ወፎች፣ አጥቢ አሳዎች፣ ተሳቢና አምፊቢያን እንስሳቶች በዋናነት በዝርዝር ውስጥ የሚገኙት ናቸው፡፡
3 - የአሜሪካ ሞቃታማ ንኡስ ክልሎች በውድቀት ላይ መገኘት
የዱር አንስሳት በብዛት ከሚገኝባው አካባቢዎች ቀዳሚ የሆነው ይህ ንኡስ ክልል ከ1970 ጀምሮ 94% የሚሆነው የዱር አንስሳ የጠፋበት አካባቢ ነው፡፡ የዓለም የዱር እንስሳት ፈንድ እንዳመለከተውም የአሜሪካ ሞቃታማ ንኡስ ክልል በየትኛውም የምድር ክፍል ያልተመዘገበ የዱር አንስሳት ጥፋት የታየበት አካባቢ ነው፡፡
4 - ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በተደጋጋሚ የሚሞቱ ዝርያዎች መብዛት
በአሜሪካ በሚገኘው የብራውን ዩኒቨርስቲ በ2014 የተደረገ ጥናት እንደሚያሳው የሰው ልጅ ወደዚች ምድር ከመምጣቱ አስቀድሞ የእንስሳትና የእፅዋት ዝርያ አልፎ አልፎ የመጥፈት እድል ነበረው፡፡ ይሁንና ሰዎች ይህችን ምድር ከተቀላቀሉ በኋላ የተለያዩ ዝርያዎች ከምድር የመጥፋት እድላቸው 1,000 ጊዜ ብልጫ እንዳለው እና ይህም ተደጋግሞ እንደሚፈፀምም ጥናቱ አመላክቷል፡፡
5 - በውሃ ውስጥ የሚኖሩ ዝርያዎች በፍጥነት መቀነስ
የዓለም የዱር እንስሳት ፈንድ ሊቪንግ ፕላኔት ኢንዴክስ በተባለው የ2020 አመታዊ ሪፖርቱ እንዳመለከተው በውሃ ውስጥ የሚኖሩ ዝርያዎች ከሌሎች የዱር አንስሳት በተለየ በፍጥነት በመቀነስ ላይ ይገኛሉ፡፡ በሪፖርቱ እንደተመለከተው ከ1970 አንስቶ እስከ 2018 ድረስ በአማካይ 84 በመቶው በውሃ ውስጥ የሚኖሩ ዝርያዎች በፍጥነት በመቀነስ ላይ ናቸው፡፡
6 - የትሮፒካል ደን በተለያዩ ምክንያቶች መጥፋት
የአለም አቀፉ የብዛ ህይወትና ስነምህዳር አገልግሎት በሳይንስ ፖሊሲ ፕላትፎርም ላይ እንዳስታወቀው አንደአውሮፓውያኑ ከ1980 አንስቶ እስከ 2000 ድረስ ብቻ 100 ሚሊዮን ሄክታር ደን በትሮፒካል የምድር አካባቢ ጠፍቷል፡፡ ይህ የደን ጭፍጨፋ በብዛት የተመዘገበው በላቲን አሜሪካ እና በደቡብ ምስራቅ እስያ ሲሆን በዋናነትም ለከብት እርባታ እና ለግብርና በሚል የተከናወነ ነው፡፡
7 - 40 በመቶው እፅዋት የመጥፋት አደጋ
የአለም የእፅዋትና ፈንገስ ሪፖርት በስሩ በሚገኘው ሮያል ቦታኒክ ጋርደን እንደሚያመለክተው ከአስሩ አፅዋቶች አራቱ የመጥፋት አደጋ የተጋረጠባቸው ሲሆን ይህም የ39.4% ልኬት ይታይበታል፡፡ በዚህ የመጥፋት አደጋ ውስጥ ከባዱ ስራ እፅዋቶቹ ከመጥፋታቸው በፊት የመለየት ስራ ሲሆን፣ በ2019 ብቻ 1,942 የእፅዋት ዝርያዎች ተለይተው ተመዝግበዋል፡፡
8 - ከግብርና ኢንዱስትሪ ጋር ተያይዞ በአያለው የቀነሱት ነፍሳቶች (insects)
በአለማችን ከግብርና ኢንዱስትሪ መስፋፋት ጋር ተያይዞ በአስር አመት ብቻ ከ40 በመቶ በላይ የነፍሳት ዝርያዎች ከምድር ላይ መጥፋታቸውን በሳይንስ ዳይሬክት ላይ በቅርቡ የወጣ አዲስ ምርምር አስታውቋል፡፡
9 - በራሪ የወፍ ዝርያዎች ብዛታቸው እየቀነሰ መምጣት
የአለም አቀፉ የብዛ ህይወትና ስነምህዳር አገልግሎት በሳይንስ ፖሊሲ ፕላትፎርም ላይ እንዳስታወቀው በአንድ ሃገር ውስጥ መኖሪያቸውን አድርገው የሚራቡ 3.5% የሚሆኑ የወፍ ዝርያዎች ከ2016 ጀምሮ የጠፉ ሲሆን ሌሎች 23 በመቶ የሚሸፍኑ ወፎች ደግሞ በአየር ንብርት ለውጥ ምክንያት ከፍተኛ የመጥፋት አደጋ ያለባቸው ናቸው፡፡
እነዚህ የተፈጥሮ ሃብቶች በዚህ መልኩ አደጋ ውስጥ መገኘታቸው ለኛ ለሰው ልጆች ትልቅ የህልውና ጥያቄ ነው፡፡ የብዛ ህይወት ሃብቶች ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታ የተላበሱ በመሆናቸው ማናቸውም በብዛ ህይወት ላይ የሚደርሱ አደጋዎች ለአየር ንብረት መቀያየር ትልቅ ሚና ይኖራቸዋል፡፡ በመሆኑም አነዚህ አሳዛኝ አውነታዎች አኛኑ ወደማጥፋት ከመሄዳቸው በፊት ተፈጥሮን ከጥፋት መታደግ የዕለት ተዕለት ተግበራችን ሊሆን ይገባል፡፡
ምንጭ፡ World Economic Forum
የምድር እጣፈንታ እና የአለማችን የተፈጥሮ ገፅታ ከመቼውም ጊዜ በላይ በከባድ ስጋት ውስጥ እንደሚገኝ የማያጠራጥር ነው፡፡ የምድርን የተፈጥሮ ሚዛኗ ሊያስቱ የሚችሉ አያሌ አደጋዎች በሰው ልጆች የህይወት ዘመን ውስጥ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መፈፀማቸው የአደባባይ ሚስጥር ነው፡፡ ዓለማችን ከዕለት ወደ ዕለት የሙቀት መጠኗ እየጨመረ፣ አቅፋ የያዘቻቸው የተለያዩ ሰብሎችና እንስሳት የመጥፋት አደጋ እየተጋረጠባቸው ይገኛል፡፡
ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ዘጠኝ እውነታዎች ወይም ምክንያቶች መኖሪያችን ብለን በምንጠራት መሬት እየተከሰቱ ያሉ እና የኛን ፈጣን ምላሽ የሚጠብቁ አሳዛኛ ሁኔታዎች ናቸው፡፡
1 - አሁን ላይ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ዝርያዎች የመጥፋት አደጋ ተጋርጦባቸዋል
የአለም አቀፉ የብዛ ህይወትና ስነምህዳር አገልግሎት በሳይንስ ፖሊሲ ፕላትፎርም ላይ እንዳስታወቀው በሰው ልጆች ታሪክ እስካሁን ያልታየ የእንስሳትና የእፅዋት ዝርያ የመጥፋት አደጋ ተደቅኗል፡፡ የተቋሙ መረጃ እንደሚያሳየው ከአንድ ሚሊዮን በላይ ዝርያዎች የመጥፋት አደጋ ተጋርጦባቸዋል፡፡
2 - የዱር አንስሳት ብዛት ከ1970 በኋላ በ2/3ኛ ቀንሷል
የዓለም የዱር እንስሳት ፈንድ ሊቪንግ ፕላኔት ኢንዴክስ በተባለው የ2020 አመታዊ ሪፖርቱ እንዳመለከተው እንደአውሮፓውያኑ ከ1970 አንስቶ እስከ 2018 ድረስ የዱር አንስሳ ብዛት መጠን በአማካይ በ68% መቀነስ አሳይቷል፡፡ በዚህ የእንስሳት መጠን ውስጥ ወፎች፣ አጥቢ አሳዎች፣ ተሳቢና አምፊቢያን እንስሳቶች በዋናነት በዝርዝር ውስጥ የሚገኙት ናቸው፡፡
3 - የአሜሪካ ሞቃታማ ንኡስ ክልሎች በውድቀት ላይ መገኘት
የዱር አንስሳት በብዛት ከሚገኝባው አካባቢዎች ቀዳሚ የሆነው ይህ ንኡስ ክልል ከ1970 ጀምሮ 94% የሚሆነው የዱር አንስሳ የጠፋበት አካባቢ ነው፡፡ የዓለም የዱር እንስሳት ፈንድ እንዳመለከተውም የአሜሪካ ሞቃታማ ንኡስ ክልል በየትኛውም የምድር ክፍል ያልተመዘገበ የዱር አንስሳት ጥፋት የታየበት አካባቢ ነው፡፡
4 - ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በተደጋጋሚ የሚሞቱ ዝርያዎች መብዛት
በአሜሪካ በሚገኘው የብራውን ዩኒቨርስቲ በ2014 የተደረገ ጥናት እንደሚያሳው የሰው ልጅ ወደዚች ምድር ከመምጣቱ አስቀድሞ የእንስሳትና የእፅዋት ዝርያ አልፎ አልፎ የመጥፈት እድል ነበረው፡፡ ይሁንና ሰዎች ይህችን ምድር ከተቀላቀሉ በኋላ የተለያዩ ዝርያዎች ከምድር የመጥፋት እድላቸው 1,000 ጊዜ ብልጫ እንዳለው እና ይህም ተደጋግሞ እንደሚፈፀምም ጥናቱ አመላክቷል፡፡
5 - በውሃ ውስጥ የሚኖሩ ዝርያዎች በፍጥነት መቀነስ
የዓለም የዱር እንስሳት ፈንድ ሊቪንግ ፕላኔት ኢንዴክስ በተባለው የ2020 አመታዊ ሪፖርቱ እንዳመለከተው በውሃ ውስጥ የሚኖሩ ዝርያዎች ከሌሎች የዱር አንስሳት በተለየ በፍጥነት በመቀነስ ላይ ይገኛሉ፡፡ በሪፖርቱ እንደተመለከተው ከ1970 አንስቶ እስከ 2018 ድረስ በአማካይ 84 በመቶው በውሃ ውስጥ የሚኖሩ ዝርያዎች በፍጥነት በመቀነስ ላይ ናቸው፡፡
6 - የትሮፒካል ደን በተለያዩ ምክንያቶች መጥፋት
የአለም አቀፉ የብዛ ህይወትና ስነምህዳር አገልግሎት በሳይንስ ፖሊሲ ፕላትፎርም ላይ እንዳስታወቀው አንደአውሮፓውያኑ ከ1980 አንስቶ እስከ 2000 ድረስ ብቻ 100 ሚሊዮን ሄክታር ደን በትሮፒካል የምድር አካባቢ ጠፍቷል፡፡ ይህ የደን ጭፍጨፋ በብዛት የተመዘገበው በላቲን አሜሪካ እና በደቡብ ምስራቅ እስያ ሲሆን በዋናነትም ለከብት እርባታ እና ለግብርና በሚል የተከናወነ ነው፡፡
7 - 40 በመቶው እፅዋት የመጥፋት አደጋ
የአለም የእፅዋትና ፈንገስ ሪፖርት በስሩ በሚገኘው ሮያል ቦታኒክ ጋርደን እንደሚያመለክተው ከአስሩ አፅዋቶች አራቱ የመጥፋት አደጋ የተጋረጠባቸው ሲሆን ይህም የ39.4% ልኬት ይታይበታል፡፡ በዚህ የመጥፋት አደጋ ውስጥ ከባዱ ስራ እፅዋቶቹ ከመጥፋታቸው በፊት የመለየት ስራ ሲሆን፣ በ2019 ብቻ 1,942 የእፅዋት ዝርያዎች ተለይተው ተመዝግበዋል፡፡
8 - ከግብርና ኢንዱስትሪ ጋር ተያይዞ በአያለው የቀነሱት ነፍሳቶች (insects)
በአለማችን ከግብርና ኢንዱስትሪ መስፋፋት ጋር ተያይዞ በአስር አመት ብቻ ከ40 በመቶ በላይ የነፍሳት ዝርያዎች ከምድር ላይ መጥፋታቸውን በሳይንስ ዳይሬክት ላይ በቅርቡ የወጣ አዲስ ምርምር አስታውቋል፡፡
9 - በራሪ የወፍ ዝርያዎች ብዛታቸው እየቀነሰ መምጣት
የአለም አቀፉ የብዛ ህይወትና ስነምህዳር አገልግሎት በሳይንስ ፖሊሲ ፕላትፎርም ላይ እንዳስታወቀው በአንድ ሃገር ውስጥ መኖሪያቸውን አድርገው የሚራቡ 3.5% የሚሆኑ የወፍ ዝርያዎች ከ2016 ጀምሮ የጠፉ ሲሆን ሌሎች 23 በመቶ የሚሸፍኑ ወፎች ደግሞ በአየር ንብርት ለውጥ ምክንያት ከፍተኛ የመጥፋት አደጋ ያለባቸው ናቸው፡፡
እነዚህ የተፈጥሮ ሃብቶች በዚህ መልኩ አደጋ ውስጥ መገኘታቸው ለኛ ለሰው ልጆች ትልቅ የህልውና ጥያቄ ነው፡፡ የብዛ ህይወት ሃብቶች ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታ የተላበሱ በመሆናቸው ማናቸውም በብዛ ህይወት ላይ የሚደርሱ አደጋዎች ለአየር ንብረት መቀያየር ትልቅ ሚና ይኖራቸዋል፡፡ በመሆኑም አነዚህ አሳዛኝ አውነታዎች አኛኑ ወደማጥፋት ከመሄዳቸው በፊት ተፈጥሮን ከጥፋት መታደግ የዕለት ተዕለት ተግበራችን ሊሆን ይገባል፡፡
ምንጭ፡ World Economic Forum
በጆሯችን አካባቢ የሚፈጠርን ምናባዊ ድምጽ (tinnitus) ለማከም ሰውሰራሽ ክህሎትን መጠቀም
*********************
በጆሯችን የምንሰማውን በገሀዱ አለም የሌለ ምናባዊ ድምጽ ለማስተካከል የጭንቅላት ምስሎችን መጠቀም የሚያስችል ሰውሰራሽ ክህሎት በመጠቀም እንደተቻለ የመረጃ ምንጫችን New scientist ዘገበ፡፡ በአውስትራሊያ ሜልቦርን በሚገኝ አንድ የምርምር ተቋም በአንድ ሰው ጭንቅላት ውስጥ ምናባዊ ድምጽ መኖር አለመኖሩንና ሊያስከትል የሚችለውን የጉዳት መጠን መለካት የሚያስችል የክትትል ሂደት (algorithm) መዘጋጀቱ ተሰምቷል፡፡
ሰውሰራሽ ክህሎቱ በጭንቅላት ውስጥ የሚፈጠርን ድምጽ በ78 በመቶ ትክክለኝነት ከቀላል እስከ ከባድ ደረጃ ያለውን መለካት ያስችላል፡፡ 15 በመቶ የሚሆኑ ጎልማሶች ከባድ በሚባል ምናባዊ ድምጽ የሚጠቁ ሲሆን በአብዛኛው የጀሮ የመስማት አቅምን በመለካትና ታማሚው በሚያቀርበው መረጃ መሰረት ህክምና ይሰጣል፡፡
የምርምር ቡድኑ በመጀመሪያ functional near-infrared spectroscopy, ወይም fNIRS የተሰኘ ሳይንሳዊ መንገድን በከባድ ችግር ላይ ባሉ 25 ሰዎችና ችግሩ በሌለባቸው 21 ሰዎች ተግባራዊ አደረጉ፡፡
ተመራማሪዎች የተለያዩ ልኬቶችን ከሰሩ በኋላ ቀደም ብለው ያዘጋጁትን አሊጎሪዝም ከ fNIRS ጋር የማላመድ ስራ እየሰሩ ነው፡፡ በዚህም በዘርፉ አዲስ ውጤት ይገኛል ተብሎ እየተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ፡ new scientist
*********************
በጆሯችን የምንሰማውን በገሀዱ አለም የሌለ ምናባዊ ድምጽ ለማስተካከል የጭንቅላት ምስሎችን መጠቀም የሚያስችል ሰውሰራሽ ክህሎት በመጠቀም እንደተቻለ የመረጃ ምንጫችን New scientist ዘገበ፡፡ በአውስትራሊያ ሜልቦርን በሚገኝ አንድ የምርምር ተቋም በአንድ ሰው ጭንቅላት ውስጥ ምናባዊ ድምጽ መኖር አለመኖሩንና ሊያስከትል የሚችለውን የጉዳት መጠን መለካት የሚያስችል የክትትል ሂደት (algorithm) መዘጋጀቱ ተሰምቷል፡፡
ሰውሰራሽ ክህሎቱ በጭንቅላት ውስጥ የሚፈጠርን ድምጽ በ78 በመቶ ትክክለኝነት ከቀላል እስከ ከባድ ደረጃ ያለውን መለካት ያስችላል፡፡ 15 በመቶ የሚሆኑ ጎልማሶች ከባድ በሚባል ምናባዊ ድምጽ የሚጠቁ ሲሆን በአብዛኛው የጀሮ የመስማት አቅምን በመለካትና ታማሚው በሚያቀርበው መረጃ መሰረት ህክምና ይሰጣል፡፡
የምርምር ቡድኑ በመጀመሪያ functional near-infrared spectroscopy, ወይም fNIRS የተሰኘ ሳይንሳዊ መንገድን በከባድ ችግር ላይ ባሉ 25 ሰዎችና ችግሩ በሌለባቸው 21 ሰዎች ተግባራዊ አደረጉ፡፡
ተመራማሪዎች የተለያዩ ልኬቶችን ከሰሩ በኋላ ቀደም ብለው ያዘጋጁትን አሊጎሪዝም ከ fNIRS ጋር የማላመድ ስራ እየሰሩ ነው፡፡ በዚህም በዘርፉ አዲስ ውጤት ይገኛል ተብሎ እየተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ፡ new scientist
ለመጀመሪያ ጊዜ በሰው የተሞከረው የሃይፐርሉፕ ቴክኖሎጂ
ሃይፐርሉፕ አዲሱ የትራንስፖርት ቴክኖሎጂ በመሆን አለማችንን የተሻለች ለማድረግ የተወጠነ እጅግ በጣም ፈጣን የትራንስፖርት አማራጭ ነው፡፡ የቴክኖሎጂው አይነት ለረዥም ጊዜ በተለያዩ የምርምር ሂደቶች ያለፈ ቢሆንም እስካሁን ድረስ ከግልና መንግስታዊ ሙከራዎች ባለፈ ለንግድ የቀረበበት ሁኔታ የለም፡፡
የአሜሪካው ቨርጅን ሃይፐርሉፕ ለመጀመሪያ ጊዜ ቴክኖሎጂውን በሰዎች ላይ የሞከር ድርጅት ሲሆን ምስረታውን ካደረገበት 2014 እንስቶ የተለያዩ ሙከራዎችን በቴክኖሎጂው ዙሪያ ሲያደርግ የቆየ ነው፡፡ ሙከራው ከላስ ቬጋስ ወጣ ባለ የበረሃ ቦታ የተካሄደ ሲሆን ኩባንያው በሰራው 500 ሜትር በሚጠጋ እንደሃዲድ በሚዘረጋ የቫኪዩም ትዩብ እና የመንገደኞች ፖድ አማካኝነት የተከናወነ ነው፡፡ የቫኪዩም ትዩብ አገልግሎት እንደባቡር ሃዲድ እጅግ በፍጥነት የሚጓዘውን የመንገደኞች መያዣ ፖድ የማሳለጥ ስራ ሲሆን ሌሎች የኤሌክትሪክ ማራዘሚያ መሳሪየዎች እና ኤሌክትሮ ማግኔቲክ መወጣጫዎች የቴክኖሎጂው ተጨማሪ አካላት ናቸው ፡፡
በትራንስፖርት ኢንዱስትሪው በጣም ፈጣን ከሚባሉት የኤሌክትሪክ ባቡሮችና በራሪ አውሮፕላኖች በላይ እጅግ ፈጣን ወይም (ultra-fast speeds) የሚባልለት እና ለዘላቂ የአካባቢ ጥበቃ አሉታዊ ተፅዕኖ የሚኖረው የሃይፐርሉፕ ቴክኖሎጂ ጥንስሱ ከዛሬ 90 አመት በፊት ቢሆንም መንገደኞቹን ይዞ የመጀመሪያው ሙከራውን ያደረገው በፈረንጆቹ 2020 ነው፡፡ ኩባንያው ቴክኖሎጂውን ለመሰራት በሚጀመርብት ግዜ 600 ማይልስ በሰዓት ሊጓዝ የሚችል ሃይፐርሉፕ ለመስራት ያለመ ሲሆን ይህም ከኒው ዮርክ ከተማ እስከ ዋሽንግተን ዲስ ያለውን ርቀት በ30 ደቂቃ የሚያጠናቅቅ ነው፡፡ የቨርጅን ግሩፕ ዋና መሰራች ሪቻርድ ብራንሰን ስለቴክኖሎጂውና ስለተሳካው ሙከራ እንደሚናገሩት በመጪዎቹ ጊዚያት የሰዎችን አጠቃላይ ህይወት መቀየር የሚያስችል ኢኖቬሽን ከመሆኑም በላይ በቴክኖሎጂው ዘርፍ ትልቅ የመሰርት ድንጋይ የሚያስቀምጥ መሆኑን ይናገራሉ፡፡
ቨርጅን ግሩፕ ቴክኖሎጂውን በመንገደኞች ላይ የሞከረ የመጀመሪው ድርጅት ቢሆንም በሃይፐርሉፕ ዘርፍ ላይ የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን የሚያደርጉ የተለያዩ ኩበንያዎች አሉ፡፡ ለአብነት በሎስ አንጀለስ መቀመጫውን ያደረገው ሃይፐርሉፕ የትራንስፖርት ቴክኖሎጂ በተባበሩት የአረብ ኢሜሬትስ፣ በፈረንሳይ እና በጀርመን የተለያዩ የሙከራ ፕሮጀክቶችን በመካሄድ ላይ የሚገኝ ሲሆን፤ እንደአውሮፓውያኑ በ2022 የመጀመሪያውን የንግድ ሃይፐርሉፕ ትራንስፖርት ለማቅረብም በዝግጅት ላይ ነው፡፡
ይህ የትራንስፖርት ቴክኖሎጂ ከደህንነትና ከፍጥነት አንጻር እጅግ የላቀ ቢሆንም ከሚፈልገው የወጪ ምጣኔ አኳያ እና ከሚወስደው የመንገድ መሰረተ ልማት አኳያ በቀላሉ ለመተግበር የሚያስቸግር ቴከኖሎጂ መሆኑን ብዙዎች ይገልፃሉ፡፡ ምንጭ፡ Big Think
ሃይፐርሉፕ አዲሱ የትራንስፖርት ቴክኖሎጂ በመሆን አለማችንን የተሻለች ለማድረግ የተወጠነ እጅግ በጣም ፈጣን የትራንስፖርት አማራጭ ነው፡፡ የቴክኖሎጂው አይነት ለረዥም ጊዜ በተለያዩ የምርምር ሂደቶች ያለፈ ቢሆንም እስካሁን ድረስ ከግልና መንግስታዊ ሙከራዎች ባለፈ ለንግድ የቀረበበት ሁኔታ የለም፡፡
የአሜሪካው ቨርጅን ሃይፐርሉፕ ለመጀመሪያ ጊዜ ቴክኖሎጂውን በሰዎች ላይ የሞከር ድርጅት ሲሆን ምስረታውን ካደረገበት 2014 እንስቶ የተለያዩ ሙከራዎችን በቴክኖሎጂው ዙሪያ ሲያደርግ የቆየ ነው፡፡ ሙከራው ከላስ ቬጋስ ወጣ ባለ የበረሃ ቦታ የተካሄደ ሲሆን ኩባንያው በሰራው 500 ሜትር በሚጠጋ እንደሃዲድ በሚዘረጋ የቫኪዩም ትዩብ እና የመንገደኞች ፖድ አማካኝነት የተከናወነ ነው፡፡ የቫኪዩም ትዩብ አገልግሎት እንደባቡር ሃዲድ እጅግ በፍጥነት የሚጓዘውን የመንገደኞች መያዣ ፖድ የማሳለጥ ስራ ሲሆን ሌሎች የኤሌክትሪክ ማራዘሚያ መሳሪየዎች እና ኤሌክትሮ ማግኔቲክ መወጣጫዎች የቴክኖሎጂው ተጨማሪ አካላት ናቸው ፡፡
በትራንስፖርት ኢንዱስትሪው በጣም ፈጣን ከሚባሉት የኤሌክትሪክ ባቡሮችና በራሪ አውሮፕላኖች በላይ እጅግ ፈጣን ወይም (ultra-fast speeds) የሚባልለት እና ለዘላቂ የአካባቢ ጥበቃ አሉታዊ ተፅዕኖ የሚኖረው የሃይፐርሉፕ ቴክኖሎጂ ጥንስሱ ከዛሬ 90 አመት በፊት ቢሆንም መንገደኞቹን ይዞ የመጀመሪያው ሙከራውን ያደረገው በፈረንጆቹ 2020 ነው፡፡ ኩባንያው ቴክኖሎጂውን ለመሰራት በሚጀመርብት ግዜ 600 ማይልስ በሰዓት ሊጓዝ የሚችል ሃይፐርሉፕ ለመስራት ያለመ ሲሆን ይህም ከኒው ዮርክ ከተማ እስከ ዋሽንግተን ዲስ ያለውን ርቀት በ30 ደቂቃ የሚያጠናቅቅ ነው፡፡ የቨርጅን ግሩፕ ዋና መሰራች ሪቻርድ ብራንሰን ስለቴክኖሎጂውና ስለተሳካው ሙከራ እንደሚናገሩት በመጪዎቹ ጊዚያት የሰዎችን አጠቃላይ ህይወት መቀየር የሚያስችል ኢኖቬሽን ከመሆኑም በላይ በቴክኖሎጂው ዘርፍ ትልቅ የመሰርት ድንጋይ የሚያስቀምጥ መሆኑን ይናገራሉ፡፡
ቨርጅን ግሩፕ ቴክኖሎጂውን በመንገደኞች ላይ የሞከረ የመጀመሪው ድርጅት ቢሆንም በሃይፐርሉፕ ዘርፍ ላይ የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን የሚያደርጉ የተለያዩ ኩበንያዎች አሉ፡፡ ለአብነት በሎስ አንጀለስ መቀመጫውን ያደረገው ሃይፐርሉፕ የትራንስፖርት ቴክኖሎጂ በተባበሩት የአረብ ኢሜሬትስ፣ በፈረንሳይ እና በጀርመን የተለያዩ የሙከራ ፕሮጀክቶችን በመካሄድ ላይ የሚገኝ ሲሆን፤ እንደአውሮፓውያኑ በ2022 የመጀመሪያውን የንግድ ሃይፐርሉፕ ትራንስፖርት ለማቅረብም በዝግጅት ላይ ነው፡፡
ይህ የትራንስፖርት ቴክኖሎጂ ከደህንነትና ከፍጥነት አንጻር እጅግ የላቀ ቢሆንም ከሚፈልገው የወጪ ምጣኔ አኳያ እና ከሚወስደው የመንገድ መሰረተ ልማት አኳያ በቀላሉ ለመተግበር የሚያስቸግር ቴከኖሎጂ መሆኑን ብዙዎች ይገልፃሉ፡፡ ምንጭ፡ Big Think
ሮቦቶች የወደፊት የህንጻ ምህንድስና ተስፋ
-----------------------------------------
ከዚህ በፊት በተለያዩ የሳይንስ ልቦለድ ፊልሞች ላይ የተለያዩ አገልግሎቶችን እንዲሰጡ ተደርገው በምናብ የተሳሉና ወደ ምስል የተለወጡ ልዩ ልዩ ፈጠራዎችን ተመልክተናል፡፡ ከእነዚህ መካከል በስታር ዋርስ ፊልም ላይና በሌሎች ሳይንስ ልቦለግ ዘውግ ባላቸው ፊልሞች አንድ ምናባዊ ፈጠራ ራሱን በመቀያየር እንደ ሰው ሲራመድ እንደ መኪና ሲሽከረከር እና ወደ ጦር መሳሪያነት ሲለወጥ ተመልክተናል፡፡
በሳይንስ ልቦለድ ፊልሞች የምንመለከታቸው ልዩ ልዩ ምናባዊ ፈጠራዎች የነገው እውናዊ አለም ፈጠራ መሰረቶች እንደሆኑ ያታመናል፡፡ በዚህ ዘገባችንም ራሳቸውን ወደ ድልድይ፣ ህንጻዎችና መኪናዎች በመለዋወጥ በተግባረ ብዙነት የህንጻ ምህንድስና ተስፋ ይሆናሉ ስለተባሉት ሮቦቶች ከthe next web ያገኘነውን መረጃ ልናካፍላችሁ ወደናል፡፡
በ MIT እና በUS ጦር የሚገኙ ተመራማሪዎች ማንናውንም አይነት ተግባር መፈጸም የሚችሉ መካኒካል የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በመስራት ላይ መሆናቸውን የዘገባ ምንጫችን መረጃ ያመለክታል፡፡ እንደ መረጃ ምንጫችን ከሆነ እየተሰራ ያለው ፈጠራ ወደምንፈልገው የህንጻ ቅርጽ ራሱን ማስተካከል የሚችል አገልግሎቱን ሲያጠናቅቅ ደግሞ ወዲያው ራሱን ወደሌላ አገልግሎት ሰጭ ቁስ ምሳሌ ጀልባ፣ ድልድይ ወይም ደግሞ መኪና መለወጥ የሚችልና በቀላሉ ተንቀሳቃሽ እንደሆነ ታውቋል፡፡
የተመራማሪዎቹ ቡድን በአነስተኛ ዋጋ ፈጣንና ተገጣጣሚ እንዲሁም ሰው ሰራሽ ክህሎትን የሚጠቀም የህንጻ ግንባታ ግብአት እንዲኖር እየሰራ ሲሆን በመነሻነት በተጨናነቀ አካባቢ አገልግሎት መስጠት የሚችል ድልድይ ለመስራት አስቦ ነበር ስራውን የጀመረው፡፡ በአሁኑ ሰዓት ግን ምርምሩ ያሳየው ውጤት ለጦር ሀይሉ ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ ያለውን የግንባታ ዘርፍ ከፍ ወዳለ ደረጃ ሊያሳድገው ይችላል ተብሎ ታምኖበታል፡፡
ምንጭ The next web
-----------------------------------------
ከዚህ በፊት በተለያዩ የሳይንስ ልቦለድ ፊልሞች ላይ የተለያዩ አገልግሎቶችን እንዲሰጡ ተደርገው በምናብ የተሳሉና ወደ ምስል የተለወጡ ልዩ ልዩ ፈጠራዎችን ተመልክተናል፡፡ ከእነዚህ መካከል በስታር ዋርስ ፊልም ላይና በሌሎች ሳይንስ ልቦለግ ዘውግ ባላቸው ፊልሞች አንድ ምናባዊ ፈጠራ ራሱን በመቀያየር እንደ ሰው ሲራመድ እንደ መኪና ሲሽከረከር እና ወደ ጦር መሳሪያነት ሲለወጥ ተመልክተናል፡፡
በሳይንስ ልቦለድ ፊልሞች የምንመለከታቸው ልዩ ልዩ ምናባዊ ፈጠራዎች የነገው እውናዊ አለም ፈጠራ መሰረቶች እንደሆኑ ያታመናል፡፡ በዚህ ዘገባችንም ራሳቸውን ወደ ድልድይ፣ ህንጻዎችና መኪናዎች በመለዋወጥ በተግባረ ብዙነት የህንጻ ምህንድስና ተስፋ ይሆናሉ ስለተባሉት ሮቦቶች ከthe next web ያገኘነውን መረጃ ልናካፍላችሁ ወደናል፡፡
በ MIT እና በUS ጦር የሚገኙ ተመራማሪዎች ማንናውንም አይነት ተግባር መፈጸም የሚችሉ መካኒካል የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በመስራት ላይ መሆናቸውን የዘገባ ምንጫችን መረጃ ያመለክታል፡፡ እንደ መረጃ ምንጫችን ከሆነ እየተሰራ ያለው ፈጠራ ወደምንፈልገው የህንጻ ቅርጽ ራሱን ማስተካከል የሚችል አገልግሎቱን ሲያጠናቅቅ ደግሞ ወዲያው ራሱን ወደሌላ አገልግሎት ሰጭ ቁስ ምሳሌ ጀልባ፣ ድልድይ ወይም ደግሞ መኪና መለወጥ የሚችልና በቀላሉ ተንቀሳቃሽ እንደሆነ ታውቋል፡፡
የተመራማሪዎቹ ቡድን በአነስተኛ ዋጋ ፈጣንና ተገጣጣሚ እንዲሁም ሰው ሰራሽ ክህሎትን የሚጠቀም የህንጻ ግንባታ ግብአት እንዲኖር እየሰራ ሲሆን በመነሻነት በተጨናነቀ አካባቢ አገልግሎት መስጠት የሚችል ድልድይ ለመስራት አስቦ ነበር ስራውን የጀመረው፡፡ በአሁኑ ሰዓት ግን ምርምሩ ያሳየው ውጤት ለጦር ሀይሉ ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ ያለውን የግንባታ ዘርፍ ከፍ ወዳለ ደረጃ ሊያሳድገው ይችላል ተብሎ ታምኖበታል፡፡
ምንጭ The next web
ያለ ዕድሜ ማርጀት በሽታ መድሃኒት ፍቃድ አገኘ
======================
ያለ ዕድሜ ማርጀት በሽታ ወይም ፕሮጄሪያ የተጠቁ ህፃናትን ዕድሜ ማስረዘሙን ተከትሎ ባሳለፍነው አርብ ዞኬንቪ ለተሰኘው መድሃኒት ፍቃድ ተሰጥቶታል፡፡ መድሃኒቶቹን በየቀኑ ሁለት ጊዜ እንዲወስዱ የተደረጉ 62 ህፃናትን ተካፋይ የሆኑባቸው ሁለት ጥናቶች ያሳዩት ውጤት መድሃኒቱን ካልወሰዱ ሌሎች በተመሳሳይ ዕድሜ እና ሁኔታዎች ላይ ከሚገኙ ሌሎች ከዓለም ዙርያ የተውጣጡ 81 ህፃናት ጋራ እንዲነፃጸር ተደርጎ ነበር፡፡ ህፃናቱ ለ11 ዓመታት ያህል ክትትል የተደረገባቸው ሲሆን በመጨረሻ ውጤቱም መድሃኒቱን በተከታታይ የወሰዱት ህፃናት ዕድሜ በሁለት ዓመት ተኩል እንደጨመረ ማረጋገጥ ተችሏል፡፡ ይህን ተከትሎ ነው ታድያ የአሜሪካ የምግብ እና መድሃኒት አስተዳደር (FDA) መድሃኒቶቹ ለፕሮጄሪያ እና ተያያዥ የጤና ጉዳዮች ይውል ዘንድ ፈቃድ የሰጠው፡፡
ህክምናው ላይ ሲደረግ የነበረው ጥናት በዋናነት በፕሮጄሪያ ጥናት ፋውንዴሽን ድጋፍ እና መድሃኒት አበልፃጊው ኢገር ባዮፋርማቱቲካልስ አማካኝነት የተከናወነ ነበር፡፡ ህክምናው አስቀድሞ ከደረሳቸው ዕድለኛ የበሽታው ተጠቂዎች መካከል የሆነችው ሜጋን ዋልድሮን ማደግ እና ክብደቷም መጨመር አቁሞ እንዲሁም ፀጉሯ እየረገፈ ነበር፡፡ መድሃኒቱን ከ2 ዓመት ዕድሜዋ አንስቶ መከታተል ስትጀምር ግን ወዲያው ውጤቱ መታየት እንደጀመረ ትናገራለች፡፡ አሁን ላይ በ19 ዓመት ዕድሜዋ ላይ የምትገኘው ሜጋን ቁመቷ 3.6 ሜትር ላይ ሲገኝ በኦክስጅን የበለጸገ ደም የሚያመላልሱት የደም ስሮቿም እየጠነከሩ መጥተዋል፡፡ አሁን ላይ ያ በህይወቷ ጅማሮ ላይ ገጥሟት የነበረው ችግር አልፎ የመሰናዶ ትምህርቷን ለመጨረስ እና የሀገር አቋራጭ ሩጫ ላይ ለመሳተፍ ሁሉ በቅታለች፡፡ መድሃኒቱን ሲወስዱ ከነበሩት ሌሎች የበሽታው ተጠቂዎች መካከል ዕድሜያቸው እስከ 24 ዓመት ድረስ የደረሱም ይገኙበታል፡፡
በአንድ ወቅት በኢትዮጵያ በብቸኝነት በዘረ መል ለዉጥ ምክንያት ሊመጡ የሚችሉ የጤና እክሎችን በሚመረምረው MRC-ET አድቫንስድ ላብራቶሪ ዳይሬክትር እና ተመራማሪ ዶ/ር ዘዉዱ ተረፈወርቅ ጋራ በነበረን ቆይታ በሽታውን “በዘረመል ለዉጥ (ጄኔቲክ ሚቹዌሽን) ምክንያት ከሚመጡ በሽታዎች” ውስጥ አንዱ እንደሆነ ሲነግሩን ቅድመ እርጅና ወይም ጊዜዉን ያልጠበቀ የእርጅና መከሰት ተብሎ ሊገለጽ የሚችለው በሽታው “ዲ.ኤን.ኤ ወይም ዘረ-መል ላይ በሚከሰት የአጋጣሚ ለዉጥ ምክንያት ሊመጣ የሚችል የጤና ጠንቅ ነዉ” መሆኑን ገልፀውልን ነበር፡፡
ፕሮጄሪያ ያለባቸው ህፃናት ብዙውን ጊዜ በታዳጊነት ዕሜያቸው ጅማሮ ላይ ህይወታቸውን ያጣሉ፡፡ ተላላፊ ያልሆነው በሽታው የዕድገት መገታት፣ የመገጣጠሚያዎች መጠንከር፣ ፀጉር መርገፍ እና ቆዳን የአዛውንትነት ገፅታ መያዝን ያመጣል፡፡ በአሁኑ ሰዓት በዓለም ዙርያ አራት መቶ የሚሆኑ ሰዎችን ብቻ አጥቅቶ የሚገኘው ፕሮጄሪያ የዚህ ህክምና ሙከራ ከመጀመሩ በፊት የሀኪሞች እርዳታ ምልክቶቹን ለመቀነስ በመጣር ላይ ብቻ የተገደበ ነበረ፡፡
መሰረቱን በሀገረ አሜሪካን ካሊፎርኒያ ግዛት ያደረገው ኢገር የዞኪንቪ መድሃኒትን ዋጋ እስካሁን ይፋ አላደረገም፡፡ ሆኖም በሽታው ተጠቂዎች ቁጥር በጣም አነስተኛ ከመሆኑ ጋራ ተያይዞ ውድ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡
ምንጭ፡ Medical Xpress እና ለዶ/ር ዘዉዱ ተረፈወርቅ የተደረገ ቃለ-መጠይቅ
======================
ያለ ዕድሜ ማርጀት በሽታ ወይም ፕሮጄሪያ የተጠቁ ህፃናትን ዕድሜ ማስረዘሙን ተከትሎ ባሳለፍነው አርብ ዞኬንቪ ለተሰኘው መድሃኒት ፍቃድ ተሰጥቶታል፡፡ መድሃኒቶቹን በየቀኑ ሁለት ጊዜ እንዲወስዱ የተደረጉ 62 ህፃናትን ተካፋይ የሆኑባቸው ሁለት ጥናቶች ያሳዩት ውጤት መድሃኒቱን ካልወሰዱ ሌሎች በተመሳሳይ ዕድሜ እና ሁኔታዎች ላይ ከሚገኙ ሌሎች ከዓለም ዙርያ የተውጣጡ 81 ህፃናት ጋራ እንዲነፃጸር ተደርጎ ነበር፡፡ ህፃናቱ ለ11 ዓመታት ያህል ክትትል የተደረገባቸው ሲሆን በመጨረሻ ውጤቱም መድሃኒቱን በተከታታይ የወሰዱት ህፃናት ዕድሜ በሁለት ዓመት ተኩል እንደጨመረ ማረጋገጥ ተችሏል፡፡ ይህን ተከትሎ ነው ታድያ የአሜሪካ የምግብ እና መድሃኒት አስተዳደር (FDA) መድሃኒቶቹ ለፕሮጄሪያ እና ተያያዥ የጤና ጉዳዮች ይውል ዘንድ ፈቃድ የሰጠው፡፡
ህክምናው ላይ ሲደረግ የነበረው ጥናት በዋናነት በፕሮጄሪያ ጥናት ፋውንዴሽን ድጋፍ እና መድሃኒት አበልፃጊው ኢገር ባዮፋርማቱቲካልስ አማካኝነት የተከናወነ ነበር፡፡ ህክምናው አስቀድሞ ከደረሳቸው ዕድለኛ የበሽታው ተጠቂዎች መካከል የሆነችው ሜጋን ዋልድሮን ማደግ እና ክብደቷም መጨመር አቁሞ እንዲሁም ፀጉሯ እየረገፈ ነበር፡፡ መድሃኒቱን ከ2 ዓመት ዕድሜዋ አንስቶ መከታተል ስትጀምር ግን ወዲያው ውጤቱ መታየት እንደጀመረ ትናገራለች፡፡ አሁን ላይ በ19 ዓመት ዕድሜዋ ላይ የምትገኘው ሜጋን ቁመቷ 3.6 ሜትር ላይ ሲገኝ በኦክስጅን የበለጸገ ደም የሚያመላልሱት የደም ስሮቿም እየጠነከሩ መጥተዋል፡፡ አሁን ላይ ያ በህይወቷ ጅማሮ ላይ ገጥሟት የነበረው ችግር አልፎ የመሰናዶ ትምህርቷን ለመጨረስ እና የሀገር አቋራጭ ሩጫ ላይ ለመሳተፍ ሁሉ በቅታለች፡፡ መድሃኒቱን ሲወስዱ ከነበሩት ሌሎች የበሽታው ተጠቂዎች መካከል ዕድሜያቸው እስከ 24 ዓመት ድረስ የደረሱም ይገኙበታል፡፡
በአንድ ወቅት በኢትዮጵያ በብቸኝነት በዘረ መል ለዉጥ ምክንያት ሊመጡ የሚችሉ የጤና እክሎችን በሚመረምረው MRC-ET አድቫንስድ ላብራቶሪ ዳይሬክትር እና ተመራማሪ ዶ/ር ዘዉዱ ተረፈወርቅ ጋራ በነበረን ቆይታ በሽታውን “በዘረመል ለዉጥ (ጄኔቲክ ሚቹዌሽን) ምክንያት ከሚመጡ በሽታዎች” ውስጥ አንዱ እንደሆነ ሲነግሩን ቅድመ እርጅና ወይም ጊዜዉን ያልጠበቀ የእርጅና መከሰት ተብሎ ሊገለጽ የሚችለው በሽታው “ዲ.ኤን.ኤ ወይም ዘረ-መል ላይ በሚከሰት የአጋጣሚ ለዉጥ ምክንያት ሊመጣ የሚችል የጤና ጠንቅ ነዉ” መሆኑን ገልፀውልን ነበር፡፡
ፕሮጄሪያ ያለባቸው ህፃናት ብዙውን ጊዜ በታዳጊነት ዕሜያቸው ጅማሮ ላይ ህይወታቸውን ያጣሉ፡፡ ተላላፊ ያልሆነው በሽታው የዕድገት መገታት፣ የመገጣጠሚያዎች መጠንከር፣ ፀጉር መርገፍ እና ቆዳን የአዛውንትነት ገፅታ መያዝን ያመጣል፡፡ በአሁኑ ሰዓት በዓለም ዙርያ አራት መቶ የሚሆኑ ሰዎችን ብቻ አጥቅቶ የሚገኘው ፕሮጄሪያ የዚህ ህክምና ሙከራ ከመጀመሩ በፊት የሀኪሞች እርዳታ ምልክቶቹን ለመቀነስ በመጣር ላይ ብቻ የተገደበ ነበረ፡፡
መሰረቱን በሀገረ አሜሪካን ካሊፎርኒያ ግዛት ያደረገው ኢገር የዞኪንቪ መድሃኒትን ዋጋ እስካሁን ይፋ አላደረገም፡፡ ሆኖም በሽታው ተጠቂዎች ቁጥር በጣም አነስተኛ ከመሆኑ ጋራ ተያይዞ ውድ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡
ምንጭ፡ Medical Xpress እና ለዶ/ር ዘዉዱ ተረፈወርቅ የተደረገ ቃለ-መጠይቅ
ከ5 ቢሊዮን ኪሎ ሜትር ጉዞ በኋላ የአስትሮይድ ናሙና እየተጠበቀ ነው
*************************************
ከስድስት ዓመት የህዋ ላይ ቆይታ በኋላ የጃፓን የህዋ ምርምር ተቋም ንብረት የሆነችው Hayabusa2 ሳተላይት ወደ መሬት እየተመለሰች እንደሆነ ተሰማ፡፡ ከህዋ ወደ መሬት 5 ቢሊዮን ኪሎሜትሮችን አቋርጣ የፊታችን ታህሳስ ስድስት 2020 በበረሀማው የደቡብ አውስትራሊያ ክፍል በምትገኘው ዉሜራ ከተማ የምትጠበቀው ሳተላይት በትንሹ 100 ሚሊግራም ክብደት ያለው የ asteroid Ryugu ናሙና ይዛ እንደምትመጣ ተነግሯል፡፡
በበረሀማዋ ከተማ ይወድቃል ተብሎ የሚጠበቀው የሳተላይቷ ክፍል በህዋ ምርምር ውስጥ ከፍተኛ ጥቅም ያለው ውጤት ሆኖ እንደሚመዘገብ ይጠብቃል፡፡ ለዚህም አጠቃላ ጉዞው 5.24 ቢሊዮን ኪሎሜትሮችን መሸፈኑ እንደ ማሳያነት ተጠቅሷል፡፡ ይህ Ryugu እየተባለ የሚጠራው አስትሮይድ ከዚህ በፊት 1999 JU3 ይባል የነበረ ሲሆን በፀሐይ ዙሪያ ባለ የመሬት ምህዋር ውስጥ ባለ እንቁላል ቅርጽ (elliptical) ምህዋር ላይ ይገኛል፡፡
የሳተላይቷ ጉዞ ሲታቀድ ወደፊት አስትሮይዱ የት ሊገኝ እንደሚችል በማስላትና የመሬት ስበትን በመጠቀም የሳተላይት የጉዞ መስመርንና ፍጥነትን ልክን ማስተካከል ትልቅ ስራ ነበር፡፡ ከዚያም ከአስትሮይዱ ጋር ናሙና መውሰድ በሚያስችል መልኩ ሁለት ጊዜ በመጋጨት ሳተላይቷ ወደመሬት እንድትመለስ የታሰበ ነበር፡፡ አሁን ሁሉም ነገር በታቀደው መሰረት እየሔደ ያለ ይመስላል፡፡ ለዚህም ነው የናሙና ሰብሳቢ ቡድኑ ቀደም ብሎ በአውስትራሊያዋ ዉማሬ የከተመው፡፡
ከህዋ ወደመሬት የሚደረግ የጭነት ጉዞ እንደ ቀላል የሚታይ አይደለም፡፡ ምክንያቱም የአስትሮይድ ናሙና ወደመሬት ለማምጣት በተደረገ ሙከራ የተሳካ የሚባለው በ2010 የ JAXAው ወደ Itokawa አስትሮይድ የተደረገው ሲሆን ይህም ሙሉ ለሙሉ ያልተሳካ እና በጣም ጥቂት የሆነ በማይክሮ ግራም የሚለካ ናሙና የተገኘበት ነው፡፡ ለዚህም ምክንያቱ የናሙና መያዣው እቃ በመውደቁ ነበር፡፡ ከዚህ ጋር ሲነጻጸር 100 ሚሊግራም እጅግ ትልቅ ናሙና ነው፡፡
ተመራማሪዎች በሚመጣው ናሙና ሰፊ የሆኑ ምርምሮችን ለመስራት አቅደዋል፡፡ ለዚህም ምክንያቱ Ryugu የተሰኘው አስትሮይድ በስርዓተ ፀሐይ ውስጥ ያልተበረዙና በመጀመሪያ ተፈጥሯቸው ያሉ ማእድናትን ይዟል ተብሎ ስለሚታሰብ ነው፡፡ አስትሮይዱም ከ4.5 ቢሊዮን ዓመታት በፊት እንደተፈጠረ ይገመታል፡፡
ከአስትሮይዱ በተወሰደ ናሙና ተመራማሪዎች የጥንቱን ስርዓተ ፀሐይ ብሎም የአለታማ ፕላኔቶችን አፈጣጠርና ዝግመተ ለውጥ ለመመርመር አስበዋል፡፡ የምርምር ተቋሙ ከዚህ በኋላ በ2026 በ2031 ወደ ሌሎች አስትሮይዶች ጉዞ ለማድረግ እቅድ እንዳለው አሳውቋል፡፡
ምንጭ Science Alert
*************************************
ከስድስት ዓመት የህዋ ላይ ቆይታ በኋላ የጃፓን የህዋ ምርምር ተቋም ንብረት የሆነችው Hayabusa2 ሳተላይት ወደ መሬት እየተመለሰች እንደሆነ ተሰማ፡፡ ከህዋ ወደ መሬት 5 ቢሊዮን ኪሎሜትሮችን አቋርጣ የፊታችን ታህሳስ ስድስት 2020 በበረሀማው የደቡብ አውስትራሊያ ክፍል በምትገኘው ዉሜራ ከተማ የምትጠበቀው ሳተላይት በትንሹ 100 ሚሊግራም ክብደት ያለው የ asteroid Ryugu ናሙና ይዛ እንደምትመጣ ተነግሯል፡፡
በበረሀማዋ ከተማ ይወድቃል ተብሎ የሚጠበቀው የሳተላይቷ ክፍል በህዋ ምርምር ውስጥ ከፍተኛ ጥቅም ያለው ውጤት ሆኖ እንደሚመዘገብ ይጠብቃል፡፡ ለዚህም አጠቃላ ጉዞው 5.24 ቢሊዮን ኪሎሜትሮችን መሸፈኑ እንደ ማሳያነት ተጠቅሷል፡፡ ይህ Ryugu እየተባለ የሚጠራው አስትሮይድ ከዚህ በፊት 1999 JU3 ይባል የነበረ ሲሆን በፀሐይ ዙሪያ ባለ የመሬት ምህዋር ውስጥ ባለ እንቁላል ቅርጽ (elliptical) ምህዋር ላይ ይገኛል፡፡
የሳተላይቷ ጉዞ ሲታቀድ ወደፊት አስትሮይዱ የት ሊገኝ እንደሚችል በማስላትና የመሬት ስበትን በመጠቀም የሳተላይት የጉዞ መስመርንና ፍጥነትን ልክን ማስተካከል ትልቅ ስራ ነበር፡፡ ከዚያም ከአስትሮይዱ ጋር ናሙና መውሰድ በሚያስችል መልኩ ሁለት ጊዜ በመጋጨት ሳተላይቷ ወደመሬት እንድትመለስ የታሰበ ነበር፡፡ አሁን ሁሉም ነገር በታቀደው መሰረት እየሔደ ያለ ይመስላል፡፡ ለዚህም ነው የናሙና ሰብሳቢ ቡድኑ ቀደም ብሎ በአውስትራሊያዋ ዉማሬ የከተመው፡፡
ከህዋ ወደመሬት የሚደረግ የጭነት ጉዞ እንደ ቀላል የሚታይ አይደለም፡፡ ምክንያቱም የአስትሮይድ ናሙና ወደመሬት ለማምጣት በተደረገ ሙከራ የተሳካ የሚባለው በ2010 የ JAXAው ወደ Itokawa አስትሮይድ የተደረገው ሲሆን ይህም ሙሉ ለሙሉ ያልተሳካ እና በጣም ጥቂት የሆነ በማይክሮ ግራም የሚለካ ናሙና የተገኘበት ነው፡፡ ለዚህም ምክንያቱ የናሙና መያዣው እቃ በመውደቁ ነበር፡፡ ከዚህ ጋር ሲነጻጸር 100 ሚሊግራም እጅግ ትልቅ ናሙና ነው፡፡
ተመራማሪዎች በሚመጣው ናሙና ሰፊ የሆኑ ምርምሮችን ለመስራት አቅደዋል፡፡ ለዚህም ምክንያቱ Ryugu የተሰኘው አስትሮይድ በስርዓተ ፀሐይ ውስጥ ያልተበረዙና በመጀመሪያ ተፈጥሯቸው ያሉ ማእድናትን ይዟል ተብሎ ስለሚታሰብ ነው፡፡ አስትሮይዱም ከ4.5 ቢሊዮን ዓመታት በፊት እንደተፈጠረ ይገመታል፡፡
ከአስትሮይዱ በተወሰደ ናሙና ተመራማሪዎች የጥንቱን ስርዓተ ፀሐይ ብሎም የአለታማ ፕላኔቶችን አፈጣጠርና ዝግመተ ለውጥ ለመመርመር አስበዋል፡፡ የምርምር ተቋሙ ከዚህ በኋላ በ2026 በ2031 ወደ ሌሎች አስትሮይዶች ጉዞ ለማድረግ እቅድ እንዳለው አሳውቋል፡፡
ምንጭ Science Alert
ቀኑ የከፋበት በጎ ሰው
-------------------
ለበጎ አድራጎት ስራ ወደ ህንድ ያቀና አንድ ብሪታንያዊ በወባ፣ ዳንጊ ትኩሳት፣ እና ኮቪድ-19 መጠቃቱ አልበቃ ብሎ መርዛማ በሆነ የኮብራ ዕባብ ተነድፎ ከፍተኛ የጤና እክል ውስጥ ይገኛል፡፡ እነዚህ ሁሉ አደገኛ በሽታዎች ያጋጠሙት ኢያን ጆንስ የተባለው ይህ ግለሰብ በምዕራባዊው የህንድ ክፍል በምትገኘው ራጃስታን ግዛት ውስጥ ባለች አንዲት መንደር ውስጥ ነው እጅግ አደገኛ በሚባል እባብ ለመነደፍ የበቃው፡፡ ምንም እንኳን ግለሰቡ ከተነደፈ በኋላም በህይወት መትረፍ ቢችልም አሁን ላይ ግን ማየት እንደተሳነው እና እግሮቹም ፓራላይዝድ መሆናቸው ተዘግቧል፡፡
ከደቡባዊ እንግሊዝ አይል ኦፍ ዌይት ደሴት የመጣው ግለሰቡ ለሁለት ሳምንታት ያህል በከፍተኛ ክትትል ውስጥ የቆየ ሲሆን አሁን ግን በህንድ የኮሮና ቫይረስ ታማሚዎች መብዛትን ተከትሎ ባጋጠመው የአልጋ ማነስ ሳብያ ሆስፒታሉን ሊለቅ ተገዷል፡፡ አያን ጆንስ በሁኔታው ከፍተኛ ፍርሀት ያደረበት ቢሆንም ሀኪሞቹ ሙሉ በሙሉ መዳን እንደሚችል ተስፋ አድርገዋል፡፡ “አባቴ ብርቱ ነው፤ በህንድ ቆይታው ከኮቪድ 19 በፊትም በወባ እና አደገኛ ትኩሳት ተይዞ ነበር” ሲል ልጁ ሰብ ጆንስ እነዚህ የጤና እክሎችን ተከትሎ ከሀገር እንዳይወጣ ያገደው ከፍተኛ የህክምና እዳን በመክፈል ዳግም ወደ እንግሊዝ ለመመለስ በተጀመረው የጎ ፈንድ ሚ እንቅስቃሴ ላይ ተናግሯል፡፡ እነዚህን በሽታዎች እየታገለ ሳለ ለህይወቱ አስጊ በሆነ ሁኔታ በእባብ መነደፉን ሲሰሙ ማመን እንዳቃታቸውም ጨምሮ ተናግሯል፡፡
ቀድሞ የጤና ባለሙያ የነበረው ኢያን ጆንስ በፈራጃስታን ግዛት ውስጥ ያሉ የእደ-ጥበብ ባለሙያዎች የእጅ ስራ ውጤታቸውን ወደ እንግሊዝ እንዲልኩ በማድረግ ከድህነት የማላቀቅ ስራዎችን በሚሰራ የበጎ አድራጎት ድርጅት ውስጥ እየሰራ ይገኛል፡፡ ወረርሺኙ በተከሰተ ጊዜ ተቋሙ በሚሰራበት አካባቢ ያለውን ማህበረሰብ እንዲረዳ ተመርጦ እዚያው በህንድ ውስጥ እንዲቆይ ተደርጓል፡፡
ህንድ በዓለማችን ቀዳሚዋ ሰዎች በአደገኛ እባቦች የሚነደፉባት ሀገር ስትሆን በየአመቱ በአማካኝ 58 ሺህ ዜጎቿ በአደገኛ እባቦች ምክንያት እንደሚሞቱባት የዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ያሳያል፡፡ በአሁኑ ሰዓትም ከ9 ሚሊዮን በላይ በኮቪድ-19 የተያዙ ተጠቂዎችን በማስመዝገብ ከአሜሪካ ቀጥላ በሁለተኛ ደረጃ ላይ የምትገኘው ህንድ 134,218 ዜጎቿን በቫይረሱ አጥታለች፡፡
ምንጭ፡ RT
-------------------
ለበጎ አድራጎት ስራ ወደ ህንድ ያቀና አንድ ብሪታንያዊ በወባ፣ ዳንጊ ትኩሳት፣ እና ኮቪድ-19 መጠቃቱ አልበቃ ብሎ መርዛማ በሆነ የኮብራ ዕባብ ተነድፎ ከፍተኛ የጤና እክል ውስጥ ይገኛል፡፡ እነዚህ ሁሉ አደገኛ በሽታዎች ያጋጠሙት ኢያን ጆንስ የተባለው ይህ ግለሰብ በምዕራባዊው የህንድ ክፍል በምትገኘው ራጃስታን ግዛት ውስጥ ባለች አንዲት መንደር ውስጥ ነው እጅግ አደገኛ በሚባል እባብ ለመነደፍ የበቃው፡፡ ምንም እንኳን ግለሰቡ ከተነደፈ በኋላም በህይወት መትረፍ ቢችልም አሁን ላይ ግን ማየት እንደተሳነው እና እግሮቹም ፓራላይዝድ መሆናቸው ተዘግቧል፡፡
ከደቡባዊ እንግሊዝ አይል ኦፍ ዌይት ደሴት የመጣው ግለሰቡ ለሁለት ሳምንታት ያህል በከፍተኛ ክትትል ውስጥ የቆየ ሲሆን አሁን ግን በህንድ የኮሮና ቫይረስ ታማሚዎች መብዛትን ተከትሎ ባጋጠመው የአልጋ ማነስ ሳብያ ሆስፒታሉን ሊለቅ ተገዷል፡፡ አያን ጆንስ በሁኔታው ከፍተኛ ፍርሀት ያደረበት ቢሆንም ሀኪሞቹ ሙሉ በሙሉ መዳን እንደሚችል ተስፋ አድርገዋል፡፡ “አባቴ ብርቱ ነው፤ በህንድ ቆይታው ከኮቪድ 19 በፊትም በወባ እና አደገኛ ትኩሳት ተይዞ ነበር” ሲል ልጁ ሰብ ጆንስ እነዚህ የጤና እክሎችን ተከትሎ ከሀገር እንዳይወጣ ያገደው ከፍተኛ የህክምና እዳን በመክፈል ዳግም ወደ እንግሊዝ ለመመለስ በተጀመረው የጎ ፈንድ ሚ እንቅስቃሴ ላይ ተናግሯል፡፡ እነዚህን በሽታዎች እየታገለ ሳለ ለህይወቱ አስጊ በሆነ ሁኔታ በእባብ መነደፉን ሲሰሙ ማመን እንዳቃታቸውም ጨምሮ ተናግሯል፡፡
ቀድሞ የጤና ባለሙያ የነበረው ኢያን ጆንስ በፈራጃስታን ግዛት ውስጥ ያሉ የእደ-ጥበብ ባለሙያዎች የእጅ ስራ ውጤታቸውን ወደ እንግሊዝ እንዲልኩ በማድረግ ከድህነት የማላቀቅ ስራዎችን በሚሰራ የበጎ አድራጎት ድርጅት ውስጥ እየሰራ ይገኛል፡፡ ወረርሺኙ በተከሰተ ጊዜ ተቋሙ በሚሰራበት አካባቢ ያለውን ማህበረሰብ እንዲረዳ ተመርጦ እዚያው በህንድ ውስጥ እንዲቆይ ተደርጓል፡፡
ህንድ በዓለማችን ቀዳሚዋ ሰዎች በአደገኛ እባቦች የሚነደፉባት ሀገር ስትሆን በየአመቱ በአማካኝ 58 ሺህ ዜጎቿ በአደገኛ እባቦች ምክንያት እንደሚሞቱባት የዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ያሳያል፡፡ በአሁኑ ሰዓትም ከ9 ሚሊዮን በላይ በኮቪድ-19 የተያዙ ተጠቂዎችን በማስመዝገብ ከአሜሪካ ቀጥላ በሁለተኛ ደረጃ ላይ የምትገኘው ህንድ 134,218 ዜጎቿን በቫይረሱ አጥታለች፡፡
ምንጭ፡ RT