የውድድር ጥሪ ለፈጠራ ባለሙያዎችና ተመራማሪዎች በሙሉ
==============================
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በCOVID-19 ቫይረስ መከላከል ላይ የተለያዩ የመፍትሔ ሃሳብና ፈጠራ ያላቸውን ተመራማሪዎችን እንዲሁም የፈጠራ ባለሙያዎችን አወዳድሮ በመደገፍ ሀገራችን ላይ የተጋረጠዉን ከፍተኛ አደጋ ለመዋጋት የፈጠራ ዉጤቶች በስፋትና በፍጥነት ተመርተው ጥቅም ላይ የሚዉሉበትን ሂደት ማመቻቸት ይፈልጋል።
በአሁኑ ሰዓት የኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ በፍጥነት እየተንሰራፋ እና ከፍተኛ ስጋት የሆነ የመጣዉን የ COVID-19 ቫይረስን ለመከላከልና ለመቆጣጠር እንዲሁም ስርጭቱን ለመግታት ከፍተኛ የሆነ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ መሆኑ ይታወቃል፡፡
በመሆኑም የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከተለያዩ አጋር ተቋማትና ድርጅቶች ጋር በጋራ በመሆን መፍትሄ ለማበጀት የሚያስችሉ ሃገር በቀል የሆኑ የፈጠራ ሃሳቦችን አወዳድሮ በቀጥታ ወደ ተግባር ለማስገባት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ በኮሮና ቫይረስ መከላከልና መቆጣጠር ላይ ሃሳብና ፈጠራ ያላችሁ በተቋማችን ድህረ ገፅ www.techin.gov.et/announcement ላይ እስከ ሚያዚያ 16፣ 2012 ዓ.ም ድረስ አስፈላጊውን መረጃ በማስገባት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
ይህ የዉድድር ፕሮግራም COVID-19 Solution Challenge የሚል ስያሜ ተሰጥቶት ከUNITED NATIONS DEVELOPMENT PROGRAMME (UNDP) ጋር በመተባበር እየተኪያሄደ የሚገኝ ነው።
ለበለጠ መረጃ በ 0111265762 ይደውሉ
ማሳሰቢያ፡ -በአካል መገኘት አስፈላጊ አይደለም
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር
==============================
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በCOVID-19 ቫይረስ መከላከል ላይ የተለያዩ የመፍትሔ ሃሳብና ፈጠራ ያላቸውን ተመራማሪዎችን እንዲሁም የፈጠራ ባለሙያዎችን አወዳድሮ በመደገፍ ሀገራችን ላይ የተጋረጠዉን ከፍተኛ አደጋ ለመዋጋት የፈጠራ ዉጤቶች በስፋትና በፍጥነት ተመርተው ጥቅም ላይ የሚዉሉበትን ሂደት ማመቻቸት ይፈልጋል።
በአሁኑ ሰዓት የኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ በፍጥነት እየተንሰራፋ እና ከፍተኛ ስጋት የሆነ የመጣዉን የ COVID-19 ቫይረስን ለመከላከልና ለመቆጣጠር እንዲሁም ስርጭቱን ለመግታት ከፍተኛ የሆነ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ መሆኑ ይታወቃል፡፡
በመሆኑም የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከተለያዩ አጋር ተቋማትና ድርጅቶች ጋር በጋራ በመሆን መፍትሄ ለማበጀት የሚያስችሉ ሃገር በቀል የሆኑ የፈጠራ ሃሳቦችን አወዳድሮ በቀጥታ ወደ ተግባር ለማስገባት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ በኮሮና ቫይረስ መከላከልና መቆጣጠር ላይ ሃሳብና ፈጠራ ያላችሁ በተቋማችን ድህረ ገፅ www.techin.gov.et/announcement ላይ እስከ ሚያዚያ 16፣ 2012 ዓ.ም ድረስ አስፈላጊውን መረጃ በማስገባት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
ይህ የዉድድር ፕሮግራም COVID-19 Solution Challenge የሚል ስያሜ ተሰጥቶት ከUNITED NATIONS DEVELOPMENT PROGRAMME (UNDP) ጋር በመተባበር እየተኪያሄደ የሚገኝ ነው።
ለበለጠ መረጃ በ 0111265762 ይደውሉ
ማሳሰቢያ፡ -በአካል መገኘት አስፈላጊ አይደለም
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር
ለማሽተትና ለመቅመስ መቸገር የመጀመሪያው የኮሮናቫይረስ ምልክት ሊሆን እንደሚችል አንድ ጥናት አረጋገጠ
===================================
ቀደም ብለው ከተረጋገጡት የኮቪድ 19 ምልክቶች በተጨማሪ በቅርቡ በተለያዩ ሚዲያዎች ለማሽተትና ለመቅመስ መቸገር ሌላኛዎቹ የኮሮናቫይረስ ቀላል ምልክቶች ሊሆኑ እንደሚችሉ ሲዘገብ ቆይቷል፡፡ ነግር ግን እነዚህ ምልክቶች በቫይረሱ የተጠቃ ሰው ለመጀመሪያ ጊዜ የሚያሳያቸው ቀላል ምልክት ስለመሆናቸው በምርምር ባለመረጋገጡ የተነሳ ተማራመሪዎች ተጨማሪ ጥናቶችን ማካሄድ የግድ ብሏቸዋል፡፡
ይህ አዲስ ጥናት በፈረንጆቹ ሚያዚያ 12 ፎረም ኦፍ አለርጂ ኤንድ ራይኖሎጂ በተሰኘ አለምአቀፍ ጆርናል የታተመ ጥናት ሲሆን፤ ለማሽተትና ለመቅመስ መቸገር ቀደም ብለው ከሚታዩ የኮሮናቫይረስ ቀላል ምልክቶች የመጀመሪያዎቹ ስለመሆናቸውም የሚያትት ነው፡፡ የጥናት ቡድኑ እንደሚለው ከሆነ ለማሽተት የሚቸገሩ ሰዎች እንዲሁ ጨዋማ ነገሮች እና ጣፋጭነት ያላቸውን የተለያዩ ጣእሞች የመለየት አቅም ሊኖራቸው ቢችልም፤ የተለየ ፍሌቨር ያላቸውን ነገሮች ለመለየት እንደሚከብዳቸው ያስረዳል፡፡ ይህም ሁሉም ለማሽተት የሚቸገሩ ሰዎች በተመሳሳይ መልኩ ጣዕም የመለየት ችግር እንዲታይባቸው ያደርጋል፡፡
በጥናቱ ላይ 1,480 የሚጠጉ ከጉንፋንና መሰል በሽታዎች ጋር የተያያዙ ምልክቶች የታዩባቸው ታካሚዎች የተሳተፉ ሲሆን፤ በኮቪድ 19 መያዛቸውን ለማረጋገጥም በሳንዲያጎ የጤና ማዕከል ምርመራ ተደርጎላቸው ነበር፡፡ ታዲያ በውጤቱ መሰረት 102 የሚሆኑት ታካሚዎች የኮሮናቫይረስ ሲገኝባቸው ከእነዚህ ውስጥ ደግሞ 59 የሚሆኑት የማሽተት ችግር እንደታየባቸው አጥኙዎቹ ገልፀዋል፡፡ በዚህ ጥናት ላይ በኮሮናቫይረስ ተጠቅተው የማሽተትና የመቅመስ ችግር የታየባቸው ታካሚዎች 68% እና 71% የሚሆኑት ሲሆኑ፤ በአንፃሩ በኮሮናቫይረስ ካልተያዙት 1300 በላይ ታከሚዎች ውስጥ የማሽተትና የመቅመስ ቸግር የታየባቸው 16% እና 17% የሚሆኑት ብቻ ናቸው፡፡ ይህ ደግሞ ሽታን እና ጣዕምን የመለየት ችግሮች ከሌሎች በሽታዎች በተለየ በኮሮናቫይረስ ላይ በቀዳሚነት የሚታዩ ምልክቶች እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል፡፡
ከዚህ ጋር አያይዘው የጥናቱ ዋና መሪ ዶ/ር ካሮል ያን እንደሚሉት በጥናታችን ውጤት መሰረት የማሽተትና የመቅመስ ችግር የታየባቸው ሰዎች ከሌሎች በሽታዎች ይልቅ በኮቪድ 19 ስለመጠቃታቸው 10 እጥፍ የሚያረጋግጡበት ጉዳይ ነው ብለዋል፡፡ እንደሳቸው ሃሳብ ከሆነ የማሽተትና የመቅመስ ችግሮች በቫይረሱ ተጠቂዎች ላይ ከ2 እስከ 4 ሳምንታት በሚቆየው የማገገሚያ ጊዜ ውስጥ ቀድመው የሚጠፉ የበሽታው ምልክቶች ቢሆኑም፤ በመጀመሪያው ሳምንት ላይ ግን በጉልህ (profoundly) የሚታዩ ምልክቶች መሆነቸውን ማወቅ ያስፈልጋል ይላሉ፡፡ በመሆኑም ቫይረሱን በመከላከል ሂደት ውስጥ ብዙዎች እንዲህ ያሉ ቀላል ምልክቶች ሲመለከቱ ቸል ብሎ ከማለፍ ይልቅ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እና የጤና በለሙያዎችም መሰል ምልክቶች የሚታዩባቸውን ሰዎች እንደሌሎቹ የበሽታው ምልክቶች በመቁጠር ምርመራ እንዲደርጉ ምክራቸውን ይለግሳሉ፡፡
ምንጭ፡ Live Science
===================================
ቀደም ብለው ከተረጋገጡት የኮቪድ 19 ምልክቶች በተጨማሪ በቅርቡ በተለያዩ ሚዲያዎች ለማሽተትና ለመቅመስ መቸገር ሌላኛዎቹ የኮሮናቫይረስ ቀላል ምልክቶች ሊሆኑ እንደሚችሉ ሲዘገብ ቆይቷል፡፡ ነግር ግን እነዚህ ምልክቶች በቫይረሱ የተጠቃ ሰው ለመጀመሪያ ጊዜ የሚያሳያቸው ቀላል ምልክት ስለመሆናቸው በምርምር ባለመረጋገጡ የተነሳ ተማራመሪዎች ተጨማሪ ጥናቶችን ማካሄድ የግድ ብሏቸዋል፡፡
ይህ አዲስ ጥናት በፈረንጆቹ ሚያዚያ 12 ፎረም ኦፍ አለርጂ ኤንድ ራይኖሎጂ በተሰኘ አለምአቀፍ ጆርናል የታተመ ጥናት ሲሆን፤ ለማሽተትና ለመቅመስ መቸገር ቀደም ብለው ከሚታዩ የኮሮናቫይረስ ቀላል ምልክቶች የመጀመሪያዎቹ ስለመሆናቸውም የሚያትት ነው፡፡ የጥናት ቡድኑ እንደሚለው ከሆነ ለማሽተት የሚቸገሩ ሰዎች እንዲሁ ጨዋማ ነገሮች እና ጣፋጭነት ያላቸውን የተለያዩ ጣእሞች የመለየት አቅም ሊኖራቸው ቢችልም፤ የተለየ ፍሌቨር ያላቸውን ነገሮች ለመለየት እንደሚከብዳቸው ያስረዳል፡፡ ይህም ሁሉም ለማሽተት የሚቸገሩ ሰዎች በተመሳሳይ መልኩ ጣዕም የመለየት ችግር እንዲታይባቸው ያደርጋል፡፡
በጥናቱ ላይ 1,480 የሚጠጉ ከጉንፋንና መሰል በሽታዎች ጋር የተያያዙ ምልክቶች የታዩባቸው ታካሚዎች የተሳተፉ ሲሆን፤ በኮቪድ 19 መያዛቸውን ለማረጋገጥም በሳንዲያጎ የጤና ማዕከል ምርመራ ተደርጎላቸው ነበር፡፡ ታዲያ በውጤቱ መሰረት 102 የሚሆኑት ታካሚዎች የኮሮናቫይረስ ሲገኝባቸው ከእነዚህ ውስጥ ደግሞ 59 የሚሆኑት የማሽተት ችግር እንደታየባቸው አጥኙዎቹ ገልፀዋል፡፡ በዚህ ጥናት ላይ በኮሮናቫይረስ ተጠቅተው የማሽተትና የመቅመስ ችግር የታየባቸው ታካሚዎች 68% እና 71% የሚሆኑት ሲሆኑ፤ በአንፃሩ በኮሮናቫይረስ ካልተያዙት 1300 በላይ ታከሚዎች ውስጥ የማሽተትና የመቅመስ ቸግር የታየባቸው 16% እና 17% የሚሆኑት ብቻ ናቸው፡፡ ይህ ደግሞ ሽታን እና ጣዕምን የመለየት ችግሮች ከሌሎች በሽታዎች በተለየ በኮሮናቫይረስ ላይ በቀዳሚነት የሚታዩ ምልክቶች እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል፡፡
ከዚህ ጋር አያይዘው የጥናቱ ዋና መሪ ዶ/ር ካሮል ያን እንደሚሉት በጥናታችን ውጤት መሰረት የማሽተትና የመቅመስ ችግር የታየባቸው ሰዎች ከሌሎች በሽታዎች ይልቅ በኮቪድ 19 ስለመጠቃታቸው 10 እጥፍ የሚያረጋግጡበት ጉዳይ ነው ብለዋል፡፡ እንደሳቸው ሃሳብ ከሆነ የማሽተትና የመቅመስ ችግሮች በቫይረሱ ተጠቂዎች ላይ ከ2 እስከ 4 ሳምንታት በሚቆየው የማገገሚያ ጊዜ ውስጥ ቀድመው የሚጠፉ የበሽታው ምልክቶች ቢሆኑም፤ በመጀመሪያው ሳምንት ላይ ግን በጉልህ (profoundly) የሚታዩ ምልክቶች መሆነቸውን ማወቅ ያስፈልጋል ይላሉ፡፡ በመሆኑም ቫይረሱን በመከላከል ሂደት ውስጥ ብዙዎች እንዲህ ያሉ ቀላል ምልክቶች ሲመለከቱ ቸል ብሎ ከማለፍ ይልቅ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እና የጤና በለሙያዎችም መሰል ምልክቶች የሚታዩባቸውን ሰዎች እንደሌሎቹ የበሽታው ምልክቶች በመቁጠር ምርመራ እንዲደርጉ ምክራቸውን ይለግሳሉ፡፡
ምንጭ፡ Live Science
የኮሮና መድሃኒትን ፍለጋ ለአራት ወራት በቤተሙከራ ብቻውን ያሳለፈው ተመራማሪ ጥረት
===================
የኮቪድ-19 ወረርሺኝ መነሳቱ ከታወጀበት ጊዜ አንስቶ በዓለማችን የተለያዩ ጥጎች የሚገኙ ተመራማሪዎች ክትባት እና መድሃኑቱን ለማግኘት ከፍተኛ መሰዋዕትነት እየከፈሉ ይገኛሉ፡፡ ለዛሬም የቫይረሱ መነሻ እንደሆነች በምትገመተው ዉሀን ከተማ ውስጥ መድሀኒት ፍለጋ ለአራት ወራት የደከመውን ተመራማሪ ቃል ይዘንልዎ መጥተናል፡፡
“ከጥር አንስቶ ለኮቪድ-19 የሚሆን መድሃኒትን ፍለጋ እያንዳዱን ቀናት በቤተ-ሙከራ ውስጥ አሳልፌያለው፡፡ በሙያዬ የስትራክቸራል ባዮሎጂስት እና ፋርማኮሎጂስት ነኝ፤ ኑሮዩም የወረርሺኙ ማዕከል በሆነችው ዉሀን፤ ቻይና በሚገኘው ኋንዦሆንግ የሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ካምፓስ ውስጥ ነው፡፡ በወርሀ ጥር ከተማዋ በተዘጋችበት ወቅት ባልደረቦቼ የቻይና አዲስ ዓመትን ለማክበር ሄደው (ከከተማ ወጥተው) ስለነበረ መመለስ አልቻሉም፡፡ አሁን በቤተ-ሙከራችን መስራት የምችለው ብቸኛው ሰው እኔ ነኝ፡፡
የመድሀኒት ፍለጋ ጉዞዬን የጀመርኩት ከኮምፒውተሬ ነበር፡፡ ከባልደረቦቼ ጋራ በመሆን ከሳርስ-ኮቭ-2 ቫይረስ ላይ የተወሰዱ ሞዴል ፕሮቲኖችን በመጠቀም በሺዎች የሚቆጠሩ ፍቃድ የተሰጣቸው መድሃኒቶችን መርምረናል፤ በፕሮቲኖቹ ተጣብቀው ቫይረሶቹ ህዋሳቶአችን (cells) እንዳያጠቁ የሚከላከሉትን ለማግኘት፡፡
ፍለጋዬን በቤተ ሙከራዬ አሸጋግሬዋለሁ፡፡ አሁን ፕሮቲኖች ኤክስፕረስ የሚያደርጉ (ህዋሳትን ማጣመር፣ ማሻሻል እና መቆጣጠር) ህዋሳትን እያሳደኩና በክሮሞቶግሪፊ ማሽኑ ውስጥ (ምስሉ ላይ በስተግራ የሚታየው) እያጣራዋቸው ነው፡፡ ፕሮቲኖችን ከተለያዩ መድሃኒቶች ጋራ ስቀላቅላቸው፤ ሌላ ማሽንን በመጠቀም መድሀኒቱ በፕሮቲኖቹ ላይ መጣበቅ አለመጣበቃቸውን አያለሁ፡፡ ሳደርግ እንደምታዩኝ በፕሮቲን-መድሃኒት ጥምረቱ ላይ የሚገኘውን ክሪስታል በማይክሮስኮፕ አማካኝነት እመለከታለሁ፡፡ በመቀጠልም በክሪስታል መልክ የሆነውን አካል በፈሳሽ ናይትሮጅን ውስጥ አቀዝቅዤ (ወደ በረዶ) ከታች በስተ ግራ በሚገኘው ሳጥን ውስጥ እከታቸዋለው፡፡
አሁን በዚህ ያለው መዘጋት (የከተማ) ስላበቃ፤ የክሪስታል አካላቱን መድሀኒት እና ፕሮቲኖች እንዴት እንደሚጠያበቁ ከሚመረምሩ አጥኚዎች ዘንድ ለመላክ አስቤያለሁ፡፡ በሻንጋይ የሚገኙ ተባባሪዎቼ የመድሀኒቶቹን የማዳን አቅም የህዋሳት እና አይጥ ኮቪድ-19 ሞዴሎችን በመፈተሸ ላይ ናቸው፡፡
በ20 ዲ.ሴ ሙቀት እንዲቆይ በተደረገውና ጠረኑ እስከ ህዋሳቴ ዘልቆ ገብቶ በሚሰማኝ በዚህ ክፍል ውስጥ በቀን ከአንድ እስከ ስምንት ሰዓት እቆያለሁ፡፡ ሴት ልጅ እና ሚስቴ ከእኔ ጋራ ይኖራሉ፡፡ ወንድ ልጄ ግን ከአያቶቹ ጋራ በሌላኛው የዉሀን ሰፈር ይኖራል፡፡ ከጥር መጀመሪያ አንስቶ እስካሁን አይቼው አላውቅም፡፡
ከዩኒቨርሲቱው ጋራ የተሳሰሩ አስር ሆስፒታሎች አሉ፤ ሁሉም ከፊት ሆነው ወረርሺኙን የመዋጋት ስራ እየሰሩ ናቸው፡፡ የድርሻዬን እንደምወጣ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡”
ምንጭ፡ Nature
ውድ ተከታታዮቻችን መዘናጋት ዋጋ ያስከፍለናልና ዛሬም ከሰዎች ጋራ ያሎትን አካላዊ ርቀት ይጠብቁ፤ እጅዎንም በየጊዜው በደንብ ይታጠቡ፤ ሌሎችም በባለሙያ የተነገሩ የጥንቃቄ እርምጃዎችን ይውሰዱ፡፡
===================
የኮቪድ-19 ወረርሺኝ መነሳቱ ከታወጀበት ጊዜ አንስቶ በዓለማችን የተለያዩ ጥጎች የሚገኙ ተመራማሪዎች ክትባት እና መድሃኑቱን ለማግኘት ከፍተኛ መሰዋዕትነት እየከፈሉ ይገኛሉ፡፡ ለዛሬም የቫይረሱ መነሻ እንደሆነች በምትገመተው ዉሀን ከተማ ውስጥ መድሀኒት ፍለጋ ለአራት ወራት የደከመውን ተመራማሪ ቃል ይዘንልዎ መጥተናል፡፡
“ከጥር አንስቶ ለኮቪድ-19 የሚሆን መድሃኒትን ፍለጋ እያንዳዱን ቀናት በቤተ-ሙከራ ውስጥ አሳልፌያለው፡፡ በሙያዬ የስትራክቸራል ባዮሎጂስት እና ፋርማኮሎጂስት ነኝ፤ ኑሮዩም የወረርሺኙ ማዕከል በሆነችው ዉሀን፤ ቻይና በሚገኘው ኋንዦሆንግ የሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ካምፓስ ውስጥ ነው፡፡ በወርሀ ጥር ከተማዋ በተዘጋችበት ወቅት ባልደረቦቼ የቻይና አዲስ ዓመትን ለማክበር ሄደው (ከከተማ ወጥተው) ስለነበረ መመለስ አልቻሉም፡፡ አሁን በቤተ-ሙከራችን መስራት የምችለው ብቸኛው ሰው እኔ ነኝ፡፡
የመድሀኒት ፍለጋ ጉዞዬን የጀመርኩት ከኮምፒውተሬ ነበር፡፡ ከባልደረቦቼ ጋራ በመሆን ከሳርስ-ኮቭ-2 ቫይረስ ላይ የተወሰዱ ሞዴል ፕሮቲኖችን በመጠቀም በሺዎች የሚቆጠሩ ፍቃድ የተሰጣቸው መድሃኒቶችን መርምረናል፤ በፕሮቲኖቹ ተጣብቀው ቫይረሶቹ ህዋሳቶአችን (cells) እንዳያጠቁ የሚከላከሉትን ለማግኘት፡፡
ፍለጋዬን በቤተ ሙከራዬ አሸጋግሬዋለሁ፡፡ አሁን ፕሮቲኖች ኤክስፕረስ የሚያደርጉ (ህዋሳትን ማጣመር፣ ማሻሻል እና መቆጣጠር) ህዋሳትን እያሳደኩና በክሮሞቶግሪፊ ማሽኑ ውስጥ (ምስሉ ላይ በስተግራ የሚታየው) እያጣራዋቸው ነው፡፡ ፕሮቲኖችን ከተለያዩ መድሃኒቶች ጋራ ስቀላቅላቸው፤ ሌላ ማሽንን በመጠቀም መድሀኒቱ በፕሮቲኖቹ ላይ መጣበቅ አለመጣበቃቸውን አያለሁ፡፡ ሳደርግ እንደምታዩኝ በፕሮቲን-መድሃኒት ጥምረቱ ላይ የሚገኘውን ክሪስታል በማይክሮስኮፕ አማካኝነት እመለከታለሁ፡፡ በመቀጠልም በክሪስታል መልክ የሆነውን አካል በፈሳሽ ናይትሮጅን ውስጥ አቀዝቅዤ (ወደ በረዶ) ከታች በስተ ግራ በሚገኘው ሳጥን ውስጥ እከታቸዋለው፡፡
አሁን በዚህ ያለው መዘጋት (የከተማ) ስላበቃ፤ የክሪስታል አካላቱን መድሀኒት እና ፕሮቲኖች እንዴት እንደሚጠያበቁ ከሚመረምሩ አጥኚዎች ዘንድ ለመላክ አስቤያለሁ፡፡ በሻንጋይ የሚገኙ ተባባሪዎቼ የመድሀኒቶቹን የማዳን አቅም የህዋሳት እና አይጥ ኮቪድ-19 ሞዴሎችን በመፈተሸ ላይ ናቸው፡፡
በ20 ዲ.ሴ ሙቀት እንዲቆይ በተደረገውና ጠረኑ እስከ ህዋሳቴ ዘልቆ ገብቶ በሚሰማኝ በዚህ ክፍል ውስጥ በቀን ከአንድ እስከ ስምንት ሰዓት እቆያለሁ፡፡ ሴት ልጅ እና ሚስቴ ከእኔ ጋራ ይኖራሉ፡፡ ወንድ ልጄ ግን ከአያቶቹ ጋራ በሌላኛው የዉሀን ሰፈር ይኖራል፡፡ ከጥር መጀመሪያ አንስቶ እስካሁን አይቼው አላውቅም፡፡
ከዩኒቨርሲቱው ጋራ የተሳሰሩ አስር ሆስፒታሎች አሉ፤ ሁሉም ከፊት ሆነው ወረርሺኙን የመዋጋት ስራ እየሰሩ ናቸው፡፡ የድርሻዬን እንደምወጣ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡”
ምንጭ፡ Nature
ውድ ተከታታዮቻችን መዘናጋት ዋጋ ያስከፍለናልና ዛሬም ከሰዎች ጋራ ያሎትን አካላዊ ርቀት ይጠብቁ፤ እጅዎንም በየጊዜው በደንብ ይታጠቡ፤ ሌሎችም በባለሙያ የተነገሩ የጥንቃቄ እርምጃዎችን ይውሰዱ፡፡
ኮቪድ-19 ከሞቱ ሰዎችም ሊተላልፍ እንደሚችል ጥናት አመላከተ
========================
ከቀናት በፊት የወጣ ጥናት በታይላንድ ባንኮክ የሚሰራ አንድ የሬሳ መርማሪ በቅርብ ለሞተ ሰው ሬሳ እንደተላለፈበት በተገመተ የኮሮና ቫይረስ መያዙን አመላክቷል፡፡ የሬሳ መርማሪው በኋላ ለሞት የተዳረገ ሲሆን ይህም የሬሳ ክፍል ውስጥ በሚሰሩ የህክምና ባለሙያዎች ላይ ሲከሰት የመጀመሪያው ሆኗል፡፡
የግለሰቡ በቫይረሱ መያዝ በተዘገበበት ወቅት ረዳት ነርሱን ጨምሮ በሀገሪቱ የነበሩ የታማሚዎች ቁጥር 272 ብቻ የነበረ መሆኑና አብዛኛዎቹም ከውጪ ሀገራት ገና መግባታቸው ስለነበረ ከሚሰራበት ሆስፒታል ውጪ በቫይረሱ የመያዙን ዕድል የጠበበ ያደርገዋል፡፡ እንደ ጥናቱ ከሆነ በሬሳ ክፍል የሚሰሩት የህክምና ባለሙያዎች ከታማሚዎቹ የባዮሎጂካል ቅንጣት/ሳምፕል አሊያም ሬሳ ጋራ ካላቸው ግንኙነት ውጪ ከቫይረሱ የመገናኘታቸው ዕድልም የጠበበ ነው፡፡
ትኩስ ሬሳ ኮቪድ-19ኝን ማስተላለፉ አስገራሚ እንዳልሆነባቸው የሚናገሩት በዴቪድ ጄፈን የህክምና ትምህርት ቤት ፕሮፌሰር የሆኑት ዶ/ር ኦቶ ያንግ መሟቾች ከህልፈታቸው በኋላ ቢያንስ ለሰዓታት ከፍ ሲልም ከቀናት በኋላ በሽታውን ሊያስተላልፉ እንደሚችሉ ያስረዳሉ፡፡
ቫይረሱ በሟቾች ሬሳ ውስጥ ለምን ያህል ጊዜ እንደሚቆይ በግልፅ አይታወቅም፡፡ በአለም የጤና ድርጅት መረጃ መሰረት መሰረት ሰዎችን ለህልፈት የሚዳርጉ ደቂቀ አካላት በሟቾች ሰውነት ውስጥ ያላቸው ቆይታ የአጭር ጊዜ እንደሆነ ያሳያል፤ በዚህ ረገድ ከፍተኛ ስጋት ካለባቸው እንደኮሌራና ኢቦላ ካሉት በሽታዎች ውጪ፡፡ ከተጠቂው ግለሰብ ሞት በኋላ ከሚተላለፉት ውስጥ በደም ንክኪ ይተላለፋሉ ብሎ ድርጅቱ ካስቀመጣቸው መካከል ሄፒታይተስ ቢ እና ሲ እንዲሁም ኤች አይ ቪ ቫይረሶች፣ የሳንባ ነቀርሳና የጨጓራና ሆድ ህመመ ኢንፌክሽኖች ይገኙበታል፡፡
የኮሮና የሟች ሰውነት ውስጥ የሚቆይበት ጊዜ መጥፎነቱ ለሬሳ ምርመራ ክፍል የህክምና ሰባለሙያዎች ብቻ አይደለም በቀብር ማስፈፀም ዙርያ ለሚሰሩም ጭምር እንጂ፡፡ ለምሳሌ የሪፖርቱን መውጣት ተከትሎ የቀብር ቦታዎች በኮሮና ምክንያት ለሞቱ ሰዎች ምንም አይነት የቀብር አገልግሎት እንደማይሰጡ አስታውቀዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የፎረንሲክ መርማሪዎች በቫይረሱ ምክንያት የሞቱ ሰዎችን በሚመረምሩበት ወቅት የጥንቃቄ እርምጃዎችነ ሊወስዱ እንደሚገባ ጥናቱ ጠቁሟል፤ ለምሳሌ የመከላከያ ልብስ፣ የጭንቅላት መሸፈኛ እና የፊት ጭምብልን መጠቀም፡፡ በማከልም በቀዶ ህክምና ክፍል የሚደረጉት የፅዳት እርምጃዎች በሙሉ በሬሳ ምርመራ ክፍሎችም ሊከወኑ እንደሚገባ አስቀምጧል፡፡
ምንጭ፡ Scientific American
========================
ከቀናት በፊት የወጣ ጥናት በታይላንድ ባንኮክ የሚሰራ አንድ የሬሳ መርማሪ በቅርብ ለሞተ ሰው ሬሳ እንደተላለፈበት በተገመተ የኮሮና ቫይረስ መያዙን አመላክቷል፡፡ የሬሳ መርማሪው በኋላ ለሞት የተዳረገ ሲሆን ይህም የሬሳ ክፍል ውስጥ በሚሰሩ የህክምና ባለሙያዎች ላይ ሲከሰት የመጀመሪያው ሆኗል፡፡
የግለሰቡ በቫይረሱ መያዝ በተዘገበበት ወቅት ረዳት ነርሱን ጨምሮ በሀገሪቱ የነበሩ የታማሚዎች ቁጥር 272 ብቻ የነበረ መሆኑና አብዛኛዎቹም ከውጪ ሀገራት ገና መግባታቸው ስለነበረ ከሚሰራበት ሆስፒታል ውጪ በቫይረሱ የመያዙን ዕድል የጠበበ ያደርገዋል፡፡ እንደ ጥናቱ ከሆነ በሬሳ ክፍል የሚሰሩት የህክምና ባለሙያዎች ከታማሚዎቹ የባዮሎጂካል ቅንጣት/ሳምፕል አሊያም ሬሳ ጋራ ካላቸው ግንኙነት ውጪ ከቫይረሱ የመገናኘታቸው ዕድልም የጠበበ ነው፡፡
ትኩስ ሬሳ ኮቪድ-19ኝን ማስተላለፉ አስገራሚ እንዳልሆነባቸው የሚናገሩት በዴቪድ ጄፈን የህክምና ትምህርት ቤት ፕሮፌሰር የሆኑት ዶ/ር ኦቶ ያንግ መሟቾች ከህልፈታቸው በኋላ ቢያንስ ለሰዓታት ከፍ ሲልም ከቀናት በኋላ በሽታውን ሊያስተላልፉ እንደሚችሉ ያስረዳሉ፡፡
ቫይረሱ በሟቾች ሬሳ ውስጥ ለምን ያህል ጊዜ እንደሚቆይ በግልፅ አይታወቅም፡፡ በአለም የጤና ድርጅት መረጃ መሰረት መሰረት ሰዎችን ለህልፈት የሚዳርጉ ደቂቀ አካላት በሟቾች ሰውነት ውስጥ ያላቸው ቆይታ የአጭር ጊዜ እንደሆነ ያሳያል፤ በዚህ ረገድ ከፍተኛ ስጋት ካለባቸው እንደኮሌራና ኢቦላ ካሉት በሽታዎች ውጪ፡፡ ከተጠቂው ግለሰብ ሞት በኋላ ከሚተላለፉት ውስጥ በደም ንክኪ ይተላለፋሉ ብሎ ድርጅቱ ካስቀመጣቸው መካከል ሄፒታይተስ ቢ እና ሲ እንዲሁም ኤች አይ ቪ ቫይረሶች፣ የሳንባ ነቀርሳና የጨጓራና ሆድ ህመመ ኢንፌክሽኖች ይገኙበታል፡፡
የኮሮና የሟች ሰውነት ውስጥ የሚቆይበት ጊዜ መጥፎነቱ ለሬሳ ምርመራ ክፍል የህክምና ሰባለሙያዎች ብቻ አይደለም በቀብር ማስፈፀም ዙርያ ለሚሰሩም ጭምር እንጂ፡፡ ለምሳሌ የሪፖርቱን መውጣት ተከትሎ የቀብር ቦታዎች በኮሮና ምክንያት ለሞቱ ሰዎች ምንም አይነት የቀብር አገልግሎት እንደማይሰጡ አስታውቀዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የፎረንሲክ መርማሪዎች በቫይረሱ ምክንያት የሞቱ ሰዎችን በሚመረምሩበት ወቅት የጥንቃቄ እርምጃዎችነ ሊወስዱ እንደሚገባ ጥናቱ ጠቁሟል፤ ለምሳሌ የመከላከያ ልብስ፣ የጭንቅላት መሸፈኛ እና የፊት ጭምብልን መጠቀም፡፡ በማከልም በቀዶ ህክምና ክፍል የሚደረጉት የፅዳት እርምጃዎች በሙሉ በሬሳ ምርመራ ክፍሎችም ሊከወኑ እንደሚገባ አስቀምጧል፡፡
ምንጭ፡ Scientific American
የሃር ምርት በኢትዮጵያና ፤ ፈተናዎቹ
==================
በኢትዮጵያ ለሺህ አመታት የተለያዩ ባህላዊና ሀይማኖታዊ ክዋዜዎች ውስጥ የራሱን ድርሻ ይይዛል፡፡ በኢትዮጵያ ሃርን ማምረት ከተጀመረም ሁለት አስርት ዓመታትን አስቆጥሯል፡፡ ምንም እንኳን በነዚህ ጊዜያት ውስጥ ዓመታዊ ምርቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ በፍጥነት በማሻቀብ ላይ ቢሆንም ኢትዮጵያ ለሃር እርሻ ምቹ ከሚያደርጓት የአየር ንብረትም ሆነ ሌሎች ገፀ-በረከቶቿ አንፃር ግን የሚመረተው የሃር መጠን አነስተኛ እንደሆነ የመረጃዎች ጥቆማ ነው፡፡ በጥሬ እቃነትም ሆነ ያለቀለት የሃር ምርትን ወደ ባህር ማዶ ልኮ ይህ ነው የሚባል ገቢ ለሐገራችን ማስገባት አልተቻለም፡፡ የተለያዩ መረጃዎችን ያየን እንደሆነ በምርትም ሆነ ለምርት በሚያስፈልጉ ግብዓቶች ላይ ያሉ ድክመቶችን መገንዘብ ይቻላል፡፡ ለምሳሌ ለኤሪ የሃር ትሎች ምግብነት የሚውለው የጉሎ ቅጠል (castor) ምርት በሐገራችን 1,300 ኪ.ግ በሄክታር ሲሆን ይህን ህንድ ውስጥ በሄክታር 2,500 ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ለኤሪ ብቻ ሳይሆን ለመልበሪ ሃር ምግብ በሚሆኑ ዕፅዋትም ተመሳሳይ የልዩነት ደረጃ ይስተዋላል፡፡ በሃር ቅርፊቶቹ ረገድም በኢትዮጵያ ያሉት የሃር ትሎች ከተቀረው ዓለም ያነሰ ነው፡፡
ለዚህ ዘርፍ ጠንክሮ አለመውጣት የተለያዩ ምክንያቶች ይሰነዘራሉ፡፡ ከነዚህ ውስጥ ቀዳሚው ኢትዮጵያ ያለው በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ኃይል እጥረት ነው፡፡ የሃር ግብርና ለሀገራችን አዲስ ከመሆኑ አንፃር በተለይ የሃር ትሎቹን ከማራባት አንስቶ ሃሩን ነጥሎ እስከማውጣት ያሉት የምርት ሂደቶች ለኛ እንግዳ የሆኑ ስልተ-ምርቶችን ይይዛሉ፡፡ ይህ የዕውቀት ክፍተት በትምህርትና ስልጠና መሟላት እስካልቻለ ድረስ በዘርፉ አጥጋቢ የሆነ ፍሬ ማግኘት አዳጋች ነው፡፡
ሁለተኛው የሃር ትሎቹ ከሚመገቧቸው እዕዋት ጋር የተገናኘ ነው፡፡ ውጤታማ የሃር ግብርናን ለማከናወን ትሎቹ የሚመገቧቸው እፅዋት ከፍተኛ የቅጠል ምርት የሚሰጡ፣ ተባይን የሚቋቋሙና የላቀ የመላመድ ብቃት ያላቸው መሆን ይገባቸዋል፡፡ በተጨማሪም በተለይ የሃር ምርት እንቅስቃሴው ባለበት ስፍራ ዕፅዋቶቹም የሚተከሉበት ስፍራ በስፋት እንዲኖር ያስፈልጋል፡፡ ሆኖም ይህ የመሬት አቅርቦት እጥረት እንዳለበት ለመረዳት ይቻላል፡፡ በተክሎቹ ዙሪያ የሚታዩት ሌሎቹ ክፍተቶች ዕፅዋቱን በተገቢው መልኩ ከማልማናት እና የዕፅዋት ዝርያዎቹን በተገቢው መልኩ አባዝቶ በቀላሉ ከምርት ስፍራው አቅራቢያ ከማድረስ አኳያ ነው፡፡
ሌላው ተጠቃሽ ክፍተት ከሃር ትሎቹ ጋር በተያያዘ ያለው ነው፡፡ ቀዳሚው የተሸሻሉ የሃር ትል ዝርያዎችን እና እንቁላሎቻቸውን በዓይነት በአይነት አባዝቶ ከምርት ስፍራዎቹ በአግባቡ ማቅረብ እንዲሁም በሃር ትሎቹ ላይ በመከሰት ጉዳት እያደረሱ ላሉት በሽታዎች መፍትሄ ማበጀት አለመቻሉ ነው፡፡ ይህን ያደርጉ ዘንድ ቅድሚያውን መውሰድ የነበረባቸው የትምህርት፣ ምርምር እና ስልጠና ተቋማትን ጨምሮ ሌሎችም አካላት ሚናቸውን በአግባቡ መወጣት አለመቻላቸው አንደኛው የክፍተቱ መንስኤ ነው፡፡
በጠቅላላው ለዘርፉ ተብሎ የተዘጋጀ ግልፅ ስትራቴጂ አለመኖር እንደ ዋና ችግር መቀመጥ ይገባዋል፡፡ ከዓመታት በፊት ኢትዮጵያን ጨምሮ በምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የሃር ምርት ላይ ትኩረቱን አድርጎ የተሰራ አንድ ጥናት እንዳመላከተው የሃር ምርትን ተንተርሶ የውጪ ምንዛሬን ለማግኘት ከመጎምዠት ያለፈ በቂ የፖሊሲ አቅጣጫና ተግባራዊ ስራ አልተሰራም፡፡ ከነዚህ መሰራት የነበረባቸው ወሳኝ ተግባራት ውስጥ ሚዲያና ሌሎች መንገዶችን ተጠቅሞ ዘርፉን በህብረተሰቡ ውስጥ ከማስረፅ አንስቶ በቂ የምርምር እና ስርፀት፣ የሀገር ውስጥ ገበያ ትስስርን የማጎልበት፣ የሃር ትሎቹን ከማራባት ጀምሮ የሃር ምርቱን ለገበያ እስከሚደርስ ድረስ ባሉት ምዕራፎች ዘርፉ የሚጠይቃቸውን ቴክኖሎጂዎች የማሰራጨት እንዲሁም አስፈላጊ ስልጠናና የዕውቀት ክፍተትን የሚደፍኑ እንቅስቃዎች ላይ የተሰሩት ስራዎች አነስተኛነትን በግንባር ቀደምነት መጥቀስ ተገቢ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በመሰረተ ልማት በተለይም በውሃና የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ረገድ እንዲሁም በዘርፉ ላይ በስፋት ከተሰማሩት ሀገራት ጋር የሚደረገው የልምድ ልውውጥ አናሳነት ላለው የምርት ውስንነት ተጠቃሽ መንስኤዎች ናቸው፡፡
ምንጭ፡ ቴክ ሳይንስ ቅፅ ፲፮ (ሙሉ መፅሐፉን ከዲጂታል ቤተ መፅሐፍታችን/ library.techin.gov.et ማግኘት ይችላሉ)
==================
በኢትዮጵያ ለሺህ አመታት የተለያዩ ባህላዊና ሀይማኖታዊ ክዋዜዎች ውስጥ የራሱን ድርሻ ይይዛል፡፡ በኢትዮጵያ ሃርን ማምረት ከተጀመረም ሁለት አስርት ዓመታትን አስቆጥሯል፡፡ ምንም እንኳን በነዚህ ጊዜያት ውስጥ ዓመታዊ ምርቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ በፍጥነት በማሻቀብ ላይ ቢሆንም ኢትዮጵያ ለሃር እርሻ ምቹ ከሚያደርጓት የአየር ንብረትም ሆነ ሌሎች ገፀ-በረከቶቿ አንፃር ግን የሚመረተው የሃር መጠን አነስተኛ እንደሆነ የመረጃዎች ጥቆማ ነው፡፡ በጥሬ እቃነትም ሆነ ያለቀለት የሃር ምርትን ወደ ባህር ማዶ ልኮ ይህ ነው የሚባል ገቢ ለሐገራችን ማስገባት አልተቻለም፡፡ የተለያዩ መረጃዎችን ያየን እንደሆነ በምርትም ሆነ ለምርት በሚያስፈልጉ ግብዓቶች ላይ ያሉ ድክመቶችን መገንዘብ ይቻላል፡፡ ለምሳሌ ለኤሪ የሃር ትሎች ምግብነት የሚውለው የጉሎ ቅጠል (castor) ምርት በሐገራችን 1,300 ኪ.ግ በሄክታር ሲሆን ይህን ህንድ ውስጥ በሄክታር 2,500 ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ለኤሪ ብቻ ሳይሆን ለመልበሪ ሃር ምግብ በሚሆኑ ዕፅዋትም ተመሳሳይ የልዩነት ደረጃ ይስተዋላል፡፡ በሃር ቅርፊቶቹ ረገድም በኢትዮጵያ ያሉት የሃር ትሎች ከተቀረው ዓለም ያነሰ ነው፡፡
ለዚህ ዘርፍ ጠንክሮ አለመውጣት የተለያዩ ምክንያቶች ይሰነዘራሉ፡፡ ከነዚህ ውስጥ ቀዳሚው ኢትዮጵያ ያለው በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ኃይል እጥረት ነው፡፡ የሃር ግብርና ለሀገራችን አዲስ ከመሆኑ አንፃር በተለይ የሃር ትሎቹን ከማራባት አንስቶ ሃሩን ነጥሎ እስከማውጣት ያሉት የምርት ሂደቶች ለኛ እንግዳ የሆኑ ስልተ-ምርቶችን ይይዛሉ፡፡ ይህ የዕውቀት ክፍተት በትምህርትና ስልጠና መሟላት እስካልቻለ ድረስ በዘርፉ አጥጋቢ የሆነ ፍሬ ማግኘት አዳጋች ነው፡፡
ሁለተኛው የሃር ትሎቹ ከሚመገቧቸው እዕዋት ጋር የተገናኘ ነው፡፡ ውጤታማ የሃር ግብርናን ለማከናወን ትሎቹ የሚመገቧቸው እፅዋት ከፍተኛ የቅጠል ምርት የሚሰጡ፣ ተባይን የሚቋቋሙና የላቀ የመላመድ ብቃት ያላቸው መሆን ይገባቸዋል፡፡ በተጨማሪም በተለይ የሃር ምርት እንቅስቃሴው ባለበት ስፍራ ዕፅዋቶቹም የሚተከሉበት ስፍራ በስፋት እንዲኖር ያስፈልጋል፡፡ ሆኖም ይህ የመሬት አቅርቦት እጥረት እንዳለበት ለመረዳት ይቻላል፡፡ በተክሎቹ ዙሪያ የሚታዩት ሌሎቹ ክፍተቶች ዕፅዋቱን በተገቢው መልኩ ከማልማናት እና የዕፅዋት ዝርያዎቹን በተገቢው መልኩ አባዝቶ በቀላሉ ከምርት ስፍራው አቅራቢያ ከማድረስ አኳያ ነው፡፡
ሌላው ተጠቃሽ ክፍተት ከሃር ትሎቹ ጋር በተያያዘ ያለው ነው፡፡ ቀዳሚው የተሸሻሉ የሃር ትል ዝርያዎችን እና እንቁላሎቻቸውን በዓይነት በአይነት አባዝቶ ከምርት ስፍራዎቹ በአግባቡ ማቅረብ እንዲሁም በሃር ትሎቹ ላይ በመከሰት ጉዳት እያደረሱ ላሉት በሽታዎች መፍትሄ ማበጀት አለመቻሉ ነው፡፡ ይህን ያደርጉ ዘንድ ቅድሚያውን መውሰድ የነበረባቸው የትምህርት፣ ምርምር እና ስልጠና ተቋማትን ጨምሮ ሌሎችም አካላት ሚናቸውን በአግባቡ መወጣት አለመቻላቸው አንደኛው የክፍተቱ መንስኤ ነው፡፡
በጠቅላላው ለዘርፉ ተብሎ የተዘጋጀ ግልፅ ስትራቴጂ አለመኖር እንደ ዋና ችግር መቀመጥ ይገባዋል፡፡ ከዓመታት በፊት ኢትዮጵያን ጨምሮ በምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የሃር ምርት ላይ ትኩረቱን አድርጎ የተሰራ አንድ ጥናት እንዳመላከተው የሃር ምርትን ተንተርሶ የውጪ ምንዛሬን ለማግኘት ከመጎምዠት ያለፈ በቂ የፖሊሲ አቅጣጫና ተግባራዊ ስራ አልተሰራም፡፡ ከነዚህ መሰራት የነበረባቸው ወሳኝ ተግባራት ውስጥ ሚዲያና ሌሎች መንገዶችን ተጠቅሞ ዘርፉን በህብረተሰቡ ውስጥ ከማስረፅ አንስቶ በቂ የምርምር እና ስርፀት፣ የሀገር ውስጥ ገበያ ትስስርን የማጎልበት፣ የሃር ትሎቹን ከማራባት ጀምሮ የሃር ምርቱን ለገበያ እስከሚደርስ ድረስ ባሉት ምዕራፎች ዘርፉ የሚጠይቃቸውን ቴክኖሎጂዎች የማሰራጨት እንዲሁም አስፈላጊ ስልጠናና የዕውቀት ክፍተትን የሚደፍኑ እንቅስቃዎች ላይ የተሰሩት ስራዎች አነስተኛነትን በግንባር ቀደምነት መጥቀስ ተገቢ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በመሰረተ ልማት በተለይም በውሃና የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ረገድ እንዲሁም በዘርፉ ላይ በስፋት ከተሰማሩት ሀገራት ጋር የሚደረገው የልምድ ልውውጥ አናሳነት ላለው የምርት ውስንነት ተጠቃሽ መንስኤዎች ናቸው፡፡
ምንጭ፡ ቴክ ሳይንስ ቅፅ ፲፮ (ሙሉ መፅሐፉን ከዲጂታል ቤተ መፅሐፍታችን/ library.techin.gov.et ማግኘት ይችላሉ)
የሁለት ሜትር ርቀር ኮሮናን ለመከላከል ላይበቃ ይችላል
===================
ሰሞኑን ከጤና ባለሙያዎች ሲነገር እንደሰማነው የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል 2 ሜትር/ ሁለት የአዋቂ እርምጃ ርቀትን መጠበቅ አስፈላጊ ነው፡፡ የዓለም ጤና ድርጅትን ጨምሮ የተለያዩ የጤና ተቋማትና ባለሙያዎች እንደሚገልፁት ዋነኛው የቫይረሱ መተላለፊያ መንገድ ቫይረሱ ያለባቸው ሰዎች ሲያስነጥሱና ሲያስሉ ከአፋቸው በሚወጣው ነጠብጣብ አማካኝነት ነው፡፡ በዚህ መሰረት ከሄድን የሁለት ሜትር ርቀትን መጠበቅ እጅን በተደጋጋሚ በደንብ መታጠብ ጋራ ተዳምሮ የበሽታውን ስርጭት ለመግታት ወይም ለመቀነስ በቂ ነው፡፡ ሆኖም አዲስ የወጣ ጥናት የሁለት ሜትር ርቀት በቂ ላይሆን እንደሚችል ጠቁሟል፡፡
ቫይረሱ በአየር ላይ የመንሳፈፍ ብቃቱ የጨመረ (airborne) ከሆነ ሰዎች በሚተነፍሱበትና በሚያወሩበት ወቅት በሚሰራጩ እጅግ አነስተኛ ነጠብጣቦች አማካኝነት ሊተላለፍ ይችላል፡፡ ሆኖም የተለያዩ ሁነቶች ሊወስኑት ይችላል፡፡ ለምሳሌ በቤት ውስጥ መሆንና አለመሆን፣ ጮክ ብሎ ማውራት፣ ጭንብል ማድረግ አለማድረግ፣ አየር በደንብ በሚዘዋወርበት ክፍል ውስጥ መሆን አለመሆን እና የቫይረሱ የመንሳፈፍ ብቃት፡፡
ሰዎች በሚተነፍሱበት፣ በሚያወሩበት፣ በሚዘፍኑበት፣ በሚያስሉበትና በሚያስነጥሱበት ወቅት በመጠናቸው የተለያዩ ጠብታዎች ከአፋቸው ይወጣል፡፡ እነዚህ ጠብታዎች በመጠናቸው አነስተኛና ከፍ ያሉ ተብለው ይመደባሉ፡፡ ታድያ ባለሙያዎችን ስጋት ውስጥ የከተተው ከ5 እስከ 10 ማይክሮ ሜትር ገደማ ዲያሜትር ያላቸው አነስተኞቹ ጠብታዎች ናቸው፡፡ ተለቅ ያሉት ጠብታዎች ብዙ ቫይረስና መሰል ቅንጣቶችን መሸከም ስለሚችሉ ከሰዎች ጋራ ሲገናኙ የማስያዝ እድላቸው ከፍ ያለ ነው፡፡ ሆኖም በዚህ መጠን ያሉ ጠብታዎች ክብደታቸው ስለሚጨምር ከአንድና ሁለት ሜትር በላይ ወደፊት ሳይጓዙ ከመሬት እንደሚወድቁ ይታመናል፡፡ እነዚህ ጠብታዎች ሰዎች በሚያስሉና በሚያስነጥሱበት ወቅት ከአፍ በመውጣት በቅርብ ያለ ሰውን ይበክላሉ፡፡ በተጨማሪም ሰዎች በሚያስሉበት ሰዓት አፋቸውን በሸፈኑበት መዳፋቸው ሌሎችን ሲጨብጡ፤ ወይም እቃ ሲነኩና ሌሎች ሰዎች እቃውን ነክተው ምግብ ሲበሉ፣ አይናቸው ሲያሻሹ፣ ወዘተ በበሽታው እንደሚጠቁ ይታመናል፡፡
ሰዎች ሲያወሩ ወይም ሲተነፍሱ የሚለቀቁ በ
መጠናቸው እጅግ አነስተኛ በሆኑ ጠብታዎችም ግን ሰዎችን የመበከለ፤ አቅም አላቸው፡፡ እነዚህ ጥቃቅን ጠብታዎች ግን ከአየር የሚመጣባቸውን ግፊት መቋቋም ስለማይችሉ ብዙውን ጊዜ ወደሰዎች ከአንድ ሜትር በላይ መቅረብ ሳይችሉ በዙርያቸው እንዲንዲዘዋወሩ ይገደዳሉ፡፡ ሆኖም ከአፍ የሚወጡት በአይን ከሚታይ እጅግ ጥቃቅን መጠን እስካላቸው ጠብታዎች ሁሉ ልክ ባልተረጋጋ አየር ምክንያት እንደሚፈጠሩ ደመናዎች በአየር ላይ ሊሰባሰቡ ይችላሉ፡፡ እነዚህ የጠብታዎች ስብስብ የሆኑ ያልተረጋጉ ደመናዎች ታድያ በውስጣቸው ያለው ሙቀት፣ እርጥበት እና አለመረጋጋት በአየር ላይ ለመጓዝ የሚበቃ ግፊትን ከሳል፣ ትንፋሽ፣ ማስነጠስ ወዘተ..ያገኛሉ፡፡ በዚህም መሰረት ነጠብጣቦቹ እስከ ስምንት ሜትር በአየር ላይ መጓዝ እንደሚችሉ በጆርናል ኦፍ አሜሪካን ሜዲካል አሶሴሽን የወጣው ጥናት ያሳያል፡፡ ታድያ ጠብታዎች ያን ያህል መጓዝ ከቻሉ ቫይረሶችም በእነርሱ ላይ ተሳፍረው ሊጓዙ ይችላሉ፡፡
በኒው ኢንግላንድ የህክምና ጆርናለ ላይ የወጣ ሌላ ጥናት በበኩሉ እጅግ ጥቃቅን ጠብታዎች የኮሮና ቫይረስን ተሸክመው ለሰዓታት በአየር ላይ ሊቆዩ እንደሚችሉ አውቋል፡፡ ይህ ግን በጥንቃቄ በተቀመረ ቤተ ሙከራ ውስጥ ነጠብጣቦቹን ከሰው ልጆች አተነፋፈስ በተለየ መልኩ በሚለቁ ማሽኖች የተሰራ በመሆኑ ጥችትን አስተናግዷል፡፡ ሆኖም መሰል ጥቃቅን ነጠብጣቦች ሁሌም በዙርያችን ያጋጥሙናል፤ ቫይረሱም በነዚህ ነጠብጣቦች ላይ የመቆየት እድል ሊኖረው ይችላል፡፡
መዝፈንም በተመሳሳይ ቫይረሱን የማሰራጨት ዕድል አለው፡፡ በአሜሪካኗ የዋሽንግተን ግዛት ውስጥ በአንድ ቦታ ተሰባስበው የነበሩ ድምፃዊያን ለዚህ አንድ ምሳሌ ናቸው፡፡ ድምፃዊያኑ ሲሰባሰቡ በመሀላቸው የ2 ሜትር ርቀትን ጠብቀው ነበር፡፡ ሆኖም ሲያቀነቅኑ እንደሆነ በሚታመን መልኩ 45 የቡድኑ አባላት በኮሮና ሲያዙ 2ቱ ሞተዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ሰዎች ከ2 ሜትር በላይ ተራርቀው ሲያወሩ ድምፃቸውን ከፍ ሊያደርጉ ይችላሉ፡፡ ይህ ደግሞ ከአፍ የሚወጡ ጠብታዎችን ስለሚያበዛ ስጋቱን ከፍ ያደርገዋል፡፡
ምንጭ፡ Science News
===================
ሰሞኑን ከጤና ባለሙያዎች ሲነገር እንደሰማነው የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል 2 ሜትር/ ሁለት የአዋቂ እርምጃ ርቀትን መጠበቅ አስፈላጊ ነው፡፡ የዓለም ጤና ድርጅትን ጨምሮ የተለያዩ የጤና ተቋማትና ባለሙያዎች እንደሚገልፁት ዋነኛው የቫይረሱ መተላለፊያ መንገድ ቫይረሱ ያለባቸው ሰዎች ሲያስነጥሱና ሲያስሉ ከአፋቸው በሚወጣው ነጠብጣብ አማካኝነት ነው፡፡ በዚህ መሰረት ከሄድን የሁለት ሜትር ርቀትን መጠበቅ እጅን በተደጋጋሚ በደንብ መታጠብ ጋራ ተዳምሮ የበሽታውን ስርጭት ለመግታት ወይም ለመቀነስ በቂ ነው፡፡ ሆኖም አዲስ የወጣ ጥናት የሁለት ሜትር ርቀት በቂ ላይሆን እንደሚችል ጠቁሟል፡፡
ቫይረሱ በአየር ላይ የመንሳፈፍ ብቃቱ የጨመረ (airborne) ከሆነ ሰዎች በሚተነፍሱበትና በሚያወሩበት ወቅት በሚሰራጩ እጅግ አነስተኛ ነጠብጣቦች አማካኝነት ሊተላለፍ ይችላል፡፡ ሆኖም የተለያዩ ሁነቶች ሊወስኑት ይችላል፡፡ ለምሳሌ በቤት ውስጥ መሆንና አለመሆን፣ ጮክ ብሎ ማውራት፣ ጭንብል ማድረግ አለማድረግ፣ አየር በደንብ በሚዘዋወርበት ክፍል ውስጥ መሆን አለመሆን እና የቫይረሱ የመንሳፈፍ ብቃት፡፡
ሰዎች በሚተነፍሱበት፣ በሚያወሩበት፣ በሚዘፍኑበት፣ በሚያስሉበትና በሚያስነጥሱበት ወቅት በመጠናቸው የተለያዩ ጠብታዎች ከአፋቸው ይወጣል፡፡ እነዚህ ጠብታዎች በመጠናቸው አነስተኛና ከፍ ያሉ ተብለው ይመደባሉ፡፡ ታድያ ባለሙያዎችን ስጋት ውስጥ የከተተው ከ5 እስከ 10 ማይክሮ ሜትር ገደማ ዲያሜትር ያላቸው አነስተኞቹ ጠብታዎች ናቸው፡፡ ተለቅ ያሉት ጠብታዎች ብዙ ቫይረስና መሰል ቅንጣቶችን መሸከም ስለሚችሉ ከሰዎች ጋራ ሲገናኙ የማስያዝ እድላቸው ከፍ ያለ ነው፡፡ ሆኖም በዚህ መጠን ያሉ ጠብታዎች ክብደታቸው ስለሚጨምር ከአንድና ሁለት ሜትር በላይ ወደፊት ሳይጓዙ ከመሬት እንደሚወድቁ ይታመናል፡፡ እነዚህ ጠብታዎች ሰዎች በሚያስሉና በሚያስነጥሱበት ወቅት ከአፍ በመውጣት በቅርብ ያለ ሰውን ይበክላሉ፡፡ በተጨማሪም ሰዎች በሚያስሉበት ሰዓት አፋቸውን በሸፈኑበት መዳፋቸው ሌሎችን ሲጨብጡ፤ ወይም እቃ ሲነኩና ሌሎች ሰዎች እቃውን ነክተው ምግብ ሲበሉ፣ አይናቸው ሲያሻሹ፣ ወዘተ በበሽታው እንደሚጠቁ ይታመናል፡፡
ሰዎች ሲያወሩ ወይም ሲተነፍሱ የሚለቀቁ በ
መጠናቸው እጅግ አነስተኛ በሆኑ ጠብታዎችም ግን ሰዎችን የመበከለ፤ አቅም አላቸው፡፡ እነዚህ ጥቃቅን ጠብታዎች ግን ከአየር የሚመጣባቸውን ግፊት መቋቋም ስለማይችሉ ብዙውን ጊዜ ወደሰዎች ከአንድ ሜትር በላይ መቅረብ ሳይችሉ በዙርያቸው እንዲንዲዘዋወሩ ይገደዳሉ፡፡ ሆኖም ከአፍ የሚወጡት በአይን ከሚታይ እጅግ ጥቃቅን መጠን እስካላቸው ጠብታዎች ሁሉ ልክ ባልተረጋጋ አየር ምክንያት እንደሚፈጠሩ ደመናዎች በአየር ላይ ሊሰባሰቡ ይችላሉ፡፡ እነዚህ የጠብታዎች ስብስብ የሆኑ ያልተረጋጉ ደመናዎች ታድያ በውስጣቸው ያለው ሙቀት፣ እርጥበት እና አለመረጋጋት በአየር ላይ ለመጓዝ የሚበቃ ግፊትን ከሳል፣ ትንፋሽ፣ ማስነጠስ ወዘተ..ያገኛሉ፡፡ በዚህም መሰረት ነጠብጣቦቹ እስከ ስምንት ሜትር በአየር ላይ መጓዝ እንደሚችሉ በጆርናል ኦፍ አሜሪካን ሜዲካል አሶሴሽን የወጣው ጥናት ያሳያል፡፡ ታድያ ጠብታዎች ያን ያህል መጓዝ ከቻሉ ቫይረሶችም በእነርሱ ላይ ተሳፍረው ሊጓዙ ይችላሉ፡፡
በኒው ኢንግላንድ የህክምና ጆርናለ ላይ የወጣ ሌላ ጥናት በበኩሉ እጅግ ጥቃቅን ጠብታዎች የኮሮና ቫይረስን ተሸክመው ለሰዓታት በአየር ላይ ሊቆዩ እንደሚችሉ አውቋል፡፡ ይህ ግን በጥንቃቄ በተቀመረ ቤተ ሙከራ ውስጥ ነጠብጣቦቹን ከሰው ልጆች አተነፋፈስ በተለየ መልኩ በሚለቁ ማሽኖች የተሰራ በመሆኑ ጥችትን አስተናግዷል፡፡ ሆኖም መሰል ጥቃቅን ነጠብጣቦች ሁሌም በዙርያችን ያጋጥሙናል፤ ቫይረሱም በነዚህ ነጠብጣቦች ላይ የመቆየት እድል ሊኖረው ይችላል፡፡
መዝፈንም በተመሳሳይ ቫይረሱን የማሰራጨት ዕድል አለው፡፡ በአሜሪካኗ የዋሽንግተን ግዛት ውስጥ በአንድ ቦታ ተሰባስበው የነበሩ ድምፃዊያን ለዚህ አንድ ምሳሌ ናቸው፡፡ ድምፃዊያኑ ሲሰባሰቡ በመሀላቸው የ2 ሜትር ርቀትን ጠብቀው ነበር፡፡ ሆኖም ሲያቀነቅኑ እንደሆነ በሚታመን መልኩ 45 የቡድኑ አባላት በኮሮና ሲያዙ 2ቱ ሞተዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ሰዎች ከ2 ሜትር በላይ ተራርቀው ሲያወሩ ድምፃቸውን ከፍ ሊያደርጉ ይችላሉ፡፡ ይህ ደግሞ ከአፍ የሚወጡ ጠብታዎችን ስለሚያበዛ ስጋቱን ከፍ ያደርገዋል፡፡
ምንጭ፡ Science News
ሲጠበቅ የነበረው የኮቪድ-19 መድሃኒት ውጤት ሳያሳይ ቀረ
==========================
በጥቂት ወራት ዕድሜው መላውን ዓለም ያዳረሰውንና እስካሁኑ ሰዓትም ከ2.7 ሚሊዮን ሰዎችን አጥቅቶ ከ191 ሺህ በላይ የሚሆኑትን ህይወት ለወሰደው ኮቪድ-19 ኢትዮጵያን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት እና ተቋማቶቻቸው መድሀኒትና ክትባት የማግኘት ሩጫ ላይ ናቸው፡፡ ታድያ ለኮሮና ቫይረስ ተብለው ሲዘጋጁ ከነበሩት መድሃኒቶች መካከል በቀዳሚነት የሚቀመጠው ሬምዲሲቪየር የተባለው መድሃኒት በመጀመሪያ ሙሉ ሙከራው ውጤት ሳያሳይ ቀርቷል፡፡ ሬምዲሲቪየርን የወሰዱና ያልወሰዱ 237 ታማሚዎችን ያሳተፈው የመድሀኒቱ ሙከራ ሳይሳካ ሲቀር ሙከራውም በሚያስከትላቸው የጎንዮሽ ጉዳቶች ምክንያት እንዲቋረጥ ተደርጓል፡፡
የመድሀኒቱ ያለመሳካት ዜና በዓለም የጤና ድርጅት የክሊኒካል ሙከራዎች የመረጃ ቋት (ዳታቤዝ) ላይ ተለጥፎ የነበረ ቢሆንም በኋላ እንዲነሳ ተደርጓል፡፡ የድርጅቱ ቃል አቀባይ ታሪክ ጃስሬቪች ሪፖርቱ በስህተት ያለጊዜው መጫኑን ተናግረዋል፡፡ “ለዓለም የጤና ድርጅት በበሚፅፉ ሰዎች የተዘጋጀው ሰነድ በስህተት በድርጅቱ ድረ-ገፁ ላይ የተጫነ ሲሆን ስህተቱ እንደታወቀ እንዲወርድ ተደርጓል” ብለዋለ ቃል አቀባዩ፡፡ አክለውም ፅሁፉ ግምገማ እየተደረገበት መሆኑንና የዓለም የጤና ድርጅትም አስተያየት ከመስጠቱ በፊት ውጤቱን እየተጠባበቀ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ጊላድ ሳይንስ በተባለው የአሜሪካን ኩባንያ የተዘጋጀው ይህ መድሃኒት ከዚህ ቀደምም በኢቦላ ላይ የተሞከረ ፀረ ቫይረስ መድሀኒት ነው፡፡ በዚያ ወቅትም በተመሳሳይ ውጤት ሳያሳይ ቀርቶ ነበር፡፡ በኮቪድ-19 ላይ የሚሰራ መድሃኒትን ለማግኘት በሚደረገው ሩጫ ብዙ ሀኪሞች የሙከራው ውጤትን ሳይጠብቁ ለታማሚዎች ሬምዲሲቪየርን ሲሰጡ ቆይተዋል፡፡ ለመድሀኒቱ በነበረው ከፍተኛ ተስፋ የተነሳም መድሀኒቱ በዓለም ዙርያ እጥረት ሲከሰትበት ለከሮና መፍትሄ ሊሆኑ ይችላሉ የተባሉ መፍትሄዎች በመሞከር ቀዳሚ የሆነው የኦክስፎርድ ማዕከል ተመራማሪዎችም መድሀኒቱን ማግኘት ባለመቻላቸው ምክንያት ጥናት ሊያደርጉበት አልቻሉም ነበር፡፡ በቻይና ተደረገው ሙከራ ታድያ ችኮላዎችን ሊገታ ይችላል፡፡ ሆኖም አምራች ግን አሁንም ቢሆን መድሃኒቱ ውጤታማ ሊሆን እንደሚችል የሚያሳዩ ምልክቶች መኖራቸውንና በተለይም የከፋ ምልክት በማይታይባቸው የበሽታው ታማሚዎች ዘንድ ጥቅም ሊኖረው እንደሚችል ገልጿል፡፡
በሙከራው በዘፈቀደ የተመረጡ 158 ታማሚዎች መድሀኒቱን እንዲወስዱ ታጭተው የነበረ ሲሆን ሌሎች 79 ታማሚዎች ደግሞ ፍቱንነት የሌለው መድሀኒትን (Placebo) ተሰጥቷቸዋል፡፡ በውጤቱም በሁለቱም ቡድኖች መካከል የድህነት ውጤት ልዩነት ሳይታይ ቀርቷል፡፡ ሬምዲሲቪየርን ከወሰዱት መካከል 14 በመቶው ህይወታቸው ሲያልፍ በአንፃሩ ካልወሰዱት ውስጥ 13 በመቶው ሞተዋል፡፡ በጥናቱ በሆስፒታል ተኝተው ህክምና በሚከታተሉ ታማሚዎች ላይ መሞከሩንና መድሃኒቱም ምንም አይነት ከቫይረሱም ሆነ ህክምና ጋር የተያያዘ ውጤት አለማሳየቱ በዓለም የጤና ድርጅት ድረ-ገፅ ላይ የወጣው ፅሁፍ አሳይቷል፡፡ መድሀኒቱን እንዲወስዱ ከታጩት 158 ታማሚዎች መካከልም 18ቱ ብቻ እንዲወስዱት ከተደረገ በኋላ ባመጣው ጉዳት ምክንያት መሰጠቱ እንዲቆም ሆኗል፡፡ በአጭሩ በተፃፈው ሪፖርት ውስጥ በጎንዮሽ ጉዳቱ ላይ ዝርዝር መረጃ አልቀረበም፡፡
ከአንድ ሳምንት በፊት ራሱ ጊላድ በ125 ታማሚዎች ላይ ባደረገው የሬምዲሲቪየር ሙከራ በቺካጎ የሚገኙ ሀኪሞችን ቀልብ ስቦ ነበር፡፡ የሙከራው አካል የነበሩት ሁሉም ታማሚዎች በአንድ ሳምንት ውስጥ ከሆስፒታል ድነው ወጥተዋል፡፡ ሆኖም በቻይናው ሙከራ እንደተደረገው ፍቱንነት የሌላቸው መድሃኒቶች ስላልቀረቡ ታማሚዎቹ ድነው የወጡት በሬምዲሲቪየር ምክንያት መሆን አለመሆኑን ተመራማሪዎች ሊያረጋግጡ አልቻሉም ነበር፡፡
ሬምዲሲቪየር እጅጉን ተስፋ ተጥሎበት የነበረና ከዶክተር እስከ ፖለቲከኛው ለኮሮና ለታማሚዎች እንዲሰጥ በስፋት ሲገፋ ቆይቷል፡፡ በተመሳሳይ ፀረ-ወባ የሆነው የክሎሮኩዊን መድሀኒት መራዛማነቱ ያነሰ አምሳያ የሆነው ሀይድሮክሲክሎሮኩዊን ለኮሮና ታማሚዎች ለመስጠች ችኮላ ነበረ፡፡ ይህም ያስከተለው የጤና ጉዳት እንዳለ ሆኖ፤ መድሀኒቱ ያስፈልጋቸው የነበሩ ሉፐስ የተባለ የሰውነት የበሽታ የመከላከል አቅምን የሚያጠቃ በሽታ ታማሚዎች እጥረት እንዲያጋጥማቸው አድርጓል፡፡ ታድያ በመድሃኒቶች ላይ ስርዓቱን የጠበቀ ሙከራ እንዲደረግ የሚሹ ተመራማሪዎች ይህ ካልተደረገ በስተቀር ከዚህ ቀደም የተሞከሩ መድሀኒቶችን እንኳን እንዲህ እንደኮሮና ገና በደንብ ላልታወቁ በሽታዎች የመጠቀምን ጉዳት ለማሳያነት እንደሚጠቀሙበት ይገመታል፡፡
ምንጭ፡ The Guardian
ውድ ተከታታዮቻችን መዘናጋት ዋጋ ያስከፍለናልና ዛሬም ከሰዎች ጋራ ያሎትን አካላዊ ርቀት ይጠብቁ፤ እጅዎንም በየጊዜው በደንብ ይታጠቡ፤ ሌሎችም በባለሙያ የተነገሩ የጥንቃቄ እርምጃዎችን ይውሰዱ፡፡
==========================
በጥቂት ወራት ዕድሜው መላውን ዓለም ያዳረሰውንና እስካሁኑ ሰዓትም ከ2.7 ሚሊዮን ሰዎችን አጥቅቶ ከ191 ሺህ በላይ የሚሆኑትን ህይወት ለወሰደው ኮቪድ-19 ኢትዮጵያን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት እና ተቋማቶቻቸው መድሀኒትና ክትባት የማግኘት ሩጫ ላይ ናቸው፡፡ ታድያ ለኮሮና ቫይረስ ተብለው ሲዘጋጁ ከነበሩት መድሃኒቶች መካከል በቀዳሚነት የሚቀመጠው ሬምዲሲቪየር የተባለው መድሃኒት በመጀመሪያ ሙሉ ሙከራው ውጤት ሳያሳይ ቀርቷል፡፡ ሬምዲሲቪየርን የወሰዱና ያልወሰዱ 237 ታማሚዎችን ያሳተፈው የመድሀኒቱ ሙከራ ሳይሳካ ሲቀር ሙከራውም በሚያስከትላቸው የጎንዮሽ ጉዳቶች ምክንያት እንዲቋረጥ ተደርጓል፡፡
የመድሀኒቱ ያለመሳካት ዜና በዓለም የጤና ድርጅት የክሊኒካል ሙከራዎች የመረጃ ቋት (ዳታቤዝ) ላይ ተለጥፎ የነበረ ቢሆንም በኋላ እንዲነሳ ተደርጓል፡፡ የድርጅቱ ቃል አቀባይ ታሪክ ጃስሬቪች ሪፖርቱ በስህተት ያለጊዜው መጫኑን ተናግረዋል፡፡ “ለዓለም የጤና ድርጅት በበሚፅፉ ሰዎች የተዘጋጀው ሰነድ በስህተት በድርጅቱ ድረ-ገፁ ላይ የተጫነ ሲሆን ስህተቱ እንደታወቀ እንዲወርድ ተደርጓል” ብለዋለ ቃል አቀባዩ፡፡ አክለውም ፅሁፉ ግምገማ እየተደረገበት መሆኑንና የዓለም የጤና ድርጅትም አስተያየት ከመስጠቱ በፊት ውጤቱን እየተጠባበቀ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ጊላድ ሳይንስ በተባለው የአሜሪካን ኩባንያ የተዘጋጀው ይህ መድሃኒት ከዚህ ቀደምም በኢቦላ ላይ የተሞከረ ፀረ ቫይረስ መድሀኒት ነው፡፡ በዚያ ወቅትም በተመሳሳይ ውጤት ሳያሳይ ቀርቶ ነበር፡፡ በኮቪድ-19 ላይ የሚሰራ መድሃኒትን ለማግኘት በሚደረገው ሩጫ ብዙ ሀኪሞች የሙከራው ውጤትን ሳይጠብቁ ለታማሚዎች ሬምዲሲቪየርን ሲሰጡ ቆይተዋል፡፡ ለመድሀኒቱ በነበረው ከፍተኛ ተስፋ የተነሳም መድሀኒቱ በዓለም ዙርያ እጥረት ሲከሰትበት ለከሮና መፍትሄ ሊሆኑ ይችላሉ የተባሉ መፍትሄዎች በመሞከር ቀዳሚ የሆነው የኦክስፎርድ ማዕከል ተመራማሪዎችም መድሀኒቱን ማግኘት ባለመቻላቸው ምክንያት ጥናት ሊያደርጉበት አልቻሉም ነበር፡፡ በቻይና ተደረገው ሙከራ ታድያ ችኮላዎችን ሊገታ ይችላል፡፡ ሆኖም አምራች ግን አሁንም ቢሆን መድሃኒቱ ውጤታማ ሊሆን እንደሚችል የሚያሳዩ ምልክቶች መኖራቸውንና በተለይም የከፋ ምልክት በማይታይባቸው የበሽታው ታማሚዎች ዘንድ ጥቅም ሊኖረው እንደሚችል ገልጿል፡፡
በሙከራው በዘፈቀደ የተመረጡ 158 ታማሚዎች መድሀኒቱን እንዲወስዱ ታጭተው የነበረ ሲሆን ሌሎች 79 ታማሚዎች ደግሞ ፍቱንነት የሌለው መድሀኒትን (Placebo) ተሰጥቷቸዋል፡፡ በውጤቱም በሁለቱም ቡድኖች መካከል የድህነት ውጤት ልዩነት ሳይታይ ቀርቷል፡፡ ሬምዲሲቪየርን ከወሰዱት መካከል 14 በመቶው ህይወታቸው ሲያልፍ በአንፃሩ ካልወሰዱት ውስጥ 13 በመቶው ሞተዋል፡፡ በጥናቱ በሆስፒታል ተኝተው ህክምና በሚከታተሉ ታማሚዎች ላይ መሞከሩንና መድሃኒቱም ምንም አይነት ከቫይረሱም ሆነ ህክምና ጋር የተያያዘ ውጤት አለማሳየቱ በዓለም የጤና ድርጅት ድረ-ገፅ ላይ የወጣው ፅሁፍ አሳይቷል፡፡ መድሀኒቱን እንዲወስዱ ከታጩት 158 ታማሚዎች መካከልም 18ቱ ብቻ እንዲወስዱት ከተደረገ በኋላ ባመጣው ጉዳት ምክንያት መሰጠቱ እንዲቆም ሆኗል፡፡ በአጭሩ በተፃፈው ሪፖርት ውስጥ በጎንዮሽ ጉዳቱ ላይ ዝርዝር መረጃ አልቀረበም፡፡
ከአንድ ሳምንት በፊት ራሱ ጊላድ በ125 ታማሚዎች ላይ ባደረገው የሬምዲሲቪየር ሙከራ በቺካጎ የሚገኙ ሀኪሞችን ቀልብ ስቦ ነበር፡፡ የሙከራው አካል የነበሩት ሁሉም ታማሚዎች በአንድ ሳምንት ውስጥ ከሆስፒታል ድነው ወጥተዋል፡፡ ሆኖም በቻይናው ሙከራ እንደተደረገው ፍቱንነት የሌላቸው መድሃኒቶች ስላልቀረቡ ታማሚዎቹ ድነው የወጡት በሬምዲሲቪየር ምክንያት መሆን አለመሆኑን ተመራማሪዎች ሊያረጋግጡ አልቻሉም ነበር፡፡
ሬምዲሲቪየር እጅጉን ተስፋ ተጥሎበት የነበረና ከዶክተር እስከ ፖለቲከኛው ለኮሮና ለታማሚዎች እንዲሰጥ በስፋት ሲገፋ ቆይቷል፡፡ በተመሳሳይ ፀረ-ወባ የሆነው የክሎሮኩዊን መድሀኒት መራዛማነቱ ያነሰ አምሳያ የሆነው ሀይድሮክሲክሎሮኩዊን ለኮሮና ታማሚዎች ለመስጠች ችኮላ ነበረ፡፡ ይህም ያስከተለው የጤና ጉዳት እንዳለ ሆኖ፤ መድሀኒቱ ያስፈልጋቸው የነበሩ ሉፐስ የተባለ የሰውነት የበሽታ የመከላከል አቅምን የሚያጠቃ በሽታ ታማሚዎች እጥረት እንዲያጋጥማቸው አድርጓል፡፡ ታድያ በመድሃኒቶች ላይ ስርዓቱን የጠበቀ ሙከራ እንዲደረግ የሚሹ ተመራማሪዎች ይህ ካልተደረገ በስተቀር ከዚህ ቀደም የተሞከሩ መድሀኒቶችን እንኳን እንዲህ እንደኮሮና ገና በደንብ ላልታወቁ በሽታዎች የመጠቀምን ጉዳት ለማሳያነት እንደሚጠቀሙበት ይገመታል፡፡
ምንጭ፡ The Guardian
ውድ ተከታታዮቻችን መዘናጋት ዋጋ ያስከፍለናልና ዛሬም ከሰዎች ጋራ ያሎትን አካላዊ ርቀት ይጠብቁ፤ እጅዎንም በየጊዜው በደንብ ይታጠቡ፤ ሌሎችም በባለሙያ የተነገሩ የጥንቃቄ እርምጃዎችን ይውሰዱ፡፡
የኮሮናቫይረስን ለመዋጋት አፍሪካውያን የተገበሯቸው 5 አስገራሚ ፈጠራዎች
****************************************
በአለማችን የታሪክ ምዕራፍ እጅግ አስጨናቂ ሁኔታዎችና ከስተቶች ለፈጠራ በር መክፈታቸው አይቀሬ ጉዳይ ነው፡፡ ኮቪድ 19 በአለም ላይ በደቀነው ከፍተኛ አደጋ ምክንያት ከዚህም ከዚያም ሁኔታውን ቀላል ለማድርግ የሚያግዙ ፈጠራዎች በመሰራት ላይ ናቸው፡፡ በአህጉራችን አፍሪካም የአደጋውን መጠን ለመቀነስ እና የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት ልዩ ልዩ ፈጠራዎች በመተግበር ላይ ናቸው፡፡ ለምሳሌ ኮ ክሬሽን ሃብ እና ቬንቸርስ ፕላትፎርም ሃብ የተሰኙ የፈጠራ ሃሳብ አጋዦች ከኮቪድ 19 ጋር የተያያዙ የፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ሰዎች በገንዘብ እና በክህሎት በመደገፍ ላይ ይገኛሉ፡፡ ሌሎች በየሃገሩ የሚገኙ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትም ለዚሁ አለማ እየተጉ የሚገኙ ናቸው፡፡ ታዲያ በዚህ ሁኔታ በተለያዩ የአፍሪካ ምድሮች ተሰርተው በመተግበር ላይ ያሉ እና ሁላችንም ልናውቃቸው የሚገቡ ፈጠራዎች ይገኛሉ፡፡
1.ቻትቦትስ (Chatbots) እና ስለራስ ማወቂያ ፈጠራዎች
እንዲህ ያሉት ፈጠራዎች የብዙሃኑን ጤና ካለበት ለመጠበቅ እና የቫይረሱን ቀላል ምልከቶች ከቤት ሆኖ ለመለየት የሚያገለግል ሲሆን፤ የሰዎችን ጭንቀት ለመቀነስና በምርመራ ማዕከሎች የሚኖረውን አጥረት ለማገዝ በእጅጉ የሚረዳ ነው፡፡ ለምሳሌ በናይጄሪያ COVID-19 Triage Tool በሚል ሰዎች በኦንላይን ስለጤናቸው ሁኔታ እንዲረዱ እና በቫይረሱ ተይዘው ከሆነ በሚታይባቸው ምልክተቶች መሰረት ምን አይነት እርምጃ መውሰድ እንደሚገባቸው ልዩ ልዩ ጤና ምክሮች የሚያገኙበት ነው፡፡ ከዚህ መሳሪያ በተጓዳኝ COVID-19 tracker የተሰኘው መገልገያም ተጠቃሚዎች የኮቪድ 19 ምልክቶች ሲታዩባቸው በሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች መሰረት ወደ ለይቶ ማቆያ እና የምርመራ ማዕከል እንዲያቀኑ የሚያግዝ ፈጠራ ነው፡፡ ይህ አሰራር በደቡብ አፍሪካም በዋትአፕ Chatbots አማካኝነት የሚከናወን ሲሆን፤ ተጠቃሚዎች በቫይረሱ ዙሪያ የሚያዩትን ምልክቶች በመናገር መውሰድ የሚገባቸውን ቀላል ህክምናዎች እና ሌሎች ምክሮችን የሚያገኙበት ነው፡፡ ፈጠራው ከሚሰጠው ጥቅም አንፃር 3.5 ሚሊዮን ተጠቃሚዎች ጋር ሁለት ወር ባለሞላ ጊዜ ውስጥ ተደራሽ ሊሆን ችሏል፡፡
2.የህክመና መሳሪያዎችን በ 3D ማተሚያ መሽን መስራት
በዚህ የፈጠራ ዘርፍ ላይ ለአፍሪካ የጤና ባለሙያዎች በእጅጉ የሚያግዝ የሰውነት መሸፈኛ መሳሪያ እና የፊት መሸፈኛ ጭምብል በ3D ማተሚያ ቴክኖሎጂ አማካኝነት በአፍሪካውያን የተሰራ ሲሆን፤ እንደቬንትሌተር ያሉ ሌሎች የህክመና መሳሪያዎችም በተለያዩ የአህጉሪቱ ክፍሎች እየተሰሩ ይገኛል፡፡ ለአብነት በአፍሪካ የአርተፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፍ ቀዳሚ የሆነቸው የጅኋንስበርጓ ናትሊ ራፍል ወረርሽኙ ከተከሰተበት ጊዜ አንስቶ በ3D ማተሚያ አማካኘነት በየቀኑ መቶ የህክምና ባለሙያዎች ማስክ በማምረት ከሃገሯ አልፋ ለሌሎች የአፍሪካ ሃገራት ምርቶችን የምታቀርብ ናት፡፡
3.የኮቪድ 19 የቀጥታ (Real-time) መረጃ መከታተያ
የቫይረሱ ስርጭት ከፍተኛ እየሆነ ሲመጣ ዜጎች ትክከለኛ መረጃን በፍጥነት እንዲገኙ እና ራሳቸውን ከሁኔታዎች ጋር እንዲያናብቡ በአፍሪካ በብዙ ቦታዎች የተሰሩት መሰል ፈጠራዎች ትልቅ ግልጋሎት እንደነበራቸው የሚታወቅ ነው፡፡ ለምሳሌ በጋና comprehensive real-time tracker በሚል በተዘጋጀው አህጉርአቀፍ የኮቪድ 19 የቀጥታ መከታተያ አማካኘነት ዜጎች ስለቫይረሱ አጠቃላይ መረጃ እንዲኖራቸው ከማድረጉም ባለፈ ለፖሊሲ አውጪዎች እና የመንግስት አካላት ትክክለኛ ውሳኔ እንዲሰጡ እና ትንበያቸውን ምክንያታዊ ለማድረግ በእጅጉ አግዛል፡፡ ይህ ፈጠራ በሃገራቸን ኢትዮጵያም ከወራት በፊት መተገብር እንደጀመረ የሚታወቅ ነው፡፡
4.የሳንባ X-ray መመርመሪያዎች
ይህ የፈጠራ ሃሳብ የሳንባ X-ray ምርመራዎችን ከኦንላይን ሲስተሞች ጋር በማዛመድ የኮቪድ 19 ምርመራን ለማካሄድ የሚውል ሲሆን፤ መሰል ችግሮች የሚታዩባቸው ሰዎች የ X-ray ውጤታቸውን በምስል በመላክ በቫይረሱ መተቃት አለመጠቃታቸውን የሚያውቁበት ነው፡፡ በቱኒዚያ መሰል ስርዓቶችን በማበልፀግ ጥቂት ምልከቶችን የሚሳዩ ሰዎች በሳንባ X-ray ምስላቸው አማካኘነት ለቫይረሱ የመጋለጥ እድላቸውን በቤት ሆነው ለማወቅ ችለዋል፡፡ ይህ የፈጠራ ሃሳብ በኬንያም T-sense በተሰኘ ሲስተም አማካኘነት ሰዎች የልባቸውንና የሳንባቸውን ድምፅ ወደ መስል በመቀየር የመተንፈሻ አካል ችግር እንዳለባቸው እንደሌለባቸው ለመለየት የሚያስችል ግሩም ፈጠራ ሆኖ ቀርቧል፡፡
5.የኮቪድ 19 መመርመሪያ ኪቶች
የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በአፍሪካ ከተከሰተ ወዲህ በየሃገራቱ የሚደረጉ የኮቪድ 19 ምርመራዎች እጅግ አነስተኛ እንደሆኑ ይታወቃል፡፡ ለምሳሌ በናይጄሪያ 200 ሚሊዮን የሚጠጋ ህዝብ ባለበት ሁኔታ የቫይረሱ ምርመራ የተደረገለት ህዝብ ከ8ሺ አያልፍም፡፡ ታዲያ ይህ ሁኔታ ለሌሎች አማራጮችን ለመመልከት ግድ ብሏል፡፡ ይህ የፈጠራ ዘርፍ በናይጄሪያ ብዙ ሙከራዎች ሲደረጉበት የቆየ ግሩም ቴክኖሎጂ ሲሆን፤ ሞባይልን ብቻ መሰረት በማድረግ ከታከሉበት የሴንሰር መተግበሪያዎች ጋር በማጣመር የኮቪድ 19 ምርመራን ለማከናውን የሚረዳ ነው፡፡
ምንጭ፡ Techpoint.Africa
****************************************
በአለማችን የታሪክ ምዕራፍ እጅግ አስጨናቂ ሁኔታዎችና ከስተቶች ለፈጠራ በር መክፈታቸው አይቀሬ ጉዳይ ነው፡፡ ኮቪድ 19 በአለም ላይ በደቀነው ከፍተኛ አደጋ ምክንያት ከዚህም ከዚያም ሁኔታውን ቀላል ለማድርግ የሚያግዙ ፈጠራዎች በመሰራት ላይ ናቸው፡፡ በአህጉራችን አፍሪካም የአደጋውን መጠን ለመቀነስ እና የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት ልዩ ልዩ ፈጠራዎች በመተግበር ላይ ናቸው፡፡ ለምሳሌ ኮ ክሬሽን ሃብ እና ቬንቸርስ ፕላትፎርም ሃብ የተሰኙ የፈጠራ ሃሳብ አጋዦች ከኮቪድ 19 ጋር የተያያዙ የፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ሰዎች በገንዘብ እና በክህሎት በመደገፍ ላይ ይገኛሉ፡፡ ሌሎች በየሃገሩ የሚገኙ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትም ለዚሁ አለማ እየተጉ የሚገኙ ናቸው፡፡ ታዲያ በዚህ ሁኔታ በተለያዩ የአፍሪካ ምድሮች ተሰርተው በመተግበር ላይ ያሉ እና ሁላችንም ልናውቃቸው የሚገቡ ፈጠራዎች ይገኛሉ፡፡
1.ቻትቦትስ (Chatbots) እና ስለራስ ማወቂያ ፈጠራዎች
እንዲህ ያሉት ፈጠራዎች የብዙሃኑን ጤና ካለበት ለመጠበቅ እና የቫይረሱን ቀላል ምልከቶች ከቤት ሆኖ ለመለየት የሚያገለግል ሲሆን፤ የሰዎችን ጭንቀት ለመቀነስና በምርመራ ማዕከሎች የሚኖረውን አጥረት ለማገዝ በእጅጉ የሚረዳ ነው፡፡ ለምሳሌ በናይጄሪያ COVID-19 Triage Tool በሚል ሰዎች በኦንላይን ስለጤናቸው ሁኔታ እንዲረዱ እና በቫይረሱ ተይዘው ከሆነ በሚታይባቸው ምልክተቶች መሰረት ምን አይነት እርምጃ መውሰድ እንደሚገባቸው ልዩ ልዩ ጤና ምክሮች የሚያገኙበት ነው፡፡ ከዚህ መሳሪያ በተጓዳኝ COVID-19 tracker የተሰኘው መገልገያም ተጠቃሚዎች የኮቪድ 19 ምልክቶች ሲታዩባቸው በሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች መሰረት ወደ ለይቶ ማቆያ እና የምርመራ ማዕከል እንዲያቀኑ የሚያግዝ ፈጠራ ነው፡፡ ይህ አሰራር በደቡብ አፍሪካም በዋትአፕ Chatbots አማካኝነት የሚከናወን ሲሆን፤ ተጠቃሚዎች በቫይረሱ ዙሪያ የሚያዩትን ምልክቶች በመናገር መውሰድ የሚገባቸውን ቀላል ህክምናዎች እና ሌሎች ምክሮችን የሚያገኙበት ነው፡፡ ፈጠራው ከሚሰጠው ጥቅም አንፃር 3.5 ሚሊዮን ተጠቃሚዎች ጋር ሁለት ወር ባለሞላ ጊዜ ውስጥ ተደራሽ ሊሆን ችሏል፡፡
2.የህክመና መሳሪያዎችን በ 3D ማተሚያ መሽን መስራት
በዚህ የፈጠራ ዘርፍ ላይ ለአፍሪካ የጤና ባለሙያዎች በእጅጉ የሚያግዝ የሰውነት መሸፈኛ መሳሪያ እና የፊት መሸፈኛ ጭምብል በ3D ማተሚያ ቴክኖሎጂ አማካኝነት በአፍሪካውያን የተሰራ ሲሆን፤ እንደቬንትሌተር ያሉ ሌሎች የህክመና መሳሪያዎችም በተለያዩ የአህጉሪቱ ክፍሎች እየተሰሩ ይገኛል፡፡ ለአብነት በአፍሪካ የአርተፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፍ ቀዳሚ የሆነቸው የጅኋንስበርጓ ናትሊ ራፍል ወረርሽኙ ከተከሰተበት ጊዜ አንስቶ በ3D ማተሚያ አማካኘነት በየቀኑ መቶ የህክምና ባለሙያዎች ማስክ በማምረት ከሃገሯ አልፋ ለሌሎች የአፍሪካ ሃገራት ምርቶችን የምታቀርብ ናት፡፡
3.የኮቪድ 19 የቀጥታ (Real-time) መረጃ መከታተያ
የቫይረሱ ስርጭት ከፍተኛ እየሆነ ሲመጣ ዜጎች ትክከለኛ መረጃን በፍጥነት እንዲገኙ እና ራሳቸውን ከሁኔታዎች ጋር እንዲያናብቡ በአፍሪካ በብዙ ቦታዎች የተሰሩት መሰል ፈጠራዎች ትልቅ ግልጋሎት እንደነበራቸው የሚታወቅ ነው፡፡ ለምሳሌ በጋና comprehensive real-time tracker በሚል በተዘጋጀው አህጉርአቀፍ የኮቪድ 19 የቀጥታ መከታተያ አማካኘነት ዜጎች ስለቫይረሱ አጠቃላይ መረጃ እንዲኖራቸው ከማድረጉም ባለፈ ለፖሊሲ አውጪዎች እና የመንግስት አካላት ትክክለኛ ውሳኔ እንዲሰጡ እና ትንበያቸውን ምክንያታዊ ለማድረግ በእጅጉ አግዛል፡፡ ይህ ፈጠራ በሃገራቸን ኢትዮጵያም ከወራት በፊት መተገብር እንደጀመረ የሚታወቅ ነው፡፡
4.የሳንባ X-ray መመርመሪያዎች
ይህ የፈጠራ ሃሳብ የሳንባ X-ray ምርመራዎችን ከኦንላይን ሲስተሞች ጋር በማዛመድ የኮቪድ 19 ምርመራን ለማካሄድ የሚውል ሲሆን፤ መሰል ችግሮች የሚታዩባቸው ሰዎች የ X-ray ውጤታቸውን በምስል በመላክ በቫይረሱ መተቃት አለመጠቃታቸውን የሚያውቁበት ነው፡፡ በቱኒዚያ መሰል ስርዓቶችን በማበልፀግ ጥቂት ምልከቶችን የሚሳዩ ሰዎች በሳንባ X-ray ምስላቸው አማካኘነት ለቫይረሱ የመጋለጥ እድላቸውን በቤት ሆነው ለማወቅ ችለዋል፡፡ ይህ የፈጠራ ሃሳብ በኬንያም T-sense በተሰኘ ሲስተም አማካኘነት ሰዎች የልባቸውንና የሳንባቸውን ድምፅ ወደ መስል በመቀየር የመተንፈሻ አካል ችግር እንዳለባቸው እንደሌለባቸው ለመለየት የሚያስችል ግሩም ፈጠራ ሆኖ ቀርቧል፡፡
5.የኮቪድ 19 መመርመሪያ ኪቶች
የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በአፍሪካ ከተከሰተ ወዲህ በየሃገራቱ የሚደረጉ የኮቪድ 19 ምርመራዎች እጅግ አነስተኛ እንደሆኑ ይታወቃል፡፡ ለምሳሌ በናይጄሪያ 200 ሚሊዮን የሚጠጋ ህዝብ ባለበት ሁኔታ የቫይረሱ ምርመራ የተደረገለት ህዝብ ከ8ሺ አያልፍም፡፡ ታዲያ ይህ ሁኔታ ለሌሎች አማራጮችን ለመመልከት ግድ ብሏል፡፡ ይህ የፈጠራ ዘርፍ በናይጄሪያ ብዙ ሙከራዎች ሲደረጉበት የቆየ ግሩም ቴክኖሎጂ ሲሆን፤ ሞባይልን ብቻ መሰረት በማድረግ ከታከሉበት የሴንሰር መተግበሪያዎች ጋር በማጣመር የኮቪድ 19 ምርመራን ለማከናውን የሚረዳ ነው፡፡
ምንጭ፡ Techpoint.Africa
ኮቪድ 19 ለምን ከሴቶች ይልቅ ወንዶች ላይ በረታ
አዲሱ ጥናት የሚለው አለ
*******************************
ስለኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ብዙ ያልታወቁ ጉዳዮች ይገኛሉ፡፡ ከቫይረሱ መነሻ መላምቶች አንስቶ ስለመተላለፊያው መንገድ እና ሌሎቹም ተያያዥ ጉዳዮች ተጨማሪ ጥናቶችን የሚፈልጉ ናቸው፡፡ ታዲያ ከእነዚህ መልስ ያልተገኘላቸው ጥያቄዎች ውስጥ ቫይረሱ ከሴቶች ይልቅ በእጥፍ ወንዶች ላይ የሚበረታበት ምከንያት ምንድን ነው የሚለው ሌላኛው ያልተፈታ እንቆቅልሽ ነው፡፡
በዚህ ጉዳይ ላይ መረጃዎችን ሲያጠናቅር የነበረው የምርምር ቡድን ለአብነት ያስቀመጣቸው ማሳያዎች ቫይረሱ ከሴቶች ይልቅ ወንዶች ላይ እንደሚበረታ በግልፅ የሚያሳዩ ናቸው፡፡ ለምሳሌ በኮሮናቫረስ በእጅጉ በተመታችው በኒው ዮርክ ከተማ በቫይረሱ ከተያዙ 100,000 ወንዶች መካከል 146 የሚጠጉት ህይወታቸው ሲያልፍ፤ በአንጻሩ በቫይረሱ ከተያዙት 100,000 ሴቶች መካከል 84 የሚሆኑት ብቻ ህይወታቸውን አተዋል፡፡ ይህ የሞት ልዩነት ሲመዘገብ ከፍተኛ መጠን ያላቸው ወንዶች በሆስፐታል ህክምና ሲደረግላቸው የቆዩ መሆኑ ጉዳዩን ይበልጥ አስገራሚ ያደርገዋል፡፡ ይህ ጥንቅር በቫይረሱ በጽኑ ታመው የትንፋሽ ማገዣ የተደረገላቸው ሰዎች በአብዛኛው ወንዶች መሆናቸውን እንዲሁ የሚያሳይ ሲሆን፤ በሌሎች እንደ ቻይና፣ ጣልያን እና ደቡብ ኮሪያ ባሉ ሃገራትም ተመሳሳይ ስታቲክስ እንዳለው ለማውቅ ተችሏል፡፡ ታዲያ የምርምር ቡድኑ ይህ እንዴት ሊሆን ቻለ ለሚለው ጥያቄ ከተለያዩ ጎኖች በማየት ጉዳዪን ለማብራራት ይሞክራል፡፡
በዚህ አለምአቀፍ ጥናት የህንዱ ካስቱርባ ሆስፖታል፣ አልበርት አንስታይን የጤና ኮሌጅ እንዲሁም ሞንቴፊዮሪ የጤና ኢንስቲትዩት በዋናነት የተሳተፉ የምርምር ቡድኑ አባላት ሲሆኑ የምርምር ፅሁፉ አጠቃላይ ዝርዝር ደግሞ
Medrxiv.org በተባለው አለምአቀፍ ጆርናል ላይ ታትሟል፡፡ የጥናቱ ይዘት በሁለቱም ፆታዎች በኩል የሚኖረውን የኮቪድ 19 በሽታን ለይቶ የመከላከል አቀም (viral clearance) እና ቀደሞ ምላሽ የመስጠት ሁኔታን በማብራራት ሴቶች ከወንዶች ባነሰ ጊዜያት ውስጥ እንዴት ለቫይረሱ ፈጣን ምላሽ እንደሚሰጡ የሚያሳይ ነው፡፡ በጥናቱ 48 የሚሆኑ ፍቃደኛ ወንዶች እና 20 ሴቶች ሲሳተፉ አማካይ እደሜ ጣሪያቸው 37 ነበር፡፡ ተመራማሪዎች የሁለቱንም ፆታዎች የደም ናሙና ከመረመሩ በኋላ በቫይረሱ መያዛቸውን በማረጋገጥ እና የትኞቹ ተጠቂዎች በፍጥነት ለቫይረሱ ምላሽ በመስጠት ወደማገገም ይሄዳሉ የሚል ነበር፡፡
ታዲያ በውጤቱ መሰረት ሁሉም ሴቶች ከወንዶቹ በመቅደም ቫይረሱን ከሰውነታቸው ለመፅዳት አጭር ጊዜ እንዳስፈለጋቸው እና ቢያንስ አንኳን የሶስትና የአራት ቀን ልዩነት በመካከላቸው እንደነበረ በጥናታቸው አረጋግጠዋል፡፡ ይህ ውጤት የሁለቱንም ፆታዎች በሽታ የመከላከል ስርዓትና ፈጣን ምላሽ የመስጠት አቅም (immune system response) በስፋት እንዲጠና መንገድ የሚከፍት ቢሆንም በወንዶች በኩል ቫይረሱን ከሰውነት ለማስወገድ የሚታየው ችግር ከሌሎች ማህበራዊና አካባቢያዊ ችግሮች የሚቀዳ ሊሆን እንሚችል ጥናቱ የጠቆመው አብይ ጉዳይ ነው፡፡ ለምሳሌ በአብዛኛው የማህበረሰብ የአኗኗር ሂደት ውስጥ ከመተንፈሻ አካል ጋር የተያያዙ ችግሮችን የሚያስከትሉ አጉል ሱሶች እና የህይወት ልምምዶች በወንዶች እንደሚተገበሩ ይታወቀል፡፡ አንደማሳያ ብንወስድ እንኳን ሲጋራ ማጨስ፣ የአልኮል መጠጦች ማዘውተር እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ ችግሮች ከሴቶች ይልቅ ወንዶች ላይ በስፋት መታየታቸው ውጤቱን ከባድ እንደሚያደርገው ይገመታል፡፡
ምንጭ፡ Bigthink እና Medrxiv.org
አዲሱ ጥናት የሚለው አለ
*******************************
ስለኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ብዙ ያልታወቁ ጉዳዮች ይገኛሉ፡፡ ከቫይረሱ መነሻ መላምቶች አንስቶ ስለመተላለፊያው መንገድ እና ሌሎቹም ተያያዥ ጉዳዮች ተጨማሪ ጥናቶችን የሚፈልጉ ናቸው፡፡ ታዲያ ከእነዚህ መልስ ያልተገኘላቸው ጥያቄዎች ውስጥ ቫይረሱ ከሴቶች ይልቅ በእጥፍ ወንዶች ላይ የሚበረታበት ምከንያት ምንድን ነው የሚለው ሌላኛው ያልተፈታ እንቆቅልሽ ነው፡፡
በዚህ ጉዳይ ላይ መረጃዎችን ሲያጠናቅር የነበረው የምርምር ቡድን ለአብነት ያስቀመጣቸው ማሳያዎች ቫይረሱ ከሴቶች ይልቅ ወንዶች ላይ እንደሚበረታ በግልፅ የሚያሳዩ ናቸው፡፡ ለምሳሌ በኮሮናቫረስ በእጅጉ በተመታችው በኒው ዮርክ ከተማ በቫይረሱ ከተያዙ 100,000 ወንዶች መካከል 146 የሚጠጉት ህይወታቸው ሲያልፍ፤ በአንጻሩ በቫይረሱ ከተያዙት 100,000 ሴቶች መካከል 84 የሚሆኑት ብቻ ህይወታቸውን አተዋል፡፡ ይህ የሞት ልዩነት ሲመዘገብ ከፍተኛ መጠን ያላቸው ወንዶች በሆስፐታል ህክምና ሲደረግላቸው የቆዩ መሆኑ ጉዳዩን ይበልጥ አስገራሚ ያደርገዋል፡፡ ይህ ጥንቅር በቫይረሱ በጽኑ ታመው የትንፋሽ ማገዣ የተደረገላቸው ሰዎች በአብዛኛው ወንዶች መሆናቸውን እንዲሁ የሚያሳይ ሲሆን፤ በሌሎች እንደ ቻይና፣ ጣልያን እና ደቡብ ኮሪያ ባሉ ሃገራትም ተመሳሳይ ስታቲክስ እንዳለው ለማውቅ ተችሏል፡፡ ታዲያ የምርምር ቡድኑ ይህ እንዴት ሊሆን ቻለ ለሚለው ጥያቄ ከተለያዩ ጎኖች በማየት ጉዳዪን ለማብራራት ይሞክራል፡፡
በዚህ አለምአቀፍ ጥናት የህንዱ ካስቱርባ ሆስፖታል፣ አልበርት አንስታይን የጤና ኮሌጅ እንዲሁም ሞንቴፊዮሪ የጤና ኢንስቲትዩት በዋናነት የተሳተፉ የምርምር ቡድኑ አባላት ሲሆኑ የምርምር ፅሁፉ አጠቃላይ ዝርዝር ደግሞ
Medrxiv.org በተባለው አለምአቀፍ ጆርናል ላይ ታትሟል፡፡ የጥናቱ ይዘት በሁለቱም ፆታዎች በኩል የሚኖረውን የኮቪድ 19 በሽታን ለይቶ የመከላከል አቀም (viral clearance) እና ቀደሞ ምላሽ የመስጠት ሁኔታን በማብራራት ሴቶች ከወንዶች ባነሰ ጊዜያት ውስጥ እንዴት ለቫይረሱ ፈጣን ምላሽ እንደሚሰጡ የሚያሳይ ነው፡፡ በጥናቱ 48 የሚሆኑ ፍቃደኛ ወንዶች እና 20 ሴቶች ሲሳተፉ አማካይ እደሜ ጣሪያቸው 37 ነበር፡፡ ተመራማሪዎች የሁለቱንም ፆታዎች የደም ናሙና ከመረመሩ በኋላ በቫይረሱ መያዛቸውን በማረጋገጥ እና የትኞቹ ተጠቂዎች በፍጥነት ለቫይረሱ ምላሽ በመስጠት ወደማገገም ይሄዳሉ የሚል ነበር፡፡
ታዲያ በውጤቱ መሰረት ሁሉም ሴቶች ከወንዶቹ በመቅደም ቫይረሱን ከሰውነታቸው ለመፅዳት አጭር ጊዜ እንዳስፈለጋቸው እና ቢያንስ አንኳን የሶስትና የአራት ቀን ልዩነት በመካከላቸው እንደነበረ በጥናታቸው አረጋግጠዋል፡፡ ይህ ውጤት የሁለቱንም ፆታዎች በሽታ የመከላከል ስርዓትና ፈጣን ምላሽ የመስጠት አቅም (immune system response) በስፋት እንዲጠና መንገድ የሚከፍት ቢሆንም በወንዶች በኩል ቫይረሱን ከሰውነት ለማስወገድ የሚታየው ችግር ከሌሎች ማህበራዊና አካባቢያዊ ችግሮች የሚቀዳ ሊሆን እንሚችል ጥናቱ የጠቆመው አብይ ጉዳይ ነው፡፡ ለምሳሌ በአብዛኛው የማህበረሰብ የአኗኗር ሂደት ውስጥ ከመተንፈሻ አካል ጋር የተያያዙ ችግሮችን የሚያስከትሉ አጉል ሱሶች እና የህይወት ልምምዶች በወንዶች እንደሚተገበሩ ይታወቀል፡፡ አንደማሳያ ብንወስድ እንኳን ሲጋራ ማጨስ፣ የአልኮል መጠጦች ማዘውተር እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ ችግሮች ከሴቶች ይልቅ ወንዶች ላይ በስፋት መታየታቸው ውጤቱን ከባድ እንደሚያደርገው ይገመታል፡፡
ምንጭ፡ Bigthink እና Medrxiv.org
CDC በጤና መመሪያው ላይ ያካተታቸው የኮቪድ 19 ስድስት ምልክቶች ምንድን ናቸው?
=============================
የአሜሪካው የበሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ መዕከል (CDC) በይፋዊ ድረ-ገፁ በሚያወጣቸው የጤና መመሪዎች ወይም (Guidelines) አማካኝነት በኮቪድ 19 ዙሪያ ቀድመው ከሚታወቁት የትኩሳት፣ ደረቅ ሳል እና የትንፋሽ መቆራራጥ ምልክቶች በተጨማሪ ሌሎች ተያያዥ የበሽታው ምልከቶች ሊኖሩ እንደሚችሉ አስታውቋል፡፡ ተቋሙ በመመሪያው ይፋ ያደረጋቸው እነዚህ የኮቪድ 19 ተያያዥ ምልክቶች አንዳንዶቹ ቀድመው በተለያዩ የጤና ኤክስፐርቶች ሲጠቆሙ የነበሩ እና በቫይረሱ ከተያዙ ሰዎች ላይ ሲስተዋሉ የነበሩ ምልክቶች ናቸው፡፡
የአሜሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ መዕከል (CDC) ይፋ ካደረጋቸው የበሽታው ተያያዥ ምልክቶች ውስጥ ብርድ፣ የጡንቻ ህመም፣ ከቅዝቃዜ ጋር የተያያዘ ተደጋጋገሚ የሰውነት ማንቀጠቀጥ፣ ራስ ምታት እና የጉሮሮ ህመም ዋናዎቹ ሲሆኑ ከዚህ በተጨማሪም ሽታንና ጣዕም የመለየት ችግርም በመጀመሪያዎቹ ቀናት ላይ ሊታዩ የሚችሉ የበሽታው ቀላል ምልክቶች እንደሆኑ አስታውቋል፡፡ እነዚህ ምልክቶች በሁሉም ሰው ላይ የመታየት እድላቸው ሙሉ ለሙሉ የተረጋገጠ ባይሆንም ከበሽታው ቀላል ምልክቶች መካከል በዋናነነት የሚመደቡ በመሆናቸው እና በተለያየ መልኩ ሰዎች ላይ የመታየት እድል ስለሚኖራቸው በጥንቃቄ ማየቱ ጥቅም እንዳለው CDC አስታውቋል፡፡
የኮሮናቫይረስ አዲስ ወረርሽኝ ከመሆኑ እንፃር እና በበሽታው ላይ የሚደረጉ ተጨማሪ ጥናቶች ገና በሂደት ላይ በመሆናቸው እነዚህ የተጠቀሱት ተያያዥ ምልክቶች አካታች ወይም (inclusive) ናቸው ማለት ባይቻልም እንደሰዎቹ የእድሜ ሁኔታ እና ሌሎች መመዘኛዎች ተመስረቶ ቫይረሱ በያዘው ሰው ላይ ከ2 እስከ 14 ባሉት ቀናት የመታየት እድል አላቸው፡፡ ይህ ሁኔታ በተለይም ከወጣቶች እና ታደጊዎች ጋር በተያያዘ አብዛኞቹ በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ቀድመው ሲጠቀሱ የነበሩ የህመም ስሜቶች ሳይሰማቸው እና ምልክቶች ሳይታይባቸው ቀናትን ሊያስቆጥሩ በመቻላቸው ሁኔታውን ከዚህ ጉዳዩ ጋር ይበልጥ ተያያዥ እንደሚያደርገው የጤና ባለሙያዎች እምነት ነው፡፡
ይሁንና አንደተቋሙ ማብራሪያ እነዚህ የተጠቀሱ የበሽታው ምልክቶች ቀላል ከሚባሉት መካከል የሚመደቡ በመሆናቸው በዙሪያችን ካሉ የጤና ባለሙያዎች ጋር በመመካከር መወሰድ የሚገቡ ጥንቃቄዎችን መወሰን እንደሚቻል እና አደጋውን ቀድሞ ለመከላከል እድል እንደሚሰጥ በመመሪያው ገልጿል፡፡ በበሽታው ዙሪያ ምናልባትም አስጊ ሁኔታ ሊባል የሚችለው እና በአፋጣኛ የሃኪም እገዛ የሚያስፈልገው አተነፋፋስ ላይ ችግር ካለ፣ በደረት አካባቢ ፅኑ የሚባል ህመምና ግፊት ካለ፣ በከንፈርና ፊት ላይ የቀለም ለውጥ ካስተዋልን እንዲሁም ከመኝታ ለመነሳት ስንቸግር ወይም ግራ የመጋባት ስሜት ሲኖረን አፋጣኝ እርምጃዎችን ማድረግ እንደሚገባ CDC በመመሪያው አሳስቧል፡፡
ለበለጠ https://www.cdc.
=============================
የአሜሪካው የበሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ መዕከል (CDC) በይፋዊ ድረ-ገፁ በሚያወጣቸው የጤና መመሪዎች ወይም (Guidelines) አማካኝነት በኮቪድ 19 ዙሪያ ቀድመው ከሚታወቁት የትኩሳት፣ ደረቅ ሳል እና የትንፋሽ መቆራራጥ ምልክቶች በተጨማሪ ሌሎች ተያያዥ የበሽታው ምልከቶች ሊኖሩ እንደሚችሉ አስታውቋል፡፡ ተቋሙ በመመሪያው ይፋ ያደረጋቸው እነዚህ የኮቪድ 19 ተያያዥ ምልክቶች አንዳንዶቹ ቀድመው በተለያዩ የጤና ኤክስፐርቶች ሲጠቆሙ የነበሩ እና በቫይረሱ ከተያዙ ሰዎች ላይ ሲስተዋሉ የነበሩ ምልክቶች ናቸው፡፡
የአሜሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ መዕከል (CDC) ይፋ ካደረጋቸው የበሽታው ተያያዥ ምልክቶች ውስጥ ብርድ፣ የጡንቻ ህመም፣ ከቅዝቃዜ ጋር የተያያዘ ተደጋጋገሚ የሰውነት ማንቀጠቀጥ፣ ራስ ምታት እና የጉሮሮ ህመም ዋናዎቹ ሲሆኑ ከዚህ በተጨማሪም ሽታንና ጣዕም የመለየት ችግርም በመጀመሪያዎቹ ቀናት ላይ ሊታዩ የሚችሉ የበሽታው ቀላል ምልክቶች እንደሆኑ አስታውቋል፡፡ እነዚህ ምልክቶች በሁሉም ሰው ላይ የመታየት እድላቸው ሙሉ ለሙሉ የተረጋገጠ ባይሆንም ከበሽታው ቀላል ምልክቶች መካከል በዋናነነት የሚመደቡ በመሆናቸው እና በተለያየ መልኩ ሰዎች ላይ የመታየት እድል ስለሚኖራቸው በጥንቃቄ ማየቱ ጥቅም እንዳለው CDC አስታውቋል፡፡
የኮሮናቫይረስ አዲስ ወረርሽኝ ከመሆኑ እንፃር እና በበሽታው ላይ የሚደረጉ ተጨማሪ ጥናቶች ገና በሂደት ላይ በመሆናቸው እነዚህ የተጠቀሱት ተያያዥ ምልክቶች አካታች ወይም (inclusive) ናቸው ማለት ባይቻልም እንደሰዎቹ የእድሜ ሁኔታ እና ሌሎች መመዘኛዎች ተመስረቶ ቫይረሱ በያዘው ሰው ላይ ከ2 እስከ 14 ባሉት ቀናት የመታየት እድል አላቸው፡፡ ይህ ሁኔታ በተለይም ከወጣቶች እና ታደጊዎች ጋር በተያያዘ አብዛኞቹ በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ቀድመው ሲጠቀሱ የነበሩ የህመም ስሜቶች ሳይሰማቸው እና ምልክቶች ሳይታይባቸው ቀናትን ሊያስቆጥሩ በመቻላቸው ሁኔታውን ከዚህ ጉዳዩ ጋር ይበልጥ ተያያዥ እንደሚያደርገው የጤና ባለሙያዎች እምነት ነው፡፡
ይሁንና አንደተቋሙ ማብራሪያ እነዚህ የተጠቀሱ የበሽታው ምልክቶች ቀላል ከሚባሉት መካከል የሚመደቡ በመሆናቸው በዙሪያችን ካሉ የጤና ባለሙያዎች ጋር በመመካከር መወሰድ የሚገቡ ጥንቃቄዎችን መወሰን እንደሚቻል እና አደጋውን ቀድሞ ለመከላከል እድል እንደሚሰጥ በመመሪያው ገልጿል፡፡ በበሽታው ዙሪያ ምናልባትም አስጊ ሁኔታ ሊባል የሚችለው እና በአፋጣኛ የሃኪም እገዛ የሚያስፈልገው አተነፋፋስ ላይ ችግር ካለ፣ በደረት አካባቢ ፅኑ የሚባል ህመምና ግፊት ካለ፣ በከንፈርና ፊት ላይ የቀለም ለውጥ ካስተዋልን እንዲሁም ከመኝታ ለመነሳት ስንቸግር ወይም ግራ የመጋባት ስሜት ሲኖረን አፋጣኝ እርምጃዎችን ማድረግ እንደሚገባ CDC በመመሪያው አሳስቧል፡፡
ለበለጠ https://www.cdc.