በኮሮና የተስተጓጎለውን ትምህርት ማገዣ መንገዶች
=======================
የኮሮና ቫይረስ በጉዳት እጆቹ ከጎበኛቸው መደበኛ የህይወት እርምጃዎቻችን መካከል ትምህርት ይገኝበታል፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያን ጨምሮ በብዙ የዓለማችን ሀገራት ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል፤ ተማሪዎችም በቤታቸው ይገኛሉ፡፡ ታድያ በነዚህ ወቅቶች ልጆች ከትምህርታቸው እንዳይርቁ የመማሪያና አጋዥ መፅሐፍቶችን እንዲያነቡ ማድረግ ተገቢና ላለንበት የትምህርት ስርዓትም ቀዳሚው ምርጫ መሆን ያለበት ነው፡፡ ከዚህ ባሻገር ግን ለልጆችም ሆነ ወላጆች ጠቃሚ የሆኑ የመማሪያ ድረ-ገፆችን ልናስተዋውቃችሁ ወደድን፡፡
BBC Bitesize ( bbc.co.uk/bitesize )
ይህ ገፅ በሁሉም የዕድሜ ክልል እና ትምህርት ደረጃ ላይ ለሚገኙ ተማሪዎች የሚሆኑ ትምህርቶችን ይዟል፡፡ የተለያዩ የትምህርት ዓይነቶችን አካቶ ከመያዙም በተጨማሪ በአንፃራዊነት ቀለል ብሎ ተቀምጧል፡፡
BBC Teach ( bbc.co.uk/teach/live-lessons )
እንደ ዩትዩብ ካሉ ምንጮች የሚገኙ የቪዲዮ ምስሎች ለልጆች እጅጉን ጠቃሚ ሊሆኑ ቢችሉም ቁም ነገሩን ለይቶ ማውጣት አዳጋች ሊሆን ይችላል፡፡ በዚህ ረገድ BBC Teach ለልጆች የሚበጁ የቪዲዮ ምስሎችን አደራጅቶ የያዘ መሆኑ ተመራጭ ያደርገዋል፡፡ ገፁ ሌሎች ለተማሪዎች የሚጠቅሙ የቢቢሲ ዝግጅቶችን እንዲከታተሉ የሚያስችልና ስትከታተሏቸው የነበሩ ምስሎችንም እየተከታተለ መረጃ የሚሰጥ ነው፡፡
Khan Academy ( khanacademy.org )
በKhan Academy የሚገኙት ማንኛውም የትምህርት ግብዓቶች በነፃ ከመቅረባቸውም ባሻገር ተማሪዎች መሻሻላቸውን እንዲከታተሉ ያግዛል፡፡ ከድረ-ገፅ በተጨማሪ በስልክ መተግበሪያዎች በኩልም መከታተል ያስችላል፡፡
Duolingo ( duolingo.com )
Duolingo በተለይ ሌሎች ቋንቋዎችን መማር በሚሹ ሰዎች ዘንድ ታዋቂ ነው፡፡ ከዚህ ባለፈ ግን ልጆች በቋንቋ ትምህርታቸው ላይ እንዲሻሻሉ ጥሩ እገዛን የሚያደርግም ነው፡፡ ድረ-ገፁ እገዛውን የሚጀምረው ልጆች ያሉበትን የቋንቋ ደረጃ በመገምገም ሲሆን በመቀጠልም ቃላት እና ሀረጋትን በማስተዋወቅ እንዲሁም ፈተናዎችን በመስጠት ይረዳቸዋል፡፡ Duolingo የንግግር እና የፅሁፍ ችሎታን የሚያዳብሩ ትምህርቶችን ሲያቀርብ ፈጣን እና የገንዘብ ፍጆታውም እጅግ ዝቅተኛ መሆኑ ተመራጭ ያደርገዋል፡፡ እንደ Khan Academy ሁሉ ይህ ገፅም በስልክ መተግበሪያ አማካኝነት አገልግሎቱን ያቀርባል፡፡
The Artful Parent ( artfulparent.com )
ይህ ገፅ ከተለምዶው የድረ ገፅ መማር ማስተማር ሂደት በተለየ ልጆችን እያዝናኑ የፈጠራና ችሎታቸውን በሚያዳብሩና የአስተሳሰብ አድማሳቸውን በሚያሰፉ ሀሳቦች የተሞላ ነው፡፡ ስዕሎችን ከመሳል ቅርፃቅርፆችን እስከመስራት ባሉ እና ሌሎችም እንቅስቃሴዎችን ልጆችን ሳይጫን ያግዛል፡፡ በተጨማሪም ፈጠራና በራስ መተማመንን ማሳደግ በሚቻልበት መንገድ ላይ ምክርን የሚሰጥ ሲሆን በመደበኛ ትምህርታቸው ላይ የሚረዷቸው እና መነሳሳትንም የሚለግስ ነው፡፡
እነዚህ ሁሉ ድረ-ገፆች ጠቃሚነታቸው ባይካድም ለኢትዮጵያዊያን ተማሪዎች የሚሆነውን መምረጥ ግን አስፈላጊ ነው፡፡ በተለይም እነዚህ ትምህርቶች በሌላ ሀገር የትምህርት ስርዓት ላይ ተመስርተው የሚሰጡ ከመሆናቸው ጋራ በተያያዘ ከእኛ ሀገር የትምህርት ስርዓት የተለዩ ሊሆኑ ስለሚችሉ ለተማሪዎች የሚስማሙትን የትምህርት አይነቶች እና አሰጣጥ መንገዶች መርጦ መውሰዱ ለጥያቄ መቅረብ የለበትም፡፡
ምንጭ፡ techradar
=======================
የኮሮና ቫይረስ በጉዳት እጆቹ ከጎበኛቸው መደበኛ የህይወት እርምጃዎቻችን መካከል ትምህርት ይገኝበታል፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያን ጨምሮ በብዙ የዓለማችን ሀገራት ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል፤ ተማሪዎችም በቤታቸው ይገኛሉ፡፡ ታድያ በነዚህ ወቅቶች ልጆች ከትምህርታቸው እንዳይርቁ የመማሪያና አጋዥ መፅሐፍቶችን እንዲያነቡ ማድረግ ተገቢና ላለንበት የትምህርት ስርዓትም ቀዳሚው ምርጫ መሆን ያለበት ነው፡፡ ከዚህ ባሻገር ግን ለልጆችም ሆነ ወላጆች ጠቃሚ የሆኑ የመማሪያ ድረ-ገፆችን ልናስተዋውቃችሁ ወደድን፡፡
BBC Bitesize ( bbc.co.uk/bitesize )
ይህ ገፅ በሁሉም የዕድሜ ክልል እና ትምህርት ደረጃ ላይ ለሚገኙ ተማሪዎች የሚሆኑ ትምህርቶችን ይዟል፡፡ የተለያዩ የትምህርት ዓይነቶችን አካቶ ከመያዙም በተጨማሪ በአንፃራዊነት ቀለል ብሎ ተቀምጧል፡፡
BBC Teach ( bbc.co.uk/teach/live-lessons )
እንደ ዩትዩብ ካሉ ምንጮች የሚገኙ የቪዲዮ ምስሎች ለልጆች እጅጉን ጠቃሚ ሊሆኑ ቢችሉም ቁም ነገሩን ለይቶ ማውጣት አዳጋች ሊሆን ይችላል፡፡ በዚህ ረገድ BBC Teach ለልጆች የሚበጁ የቪዲዮ ምስሎችን አደራጅቶ የያዘ መሆኑ ተመራጭ ያደርገዋል፡፡ ገፁ ሌሎች ለተማሪዎች የሚጠቅሙ የቢቢሲ ዝግጅቶችን እንዲከታተሉ የሚያስችልና ስትከታተሏቸው የነበሩ ምስሎችንም እየተከታተለ መረጃ የሚሰጥ ነው፡፡
Khan Academy ( khanacademy.org )
በKhan Academy የሚገኙት ማንኛውም የትምህርት ግብዓቶች በነፃ ከመቅረባቸውም ባሻገር ተማሪዎች መሻሻላቸውን እንዲከታተሉ ያግዛል፡፡ ከድረ-ገፅ በተጨማሪ በስልክ መተግበሪያዎች በኩልም መከታተል ያስችላል፡፡
Duolingo ( duolingo.com )
Duolingo በተለይ ሌሎች ቋንቋዎችን መማር በሚሹ ሰዎች ዘንድ ታዋቂ ነው፡፡ ከዚህ ባለፈ ግን ልጆች በቋንቋ ትምህርታቸው ላይ እንዲሻሻሉ ጥሩ እገዛን የሚያደርግም ነው፡፡ ድረ-ገፁ እገዛውን የሚጀምረው ልጆች ያሉበትን የቋንቋ ደረጃ በመገምገም ሲሆን በመቀጠልም ቃላት እና ሀረጋትን በማስተዋወቅ እንዲሁም ፈተናዎችን በመስጠት ይረዳቸዋል፡፡ Duolingo የንግግር እና የፅሁፍ ችሎታን የሚያዳብሩ ትምህርቶችን ሲያቀርብ ፈጣን እና የገንዘብ ፍጆታውም እጅግ ዝቅተኛ መሆኑ ተመራጭ ያደርገዋል፡፡ እንደ Khan Academy ሁሉ ይህ ገፅም በስልክ መተግበሪያ አማካኝነት አገልግሎቱን ያቀርባል፡፡
The Artful Parent ( artfulparent.com )
ይህ ገፅ ከተለምዶው የድረ ገፅ መማር ማስተማር ሂደት በተለየ ልጆችን እያዝናኑ የፈጠራና ችሎታቸውን በሚያዳብሩና የአስተሳሰብ አድማሳቸውን በሚያሰፉ ሀሳቦች የተሞላ ነው፡፡ ስዕሎችን ከመሳል ቅርፃቅርፆችን እስከመስራት ባሉ እና ሌሎችም እንቅስቃሴዎችን ልጆችን ሳይጫን ያግዛል፡፡ በተጨማሪም ፈጠራና በራስ መተማመንን ማሳደግ በሚቻልበት መንገድ ላይ ምክርን የሚሰጥ ሲሆን በመደበኛ ትምህርታቸው ላይ የሚረዷቸው እና መነሳሳትንም የሚለግስ ነው፡፡
እነዚህ ሁሉ ድረ-ገፆች ጠቃሚነታቸው ባይካድም ለኢትዮጵያዊያን ተማሪዎች የሚሆነውን መምረጥ ግን አስፈላጊ ነው፡፡ በተለይም እነዚህ ትምህርቶች በሌላ ሀገር የትምህርት ስርዓት ላይ ተመስርተው የሚሰጡ ከመሆናቸው ጋራ በተያያዘ ከእኛ ሀገር የትምህርት ስርዓት የተለዩ ሊሆኑ ስለሚችሉ ለተማሪዎች የሚስማሙትን የትምህርት አይነቶች እና አሰጣጥ መንገዶች መርጦ መውሰዱ ለጥያቄ መቅረብ የለበትም፡፡
ምንጭ፡ techradar
BBC
Home - BBC Bitesize
Use BBC Bitesize to help with your homework, revision and learning from KS1 to GCSE. Find free videos, step-by-step guides, activities and quizzes.
የኮሮና ወረርሺኝ እና የኢውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪው ተስፋ ሰጪ እርዳታ
=======================
የኮሮና ቫይረስ በዓለም አቀፍ ደረጃ መስፋፋቱን ተከትሎ ብዙ ታላላቅ ኢንዱስትሪዎች ምርት ስጠት ማቆማቸው ይታወቃል፡፡ አሁን ታድያ እነዚህ ግዙፍ ኢንዱስትሪዎች ከፍተኛ እጥረት እየተከሰተባቸው ያሉ የህክምና ዕቃዎችን ለማምረት እንቅስቃሴ ላይ ናቸው፡፡
ግዙፉ የመኪና አምራች ኩባንያ ፊያት ቼስለር በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ እጥረት የተከሰተበትን የፊት ማስክ ማምረት እንደሚጀምር አስታውቋል፡፡ በዚህ አንድ ወር ውስጥም አንድ ሚሊዮን የፊት ማስኮችን በማምረት ሀገራት ውስጥ በሚገኙ ሆስፒታል፣ ክሊኒክ፣ ፖሊስ ጣብያ እና እሳት አደጋ መከላከል ለሚሰሩ ሰራተኞች ማሰራጨት እንደሚጀምር አስታውቋል፡፡ ይህን የምርት ለውጥ ለማድረግ ፊያት ቼስለር ብቸኛው የመኪና አምራች አይደለም፡፡ ሌሎችም በእሲያ አውሮፓ እና አሜሪካ እሚንቀሳቀሱ የመኪና አምራቾችም በተመመሳሳይ እጥረት የተከሰረተባቸውን የህክምና ቁሳቁሶችን ለማምረት በዝግጅት ላይ ናቸው፡፡ ባሳለፍነው ማክሰኞ ፎርድ ከጀነራል ኤሌክትሪክ እና 3ኤም ጋር በመተባበር የፊት መከለያዎችን እና የትንፋሽ መሳሪያዎችን (ventilator) ለማምረት እየሰራ መሆኑን አስታውቋል፡፡ ፎርድ በአሁኑ ሰዓትም ቢሆን ለሆስፒታል ሰራተኞች ይሆን ዘንድ የፊት መከላከያዎችን በማምረት ላይ ሲሆን 75 ሺህ ያህሉን በዚህ ሳምንት ብቻ እንደሚያመርት ገልጿል፡፡
ዓለም አቀፍ እጥረት የተከሰተባቸው እነዚህን የህክምና ቁሳቁሶች ለማምረት እና እርዳታ ለመለገስ ከተሰናዱት ሌሎች የዘርፉ ተቋማት ውስጥ ኒሳን፣ ቴስላ፣ ማክላረን እንዲሁም የፎርምዩላ 1 መኪና ውድድር ተሳታፊ ቡድኖች ይገኙበታል፡፡ ከመኪና አምራች ኢንዱስትሪዎችም በተጨማሪ እንደ ዳይሶን፣ እና ኤርባስ ያሉ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች የስራው ተካፋይ ለመሆን ከመንግስት አካላት ፍቃድ በመጠባበቅ ላይ ናቸው፡፡
ሆኖም ይህ መንገድ አልጋ በአልጋ እንደማይሆን የሚጠቁሙ ባለሙያዎች አሉ፡፡ የትንፋሽ መሳሪያዎች አምራቹ ሀሚልተን ሜዲካል ሀላፊ የሆኑት ጄምስ ሀልክ መሳሪያዎቹ ከፍ ያለ ዕውቀትን የሚጠይቁ ናቸው ይላሉ፡፡ እንደ እርሳቸው ከሆነ እነዚህ መሳሪያዎች ከቁሳዊ ይዘታቸው ባሻገር ብዙ ሶፍትዌሮችን የሚፈልጉና በውስጥ ከሚካተቱት ግብዓቶች መካከል አንዱም እንኳን በትክክል አለመስራት ሙሉ መሳርያውን ጥቅም አልባ ያደርገዋል፡፡
ሌሎች ኢንዱስትሪዎች የህክምና ቁሳቁሶችን እንዲያመርቱ ከመንግስታት እና ልዩ ልዩ ፖለቲከኞችም ከፍተኛ ፍላጎት እየታየ ይገኛል፡፡ እየአሜሪካን የምግብ እና መድሃኒት አስተዳደር (FDA) በገበያው ላይ ያለውን እጥረት እንዲቀርፉ በማሰብ ቁሳቁሶቹን በማምረት ረገድ ያለውን የፍቃድ አሰጣጥ ስርዓት ማሻሻሉን አስታውቋል፡፡
ምንጭ፡ Drivetribe፣ BBC እና The Guardian
=======================
የኮሮና ቫይረስ በዓለም አቀፍ ደረጃ መስፋፋቱን ተከትሎ ብዙ ታላላቅ ኢንዱስትሪዎች ምርት ስጠት ማቆማቸው ይታወቃል፡፡ አሁን ታድያ እነዚህ ግዙፍ ኢንዱስትሪዎች ከፍተኛ እጥረት እየተከሰተባቸው ያሉ የህክምና ዕቃዎችን ለማምረት እንቅስቃሴ ላይ ናቸው፡፡
ግዙፉ የመኪና አምራች ኩባንያ ፊያት ቼስለር በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ እጥረት የተከሰተበትን የፊት ማስክ ማምረት እንደሚጀምር አስታውቋል፡፡ በዚህ አንድ ወር ውስጥም አንድ ሚሊዮን የፊት ማስኮችን በማምረት ሀገራት ውስጥ በሚገኙ ሆስፒታል፣ ክሊኒክ፣ ፖሊስ ጣብያ እና እሳት አደጋ መከላከል ለሚሰሩ ሰራተኞች ማሰራጨት እንደሚጀምር አስታውቋል፡፡ ይህን የምርት ለውጥ ለማድረግ ፊያት ቼስለር ብቸኛው የመኪና አምራች አይደለም፡፡ ሌሎችም በእሲያ አውሮፓ እና አሜሪካ እሚንቀሳቀሱ የመኪና አምራቾችም በተመመሳሳይ እጥረት የተከሰረተባቸውን የህክምና ቁሳቁሶችን ለማምረት በዝግጅት ላይ ናቸው፡፡ ባሳለፍነው ማክሰኞ ፎርድ ከጀነራል ኤሌክትሪክ እና 3ኤም ጋር በመተባበር የፊት መከለያዎችን እና የትንፋሽ መሳሪያዎችን (ventilator) ለማምረት እየሰራ መሆኑን አስታውቋል፡፡ ፎርድ በአሁኑ ሰዓትም ቢሆን ለሆስፒታል ሰራተኞች ይሆን ዘንድ የፊት መከላከያዎችን በማምረት ላይ ሲሆን 75 ሺህ ያህሉን በዚህ ሳምንት ብቻ እንደሚያመርት ገልጿል፡፡
ዓለም አቀፍ እጥረት የተከሰተባቸው እነዚህን የህክምና ቁሳቁሶች ለማምረት እና እርዳታ ለመለገስ ከተሰናዱት ሌሎች የዘርፉ ተቋማት ውስጥ ኒሳን፣ ቴስላ፣ ማክላረን እንዲሁም የፎርምዩላ 1 መኪና ውድድር ተሳታፊ ቡድኖች ይገኙበታል፡፡ ከመኪና አምራች ኢንዱስትሪዎችም በተጨማሪ እንደ ዳይሶን፣ እና ኤርባስ ያሉ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች የስራው ተካፋይ ለመሆን ከመንግስት አካላት ፍቃድ በመጠባበቅ ላይ ናቸው፡፡
ሆኖም ይህ መንገድ አልጋ በአልጋ እንደማይሆን የሚጠቁሙ ባለሙያዎች አሉ፡፡ የትንፋሽ መሳሪያዎች አምራቹ ሀሚልተን ሜዲካል ሀላፊ የሆኑት ጄምስ ሀልክ መሳሪያዎቹ ከፍ ያለ ዕውቀትን የሚጠይቁ ናቸው ይላሉ፡፡ እንደ እርሳቸው ከሆነ እነዚህ መሳሪያዎች ከቁሳዊ ይዘታቸው ባሻገር ብዙ ሶፍትዌሮችን የሚፈልጉና በውስጥ ከሚካተቱት ግብዓቶች መካከል አንዱም እንኳን በትክክል አለመስራት ሙሉ መሳርያውን ጥቅም አልባ ያደርገዋል፡፡
ሌሎች ኢንዱስትሪዎች የህክምና ቁሳቁሶችን እንዲያመርቱ ከመንግስታት እና ልዩ ልዩ ፖለቲከኞችም ከፍተኛ ፍላጎት እየታየ ይገኛል፡፡ እየአሜሪካን የምግብ እና መድሃኒት አስተዳደር (FDA) በገበያው ላይ ያለውን እጥረት እንዲቀርፉ በማሰብ ቁሳቁሶቹን በማምረት ረገድ ያለውን የፍቃድ አሰጣጥ ስርዓት ማሻሻሉን አስታውቋል፡፡
ምንጭ፡ Drivetribe፣ BBC እና The Guardian
!ሰበር ዜና! የኮሮና ቫይረስን በሳይንሳዊ ምርምር በተደገፈ የሀገር በቀል እውቀት ከዘመናዊ ሳይንስ ጋር በማቀናጀት ቫይረሱን ለማከም የተሰራው መድሃኒት መሰረታዊ የምርምር ሂደት በማለፍ ተደጋጋሚ የቤተ ሙከራ ሞዴሊንግ ሂደቶችን በስኬት ማለፉን የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
ምርምሩ የኮሮና ቫይረስ በዓለም ላይ መከሰቱ ከተሰማ ጊዜ ጀምሮ ከተለያዩ በሃገር ውስጥና ከሃገር ውጪ ከሚገኙ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር በመሆን ሲካሄድ የቆየ ሲሆን ተደጋጋሚ የምርመር ሂደት አልፎ ወደ ምርት እና ቀጣይ የእንስሳት ፍተሻ እና ክሊኒካል ፍተሻ ስራዎች እንዲሸጋገር ተደርጓል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር ኢንጂ.)፣ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰና ከኢትዮጵያዊያን የባህል ሃኪሞች ጋር እና የህክምና ተመራማሪዎች ጋር በመሆን የሀገር በቀል እውቀቶችን በሳይንሳዊ ሂደቶች በማሳለፍ ለዘመን አመጣሹ ኮሮና ቫይረስ( ኮቪድ -19) ወረርሽኝ ህክምና የተዘጋጀውን መድሃኒት ጥቅም ላይ ለማዋል የሚያስችላቸውን ስራ በመስራት ላይ ይገኛሉ።
መድሃኒቱ የመከላከል አቅም የሚጨምር፣ መርዛማነት የሌለው እና አዋጭነቱ የተረጋገጠ ነው፡፡
የምርምር ሂደቱ ተጠናቅቆ ወደ ምርት ለመግባት ዝግጅት እየተደረገ ሲሆን ዝርዝር መረጃዎችን በተመለከተ ዛሬ መግለጫ እንደሚሰጥ ተነግሯል፡፡
ምንጭ፡ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር
ምርምሩ የኮሮና ቫይረስ በዓለም ላይ መከሰቱ ከተሰማ ጊዜ ጀምሮ ከተለያዩ በሃገር ውስጥና ከሃገር ውጪ ከሚገኙ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር በመሆን ሲካሄድ የቆየ ሲሆን ተደጋጋሚ የምርመር ሂደት አልፎ ወደ ምርት እና ቀጣይ የእንስሳት ፍተሻ እና ክሊኒካል ፍተሻ ስራዎች እንዲሸጋገር ተደርጓል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር ኢንጂ.)፣ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰና ከኢትዮጵያዊያን የባህል ሃኪሞች ጋር እና የህክምና ተመራማሪዎች ጋር በመሆን የሀገር በቀል እውቀቶችን በሳይንሳዊ ሂደቶች በማሳለፍ ለዘመን አመጣሹ ኮሮና ቫይረስ( ኮቪድ -19) ወረርሽኝ ህክምና የተዘጋጀውን መድሃኒት ጥቅም ላይ ለማዋል የሚያስችላቸውን ስራ በመስራት ላይ ይገኛሉ።
መድሃኒቱ የመከላከል አቅም የሚጨምር፣ መርዛማነት የሌለው እና አዋጭነቱ የተረጋገጠ ነው፡፡
የምርምር ሂደቱ ተጠናቅቆ ወደ ምርት ለመግባት ዝግጅት እየተደረገ ሲሆን ዝርዝር መረጃዎችን በተመለከተ ዛሬ መግለጫ እንደሚሰጥ ተነግሯል፡፡
ምንጭ፡ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር
ስለኮሮና እገዛ የሚሰጥዎ የስልክ መተግበሪያ (mobile app)
====================
በአሁኑ ሰዓት ለኢትዮጵያና መላው ዓለም ትልቅ ስጋት ስለሆነው የኮሮና ቫይረስ መረጃ የሚሰጥ የስልክ መተግበሪያ (mobile app) በተቋማችን ሰራተኞች ተሰርቶ ቀርቦልዎታል፡፡ መተግበሪያው ለእርስዎ እንዲመች ተደርጎ በአማርኛም ሆነ በእንግሊዝኛ የሚሰራ ነው፡፡ ይህን ጠቃሚ መተግበሪያ እንድሮይድ ስልክ ያላችሁ በሙሉ አውርዳችሁ ትጠቀሙበት ዘንድ ምክራችን ነው፡፡ ለወዳጅ ዘመድዎ ማጋራቱን እንዳይረሱት፡፡
====================
በአሁኑ ሰዓት ለኢትዮጵያና መላው ዓለም ትልቅ ስጋት ስለሆነው የኮሮና ቫይረስ መረጃ የሚሰጥ የስልክ መተግበሪያ (mobile app) በተቋማችን ሰራተኞች ተሰርቶ ቀርቦልዎታል፡፡ መተግበሪያው ለእርስዎ እንዲመች ተደርጎ በአማርኛም ሆነ በእንግሊዝኛ የሚሰራ ነው፡፡ ይህን ጠቃሚ መተግበሪያ እንድሮይድ ስልክ ያላችሁ በሙሉ አውርዳችሁ ትጠቀሙበት ዘንድ ምክራችን ነው፡፡ ለወዳጅ ዘመድዎ ማጋራቱን እንዳይረሱት፡፡
# ከኮሮና # ቫይረስ ጋር በተያያዘ # ስራዎን # ለመስራት
# ተቸግረዋል? እነዚህን የቴክኖሎጁ አማራጮች ይሞክሩ
***************************************
ወቅታዊው የዓለማችን አደጋ COVID-19 የስርጭት መጠኑ እጅግ ከፍተኛ በመሆኑ በመላው ዓለም የሚገኙ ሰዎችን ከእንቅስቃሴ ውጭ እያደረገ መምጣቱ የሚታወቅ ነው፡፡ ብዙዎች በሽውታውን ለመከላከል እና የስርጭት መጠኑን ለመግታት ከመንግስት በወረዱ መመሪያዎች አማካኘነት ስራዎችን ከቤት በመሆን በመከወን ላይ ይገኛሉ፡፡ ሌሎችም እያንዳንዷን ግንኙነታቸውን በርቀት እየተገበሩ ይገኛል፡፡ ታዲያ በዚህ ወቅት እነዚህን እንቅስቃሴዎች በቀላሉ ለመፈፀም እና ደህንነታችንንም በሚገባ ለመጠበቅ የቴክኖሎጂ እገዛ በእጅጉ ያስፈልገናል፡፡
እነዚህ ከስር የምትመለከቷቸው መተግበሪያዎች እና ድረ ገፆች በአብዛኛው የአለም ክፍል መሰል እንቅስቃሴዎችን ከቤት ሆኖ ለመከወን እና ስራዎችን ለማቅለል የሚያገለግሉ ሲሆን፤ በእኛ ሃገር ሁኔታም በሚቻለው አቅም ቢተገበሩ የሚጠቅሙ ናቸው፡፡
መረጃዎችን በአካል መገናኘት ሳያስፈልግ መላላክ የሚቻልባቸው ዌብ ቤዝድ መተግበሪያዎች
1. Dropbox
2. Pipebytes
3. MailBigFile
4. filedropper
5. Google drive
ስብሰባዎችን እና ውይይቶችን በርቀት ለማከናወን የሚያግዙ ዌብ ቤዝድ መተግበሪያዎች
1. Crowdcast
2. GoToMeeting
3. Cisco Webex Teams
4. Intermedia AnyMeeting
5. https://zoom.us/download ፡ ይህ በተለይም መረጃዎችን ፊት ለፊት በገጽታ ለማዉራት የሚያስችል ታወቂ ሶፍትዌር ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ ሌሎችንም ተግባራት ለማከናወን ይረዳል፤ መረጃን (File) ለመላላክ፣ ጽሁፍ ለመጻጻፍ እና ከ ሁለት በላይ የሆኑ ሰዎችን በተመሳሳይ ሰዓት በተለያየ ጊዜ አስቻይ በሆነ መንገድ ለማገናኘት፣ የተለያዩ ቦታ ሆኖ ህክምና ለመስጠት፣ ሪፖርት ለማድረግ፣ ኮንፈረንስ ለማካሄድ እና ሌሎችም
የርቀት ትምህርቶቸን በኢተርኔት ለማግኘት እና ለመማማር የሚያግዙ ድረገፆች
1. Adobe Connect
2. Blackboard Collaborate
3. WizIQ
4. LearnCube
5. BigBlueButton ፡ ይህ በተለይም ብዙዎች የሚመርጡት የመስመር ላይ መማሪያ ስርዓት ሲሆን፤ ሩቅ ላሉ ተማሪዎች ከፍተኛ ጥራት ያለው የትምህርት እንዲያገኙ በማስቻል የተለያዩ የትምህርት አይነቶችን በቪዲዮ እና ኦውዲዮ ማጋራት የሚያስችል ነው፡፡
ከዛ ባለፈ በሃገራችን የካሽ ብር መያዝ ሳያስፈልግ ሂሳብ መክፈል የሚችሉባቸውን እነዚህን መንገዶች በሚቻለው ቦታ በመጠቀም ከበሽታው ራሳችንን መከላከል እንችላለን
1. M-birr
2. Amole
3. Helocash
4. Awash mobile
# ተቸግረዋል? እነዚህን የቴክኖሎጁ አማራጮች ይሞክሩ
***************************************
ወቅታዊው የዓለማችን አደጋ COVID-19 የስርጭት መጠኑ እጅግ ከፍተኛ በመሆኑ በመላው ዓለም የሚገኙ ሰዎችን ከእንቅስቃሴ ውጭ እያደረገ መምጣቱ የሚታወቅ ነው፡፡ ብዙዎች በሽውታውን ለመከላከል እና የስርጭት መጠኑን ለመግታት ከመንግስት በወረዱ መመሪያዎች አማካኘነት ስራዎችን ከቤት በመሆን በመከወን ላይ ይገኛሉ፡፡ ሌሎችም እያንዳንዷን ግንኙነታቸውን በርቀት እየተገበሩ ይገኛል፡፡ ታዲያ በዚህ ወቅት እነዚህን እንቅስቃሴዎች በቀላሉ ለመፈፀም እና ደህንነታችንንም በሚገባ ለመጠበቅ የቴክኖሎጂ እገዛ በእጅጉ ያስፈልገናል፡፡
እነዚህ ከስር የምትመለከቷቸው መተግበሪያዎች እና ድረ ገፆች በአብዛኛው የአለም ክፍል መሰል እንቅስቃሴዎችን ከቤት ሆኖ ለመከወን እና ስራዎችን ለማቅለል የሚያገለግሉ ሲሆን፤ በእኛ ሃገር ሁኔታም በሚቻለው አቅም ቢተገበሩ የሚጠቅሙ ናቸው፡፡
መረጃዎችን በአካል መገናኘት ሳያስፈልግ መላላክ የሚቻልባቸው ዌብ ቤዝድ መተግበሪያዎች
1. Dropbox
2. Pipebytes
3. MailBigFile
4. filedropper
5. Google drive
ስብሰባዎችን እና ውይይቶችን በርቀት ለማከናወን የሚያግዙ ዌብ ቤዝድ መተግበሪያዎች
1. Crowdcast
2. GoToMeeting
3. Cisco Webex Teams
4. Intermedia AnyMeeting
5. https://zoom.us/download ፡ ይህ በተለይም መረጃዎችን ፊት ለፊት በገጽታ ለማዉራት የሚያስችል ታወቂ ሶፍትዌር ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ ሌሎችንም ተግባራት ለማከናወን ይረዳል፤ መረጃን (File) ለመላላክ፣ ጽሁፍ ለመጻጻፍ እና ከ ሁለት በላይ የሆኑ ሰዎችን በተመሳሳይ ሰዓት በተለያየ ጊዜ አስቻይ በሆነ መንገድ ለማገናኘት፣ የተለያዩ ቦታ ሆኖ ህክምና ለመስጠት፣ ሪፖርት ለማድረግ፣ ኮንፈረንስ ለማካሄድ እና ሌሎችም
የርቀት ትምህርቶቸን በኢተርኔት ለማግኘት እና ለመማማር የሚያግዙ ድረገፆች
1. Adobe Connect
2. Blackboard Collaborate
3. WizIQ
4. LearnCube
5. BigBlueButton ፡ ይህ በተለይም ብዙዎች የሚመርጡት የመስመር ላይ መማሪያ ስርዓት ሲሆን፤ ሩቅ ላሉ ተማሪዎች ከፍተኛ ጥራት ያለው የትምህርት እንዲያገኙ በማስቻል የተለያዩ የትምህርት አይነቶችን በቪዲዮ እና ኦውዲዮ ማጋራት የሚያስችል ነው፡፡
ከዛ ባለፈ በሃገራችን የካሽ ብር መያዝ ሳያስፈልግ ሂሳብ መክፈል የሚችሉባቸውን እነዚህን መንገዶች በሚቻለው ቦታ በመጠቀም ከበሽታው ራሳችንን መከላከል እንችላለን
1. M-birr
2. Amole
3. Helocash
4. Awash mobile
Zoom
Download Center for Zoom Apps and Plugins | Zoom
Download Zoom apps, plugins, and add-ons for mobile devices, desktop, web browsers, and operating systems. Available for Mac, PC, Android, Chrome, and Firefox.
የስፓኒሽ ፍሉን መአት ያለፉት የ 101 ዓመት አዛውንት ለኮሮናም እጅ አልሰጡም
********************************
በሃገረ ጣልያን የኮሮናቫይረስ አደጋ እጅግ በተባባሰበት በአሁን ወቅት በተደጋጋሚ ሁኔታ እጅግ ልብ የሚሰብሩ ታሪኮችን ሲሰሙ እንደነበር የሚታወቅ ነው፡፡ በተለይም ሃገሪቱ ከጃፓን ቀጥሎ የብዙ አዛውንቶች መኖሪያ በመሆኗ ብዙ ሞት ለማስተናገዷም ዋና ምክንያት እንደነበረ ሲገለፅ ቆይቷል፡፡ ከዚህ ሲሻገርም አስፈላጊውን ቅድመ ጥንቃቄ በጊዜው ማድረግ ባለመቻሏ የአደጋው መጠን የከፋ እንዲሆን ትልቅ በር ከፍቷል፡፡ ታዲያ እነዚህ እና ሌሎች ሁነቶች ተደማምረው ወጤቱን የከፋ አደረገው፡፡
ይሁንና በእነዚህ አሳዛኝ ሁኔታዎች ወስጥ ያለፈቸው ይህች ሃገር ተስፋን የሚያለመልም መልካም ዜና ፈፅሞ አልጠፋባትም ነበር፡፡ የ 101 ዓመት አዛውንት የሆኑት Mr. P ደግሞ ለዚህ ተስፋ መለምለም ዋነኛው ምክንያት ናቸው፡፡ እኝህ የ 101 ዓመት አዛውንት በኮሮናቫይረስ ተጠቅተው ብዙዎች ሞታቸውን ሲጠባበቁላቸው የቆዩ ቢሆንም በተደረገላቸው የሃኪም እገዛ እና በሰነቁት ትልቅ ተስፋ ከቫይረሱ ሙሉ ለሙሉ አገግመው የታሪክ ነጋሪ መሆናቸውን ቀጥለዋል፡፡ እኝህ አባት የስፓኒሽ ፍሉ ተብሎ በሚታወቀውና የብዙዎችን ነፍስ በቀጠፈው በዚያ ስከፊ ጊዜ እንደተወለዱ ያስታወቁት የኢንፈርሚ ሆስፒታል ዶክተሮች የዘመናችን አደጋ የሆነውን ኮሮናቫይረስን ዳግም ያሸነፉ ትልቅ አባት ሲሉ አሞግሰዋቸዋል፡፡
Mr. P በዚህ እድሜያቸው ከቫይረሱ አገግመው ወደቤታቸው የሄዱ ብቸኛው የጣልያን ዜጋ ሲሆኑ፤ ከዚህ ቀደምም በቻይና የሚኖሩ የ 103 የእድሜ ባለፀጋ ከሀኪሞች በተደረገላቸው ከፍተኛ እገዛ ከኮሮናቫይረስ ሙሉ ለሙሉ አገግመው ለብዙዎች ተስፋ እንደሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡
ምንጭ፡ IFLScience Store
********************************
በሃገረ ጣልያን የኮሮናቫይረስ አደጋ እጅግ በተባባሰበት በአሁን ወቅት በተደጋጋሚ ሁኔታ እጅግ ልብ የሚሰብሩ ታሪኮችን ሲሰሙ እንደነበር የሚታወቅ ነው፡፡ በተለይም ሃገሪቱ ከጃፓን ቀጥሎ የብዙ አዛውንቶች መኖሪያ በመሆኗ ብዙ ሞት ለማስተናገዷም ዋና ምክንያት እንደነበረ ሲገለፅ ቆይቷል፡፡ ከዚህ ሲሻገርም አስፈላጊውን ቅድመ ጥንቃቄ በጊዜው ማድረግ ባለመቻሏ የአደጋው መጠን የከፋ እንዲሆን ትልቅ በር ከፍቷል፡፡ ታዲያ እነዚህ እና ሌሎች ሁነቶች ተደማምረው ወጤቱን የከፋ አደረገው፡፡
ይሁንና በእነዚህ አሳዛኝ ሁኔታዎች ወስጥ ያለፈቸው ይህች ሃገር ተስፋን የሚያለመልም መልካም ዜና ፈፅሞ አልጠፋባትም ነበር፡፡ የ 101 ዓመት አዛውንት የሆኑት Mr. P ደግሞ ለዚህ ተስፋ መለምለም ዋነኛው ምክንያት ናቸው፡፡ እኝህ የ 101 ዓመት አዛውንት በኮሮናቫይረስ ተጠቅተው ብዙዎች ሞታቸውን ሲጠባበቁላቸው የቆዩ ቢሆንም በተደረገላቸው የሃኪም እገዛ እና በሰነቁት ትልቅ ተስፋ ከቫይረሱ ሙሉ ለሙሉ አገግመው የታሪክ ነጋሪ መሆናቸውን ቀጥለዋል፡፡ እኝህ አባት የስፓኒሽ ፍሉ ተብሎ በሚታወቀውና የብዙዎችን ነፍስ በቀጠፈው በዚያ ስከፊ ጊዜ እንደተወለዱ ያስታወቁት የኢንፈርሚ ሆስፒታል ዶክተሮች የዘመናችን አደጋ የሆነውን ኮሮናቫይረስን ዳግም ያሸነፉ ትልቅ አባት ሲሉ አሞግሰዋቸዋል፡፡
Mr. P በዚህ እድሜያቸው ከቫይረሱ አገግመው ወደቤታቸው የሄዱ ብቸኛው የጣልያን ዜጋ ሲሆኑ፤ ከዚህ ቀደምም በቻይና የሚኖሩ የ 103 የእድሜ ባለፀጋ ከሀኪሞች በተደረገላቸው ከፍተኛ እገዛ ከኮሮናቫይረስ ሙሉ ለሙሉ አገግመው ለብዙዎች ተስፋ እንደሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡
ምንጭ፡ IFLScience Store
በቤልጂየም የ12 ዓመቷ ህፃን በኮሮናቫይረስ ህይወቷ አልፏል
ይህ ለወጣቶች ምን መልእክት ይሰጣል
************************************
በቤልጂየም በኮሮናቫይረስ የተያዘች አንዲት የ12 ዓመት ህፃን ህይወቷ ማለፉን የሃገሪቱ የጤና ሚኒስትር አስታውቋል፡፡ የሃገሪቱ የመንግስት ቃል አቀባይ ኢማኑዬል አንድሬ በዛሬ መግለጫቸው እንዳስረዱት ህፃኗ የትኩሳት ምልክት ከታየባት ከሶስት ቀን በኋላ በቫይረሱ መየዟን ለመረጋገጥ የተቻለ ቢሆንም በዚህ ፍጥነት ህይወቷ እንዴት ሊያልፍ እንደቻለ አለመታወቁን ተናግረዋል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ወጣቶችና ህፃናት በኮሮናቫይረስ መሞታቸው እየተስተዋለ መምጣቱን ያስረዱት ቃል አቀባዩ አንድሬ ምንም አይነት መዘናጋት ሳየስፈልግ ተገቢው ጥንቃቄ በወጣቶች እንዲወሰድ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡
በአውሮፓ ከዚህ በፊት በእንግሊዝ የ18 ዓመት ወጣት፣ በፈረንሳይ የ16 ዓመት ሴት ልጅ፣ በፖርቹጋል የ14 ዓመት ልጅ እንዲሁም አሁን ደግሞ 12 ህፃን በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መሞታቸውን ተከትሎ ወጣቶች እና ህፃናት ከአላስፈላጊ መዘናጋት ወጥተው ራሳቸውን እና ማህበረሰቡን ከበሽታው እንዲጠብቁ የጤና ባለሙያዎች እየተናገሩ ይገኛል፡፡
በበርካታ አገራት በእድሜ የገፉ ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ በመሆናቸው እና የሚሰጡ የጤና ማሳሰቢያዎችም ከዚህ ጋር ብቻ የተያያዙ በመሆናቸው ወጣቶች እኛን አየጠቃንም ወደሚል እሳቤ እንዲሄዱና ከፍተኛ መዘናጋት ውስጥ እንዲገቡ እንዳደረጋቸው የሚታወቅ ነው፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ በቅርቡ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ለወጣቶች እንዳስጠነቀቁት የኮሮናቫረስ እድሜያቸው እንደገፋ ሰዎች ወጣቶችን በፍጥነት ባይገድልም ለሳምንታት ሆስፒታል ሊያስተኛቸው እና ከዚያም ሲያልፍ ለሞት ሊያደርሳቸው አንደሚቸል መገንዘብ ያስፈልጋል ብለዋል። ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም ወጣቶች ምንም የህመም ስሜት ባይሰማቸው እንኳ ወዴት መንቀሳቀስ እንዳለባቸው እና የሚወስኗቸው እያንዳንዷ ውሳኔዎች ለሌሎች የሞትና የሕይወት ጉዳይ ሊሆን እንደሚችል በማሰብ ከመቼውም ጊዜ በማስተዋል እንዲጓዙ ጥሪ አስተላልፈው ነበር።
በህጻናት በኩልም እስካሁን በይፋ እንደተረጋገጠው አብዛኞቹ በዚህ ቫይረስ የተጠቁ ህፃናት በበሽታው የመሞት መጠናቸው እጅግ ዝቅተኛ ቢሆንም በሽታውን ወደሌሎች የማስተላለፍ እድላቸው ከፍተኛ ሊሆን እንደሚችል ግን ባለሙያዎች ያስረዳሉ፡፡ ምክንያቱም በዚህ የዕድሜ ክልል ያሉ ህጻናት የሚታይባቸው የበሽታው ምልክት በጣም አናሳ በመሆኑ እና በሃላፊነት ስሜት ራሳቸውን እና አካባቢያቸውን መጠበቅ ስለማይችሉ ምናልባት የበሽታው ዋነኛ አስተላለፊዎች ሊሆኑ ይችላሉ። ያም ሆነ ይህ ግን ነገሮች ይበልጥ አስከሚታወቁ ድረስ ወጣቶች እና ህፃናት በፍፁም ሃላፊነት ራሳቸውን እና በዙሪያቸው ያሉ ሰዎችን ከቫይረሱ መጠበቅ እንደሚገባቸው የሁሉም መልዕክት ነው፡፡
ምንጭ፡ express.co.uk/
ይህ ለወጣቶች ምን መልእክት ይሰጣል
************************************
በቤልጂየም በኮሮናቫይረስ የተያዘች አንዲት የ12 ዓመት ህፃን ህይወቷ ማለፉን የሃገሪቱ የጤና ሚኒስትር አስታውቋል፡፡ የሃገሪቱ የመንግስት ቃል አቀባይ ኢማኑዬል አንድሬ በዛሬ መግለጫቸው እንዳስረዱት ህፃኗ የትኩሳት ምልክት ከታየባት ከሶስት ቀን በኋላ በቫይረሱ መየዟን ለመረጋገጥ የተቻለ ቢሆንም በዚህ ፍጥነት ህይወቷ እንዴት ሊያልፍ እንደቻለ አለመታወቁን ተናግረዋል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ወጣቶችና ህፃናት በኮሮናቫይረስ መሞታቸው እየተስተዋለ መምጣቱን ያስረዱት ቃል አቀባዩ አንድሬ ምንም አይነት መዘናጋት ሳየስፈልግ ተገቢው ጥንቃቄ በወጣቶች እንዲወሰድ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡
በአውሮፓ ከዚህ በፊት በእንግሊዝ የ18 ዓመት ወጣት፣ በፈረንሳይ የ16 ዓመት ሴት ልጅ፣ በፖርቹጋል የ14 ዓመት ልጅ እንዲሁም አሁን ደግሞ 12 ህፃን በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መሞታቸውን ተከትሎ ወጣቶች እና ህፃናት ከአላስፈላጊ መዘናጋት ወጥተው ራሳቸውን እና ማህበረሰቡን ከበሽታው እንዲጠብቁ የጤና ባለሙያዎች እየተናገሩ ይገኛል፡፡
በበርካታ አገራት በእድሜ የገፉ ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ በመሆናቸው እና የሚሰጡ የጤና ማሳሰቢያዎችም ከዚህ ጋር ብቻ የተያያዙ በመሆናቸው ወጣቶች እኛን አየጠቃንም ወደሚል እሳቤ እንዲሄዱና ከፍተኛ መዘናጋት ውስጥ እንዲገቡ እንዳደረጋቸው የሚታወቅ ነው፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ በቅርቡ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ለወጣቶች እንዳስጠነቀቁት የኮሮናቫረስ እድሜያቸው እንደገፋ ሰዎች ወጣቶችን በፍጥነት ባይገድልም ለሳምንታት ሆስፒታል ሊያስተኛቸው እና ከዚያም ሲያልፍ ለሞት ሊያደርሳቸው አንደሚቸል መገንዘብ ያስፈልጋል ብለዋል። ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም ወጣቶች ምንም የህመም ስሜት ባይሰማቸው እንኳ ወዴት መንቀሳቀስ እንዳለባቸው እና የሚወስኗቸው እያንዳንዷ ውሳኔዎች ለሌሎች የሞትና የሕይወት ጉዳይ ሊሆን እንደሚችል በማሰብ ከመቼውም ጊዜ በማስተዋል እንዲጓዙ ጥሪ አስተላልፈው ነበር።
በህጻናት በኩልም እስካሁን በይፋ እንደተረጋገጠው አብዛኞቹ በዚህ ቫይረስ የተጠቁ ህፃናት በበሽታው የመሞት መጠናቸው እጅግ ዝቅተኛ ቢሆንም በሽታውን ወደሌሎች የማስተላለፍ እድላቸው ከፍተኛ ሊሆን እንደሚችል ግን ባለሙያዎች ያስረዳሉ፡፡ ምክንያቱም በዚህ የዕድሜ ክልል ያሉ ህጻናት የሚታይባቸው የበሽታው ምልክት በጣም አናሳ በመሆኑ እና በሃላፊነት ስሜት ራሳቸውን እና አካባቢያቸውን መጠበቅ ስለማይችሉ ምናልባት የበሽታው ዋነኛ አስተላለፊዎች ሊሆኑ ይችላሉ። ያም ሆነ ይህ ግን ነገሮች ይበልጥ አስከሚታወቁ ድረስ ወጣቶች እና ህፃናት በፍፁም ሃላፊነት ራሳቸውን እና በዙሪያቸው ያሉ ሰዎችን ከቫይረሱ መጠበቅ እንደሚገባቸው የሁሉም መልዕክት ነው፡፡
ምንጭ፡ express.co.uk/
Express.co.uk
Latest UK and World News, Sport and Comment | Express.co.uk
Latest news, showbiz, sport, comment, lifestyle, city, video and pictures from the Daily Express and Sunday Express newspapers and Express.co.uk
25 በመቶው የኮሮናቫይረስ ተጠቂ ምልክቶችን ላያሳይ ይችላል፡ ጥናት
**********************
ቀላል ቁጥር የሌለው የኮሮና ቫይረስ ተጠቂ ምልክቶችን በትክክል ሊያሳይ ባለማቻሉ የቫይረሱን ስርጭት በከፍተኛ ሁኔታ ሊያበዛው እንደሚችል አንድ የአሜሪካ የጤና ባለስልጣን አስታወቁ፡፡ በአሜሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ መዕከል (CDC) ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ዶክተር ሮበርት ሬድፊልድ 25 በመቶ የሚሆነው በቫይረሱ የተያዘ ሰው ምልክቶችን ማሳየት በሚገባበት በመጀመሪያዎቹ አጭር ቀናት ውስጥ የትኞቹም ምልክቶች የማይታዩበት ወይም በህክምና አጠራሩ (asymptomatic) በመሆኑ ለቫይረሱ መዛመት ትልቅ መደላድል ሊሆን እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡
ዋና ዳይሬክተሩ በተለይም በትናትናው ዕለት በ CDC ጆርናል የታተመውን እንድ ጥናት ዋቢ በማድረግ የቫይረሱ ስርጭት ከዚህ ጉዳይ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ሊኖረው እንደሚችል አስረድተዋል፡፡ ይህ ጥናት ከጥቂት ወራት በፊት በሲንጋፖር መረጃቸው ተሰብስቦ ክትትል ሲደረግባቸው በነበሩ 243 ኬዞች ላይ የሚያተኩር ሲሆን፤ ከእነዚህ ኬዞች ውስጥ ደግሞ 150 የሚሆኑት ከላይ ከተጠቀሰው ጉዳይ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት አላቸው በሚል የተለዩ ነበር፡፡ ታዲያ ተለይተው በተቀመጡት 150 ኬዞች ላይ በተደረገ ሰፊ ምርምር 6.4 በመቶ ወይም 19 የሚሆኑት ሰዎች ምንም አይነት የህመም ምልክት ሳይታይባቸው ቫይረሱን ወደሌሎች ሲያሰራጩ እንደነበር ለመረዳት ተችሏል፡፡
ይህ ጉዳይ በመጋቢት 19 በወጣ አንድ ጥናት ላይ እንዲሁ በስፋት የተጠቀሰ ሲሆን ይህም ቀደም ብለው በቻይና ከሁቤይ ግዛት ውጭ በሆኑ ቦታዎች በተሰበሰቡ 468 ኬዞች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነበር፡፡ ታዲያ በዚህም ጥናት እንደታየው ክትትል ሲደረግባቸው ከነበሩት 468 ኬዞች ውሰጥ 58 የሚሆኑት ቫይረሱን ያስተላለፉባቸው ተጠቂዎች ምንም ምልክት ሳይታይባቸው፤ እነዚህ 58 ሰዎች ግን የበሽታው ዋና ዋና ምልክት ታይቶባቸው እንደነበረ በጥናቱ ተገልጿል፡፡ ይህም 12.6% የሚሆነው ኬዝ በአንድም ይሁን በሌላ በ asymptomatic transmission ሁኔታ ውስጥ ያለፈ መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡
ታዲያ እነዚህን መረጃዎች ሲያጠናቅር የነበረው ተቋሙ በዚህ ጉዳይ ላይ የሚሰሩት ተጨማሪ ምርምሮች ይበልጥ እስከሚጠናከሩ ሰዎች የሚጠቀሟቸው የፊት መሸፈኛ ጭብሎች እጀግ አስፈላጊ እንደሚሆኑ ተነግረዋል፡፡ ይህም የሆነበት ዋና ምክንያት ሰዎች በዚህ መልኩ በቫይረሱ ተጠቅተው ምልክቶች የማይታዩባቸው ከሆነ የቫይረሱን ስርጭት ለመቀነስ አንደኛው መንገድ የሚሆነው ይህን ማስክ ማድረግ ነው፡፡ ምክንያቱም ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ እንደተነገረው የፊት ማስክ ማድረግ ያለባቸው ሰዎች የጤና ባለሙያዎች ወይም በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች (ወደሌሎች እንዳያስተላልፉ በሚል ስለሆነ) አሁን ላይ በዚህ ጉዳይ የተነሳ ብዙ የፊት መሸፈኛ ጭብሎች ሊያስፈልጉ እንደሚችለ ግምታቸውን ያስቀምጣሉ፡፡
ታዲያ ከዚህ ተያይዞ ሁላችንም ልብ ልንለው የሚገባው ነገር ቫይረሱ የሚተላለፍብን ብቻ ሳንሆን አኛ እራሳችን ቫይረሱን ወደሌሎች የምናስተላልፍ መሆናችንን ተረድተን ለይምሰል ያልሆነ ጥንቃቄን ማድረግ እንደሚገባን ነው፡፡ በተለይም ወጣቶች እና ታደጊዎች በቫይረሱ ከተጠቁ በኋላ የትኛውም የህመም ስሜት ሳይሰማቸው እና ምልክቶች ሳይታይባቸው ቀናትን ሊያሰቆጥሩ ይችላሉና የሚያደርጉት ጥንቃቄ ይህን ከግምት ያስገባ መሆኑ እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡
ለበለጠ፡ https://www.livescience.com/
coronavirus-asymptomatic-spread.html
**********************
ቀላል ቁጥር የሌለው የኮሮና ቫይረስ ተጠቂ ምልክቶችን በትክክል ሊያሳይ ባለማቻሉ የቫይረሱን ስርጭት በከፍተኛ ሁኔታ ሊያበዛው እንደሚችል አንድ የአሜሪካ የጤና ባለስልጣን አስታወቁ፡፡ በአሜሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ መዕከል (CDC) ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ዶክተር ሮበርት ሬድፊልድ 25 በመቶ የሚሆነው በቫይረሱ የተያዘ ሰው ምልክቶችን ማሳየት በሚገባበት በመጀመሪያዎቹ አጭር ቀናት ውስጥ የትኞቹም ምልክቶች የማይታዩበት ወይም በህክምና አጠራሩ (asymptomatic) በመሆኑ ለቫይረሱ መዛመት ትልቅ መደላድል ሊሆን እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡
ዋና ዳይሬክተሩ በተለይም በትናትናው ዕለት በ CDC ጆርናል የታተመውን እንድ ጥናት ዋቢ በማድረግ የቫይረሱ ስርጭት ከዚህ ጉዳይ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ሊኖረው እንደሚችል አስረድተዋል፡፡ ይህ ጥናት ከጥቂት ወራት በፊት በሲንጋፖር መረጃቸው ተሰብስቦ ክትትል ሲደረግባቸው በነበሩ 243 ኬዞች ላይ የሚያተኩር ሲሆን፤ ከእነዚህ ኬዞች ውስጥ ደግሞ 150 የሚሆኑት ከላይ ከተጠቀሰው ጉዳይ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት አላቸው በሚል የተለዩ ነበር፡፡ ታዲያ ተለይተው በተቀመጡት 150 ኬዞች ላይ በተደረገ ሰፊ ምርምር 6.4 በመቶ ወይም 19 የሚሆኑት ሰዎች ምንም አይነት የህመም ምልክት ሳይታይባቸው ቫይረሱን ወደሌሎች ሲያሰራጩ እንደነበር ለመረዳት ተችሏል፡፡
ይህ ጉዳይ በመጋቢት 19 በወጣ አንድ ጥናት ላይ እንዲሁ በስፋት የተጠቀሰ ሲሆን ይህም ቀደም ብለው በቻይና ከሁቤይ ግዛት ውጭ በሆኑ ቦታዎች በተሰበሰቡ 468 ኬዞች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነበር፡፡ ታዲያ በዚህም ጥናት እንደታየው ክትትል ሲደረግባቸው ከነበሩት 468 ኬዞች ውሰጥ 58 የሚሆኑት ቫይረሱን ያስተላለፉባቸው ተጠቂዎች ምንም ምልክት ሳይታይባቸው፤ እነዚህ 58 ሰዎች ግን የበሽታው ዋና ዋና ምልክት ታይቶባቸው እንደነበረ በጥናቱ ተገልጿል፡፡ ይህም 12.6% የሚሆነው ኬዝ በአንድም ይሁን በሌላ በ asymptomatic transmission ሁኔታ ውስጥ ያለፈ መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡
ታዲያ እነዚህን መረጃዎች ሲያጠናቅር የነበረው ተቋሙ በዚህ ጉዳይ ላይ የሚሰሩት ተጨማሪ ምርምሮች ይበልጥ እስከሚጠናከሩ ሰዎች የሚጠቀሟቸው የፊት መሸፈኛ ጭብሎች እጀግ አስፈላጊ እንደሚሆኑ ተነግረዋል፡፡ ይህም የሆነበት ዋና ምክንያት ሰዎች በዚህ መልኩ በቫይረሱ ተጠቅተው ምልክቶች የማይታዩባቸው ከሆነ የቫይረሱን ስርጭት ለመቀነስ አንደኛው መንገድ የሚሆነው ይህን ማስክ ማድረግ ነው፡፡ ምክንያቱም ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ እንደተነገረው የፊት ማስክ ማድረግ ያለባቸው ሰዎች የጤና ባለሙያዎች ወይም በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች (ወደሌሎች እንዳያስተላልፉ በሚል ስለሆነ) አሁን ላይ በዚህ ጉዳይ የተነሳ ብዙ የፊት መሸፈኛ ጭብሎች ሊያስፈልጉ እንደሚችለ ግምታቸውን ያስቀምጣሉ፡፡
ታዲያ ከዚህ ተያይዞ ሁላችንም ልብ ልንለው የሚገባው ነገር ቫይረሱ የሚተላለፍብን ብቻ ሳንሆን አኛ እራሳችን ቫይረሱን ወደሌሎች የምናስተላልፍ መሆናችንን ተረድተን ለይምሰል ያልሆነ ጥንቃቄን ማድረግ እንደሚገባን ነው፡፡ በተለይም ወጣቶች እና ታደጊዎች በቫይረሱ ከተጠቁ በኋላ የትኛውም የህመም ስሜት ሳይሰማቸው እና ምልክቶች ሳይታይባቸው ቀናትን ሊያሰቆጥሩ ይችላሉና የሚያደርጉት ጥንቃቄ ይህን ከግምት ያስገባ መሆኑ እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡
ለበለጠ፡ https://www.livescience.com/
coronavirus-asymptomatic-spread.html
Live Science
Live Science | Latest science news and articles for those with curious minds
Daily discoveries, groundbreaking research and fascinating science breakthroughs that impact you and the wider world, reported by our expert journalists.
ኮሮናን ለመከላከል ሲባል የሰዎችን እንቅስቃሴ መረጃ ይፋ እንደሚያደርግ ጎግል አስታውቋል
========================
የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ከሚከላከሉ መንገዶች ውስጥ ዋነኛው ከሰዎች ጋራ ያለ ርቀርን መጠበቅ ነው፡፡ ይህ ግን በሁሉም ዘንድ እኩል ሲተገበር አናየውም፡፡ ታድያ መንግስታት ዜጎቻቸው በምን ያህል የአካላዊ ርቀታቸውን መጠበቅ አሰለመጠበቃቸውን እንዲያውቁ በማሰብ የተጠቃሚዎቹን እንቅስቃሴ ይፋ እንደሚያደርግ ጎግል አስታውቋል፡፡ መረጃው በ131 ሀገራት ያሉ ተጠቃሚዎቹን የእንቅስቃሴ መረጃ በልዩ ድረ-ገፅ ላይ ይፋ የሚደረግ ሲሆን ሰዎች መቼና የት ተገኝተው እንደነበረ ያሳያል፡፡ መረጃዎቹ ሰዎች እንደ ገበያ ማዕከል፣ ሱቅ፣ ቤቶች እና ፓርኮች ባሉ ስፍራዎች የሚያደርጉት ምልልስ በምን ያህል መጠን እንደጨመረና እንደቀነሰ በመቶኛ አስልቶ የሚያቀርብ ይሆናል፡፡ ለምሳሌ ከሰሞኑን በፈረንሳይ ሰዎች ወደ ምግብ ቤት፣ ካፌ፣ ገበያ ማዕከላት፣ ቤተ-መዘክሮች እና መዝናኛፓርኮች ያደረጉት ጉዞ በ88 በመቶ መቀነሱን መረጃው አመላክቷል፡፡ ወደ አቅራቢያ ገበያዎች የሚደረጉት ጉዞዎች ቀድሞ በ40 በመቶ ያደጉ ቢሆንም የኋላ ኋላ ግን በሰባ በመቶ ወርደዋል፡፡ በቢሮ አካባቢ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችም እንዲሁ በ56 በመቶ ቀንሷል፡፡
መረጃዎቹ በዓለም ዙርያ ከአንድ ቢሊዮን በላይ የሞባይል ተጠቃሚዎች ባሉት የጎግል ማፕ አገልግሎት አማካኝነት የሚሰበሰብ ነው፡፡ ይህም በዓለም ላይ ካለ ማንኛውም ስርዓት በላይ የሰዎችን መረጃ አጥርቶ የሚያቀርብ እንደሆነ ይነገርለታል፡፡ መረጃዎቹ ግን የግንኙነት ዝርዝር፣ መገኛ እና እንቅስቃሴን የመሰሉ የግለሰቦችን ማንነት ይፋ የሚያደርጉ መረጃዎችን እንደማይሰጡ የተገለፀ ሲሆን የግለሰቦቹን ማንነት እንዳይታታወቅ የሚረዱ ስልቶችንም በግብዓትነት መያዙ ተነግሮለታል፡፡
የቻይና፣ ሲንጋፖር እና እስራኤልን ጨምሮ የተለያዩ የዓለም መንግስታት የኮቪድ-19 ስርጭትን ለመግታት ያግዝ ዘንድ በዜጎቻቸው ላይ የኤሌክትሮኒክስ ክትትል እንዲደረግ አዘዋል፡፡ በአውሮፓና አሜሪካን የሚገኙ የቴክኖሎጂ ተቋማትም የተጠቃሚዎቻቸውን ማንነት በሚሰውር መልኩ የስማርት ስልኮችን መረጃ ቫይረሱን ለመከላከል እያዋሉት ይገኛሉ፡፡ ግለሰበዊ ነፃነትን የሚጋፋ መረጃ ስብሰባን አጥብቃ የምትቃወመው ጀርመን እንኳን ቫይረሱን ለመቆጣጠር የሚያስችል የስማርት ስልክ መተግበሪያ ወደስራ ለማስገባት እያሰበች ትገኛለች፡፡
ሆኖም ይህ አይነት አሰራር ከትችት አላመለጠም፡፡ የተለያዩ የመብት ተሟጋቾች ይህ ዘዴ ኮሮናን ምክንያት በማድረግ አምባገነን መንግስታት የገለልተኞችን ድምፅ ለማፈን እና መንግስታዊ ስለላን ለማጠናከር እየተጠቀሙበት መሆኑን ቅሬታ እያሰሙ ናቸው፡፡ ዲሞክራሲያዊ በሚባሉ ሀገራት ዘንድም ይህ ዘዴ የሰዎችን ግለሰበዊ ነፃነት በዘላቂነት እንደሚጎዳ ተፈርቷል፡፡
ምንጭ፡ Bloomberg እና Tech Xplore
========================
የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ከሚከላከሉ መንገዶች ውስጥ ዋነኛው ከሰዎች ጋራ ያለ ርቀርን መጠበቅ ነው፡፡ ይህ ግን በሁሉም ዘንድ እኩል ሲተገበር አናየውም፡፡ ታድያ መንግስታት ዜጎቻቸው በምን ያህል የአካላዊ ርቀታቸውን መጠበቅ አሰለመጠበቃቸውን እንዲያውቁ በማሰብ የተጠቃሚዎቹን እንቅስቃሴ ይፋ እንደሚያደርግ ጎግል አስታውቋል፡፡ መረጃው በ131 ሀገራት ያሉ ተጠቃሚዎቹን የእንቅስቃሴ መረጃ በልዩ ድረ-ገፅ ላይ ይፋ የሚደረግ ሲሆን ሰዎች መቼና የት ተገኝተው እንደነበረ ያሳያል፡፡ መረጃዎቹ ሰዎች እንደ ገበያ ማዕከል፣ ሱቅ፣ ቤቶች እና ፓርኮች ባሉ ስፍራዎች የሚያደርጉት ምልልስ በምን ያህል መጠን እንደጨመረና እንደቀነሰ በመቶኛ አስልቶ የሚያቀርብ ይሆናል፡፡ ለምሳሌ ከሰሞኑን በፈረንሳይ ሰዎች ወደ ምግብ ቤት፣ ካፌ፣ ገበያ ማዕከላት፣ ቤተ-መዘክሮች እና መዝናኛፓርኮች ያደረጉት ጉዞ በ88 በመቶ መቀነሱን መረጃው አመላክቷል፡፡ ወደ አቅራቢያ ገበያዎች የሚደረጉት ጉዞዎች ቀድሞ በ40 በመቶ ያደጉ ቢሆንም የኋላ ኋላ ግን በሰባ በመቶ ወርደዋል፡፡ በቢሮ አካባቢ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችም እንዲሁ በ56 በመቶ ቀንሷል፡፡
መረጃዎቹ በዓለም ዙርያ ከአንድ ቢሊዮን በላይ የሞባይል ተጠቃሚዎች ባሉት የጎግል ማፕ አገልግሎት አማካኝነት የሚሰበሰብ ነው፡፡ ይህም በዓለም ላይ ካለ ማንኛውም ስርዓት በላይ የሰዎችን መረጃ አጥርቶ የሚያቀርብ እንደሆነ ይነገርለታል፡፡ መረጃዎቹ ግን የግንኙነት ዝርዝር፣ መገኛ እና እንቅስቃሴን የመሰሉ የግለሰቦችን ማንነት ይፋ የሚያደርጉ መረጃዎችን እንደማይሰጡ የተገለፀ ሲሆን የግለሰቦቹን ማንነት እንዳይታታወቅ የሚረዱ ስልቶችንም በግብዓትነት መያዙ ተነግሮለታል፡፡
የቻይና፣ ሲንጋፖር እና እስራኤልን ጨምሮ የተለያዩ የዓለም መንግስታት የኮቪድ-19 ስርጭትን ለመግታት ያግዝ ዘንድ በዜጎቻቸው ላይ የኤሌክትሮኒክስ ክትትል እንዲደረግ አዘዋል፡፡ በአውሮፓና አሜሪካን የሚገኙ የቴክኖሎጂ ተቋማትም የተጠቃሚዎቻቸውን ማንነት በሚሰውር መልኩ የስማርት ስልኮችን መረጃ ቫይረሱን ለመከላከል እያዋሉት ይገኛሉ፡፡ ግለሰበዊ ነፃነትን የሚጋፋ መረጃ ስብሰባን አጥብቃ የምትቃወመው ጀርመን እንኳን ቫይረሱን ለመቆጣጠር የሚያስችል የስማርት ስልክ መተግበሪያ ወደስራ ለማስገባት እያሰበች ትገኛለች፡፡
ሆኖም ይህ አይነት አሰራር ከትችት አላመለጠም፡፡ የተለያዩ የመብት ተሟጋቾች ይህ ዘዴ ኮሮናን ምክንያት በማድረግ አምባገነን መንግስታት የገለልተኞችን ድምፅ ለማፈን እና መንግስታዊ ስለላን ለማጠናከር እየተጠቀሙበት መሆኑን ቅሬታ እያሰሙ ናቸው፡፡ ዲሞክራሲያዊ በሚባሉ ሀገራት ዘንድም ይህ ዘዴ የሰዎችን ግለሰበዊ ነፃነት በዘላቂነት እንደሚጎዳ ተፈርቷል፡፡
ምንጭ፡ Bloomberg እና Tech Xplore
ቅዳሜ በ10 ሰዓት ይጠብቁን!!!
===================
የቴክ-ሳይንስ የቴሌቪዥን ፕሮግራማችን በምዕራፍ 2 ክፍል 5 ዝግጅቱ ነገ ቅዳሜ ከቀኑ አስር ሰዓት ጀምሮ ወደ እናንተ ይደርሳል፡፡ በዚህ ሳምንቱም ፕሮግራማችን እንደወትሮው ሁሉ ከልዩ ልዩ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ እንዲሁም ኢኖቬሽንን የተመለከቱ ዜናዎች፣ መረጃዎች፣ ታሪኮች፣ ትንታኔዎችቻችን ጋራ እንጠብቆታለን፡፡ ቻናሎን በ # MOE # TV ላይ በማድረግ በውብ ዝግጅቶቻችን እየተዝናኑ የሳይንስ እውቀቶን ያሳድጉ፤
በነገው መሰናዷችን
• በአብይ ፕሮግራም ውሽውሽ የሻይ ቅጠል እርሻ
• በተቋማት ታሪክ የባዮቴክኖሎጂ ኢኒስቲትዩት
• በብላቴናት ፕሮግራም ስካቫተር ስለሰራው የኮንሶ ታዲጊ
• በቴክኖሎጂ ታሪክ ስለፕሌን እና ሌሎችም አጓጊ ዝግጅቶች አንጠብቃችኋለን
===================
የቴክ-ሳይንስ የቴሌቪዥን ፕሮግራማችን በምዕራፍ 2 ክፍል 5 ዝግጅቱ ነገ ቅዳሜ ከቀኑ አስር ሰዓት ጀምሮ ወደ እናንተ ይደርሳል፡፡ በዚህ ሳምንቱም ፕሮግራማችን እንደወትሮው ሁሉ ከልዩ ልዩ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ እንዲሁም ኢኖቬሽንን የተመለከቱ ዜናዎች፣ መረጃዎች፣ ታሪኮች፣ ትንታኔዎችቻችን ጋራ እንጠብቆታለን፡፡ ቻናሎን በ # MOE # TV ላይ በማድረግ በውብ ዝግጅቶቻችን እየተዝናኑ የሳይንስ እውቀቶን ያሳድጉ፤
በነገው መሰናዷችን
• በአብይ ፕሮግራም ውሽውሽ የሻይ ቅጠል እርሻ
• በተቋማት ታሪክ የባዮቴክኖሎጂ ኢኒስቲትዩት
• በብላቴናት ፕሮግራም ስካቫተር ስለሰራው የኮንሶ ታዲጊ
• በቴክኖሎጂ ታሪክ ስለፕሌን እና ሌሎችም አጓጊ ዝግጅቶች አንጠብቃችኋለን