TechIn2
1.22K subscribers
1.47K photos
1 video
120 files
500 links
Technology & Innovation Institute (TechIn2), Ethiopia

የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት

ጠቃሚና ወቅታዊ የሆኑ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ፈጠራ፣ ጤና እና ሰብአዊ-ኣቅም ግንባታ(Human Development)መረጃዎችንና ምክሮችን በየእለቱ እናደርሶታለን።
Download Telegram
ኮሮናቫይረስ እና ኤች.አይ.ቪን በስልክ አማካኝነት የሚመረምር መሳሪያ ተሰራ
=========================
ብዙ ጊዜ በሀኪም ቤቶች ውስጥ ካሉት አሰልቺ ነገሮች አንዱ የቤተ-ሙከራ ምርመራ ውጤትን መጠበቅ ነው፡፡ በሽታው ሳይታወቅ ስር የሰደደ ከሆነ ደግሞ የቤተ-ሙከራ ውጤትን በሚጠበቅ ወቅት በሽታው ምን እንደሆነ ገና ሳይታወቅ ለከፋ ችግር የሚዳረጉ ህመምተኞች ይኖራሉ፡፡
ይህን ችግር ሊቀርፍ የሚችል የቴክኖሎጂ ግኝት ከቀናት በፊት ከወደ ሲንሲናቲ ዩኒቨርሲቲ ተሰምቷል፡፡ መሐንዲሶች ከሲንሲናቲ ዩኒቨርስቲ ጋር በመሆን አነስ ያለች ተንቀሳቃሽ የስማርት ስልክ ቤተ-ሙከራ ፈጥረዋል፡፡ ይህች የኤ.ቲ.ኤም ካርድ መጠን ያላት መሳሪያ ስልኩ ላይ ተሰክታ የምትሰራ ናት፡፡ በዩኒቨርሲቲው የኤሌክትሪካል ምህንድስና ፕሮፌሰር ሆነው እያገለገሉ የሚገኙት ቾንግ አህን ከምርምር ቡድናቸው ጋራ በመሆን የስማርት ስልክ መሣሪያዋን ለወባ በሽታ መመርመሪያነት የተጠቀሙባት ቢሆንም ሌሎች ስር የሰደዱ እና ተላላፊ በሽታዎችን ብሎም ከድብርት ጋራ የተያያዙ ሆርሞኖችን መመርመር እንደምትችል ተገልጿል፡፡ መሳሪያዋ መመርመር ከምችላቸው ከነዚህ በሽታዎች ውስጥ ኤች. አይ. ቪ እና አሳሳቢው የኮሮና ቫይረስ ተጠቃሾች ናቸው፡፡
ምርመራውን ለማድረግ ታማሚው በቀላሉ የፕላስቲክ ከነዚህ ቺፑን ወደ አፉ በማስገባት የምራቅ ናሙና መውሰድና የወሰደውን ምራቅ ለፍተሻ መሳሪያዋ ላይ ወዳለው ማስገቢያ መክተት ይኖርበታል፡፡ የተወሰዱት ናሙናዎች መሳሪያዋ ላይ ካሉ ሁለት መተላለፊያዎች እንዲሰርጉ ይደረጋል፡፡ አንደኛው መተላለፊያ ናሙናውን ቀዝቅቀዘው ከደረቁ ተከላካይ ፀረ-እንግዳ አካላት (Antibodies) ጋራ ሲያቀላቅለው ሌላኛው ደግሞ የተለያዩት ናሙናዎች በሶስት ሴንሰሮች ላይ መልሰው በሚደባለቁበት ወቅት የሚያሳዩትን ውጤት የሚያነብ በቅዝቃዜ የደረቀ ሙቀት አልባ መብራትን (Luminescent) ይዟል፡፡ መሳሪያዋ በዚህ መልክ ምርመራውን ካከናወነች በኋላ ውጤቱን ለዚህ ተብሎ በተሰራ መተግበሪያ ወይም አፕሊኬሽን አማካኝነት ወደ ሀኪሙ እንዲደርስ ታደርጋለች፡፡
እንደ ተመራማሪዎቹ ከሆነ ከተለምዷዊው ቤተ-ሙከራ አንፃር ይህች መሳሪያ ተመሰሳሳይ ውጤትን የምትሰጥ ቢሆንም ከዋጋ እና አጠቃቀም ቅለት አንፃር ግን የተሻለች ናት፡፡ ከዚህ ባሻገር ግንየመሳሪያውትልቁ ግኝት ናሙናዎቹን ተፈጥሮአዊ መንገድን በመጠቀም በሁለቱ እጅግ ጠባባብ መተላለፊያዎች በማሳለፍ ከሴንሰሮቹ ማድረሷ ላይ መሆኑን የጥናቱ ዋና ፀሐፊ ስትሂቶድሂ ጎሆሽ ገልፀዋል፡፡ ምንም እንኳን መሳሪያዋ የተሰራችው የተጠቀሱት አይነት በሽታዎችን ለመመርመር ቢሆንም ስማርት ስልኮች ጥቅም ላይ እየዋሉበት ባለው የአዕምሮ ጤና ህክምና ዘርፍ የማገልገል አቅም እንዳላት የተመራማሪዎቹ እምነት ነው፡፡
ምንጭ፡ SciTechDaily
ዩትዩብ youtube.com/channel/UC6jvUOLRSkVEQtc
5Annfwvg
ፌስቡክ facebook.com/TechinEthiopia/
ትዊተር twitter.com/TechinEthiopia
ካሉበት ሆነው ዕውቀትን ይሸምቱ፤ የብሄራዊ ዲጂታል ቤተ-መጽሐፍትን ይጠቀሙ!!!
=======================
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት የብሔራዊ ዲጂታል ቤተ-መጽሐፍት በመገንባት ባለፉት ዓመታት ለተጠቃሚዎች ከፍተኛ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ ዲጂታል ቤተ-መጽሐፍቱ የተለያዩና ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን መረጃዎችን ሰብስቦ ያካተተና በሃገር አቀፍ ደረጃ አገልግሎት መስጠት በሚችል መልኩ የተገነባ ሲሆን፤ library.techin.et ብለው በመግባት በቀላሉ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን ይችላሉ፡፡
ዲጂታል ቤተ-መጽሐፍቱ በይዘቱ ሁሉንም የዕድሜ ክፍል፣ የትምህርትና የዕውቀት ደረጃ ያማከለ መሆኑ እና ለአጠቃቀም ምቹ ሆኖ መሰናዳቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ቁጥር ባላቸው ተጠቃሚዎች እንዲጎበኝና አገልግሎት እንዲሰጥ አድርጎታል፡፡ እርስዎም በስራዎ፣ በትምህርትዎ፣ በልጆችዎ ውጤታማነት ላይ አስተዋፅኦ ለማድረግ የብሔራዊ ዲጂታል ቤተ-መጽሐፍትን ይጠቀሙ፤ ለሌሎችም ይጋብዙ!!!
ዩትዩብ youtube.com/channel/UC6jvUOLRSkVEQtc
5Annfwvg
ፌስቡክ facebook.com/TechinEthiopia/
ትዊተር twitter.com/TechinEthiopia
ይቅርታ ወይስ በቀል፡ የትኛው ደስታን ይሰጥዎታል?
===============
ብዙዎቻችን ስለ ይቅርታ አስፈላጊነት ሲነገር ሰምተናል፤ እኛም ተናግረናል፡፡ በመዝናኛው ዘርፍ ላይ ተሰርቶ የተሰራ አዲስ ጥናት ግን ሰዎች ከይቅርታ ይልቅ ለመጥፎ ስራ ቅጣት ሲሰጥ ማየት እንደሚስደስታቸው ያስረዳል፡፡
በጆርናል ኦፍ ኮምዩኒኬሽን ሪሰርች ላይ የወጣው ይህ ጥናት 184 የኮሌጀ ተማሪዎችን ማዕከል በማድረግ የተሰራ ነው፡፡ ለእያንዳንዳቸው ለቴሌቪዥን ሊቀርብ እንደሚችል ተነግሮ 15 አጫጭር ታሪኮች እንዲያነቡ ሲሰጣቸው፤ ከነዚህ መካከል የመጀመሪያ አምስቱ ክፉ ሰው ከበደላቸው ሰዎች ዘንድ በቅንነት ሲስተናገድ፣ ሁለተኛዎቹ አምስት ታሪኮች በደለኛው ተመጣጣኝ ቅጣትን ሲቀበል፣ ሶስተኛዎቹ ደግሞ በደለኛው ላጠፋው ጥፋት ከሚገባው በላይ ቅጣትን ሲቀበል የሚያሳዩ ናቸው፡፡ ከአጫጭር ታሪኮቹ ውስጥ በአንዱ የሆነ ሰው 50 ዶላርን ከስራ ባልደረባው እንደሰረቀ ይተርካል፡፡ ተሳታፊዎቹ ለዚህ ታሪክ ከተሰጠው ሶስት አይነት መቋጫ ውስጥ አንዱ እንዲደርሳቸው ተደርጓል፡፡ በአንደኛው የታሪኩ መቋጫ ተበዳዩ ለሰራቂ ጓደኛው ይቅርታን ሰጥቶ ቡና እደሚጋብዘው ይተርካል፡፡ በሁለተኛው አፈፃፀም ተበዳዩ ከሰራቂው 50 ዶላር የሚያወጣ አንድ ጠርሙስ ውስኪ ሲወስድበት፤ ሶስተኛው ደግሞ ውስኪውንም ወስዶ የተሰረቀበትን ገንዘብ ሲያስመልስ ይተርካል፡፡
እነዚህን አጨራረሶች ካነበቡ በኋላ ተሳታፊዎቹ ታሪኩን መውደድ ወይ መጥላታቸውን እነዲገልፁ ይጠየቃሉ፡፡ በዚህ ሰዓት ተበዳዩ ይቅርታን ከሰጠውም ሆነ ከሚገባው በላይ መልስ ከሰጠው በላቀ ተመጣጣኝ ቅጣት ለተሰጠበት ትረካ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል፡፡ ተሳታፊዎቹ ባነበቧቸው 15 ታሪኮች ውስጥ ያለው የአዝናኝነት ደረጃ በሚገልፁበት ወቅት ደግሞ የይቅርታ ታሪኮቹ የመጨረሻውን ደረጃ ሲይዙ የልተመጣጠነ ቅጣት የሚሰጥባቸው ደግሞ ከሁሉም በበለጠ አዝናኝ ሆነው እንዳገኟቸው የሰጡት መልስ ያሳያል፡፡
ግን ምንም እንኳን ይቅርታ በበቀል ልክ ባያስደስታቸውም ይቅርታን ከበቀል በላይ ጥልቅና ስሜት የሚሰጥ እንደሆነ የተሳታፊዎቹ ዕምነት ነው፡፡ እንደ ግምገማ ከሆነ ሰዎች ላጠፉት ጥፋት ተመጣጣኝ ቅጣት እንዲያገኙ መታሰቡ የሰዎች ተፈጥሮአዊ እሳቤ ሲሆን የፍርድ መጓደልን መዳኘት ግን ለሁላችንም እኩል ያልተሰጠ ማመዛዘንን ይጠይቃል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ መውደድ አለመውደዳቸውን በሚያመነቡበት ኮምፒውተር ላይ የሚገልፁበት ፍጥነትም የተመዘገበ ሲሆን በዚህም መሰረት ጥናቱ ተሳታፊዎች ለተመጣጣኝ ቅጣቱ ትረካ የሚሰጡት ምላሽ ከከፍተኛ አፀፋም ሆነ የይቅርታ ትረካዎቹ የዘገየ ነበረ፡፡ እንደ ጥናቱ ዋና ፀሐፊ ፐሮፌሰር ማቲው ግሪዛርድ ከሆነ ሰዎች የበዳይ ተበዳይ ታሪክ በጠበቁት መልኩ ተጠናቆ ሲገኙት በፍጥነት ምላሽ ይሰጣሉ፡፡ ይህ ሳይሆን ቀርቶ ቅጣቱ ወንጀሉን የማይመጥን ሆኖ ሲያገኙት ግን መውደድ መጥላታቸውን ለመግለፅ ረዘም ያለ ጊዜ ሲወስድባቸው ታይቷል፡፡ ሆኖም ፍጥነታቸው ታሪኩ በይቅርታ አሊያም በበዛ አፀፋ ከመጠናቀቁ ጋራ ተያይዞ የተለያየ ነው፡፡ ይህ ግን በሚቀጥሉ ጥናቶች የሚሸፈን ይሆናል፡፡
ምንጭ፡ Medical Xpress
ዩትዩብ youtube.com/channel/UC6jvUOLRSkVEQtc
5Annfwvg
ትዊተር twitter.com/TechinEthiopia
የምድር በ habitable zone መገኘት
********************
ማንኛውም ኮከብ (ፀሀያችንን ጨምሮ) የራሱ የሆነ ሀቢቴብል ዞን (habitable zone) አለው። ሀቢቴብል ዞን ማለት ከኮከቡ በጣም ያልራቀ ወይንም ለኮከቡ በጣም ያልቀረበ የመኖሪያ ዞን ማለት ነው። ፀሀይ ወደ እኛ የተወሰነ የቀረበች ብትሆን ኖሮ ልክ እንደሜርኩሪ ሁሉ በመሬት ላይ ያለው ነገር በሙሉ በመድረቅ ይቃጠል ነበር፡፡ ከመሬት ትንሽ የራቀች ቢሆን ኖሮ ደግሞ ሁሉም ነገር በበረዶ ይሸፈን ነበር፡፡
በሁለቱም ሁኔታዎች መኖር አይቻልም፡፡ ከፀሀይ ጥቂት ሙቀትን የሚያገኙት የዋልታ አካባቢዎች ሁል ጊዜም በበረዶ የተሸፈኑ ሲሆኑ ከዛ የተሻለ ሙቀትን የሚያገኙት የምድር ወገብ አከባቢዎች ሁሌም ሞቃታማ ናቸው፡፡ በዋልታው እና በምድር ወገብ አካባቢ ያለው የሙቀት ልዩነት መሬት ላይ መጠነኛ ሙቀት እንዲኖር በማስቻል መሬት ለህይወት አመቺ እንድትሆን አድርጓታል፡፡
በዚህ ዞን የምትገኘው መሬት በምድር ወገብ ላይ 12,756 ኪሎሜትሮች የምትረዝም ቢሆንም በራሱዋ ዛቢያ ላይ የምትዞርበት ፍጥነት ግን ከግዜ ወደ ግዜ በጣም በዝግታ እየቀነሰ እንደሚገኝ የስነ ፈለክ ሊቃውንት ያስረዳሉ። ይሁንና እንደተመራማሪዎቹ ትንታኔ ከሆነ ይህ ብዙም የሚያሰጋ አይደለም ምክንያቱም በ 100 አመታት ውስጥ በ17 ሚሊ ሰኮንድ ብቻ ነው የሚቀንሰው። ይህም ማለት ከ 140 ሚሊየን አመታት በኋላ ምድር ላይ 25ኛ ሰአት ይጨመራል ማለት ነው።
ምድራችን ከ7 ትላልቅ አለቶች ተገጣጥማ ነው የተሰራችው። እነዚህን አለቶች ቴክቶኒክ ፕሌት (tectonic plates) እንላቸዋለን። ከሌሎች ፕላኔቶች በተለየ ለፀሃይ ብዙም ያልራቀች እና ያለቀረበችው መሬት በተመጣጠነ የህይወት ኡደቷ የእነዚህ አለቶች ተከፋፍሎ መቀመጥን በማስቻል፤ አንዱ ክፍለ መሬት ላይ የተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ ሌላኛው ላይ እንዳይሰማ ሆኗል። እዛው አለት ላይ ያሉ ሀገራት ብች ነው ሊሰማቸው የሚችለው። ምድር እንደሌሎቹ ከ 1 ወጥ አለት ተሰርታ ቢሆን ኖሮ ህንድ ላይ የተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ ኢትዪጲያ ላይ ይሰማ ነበር።
ምድር በጠቅላላው በውስጡዋ 32.1%ብረት፣ 30.1% ኦክስጂን፣ 15.1% ሲልኮን እና 13.9% ማግኒዝየም ይዛለች። ከዚህ የምድር የተመጣጠነ የህይወት ኡደት ጀርባ ከፍተኛ ሚና ከሚጫወቱ የጠፈር አካለት መካከል ጨረቃ ዋነኛዋ ስትሆን ከዛ ውጪ ደግሞ እንዲሁ ምድርን የሚዞሩ 2 አስትሮይዶች አሉ።
ምንጭ፡ Airtable universe እና E.A
የኮሮና ቫይረስ በአለማችን የደቀነው የኢኮኖሚ ፈተና
**********************************
በዓለም ኢኮኖሚ ላይ የተለያዩ አደጋዎች ሲያንዣብቡ ቀጥሎ የሚመጣውን ነገር ለመመልከት ግዙፉ የፋይናንስ ማዕከል ዎል ስትሪት ብዙ ታሪኮችን ያገላብጣል፡፡ እ.ኤ.አ. በ 2003 በተከሰተው የሳርስ ወረርሽኝ የቻይና ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት በከባድ ሁኔታ የተመታ ቢሆንም ቶሎ ለማገገም ብዙ ጊዜ አልፈጀበትም ነበር፡፡ አሁን የተከሰተው ኮቪድ-19 ከሳርስ የበለጠ የሰዎችን ሕይወት የቀጠፈ ቢሆንም ባለሀብቶች የኢኮኖሚ ተፅዕኖው በተመሳሳይ ሁኔታ ይስተካከላል የሚል እምነት አላቸው፡፡ በተለይም ወረርሽኙ በሁቤ ግዛት ውስጥ በከፍተኛ ሁኔታ እተስፋፋ ቢሆንም ከሁቤ ግዛት ውጭ ግን የመስፋፋት ፍጥነቱም እየቀነሰ በመምጣቱ አደጋው ብዙም እንደማይሆን ያነሳሉ፡፡ ታዲያ እነዚህን ሁኔታዎች ከግምት ውስጥ በማስገባት ዎል ስተሪት እና ብዙ ኢኮኖሚስቶች ኮሮና ቫይረስ በአለም ኢኮኖሚ ላይ የሚያስከተለው አሉታዊ ተጽእኖ ዘላቂና የከፋ እንደማይሆን ይተነብያሉ፡፡
ይሁንና በታዋቂው የኢኮኖሚስት መጽሄት ላይ የወጣው ዘገባ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በአለም ኢኮኖሚ ላይ ያስከተለውና የሚያስከትለው አሉታዊ ተጽእኖ ቀለል እንደማይሆን ነው፡፡ ዘገባው እንደማሳያ ከሚያቀርባቸው ጉዳቶች መካካል የሚከተሉትን መጥቀስ ይቻላል፡፡
የድንጋይ ከሰል ፍጆታ ከሌላ ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጻር ከአማካዩ ከአንድ-ሦስተኛ በላይ በሆነ መጠን ቀንሷል፡፡ እንዲሁም የንብረት ሽያጮች ከ 90% በላይ ቀንሰዋል፡፡ እንደሚታወቀው ከቻይና የዘመን መለወጫ በዓል በኋላ ወደ 200 ሚሊዮን የሚሆኑ ሰዎች ብዙውን ጊዜ ከትውልድ ቀያቸው ወደ ስራ ይመለሳሉ፡፡ በዚህ ዓመት ግን ከወረርሽኙ ጋር ተያይዞ ከበአል ተመላሾችን የሚያጓጉዙት ባቡሮች ባዶ ሆነው ነበር፡፡ በዚህም እንግዶች ለ 14 ቀናት ተገልለው የመቆየት ሁኔታ ሊያጋጥማቸው እንደሚችል ከተሞች አስጠንቅቀዋል፡፡
የአሜሪካ ንግድ ምክር ቤት ባጠናው ጥናት መሰረት ከተመረመሩ አስር በሻንጋይ ከሚገኙ ኩባንያዎች ውስጥ ዘጠኝ የሚሆኑት በቤት ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞች አሏቸው። ፖስተኞችና መልእክት አመላላሾች አሁንም በኤሌክትሪክ ሞተር ብስክሌታቸው ላይ በጎዳናዎች በብዛት ይታያሉ፤ ነገር ግን ሰዎች በሆቴሎችና ምግብ ቤቶች ውስጥ በማያውቋቸው ሰዎች የተዘጋጁ ምግቦችን ለመብላት ይፈራሉ፤ ምክንያቱም አዘጋጆቹ በበሽታው ተጠቅተው ሊሆን ይችላል በሚል፡፡ ማኪያቶ፣ ቡና ወዘት መጠጣት በጣም አደገኛ ነው። በዚህም የተነሳ ታዋቂው የቡና ንግድ ኩባንያ ስታርባክስ እንኳን በቻይና ውስጥ ካሉት ከ4,000 በላይ ካፌዎች ግማሹን ለመዝጋት ተገዷል፡፡
ሌላው ልብ ሊባል የሚገባው ነገር ደግሞ የኮሮናን ተጽእኖ በሳርስ መነጸር ማየት ይቻላል ወይ የሚለው ጉዳይ ነው፡፡ ቻይና አሁን 16% የዓለም አቀፍ ገቢ ትሸፍናለች፤ የሳርስ ወረርሽኝ በተነሰበት ጊዜ ግን ይሄ ድርሻ 4% ብቻ ነበር፡፡ በአሁን ጊዜ ቻይና የአለም ሁለተኛዋ ትልቅ አስመጪ (የሌላ አገር ምርት ገዥ) ናት፣ ስለሆነም ማንኛውም በቻይና ኢኮኖሚ ላይ የሚፈጠር ድክመት ጊዜያዊ ቢሆንም እንኳን በሌሎች ሀገሮች ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ ይፈጥራል፡፡ አንዳንድ የቻይና ኩባንያዎች ከውጭ ለማስገባት የተዋዋሉትን መዳብ እና የተፈጥሮ ጋዝ ለመሰረዝ እየሞከሩ ነው፡፡ ከ250 ቢሊዮን ዶላር በለይ ወጭ የሚያወጡ ቱሪስቶችም እቤት ውስጥ ዉለዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የቻይና ኩባንያዎች በአለም የምርት ሰንሰለት ውስጥ በእጅጉ የሚሳተፉ በመሆናቸው፤ የእነሱ ስራ መስተጓጎል በምርት ስንሰለት ውስጥ የሚሳተፉትን በመለው አለም የሚገኙ የሌሎች ኩባንያዎችን ስራ ማስተጓጎሉ እንደማይቀር ግልፅ ነው፡፡ ከዚህ አንፃር ዎል ስትሪት እና ኢኮኖሚስቶች የሚያቀርቡት የሳርስ ማነፃፀሪያ ብዙም አሳማኝ እንደማይሆን የሚያመለክት ነው፡፡
ዘ ኢኮኖሚስት
cut, copy and paste የሚሉትን የኮምፒውተር መከወኛዎች የፈለሰፈው ሳይንቲስት በ74 ዓመቱ አልፏል
***********************
አለም አቀፍ የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ማዕከል በሆነቸው የሳን ፍራንሲኮዋ ሲልከን ቫሊ ስራውን የጀመረው ላሪ ቴስለር በኮምፒውተር ሳይንስ ዘርፍ ላይ ትልቅ አሻራ ያኖረለትን የ cut copy and paste ትዕዛዞችን በኮምፒውቲንግ ስርዓት ውስጥ ያስተዋወቀ ትልቅ ባለሙያ ነው፡፡ ሳይንቲስቱ በ1960ዎቹ አካባቢ አነዚህ ስራዎችን ለመስራት ሲነሳ የኮምፒውተር እንቅስቃሴ እንዳሁኑ ምንም ያልተስፋፋ በመሆኑ የራሱን ከፍተኛ ጥረት ያሳየበት እንደሆነ ይነገራል፡፡
ኒው ዮርክ ውስጥ በምትገኝ ብሮንክስ በተባለች ስፍራ በ1945 የተወለደው ቴስለር ካሊፎርኒያ በሚገኘው ስታንፎርድ ዩኒቨርስቲ በኮምፒውተር ሳይንስ የመጀመሪያ ዲግሪውን ያገኘ ሲሆን፤ ከዛም በኋላ የተጠቃሚ በይነገፅ ዲዛይን (user interface design) በሚለው የትምህርት ዘርፍ ላይ በይበልጥ በመስራት የኮምፒውተር ሲስተምን ከሰዎች ጋር ለማቀራረብ በትኩረት እንደሰራ ይነገርለታል፡፡ በረዥም የስራ ህይወቱ ለተለያዩ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ትልልቅ ስራዎችን የሰራው ላሪ ቴስለር፤ አብዛኛውን የህይወቱን ክፍል ካሳለፈበት እና ታወቂ ስራውን ከሰራበት ዜሮክስ የምርምር ማዕከል በተጨማሪ ስቲቭ ጆብስ በመሰረተው አፕል ኩባንያ ውስጥ ለ17 ዓመት በቺፍ ሳይንቲስትነት የሰራበት ሁኔታ ከሰፊው የስራ ህይወቱ በዋናነት የሚጠቀሱለት ናቸው፡፡
ሳይንቲስቱ የታወቀበት ይህ የ cut copy and paste ፈጠራ ቀድም ባለው ጊዜ ታትሞ የወጣ ፅሁፍን በአካል በማውጣት እና በማጣበቂያ ወይም በሌሎች ቁሶች በመቀየር የሚከናውን ቢሆንም ከፈጠራው በኋላ ግን ብዙ ለውጦች መታየታቸውን በዘርፉ የሚንቀሳቀሱ ባለሙያዎች ያስረዳሉ፡፡ በተለይም በሲልከን ቫሊ የሚገኘው የኮምፒውተር ታሪክ ሙዚየም ስለሳይንቲስቱ ታላቅ ስራ ህያው ምስክሩን ሲያስቀምጥ የኮምፒውተር ሳይንስ ስልጠናን ከነባሩ አሰራር ጋር አጣምሮ ኮምፒውተርን ለሁለም እንዲሆን ያደረገ የፈጠራ ሰው ሲል ይገልፀዋል፡፡
ቢቢሲ
ሳምንታዊው የቴኪኢን ሴሚናር ተካሄደ
****************************
የቴክኖሎጂ እና አኖቬሽን ኢንስቲትዩት በየሳምንቱ ሃሙስ የሚዘጋጀው የቴኪኢን ሳምንታዊ ሴሚናር በዛሬው እለትም በኢትዮጵያ መሰረታዊ በሆኑ ሁለት ጉዳዮች ላይ ትኩረቱን አድርጎ ተካሂዷል፡፡ በዕለቱ በተከናወነው የሁለት ፕሮጀክቶች አቅርቦት በቅድሚያ አቶ አብዱላጢፍ ሃቢብ ያቀረቡት በህንድ እና ኢትዮጵያ ላይ ያተኮረው የቲውኒንግ (twinning) ፕሮግራም ግምገማ ለታዳሚዎች የቀረበ ሲሆን፤ ይህም በሁለቱ ሃገራት በሚገኙ የተመረጡ የኢንዱስትሪና የምርምር ተቋማት ውስጥ የቴክኖሎጂ እና የክህሎት ሽግግር ምን አይነት ገፅታና ውጤት አለው የሚለውን የሚቃኝ ነበር፡፡
በሴሚናሩ በተከታይነት ለታደሚዎች የቀረበው የምርምር ጥናት በአቶ ክንዴ አስማማው የተከናወነው በባዮማስ አመራረት ላይ ያተኮረ የፕሮጀክት ሃሳብ ሲሆን ይህም በአብዛኛው የሃገራችን ክፍሎች ለባዮማስ ኢነርጂ የሚውሉትን የኩበት እና የቻርኮል ግብዓቶች በተሻሻሉና ብዙ ቦታ በማይፈጁ ቀሳቁሶች በመተካት ለተሻለ ውጤት የሚውሉበትን ሁኔታ የሚያሳይ ነበር፡፡ አቶ ክንዴ በዚህ ምርምራቸው ላይ አንደአማራጭ ያቀረቡት የግብዓት አይነት የሩዝ ገለባ እና የበቆሎ ቆሮቆንዳ ሲሆን በተደረገው ሰፊ የምርምር ሂደትም በእነዚህ ቁሳ ቁሶች አማካኝነት ለባዮማስ ኢነርጂ ግብዓት የሚሆን የተሻለ ብስባሽ ወይም (briquettes) ማግኘት እንደሚቻል ለማሳየት የተሞከረበት ነው፡፡
በዚህ ሳምንቱ ሴሚናር፤ እንደወትሮው ሁሉ ከተሳታፊዎች በኩል በርዕሰ ጉዳዮቹ ላይ ጥያቄና አስታያየቶች የቀረቡ ሲሆን በአቅራቢዎቹ ዘንድም ማብራሪያ ተሰጥቶባቸው አልፈዋል፡፡ የቴክኢን ሴሚናር በየሳምንቱ ሐሙስ ከሰዓት የሚደረግ ሲሆን በተመራማሪዎች የተሰሩ የተለያዩ ጥናት እና ምርምሮች የሚቀርቡበትና ለማንኛውም ሰው ክፍት የሆነ የእውቀት ማዕድ ነው፡፡
በአመጋገባችን ላይ የኢንዛይም አስፈላጊነት ምን ያህል ነው?
**************************************
ሠውነታችን ከሚያስፈልገው የኢንዛይም መጠን ውስጥ 5ዐ% ያህሉን ራሱ የሚያመርት ሲሆን ቀሪውን 5ዐ% ግን ከጥሬ ምግቦች (Raw Foods) እንድናቀርብለት ይፈልጋል፡፡ ኤንዛይሞች ከ450c በላይ የሆነን ሙቀት መቋቋም ስለማይችሉ ምግቡ ከዚህ መጠነ ሙቀት በላይ በሆነ እሳት ሲበስል ኢንዛይሞቹ ከጥቅም ውጪ ይሆናሉ/ይሞታሉ፡፡ ስለዚህ ይህንን የ5ዐ% የኢንዛይም አቅርቦት ከጥሬ ምግቦች /አትክልት፣ ፍራፍሬ/ ለሠውነታችን ካላቀረብንለት ያለችውን 5ዐ% የኢንዛይም አቅርቦት አሟጦ ለመጠቀም ብቻ ይገደዳል፡፡ እድሜ እየጨመረ ሲሄድ የኤንዛይሞች ምርት በአንጻሩ እየቀነሰ ይሔዳል፡፡
ኢንዛይሞች በሠውነታችን ውስጥ ለሚከናወን ማንኛውም አይነት ኬሚካላዊ ኡደት (Chemical Reactions) አነሳሽ ሞተር ናቸው፡፡ ለምሳሌ፣ ምግብን ለመፍጨት፣ ልዩ ልዩ ጠቃሚ ንጥረ ነገሮችን ሰውነት በሚገባ እንዲጠቀም፣ ሰውነትን ራሱን በራሱ የመጠገን ሥራ ወዘተ በኬሚካላዊ ዑደት ወቅት ሳይቀየሩ ተሳትፎ በማድረግ ከፍተኛ ግልጋሎት ይሰጣሉ፡፡
ኢንዛይም የተፈጥሮ የምግብ ስርአተ ልመት ስጦታ እንደመሆኑ መጠን ያለ ኢንዛይም ምንም አይነት የምግብ ስርአተ ልመት ወይም (digestion system) አይካሄድም፡፡ ሰውነታችን ውስጥ ያለው የኢንዛይም መጠን አነስተኛ ሲሆን የምግባችን የንጥረ ነገር ይዞታ በእጅጉ እንዲቀነሰ ከማድረጉም ባለፈ የሠውነታችን ሥራ በቀላሉ ሚዛኑን እንዲስት በማድረገም ከፍተኛ ችግር ሊፈጥር ይችላል፡፡ ይህም ምግብ መፍጫ ንጥረ ነገሮችን በሠውነታችን ውስጥ የማሠራጨት ሥራ የሚሰሩ የሆድ ዕቃዎች ማለትም ጣፊያ፣ ቆሽት፣ ጨጓራ፣ ትንሹ አንጀትና ትልቁ አንጀት ከፍተኛ ጫና ውስጥ እንዲገቡ ያደርጋል፡፡ ይህም በሂደት እንደ ጉበት ባሉ አካላት ላይ የሥራ ማስተጓጎል ያመጣል፡፡ ጉበት የዕለት ተዕለት ሥራው ሲስተጓጎል ደግሞ የሚከተሉት የጤና ችግሮች ይፈጠራሉ፡- ለምሰሌ የደም ቅምር ሚዛኑ ይዛባል (Blood Composition Imbalance)፣ የደም ዝውውር ሂደት ይስተጓጎላል፣ የኮሌስትሮል መጠን ይጨምራል፣ የደም ግፊት እንዲሁም የልብ ችግር ይከሰታል ሊከሰት ይችላል፡፡
በመሆኑም የኢንዛይም መጠናችንን በተገቢው ሁኔታ ለማመዛዘን ማንኛውም የሚዘጋጁ ምግቦች አጠቃላይ ይዘት እንዳይበላሽ እና ከጥቅማቸው ይልቅ የጎንዮሽ ጉዳት እንዳያስከትሉ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ እጅግ መሰረታዊ ነው፡፡ ከዚህ አኳያ አትክልት እና ፍራፍሬ በብዛት አዘውትሮ መመገብ ሰውነታችን የሚፈልገው የኢንዛይም መጠን ሳይጓደል እንዲቀርብ ከማድረጉም ባለፈ ሌሎች ተጨማሪ ጥቅም እንድናገኝ ይረዳናል፡፡ በተለይም ጥሬ አትክልት እና ፍራፍሬን መመገብ የሠውነታችን የአሲድ/አልካላይን ሚዛን (Acid/Alkaline Balance) እንዲጠበቅ ስለሚረዳ የሆድ ዕቃ ተግባር ወይም የሠውነት የአሠራር ስርዐት ሚዛን ይጠበቃል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በምግብ፣ በመጠጥ፣ በአየር፣ እንዲሁም በመጽሐኒት አማካኝነት ወደ ሰውነታችን የሚገቡ መርዛማ ነገሮች (Toxins) በአግባቡ ከሠውነታችን አንዲወገዱ (Detoxification) ይረዳል፡፡ ይህ ሲሆን ታዲያ ሠውነት በሽታ የመከላከል አቅሙ (Immune System) ይዳብራል፣ ቆዳ ይጠነክራል፣ ሰውነታችን በቂ ኃይል (Energy) ይኖረዋል፣ ሠውነታችንም በተስተካከለ አቋም ላይ ይገኛል፡፡
ምንጭ፡ ScienceDirect
ኮሮና በቻይና እየተረታ መስሏል፤ በተቀረው ዓለምስ?
======================
ከቻይና ውጪ በኮሮና ቫይረስ እየተያዙ ያሉ ሰዎች ቁጥር በቻይና ውስጥ እየተመዘገባ ካለው መብለጡን የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቋል፡፡ እንደ ድርጅቱ ከሆነ በትናንትናው ዕለት 427 አዳዲስ የቫይረሱ ተጠቂዎች በ37 የዓለም ሀገራት ውስጥ ተገኝተዋል፡፡ ይህም በዕለቱ ቻይና ውስጥ ከተመዘገበው 411 አዳዲስ ተጠቂዎች አንፃር የቁጥጥር ብልጫውን የወሰደ ሆኗል፡፡ ምንም እንኳን እስከዛሬ ከተመዘገቡት የቫይረሱ ተጠቂዎች መካከል ከ96 በመቶ በላይ የሚሆኑት በቻይና የተመዘገቡ ቢሆንም ሀገሪቱ የቫይረሱን ስርጭት ለመቆጣጠር የወሰደቻቸው ጠንካራ እርምጃዎች በጎ ውጤት ማሳየት ችሏል፡፡ ቻይና መቀነስ የቻለችው የአዳዲስ ተጠቂዎችን ቁጥር ብቻም አይደለም የሟቾችም ቁጥር ወደ 52 ማውረድ ችላለች (በሦስት ሳምንታት ውስጥ የተመዘገበው አነስተኛ ቁጥር)፤ የመሽታው ዋና መነሾ ከነበረው ሁቤ ግዛት ውጪም ምንም ዓይነት ሞት ሳይከሰት ቀርቷል፡፡
ሆኖም ቫይረሱ በአውሮፓ፣ መካከለኛው ምስራቅ እና ሌሎች የእሲያ ክፍሎች በፍጥነት እተስፋፋ ይገኛል፡፡ በደቡብ ኮርያ በበሽታው የተያዙ ሰዎች ቁጥር 1700 ሲሻገር፤ ደቡብ አሜሪካንም ከጣሊያን በተመለሰ አንድ ብራዚላዊ አማካኝነት የመጀመሪያ የበሽታውን ተጠቂ አይታለች፡፡ በበሽታው ስርጭት ከአውሮፓ በቀዳሚነት በተቀመጠችው ጣሊያን የአጠቃላይ የተጠቂዎች ቁጥር 453 ሲደርስ 12 ሞትም ተመዝግቧል፡፡ ከዚህም ባለፈ በሽታው በጣሊያን አማካኝነት ወደ ጎረቤት የአውሮፓ ሀገራትም ጭምር እየተስፋፋ ይገኛል፡፡ ይህን ተከትሎ የጣሊያን መርማሪዎች በሽታውን ቀድሞ ማስቆም ይቻል የነበረ እንደሆን ምርመራ ከፍተዋል፡፡ ልክ እንደ ጣልያን ሁሉ ኢራንም በመካከለኛው ምስራቅ በቫይረሱ ክፉኛ የተጎዳችው ሀገር ናት፡፡ 26 ነዋሪዎቿን ስታጣ የሀገሪቱ ምክትል የጤና ሜኒስቴሩን ጨምሮ 245 ሰዎችም ሰለባ ሆነውባታል፡፡
እነዚህ ተደማምረው ቫይረሱ በዓለም አቀፍ ወረርሺኝነት እንዲፈረጅና እንቅስቃሴዎችም በዚያው ልክ እንዲሆኑ ከተለያዩ አቅጣጫዎች ሀሳብ እየተሰነዘረ ይገኛል፡፡ ይህ ግን እንደ ዓለም ጤና ድርጅት ዋና ሀላፊው ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሀኖም ከሆነ አላስፈላጊና ፈርሀት ውስጥ በመክተት ነገሮችን ሊያበለሻሽ ይችላል፡፡ በተጨማሪም ከዕውነታው በራቀ መልኩ በሽታውን መከላከልን አይቻልም የሚል አመለካከትን ይከስታል፡፡
ምንጭ፡ The Guardian
ዩትዩብ youtube.com/channel/UC6jvUOLRSkVEQtc
5Annfwvg
ትዊተር twitter.com/TechinEthiopia
የግዙፍ ፕሮጀክቶች ውድቀት እና መፍትሄዎቹ
======================
እንደ ትላልቅ ግድብ፣ አውሮፕላን ማረፊያ፣ የባቡር መስመር እና የፍጥነት መንገድ ያሉ ግዙፍ ፕሮጀክቶች በቢሊዮኖች የሚቆጠር ሐብት ፈሰስ ይደረግባቸዋል፡፡ ብዙውን ጊዜ እነዚህ ፐሮጀክቶች በስኬት ሳይጠናቀቁ ማየት ለብዙዎቻችን ሩቅ አይደለም፡፡ ኢትዮጵያም ለዚህ ተጠቃሽ የሚሆኑ ከበቂ በላይ ምሳሌዎችን ይዛለች፡፡
እንደ ለንደን ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎችን ገለፃ እነዚህ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ከፍተኛ ውስብስብነት ስላላቸው፣ እንዲሁም በማህበረሰብ፣ በአከባቢ እና በመንግስት ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ የሚያሳድሩ መሆናቸው “ለማስተዳደር አስቸጋሪ” ያደርጋቸዋል። በፕሮጀክት ማኔጅመንት ጆርናል ላይ ታትሞ የወጣ አንድ ጥናት በነዚህ ፕሮጀክቶች ላይ ለሚከሰተው ውድቀት መፍትሄ ሊሰጥባቸው ይገባል ያሏቸውን 18 ጉዳዮች አስቀምጧል፡፡ ከነዚህ ፕሮጀክቶችን ከተያዘላቸው ጊዜና በጀት በላይ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል ህልመኝነት፣ ደካማ አመራር፣ ከአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ጋራ የተገናኘ የአደጋ ስጋት ይገኙበታል፡፡
ጥናቱ ከዳሰሳቸው ግዙፍ ፕሮጀክቶች ውስጥ ሆነው የእንግሊዝ ፈጣን ባቡር ግንባታ (HS2) በ15.9 ቢሊዮን ፓውንድ ወጪ ከሁለት ዓመት በፊት ይጠናቀቃል ተብሎ የነበረ ቢሆንም ወጪው 18 ቢሊዮን ፓውንድን ተሻግሯል፤ እስካሁንም ስራው አልተጠናቀቀም፡፡ ከዚህ ባሻገር በዓለማችን በግዝፈቱ አቻ የሌለውን የቻይናው ዳሺንግ ኤርፖርት፣ ከዓለማችን በርዝመቱ ቀዳሚ የዋሻ ውስጥ ባቡር መስመር እንዲሁም በካሊፎርኒያ የሚገኘው የፈጣን ባቡር መስመር ያሉ ግንባታዎችንም በጥናቱ የተካተቱ ሲሆን 6000 ሌሎች ጥናቶችንም ተመልክቷል፡፡
ታድያ ችግሮችን በመጠቆም ብቻ ያላበቃው ጥናቱ ለችግሮቹ መልስ ይሆናሉ ያላቸውን የበዙ የመፍትሄ ሀሳቦችን አስቀምጧል፡፡ ባለፈው የጊዜ ሰሌዳ ላይ ምን መሻሻል እንደሚገባው የሚዘረዝሩ ጥናቶችን ማከናወን፣ በስራው አላማ ላይ ያለ አሻሚነትን ማስወገድ እንዲሁም ነገሮችን በማቅለል ላይ ማተኮር ከነዚህ የመፍትሄ ሀሳቦች መካከል ተጠቃሾቹ ናቸው፡፡
ምንጭ፡ E & T እና Daily Mail
ዩትዩብ youtube.com/channel/UC6jvUOLRSkVEQtc
5Annfwvg
ትዊተር twitter.com/TechinEthiopia